fa
Feedback
የቅዱሳን ታሪክ

የቅዱሳን ታሪክ

رفتن به کانال در Telegram

በዚህ ቻናል ውስጥ፦ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ @kidanemiherat_bot

نمایش بیشتر
8 621
مشترکین
-124 ساعت
+37 روز
-2330 روز
آرشیو پست ها
በረከቱ ይደርብንና በዛሬዋ ዕለት ግመልን በመርፌ ቀዳዳ ያሳለፈ የሐዋርያው የቅዱስ ታዴዎስ(ይሁዳ) መታሰቢያ በዓሉ ነው ወኩሎሙ ሰማዕተ ኮኑ በሃይማኖት እነዚህም ሁሉ በሃይማኖት ተመስክሮላቸዋል ዕብ 11:39 ወርሃ ክረምት የሰማዕትነት ምሳሌ ነው የሚደንቀው ደግሞ ከሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ ጀምሮ የብዙ ሐዋርያት ሰማዕታትና ቅዱሳን የሰማዕትነት መታሰቢያ በዓላቸውም ነው በዚች ዕለት ሐምሌ ሁለት ቀንም የሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ መታሰቢያ በዓል ነው ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን ብላ የምትጠራቸውና የምታከብራቸው የሃይማኖት ምስክሮች ትርጓሜ የሚያስፈልገውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በሁለት መንገድ የተረጎሙ ሰዎችን ነው እነርሱም 1ኛ ትርጉም የሚያስፈልገውን በምሥጢር አራቀው በመዘርዘርና በማብራራት 2ኛ በሕይወት ኖረው ገቢረ ተአምራት በማድረግ ቅዱስ ታዴዎስም ልዩ ትርጉም የሚጠይቀውን የመጽሐፍ ቅዱስ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብታልፍ ይቀላል የሚለውን ቃል በሥራ ተርጉሞልናል❤ ቅዱሳን አባቶቻችን በቅድስና በቅተናል ተአምር አድራጊዎች ነን ብለው ለጀብድና ለቤተ ሙከራ ብለው ታምር አያደርጉም ነበር ነገር ግን ሃይማኖታቸው ሲፈተንና ጥያቄ ሲቀርብበት ግን ድንቅ ድንቅ ተአምራት በማድረግ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ አድሮ በሚሠራው ሥራ ዓለምን ማርከውበታል። ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስም በአንድ ቀን እህል ተዘርቶ እንዲያፈራ አድርጓል ዘማዊቷን ሴት በገቢረ ተአምራት አሳምኖ በማጥመቅ እግዚአብሔርን በማገልገል መላ ሕይወቷን ለቅድስና እንድታቀርብ አድርጓል አንድ ኢአማኒ መጣና አንተ በምታምነውና በምታስተምረው ወንጌል ላይ ባለጠጋ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብታልፍ ይቀላል የሚል ቃል አለ እስኪ እውነት ከሆነ አድርገህ አሳየኝና ልመን ብሎ ሐዋርያውን ጠየቀው ሰው ቅዱስ ታዴዎስም ከእነ ጭነቷ በመርፌ ቀዳዳ በማሳለፍ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል የሚለውን ሃይማኖታዊ ቃል በተግባር አሳይቷል ነገር ግን ገቢረ ተአምራቱን የሚፈጽምበት መርፌ ሲፈልግ መርፌ የሚሠራው አንጠረኛ ግን ቅዱስ ታዴዎስ መርፌ ላክልኝ ሲለው ወዳጁ ነበርና ነገሩንም ቀድሞ ሰምቶ ስለነበር ሐዋርያውን የረዳው መስሎት የመርፌውን ቀዳዳ ትንሽ ሰፋ ሰፋ አድርጎ ላከለት ሐዋርያውም በሰውየው ደግነትና ድጋፍ ተደንቆ እንደ ቀድሞው አርገህ ሥራልኝና ላክልኝ አለው ይደንቃል የሰውየው እርዳታ የመርፌ ቀዳዳ ምን ቢሰፋ ግመልን ያሳልፋልን? ዛሬም ሃይማኖታችን ላይ ድጋፍና እርዳታ ያደረግን እየመሰለን ሃይማኖቱን ያስፋፋን እየመሰለን የሕግ ቀዳዳ የሥርዓት ቀዳዳ የምናስፋፋ ብዙዎች ነን ክርስትና አይሰፋም ሲሰጠንም ያልጠበበና ያነሰ አይደለምና በእንደዚህ አይነት መንገድ ደግሞ እግዚአብሔር አይከብርበትም ክርስትናው በእርዳታና በብልጠት ሳይሆን በመንፈሳዊ ጥበብ ብቻ ነው የሚሰፋው በእውነት የዛሬ ሕይወታችን ይደንቃል ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ በመርፌ ቀዳዳ ግመል እንድትመላለስ ባደረገበት ሃይማኖት ውስጥ እየኖርን ዛሬ ብዙዎቻችን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የጾም የጸሎት የአምልኮት ሥርዓታችን ከመርፌ ቀዳዳ በላይ የጠበበብን የሚመስለን ለምን ይሆን? በሃይማኖታችን ላይ ያለን ጥንካሬና ቁርጠኝነት እየላላ ዓለማዊነት እየዋጠን እምነታችን እየከሳ ፍርሐታችን አየገዘፈ ሲሄድ እንኳን በሃይማኖታችን ተአምራት ልናደርግ ይቅርና ቅዱሳን አባቶቻችንን ያደረጉትን ተአምራትና የፈጸሙትን ገድል ሳይቀር እንዴት ይህ ሊሆን ቻለ? ወደሚል የክህደትና የጥርጣሬ ባህር መስጠም እንጀምራለን ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስም ብዙ ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራትን አድርጎ ክርስቶስን ሰብኮ ነፍሳትን ማርኮ ብዙ መከራንና ስቃይን ከተቀበለ በኋላ ሐምሌ 2 ቀን በሰማዕትነት አርፏል እግዚአብሔር አምላክ ሐዋርያዊት በሆነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና አምልኮት ጸንተን እንድንኖር ይርዳን። በእኛ ላይም የሐዋርያው የቅዱስ ታዴዎስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን። ዛሬ እኛ ግን እንኳን በመርፌ ቀዳዳ ግመል ልናሳልፍ ይቅርና በግመል መንገድ ሳይቀር መርፌ ማሳለፍ ተስኖን በዚህ ገቢረ ተአምራት በተሞላች ክርስትና ውስጥ እየኖርን ነው ተአምር ማድረግ ባንችል እንኳን እንዴት በአንድነት በፍቅርና በሰላም መኖር እንዴት ከተአምር በላይ ሆኖብን ያቅተናል? ሃይማኖቱ ሳይጎድል እኛ ጎድለንበትና በብዙ ጉድለት እየተመላለስንበት በሃይማኖቱ ላይ እየኖርን ሳለን ነገር ግን አማኝነቱ ላይ ብዙ ነገር ጎድሎንኮ ነው አምላከ ሐዋርያት ልባችንን ወደ በጎ ይቀይርልን🙏 እንኳን አደረሳችሁ።

ፍሬዋ : የማይነጥፍ : የወንዝ : ዳር : ዛፍ ነቢዩ ሕዝቅኤል በወንዝ ዳር ለምልማ አብባ አፍርታ የተመለከታት ዛፍ እመቤታችን ናት ። ይህቺ ሕዝቅኤል ያያት ዛፍ እንደሌላው ዛፍ ቅጠሏ አይደርቅም፣ አ
ፍሬዋ : የማይነጥፍ : የወንዝ : ዳር : ዛፍ ነቢዩ ሕዝቅኤል በወንዝ ዳር ለምልማ አብባ አፍርታ የተመለከታት ዛፍ እመቤታችን ናት ። ይህቺ ሕዝቅኤል ያያት ዛፍ እንደሌላው ዛፍ ቅጠሏ አይደርቅም፣ አበባዋም አይረግፍም፣ ፍሬዋም ከዓመት ዓመት አይቋረጥም፤ ፍሬው ለመብል፤ ቅጠሉ ለመድኀኒት ይሆናልና ፡፡ ይህቺን ዛፍ የሚያጠጧት ውኃዎች ከሃያ ክንድ የነቁ ከአርባ ክንድ የፈለቁ ናቸው ምንጩም ከመቅደስ ውስጥ ነው ይህ ምሳሌ ነው ። ዛፏ የእመቤታችን ምሳሌ ነው ይህች ዛፍ ቅጠሏ ለመድኃኒት ፍሬዋ ለምግብ እንደሚሆን እመቤታችንም ለዘለዓለም መድኃኒት የሚሆን የሕይወት ምግብ ክርስቶስን ወልዳለችና ነው ። አንድም ይህች ቅጠሏ የማይረግፍ እንደሆነ የእመቤታችንም ክብረ ድንግልናዋ ለዘለዓለም ሳይረግፍ ይኖራልና ነው ። ከዓመት ዓመት ፍሬዋም እንደማያቋርጥ የእመቤታችንም የማኅፀኗ ፍሬ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋወ ደሙ ሳያቋርጥ ለምእመናን ሲሰጥ ይኖራልና ነው ። አንድም ቅጠል የሃይማኖት፤ ፍሬው የምግባር ምሳሌ፤ ይህቺ ዛፍ ቅጠልን ከፍሬ፣ ፍሬን ከቅጠል አስተባብራ ይዛ እንደተገኘች ሁሉ ሃይማኖት ይዞ ምግባር ሠርቶ መዳን የተገኘው በእመቤታችን ነውና ነው ። ይህቺን ዛፍ የሚያጠጣት ውኃ ምንጩ ከመቅደስ ውስጥ እንደሆነ ሁሉ እመቤታችንም አሥራ ሁለት ዓመት በቅዱስ ፋኑኤል ሞግዚትነት በመላእክት አረጋጊነት ኅብስት ሰማያዊ ጽዋ ሰማያዊ ተመግባ የማደጓ ምሳሌ ነው ። በሰማይም በምድር የሥላሴ መመለኪያ መስገጃ አዳራሽ የሆንሽ ክብርሽ የማይጠወልግ ቅድስናሽ የማይጎደል ድንግልናሽ የማይለወጥ የጳጦስ ዕፅ ቅድስተ ቅዱሳን ሆይ ከከናፍሮችሽ የማር ወለላ የሚፈሱብሽ አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ🙏

እሳቱን : በውኃ : ያጠመቀ : እነሆ : ተወለደ ገና በተወለደ በስምንተኛ ቀኑ ገድሉ በብራና መጻፍ የተጀመረለት ሕፃን እንደምን ያለ ነው ? አፉን ሳይፈታ በእግሩ መሔድ ሳይጀምር ብራና የሚለመንለት
እሳቱን : በውኃ : ያጠመቀ : እነሆ : ተወለደ ገና በተወለደ በስምንተኛ ቀኑ ገድሉ በብራና መጻፍ የተጀመረለት ሕፃን እንደምን ያለ ነው ? አፉን ሳይፈታ በእግሩ መሔድ ሳይጀምር ብራና የሚለመንለት ሕፃን እንደምን ያለ ነው ? ገና ከእናቱ ማሕፀን ሳይወጣ ስግደት የጀመረ መናኝ የድንግል ማርያምን ድምፅ ከሌላ ሰው ድምፅ ለይቶ ሰላምታዋን ሲሰማ የሚዘል ሕፃን ። መጥምቁን ለማክበር « የእግዚአብሔር ጸጋ የእግዚአብሔር ሥጦታ » ብሎ ከመጥራት በላይ ምን ውዳሴ ሊቀርብ ይችላል ፡፡ አባቱ ዘካርያስ የልጁን ስም በብራና ላይ ሲጽፍ የተዘጋ አፉ ተከፈተ ምላሱ ተፈታ ስሙን ብቻ ጽፎ የተዘጋ አፉ ከተከፈተ ጨምሮ ቢጽፍ ምን ይከፈትለት ይሆን ? « የሚጮህ ሰው ድምፅ ነኝ » ያለው ዮሐንስ ስሙ በመጻፉ ብቻ ለአባቱ ድምፅ ሠጠው ዘካርያስ ስሙን ጽፎ እንዲህ አንደበቱ ከተከፈተ የዮሐንስን ገድሉን መልኩን የጻፉ ምስጋናውን የደረሱ ሰዎች ምን ይከፈትላቸው ይሆን ? ከመጥምቀ : መለኮት : ከቅዱስ : ዮሐንስ : ዓመታዊ በዓለ : ልደቱ : ረድኤት : በረከትን : አምላከ : ቅዱሳን : ያድለን ።

አይሁድ በውስጣቸው ባደረ ጠላት ዲያቢሎስ ምክንያት ክፋት ጭካኔያቸው የበዛ ሆነ አዳኝ መድኃኒት ህይወት ፍቅር ተስፋ የሆነውን መድኃኔዓለም ክርስቶስ በክፋት ተነሳስተው ቢሰቅሉትም ለእኛ ግን መዳን ሆነ
አይሁድ በውስጣቸው ባደረ ጠላት ዲያቢሎስ ምክንያት ክፋት ጭካኔያቸው የበዛ ሆነ አዳኝ መድኃኒት ህይወት ፍቅር ተስፋ የሆነውን መድኃኔዓለም ክርስቶስ በክፋት ተነሳስተው ቢሰቅሉትም ለእኛ ግን መዳን ሆነልን ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን የምንድን ሆንን ።

አቡነ : ሙሴ : ጸሊም #ሰኔ_24_ቀን አንገታቸውን በሰይፍ ተቆርጠው ከብዙ ተጋድሎ በውኋላ ሰማእትነትን የተቀበሉት አቡነ ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊ ተጋድሎአቸው በግብፅ የሆነ ዓመታዊ ክብረ በዓላቸውን ቅድስት ቤ.ክ በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች ። መጀመሪያ ላይ እንደ አብርሃም በየዋህ ልቡና ሆነው ስነ ፍጥረትን በመመራመር እግዚአብሔር አምላካቸውን ያገኙ ታላቅ አባት ናቸው። ወላጆቻቸው ፀሐይ ያመልኩ ስለነበር ከልጅነታቸው ጀምሮ ኃጢአት በሠሩ ቁጥር ‹‹ ተው አምላካችን ፀሐይ ይጣላሃል ›› ይሏቸው ነበር። እሳቸው ግን ባደጉ ጊዜ ቀማኛ ዘራፊ ዱርዬ ሆኑ እየዘረፉ ብዙ ይመገቡ ስለነበር ከትልቅነታቸውና ኃይለኛነታቸው የተነሳ ‹‹ በገ ፈጅ ›› እየተባሉም ይጠሩ ነበር። ብዙ ወርቅ ከባለ ሀብቶች ሰብስባ ለነዳያንና ለቤተክርስቲያን ልትሰጥ ትሄድ የነበረችን አንዲት ክርስቲስቲያን ሴት ልጅ ሙሴና ግብረ አበሮቻቸው ለወርቁ ሲሉ እርሷንም ማርከው ወሰዷት ። ማታ ላይ ስለ ውበቷ ሲያወሩ እርሷ ግን ‹‹ስምህ ማን ነው?›› ስትላቸው «ሙሴ ነኝ›› ቢሏት ‹‹ይሄ ስምኮ እጅግ የተባረከ ስም ነው….” ብላ ስለ ሊቀ ነቢያት ሙሴና ስለ ክርስቶስ አስረዳቻቸው። ከዚህ በኋላ በወላጆቻቸው ስለ ፀሐይ አምላክነት ሲነገራቸው ያደጉትን ነገር መመርመር ጀመሩ። ‹‹ ፀሐይ አምላክ ከሆነ እስከዛሬ ድረስ ሽፍታና ዘራፊ ሆኜ ሰው ስገድልና ይህን ሁሉ ኃጢአት ስሠራ እንዴት ፀሐይ ሳታቃጥለኝ ቀረች …” ? በማለት ፀሐይን ጨረቃን፣ እሳትን፣ ነፋስን በየተራ አምላክ መሆናቸውን አለመሆናቸውን በሚገባ ከፈተኑና ከመረመሩ በኋላ ‹‹የፀሐይ የጨረቃ የሁሉ አስገኚ አምላክ ተናገረኝ” ብለው ሲጸልዩ ። ከሰማይ ድምዕ መጥቶላቸው ወደ ገዳም አስቄጥስ ሄደው ከአባቶች ትምህርተ ሃይማኖትን እንዲማሩ ተነገራቸው ። ገዳም ከገቡ ብኋላም ትንሹም ትልቁም ‹‹ሙሴ ይህን አድርግልኝ›› ይሉታል እርሱም ራሱን በትሕትና ዝቅ በማድረግ በተጋድሎ ሁሉንም እሺ እያለ ያገለግል ነበር ። በጸሎቱ ዝናብ ያዘንብ ነበር ለቅድስና ደረጃ ከበቁም በኋላ 40 ዓመት ሙሉ ከሰው ሳይገናኙ ብቻቸውን ዘግተው ከኖሩ በኋላ ለ500 መነኮሳት አበምኔት ሆነው ተሾሙ ። ቀን ወንጌል ሲያስተምሩ ይውሉና ሌሊት እየተነሱ አገልግሎታቸው የታይታ እንዳይሆንባቸው ከበረሃ ሄደው ለሁሉም መነኮሳት ውኃ እየቀዱላቸው በየደጃፋቸው ላይ ያስቀምጡላቸው ነበር ። በዕድሜአቸው መጨረሻ አካባቢ ቡራኬ ለመቀበል ከመነኮሳት ደቀ መዛሙርቶቻቸው ጋር ወደ አባ መቃርስ ሄዱ። አባ መቃርስም ‹‹ ልጆቼ ከናንተ መካከልበሰማዕትነት የሚሞት ›› አለ ብለው ትንቢት ሲናገሩ ሙሴ ጸሊምም ‹‹ አባቴ ያ ሰው እኔ ነኝ፣ ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ የሚል ቃል አለ። ይህን ጊዜ በጉጉት ስጠባበቀው ነበር›› አላቸው። እንደተባለውም የበርበር ሰዎች ገዳሙን ዘርፈው መነኮሳቱን ሊገድሉ ሲመጡ ደቀመዛሙርቶቻቸው ‹‹ሸሽተን እናምልጥ›› አሏቸው ። አቡነ ሙሴ ግን ‹‹ በጎልማሳነቴ ጊዜ ደም አፍስሼያለሁና አሁን የእኔም ደም ሊፈስ ይገባል›› በማለት ራሳቸውን ለመሰየፍ አዘጋጁ ። ሰኔ 24 ቀን አንገታቸውን በሰይፍ ቆርጠዋቸዋል ፈርተውና ሸሽተው የነበሩት ደቀመዛሙርቶቻቸውም ተመልሰው አብረዋቸው ተሰይፈዋል። የአባታችን የሙሴ ጸሊም ቅዱስ ሥጋቸው በገዳመ አስቄጥስ በክብር ይገኛል ። ግብፆች አቡነ ሙሴ ጸሊምን በእጅጉ ያከብሯቸዋል በስማቸው ጽላት ቀርጸው ቤተክርስቲያን ሠርተው ሥዕላቸውን አሠርተው ገድላቸውን ጽፈው በስንክሳራቸው መዝግበው የዕረፍታቸውን መታሰቢያ በደማቅ ሁኔታ ያከብሩታል ። ( የሰኔ ወር ስንክሳር )

ዛሬ ሰኔ 23 ቀን የወልደ ዳዊት የንጉሥ ሰሎሞን መታሰቢያ በዓል ነው ወናሁ ዘየዓቢ እምሰሎሞን ሀሎ ዝየ እነሆ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ ማቴ 21:42 በአንደኛ ነገ 2:19 ላይ እንደ ተጻፈው የ
ዛሬ ሰኔ 23 ቀን የወልደ ዳዊት የንጉሥ ሰሎሞን መታሰቢያ በዓል ነው ወናሁ ዘየዓቢ እምሰሎሞን ሀሎ ዝየ እነሆ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ ማቴ 21:42 በአንደኛ ነገ 2:19 ላይ እንደ ተጻፈው የንጉሥ ሰሎሞን እናት ቤርሳቤህ ትባላለች አንድ ቀን አንድ ጉዳይ ይዛ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ቤተ መንግሥት ትመጣለች የንጉሥ እናት ስለሆነች እንደ ሌላው ሕዝብ ደጅ ጠንታ አይደለም ወደ ቤተ መንግሥቱ የምትገባው በብዙ ክብርና እንክብካቤ እንጂ ወደ ሰሎሞን ዙፋን ቀረበች ንጉሡም ከዙፋኑ ተነስቶ ተቀበላት ሳማትም የተለየ የዙፋን ወንበርም ተነጥፎላት በንጉሡ ቀኝ አስቀመጣት ሰሎሞን ምን ንጉሥ ቢሆን እርሷም እናቱ ናታ ለእናቱ ክብር ሲያንስባት ነው እናቱም እንደ ሌላው ፍርድና ልመና አቅራቢ እስራኤላዊ ቆማ ሳይሆን በአጠገቡ ተቀምጣ ልጄ ሆይ አንዲት ነገር እለምንሃለሁ አታሳፍረኝ አለችው ንጉሡም እናቴ ሆይ አላሳፍርሽም ጠይቂኝ አላትና ጥያቄዋን አቀረበች ንጉሥ ሰሎሞን ለእናቱ እንዲህ ያለ ክብር ካደረገ እኔ የዋህ በልቤም ትሁት ነኝ ያለ የንጉሥ ሰሎሞን አምላክማ ለእናቱ እንዴታ ከዚህ በላይ አያከብራትምን? የሰሎሞን እናት ቤርሳቤህ የምትለምነው መልካም መስሎ የታያትን ብቻ ነው የነገሥታት ንጉሥ የሆነው የክርስቶስ እናት ድንግል ማርያም ግን የምትጠይቅልን መልካም መልካሙንና የጎደለው እንዲቃናልን ብቻ ነው ሰሎሞን እናቱን እንዲህ ካከበረ እናትና አባትህን አክብር ያለ ጌታማ ምን ያህል ያከብራትና ይሰማት ይሆን? ሰሎሞን ጠቢብ ነው ክርስቶስ ግን እራሱ ጥበብና የጥበብ መገኛ ነው ሰሎሞን መቅደሱን ሠርቷል ክርስቶስ ግን በመቅደሱ ይመለካል የሰሎሞን እናት ቤርሳቤህ ልጆችን ከወለዱ ሴቶች አንዲት ናት የክርስቶስ እናት ድንግል ማርያም ግን ከሴቶች ሁሉ መካከል ተለይታ የከበረችና የተቀደሰች ማኅደረ መለኮት ናት።

የ አ ሚ ና ዳ ብ : ሠ ረ ገ ላ አባ ሕርያቆስ እመቤታችንን የአሚናዳብ ሠረገላ አንቺ ነሽ በማለት አመስግኗታል ። መተርጉማኑ ደግሞ እመቤታችን በአሚናደብ ሠረገላ የተመሰለችበትን ምሥጢራዊ ምክንያት
የ አ ሚ ና ዳ ብ : ሠ ረ ገ ላ አባ ሕርያቆስ እመቤታችንን የአሚናዳብ ሠረገላ አንቺ ነሽ በማለት አመስግኗታል ። መተርጉማኑ ደግሞ እመቤታችን በአሚናደብ ሠረገላ የተመሰለችበትን ምሥጢራዊ ምክንያት ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ ፦ የአሚናደብ ሠረገላ ልዝብና ፈጣን ምቹ ነበረች እመቤታችንም ለነፍስ ለሥጋ የምትመች በንጽሕና በቅድስና የለዘበች ለምሕረት የፈጠነች አፍጣኒተ ረድኤት ሰአሊተ ምሕረት ምዕራገ ጸሎት ናትና ነው። « አንቀጸ : ሰላማዊት : ድንግል : ሆይ : ያንቺ : ሰላም ከሁላችን : ጋር : ይሁን : የጌታችን : እናት : እናታችን ማርያም : ሆይ : ለምኚልን : ከደጅ : እንዳንቆም : አማልጂን » !!!

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሕይወትን እንደሰጠን ሁሉ የእርሱ ባለሟል የሆኑት ቅዱሳን በሞታቸው ቂም በቀል ሳይሆን ወደ ሕይወት ወደ ሃይማኖት ይወስዱናል ። ሕያው ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን መካከል
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሕይወትን እንደሰጠን ሁሉ የእርሱ ባለሟል የሆኑት ቅዱሳን በሞታቸው ቂም በቀል ሳይሆን ወደ ሕይወት ወደ ሃይማኖት ይወስዱናል ። ሕያው ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን መካከል አንዱ ደግሞ ቀዳሚ ሰማዕት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ነው።

በኃጢአት በተሰነካከልን ጊዜ ሰይጣን ምሕረት አታገኙም አትረቡም አትጠቅሙም ብሎ በቀቢጸ ተስፋ ሰንሰለት እየጎተተ ወደ ጥልቁ እንዳያወርደን የእናት አማላጅ የመስቀል ምርኩዝ #ኪዳነ_ምሕረትን ሰጠን !!
በኃጢአት በተሰነካከልን ጊዜ ሰይጣን ምሕረት አታገኙም አትረቡም አትጠቅሙም ብሎ በቀቢጸ ተስፋ ሰንሰለት እየጎተተ ወደ ጥልቁ እንዳያወርደን የእናት አማላጅ የመስቀል ምርኩዝ #ኪዳነ_ምሕረትን ሰጠን !!!።

ማ ር : ሚ ና ስ #ሰኔ_15 የቅዱስ ሚናስ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ቀን ነው በተማፀኑትም ጊዜ በምልጃው ፈጥኖ በመድረስ የሚታወቀው ታላቅ ሰምዕት ነው፡፡ ቅዱስ ሚናስ በመላው ዓለም በተለይ በግብጽ ቤተ
ማ ር : ሚ ና ስ #ሰኔ_15 የቅዱስ ሚናስ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ቀን ነው በተማፀኑትም ጊዜ በምልጃው ፈጥኖ በመድረስ የሚታወቀው ታላቅ ሰምዕት ነው፡፡ ቅዱስ ሚናስ በመላው ዓለም በተለይ በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ልክ እንደ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በእጅጉ የሚወደድና ተአምር አድራጊ « ገባሬ ተአምር ወመንክር » በመባል የሚታወቅ ሰማዕት ነው። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፡- (የክርስቶስ ምርጥ ጭፍራ ከገንዘብ ይልቅ ጽድቅን የመረጠ እንደ ምሳሌው እንደጨረቃ ለደመቀና እንደ ፀሓይም ብሩህ ለኾነ ለሚናስ ሰላምታ ይገባል ) በማለት አወድሶታል፡፡ የ ቅ ዱ ስ : ሚ ና ስ : በ ረ ከ ት: ይ ደ ር ብ ን ፡፡

ንግስናን : ከቅድስና : አዋድዶ : የያዘ : ቅዱስ : ላልይበላ !!! #ሰኔ_12_ቀን የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ የነበረ በመላአክት አብሳሪነተ በላስታ ሮሃ የተወለደው የቅዱስ ላልይበላ የዕረፍቱ መታሰቢያው ቀን ነው ። በአንድ ወቅትም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ወደ ሰማያት አወጣው አብያተ ክርስቲያናትንም እንዴት መሥራት እንደሚችል አሳየው ወደ ምድርም ተመልሶ መንፈስ ቅዱስ እንዳረቀቀው በአስደናቂ ጥበብ ብዙ አብያተ ቤተ ክርስቶያናትን ሰራ ። ቤተ ጎልጎታ ፣ ቤተ ሊባኖስ ፣ ቤተ ደናግል ፣ ቤተ ማርያም ፣ ቤተ መስቀል ፣ ቤተ ሚካኤል ፣ ቤተ ጊዮርጊስ ቤተ ገብርኤል ፣ ቤተ አማኑኤል ፣ ቤተ መርቆሬዎስ ፣ ቤተ መድኃኔዓለምን ያነጸ ደገኛ ንጉሥ ነው ። አብያተ ክርስቲያነቱንም አንጾ ከጨረሰ በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በብርሃን ሠረገላ ተቀምጦ የሚስፈራ መብረቅን የተጎናጸፉ አእላፍት ሠራዊቶቹ ዙሪያውን ሆነው ወደርሱ መጥቶ እንዲህ አለው፤ ‹‹ ወዳጄ ላሊበላ ሆይ ሰላም ይሁንልህ እኔ በማይታበል ቃሌ እነግርሃለሁ፤ ማደሪያህ በክብር ሁሉ ከከበሩ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያቶቼ ጋር ይሁን፡፡ በጸሎትህና በቃል ኪዳንህ ለሚታመን እምነቱ እንደ ጴጥሮስና ጳውሎስ ደም መፍሰስ ይሆንለታል ፡፡ ወደ ቤተ መቅደስህም የሄደ በኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደሴ እንደ ሄደ ይሆንለታል ። መቃብርህንም የተሳለመ የሥጋዬን መቃብር እን ተሳለመ ይሆንለታል ፡፡ በዓመታቱ ወሮች ሁሉ የተራቡትን እያጠገበ የተጠመቁትንም እያጠጣ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ የተሠወረ መና እመግበዋለሁ ፤ የሕይወት ጽዋንም አጠጣዋለሁ፡፡ በመታሰቢያህ ቀንም ዕጣን ወይም ስንዴ የሚያገባውን እኔ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በውስጠኛው መጋረጃ አስቀምጬ ከተቆረሰው ሥጋዬ አቆርበዋለሁ ። በአማላጅነትህም እየታመነ የገድልህንና የቃል ኪዳንህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ያንተ ስም በተጻፈበት ቦታ  እኔ ስሙን እጽፋለሁ ። በፍጹም ልቡ ለሚያምን ይህን የማይታበል ቃል የተናገርኩ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ እኔ ነኝ ፡፡ ›› ቅዱስ ላሊበላም ይህን ቃል ኪዳን በተሰጠው ጊዜ ጌታችን እያመሰገነ በምድር ወድቆ ሰገደ፡፡ ጌታችንም ሰላምታ ከሰጠው በኋላ በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ከዚህ በኋላ ጥቂት ታሞ በሰላም ዐረፈ፤ የብርሃን መላእክትም ነፍሱን ተቀብለው የዘለዓለም ሕይወት ማደሪያ ወደሆነው ማረፊያው ገነት አስገቡት ፡፡ እግዚአብሔር : አምላክ : በቅዱስ : ላሊበላ ጸሎት : ነፍሳችንን : ይማርልን : አሜን፡፡

የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት
የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ልጆቿን ሰብስባ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ከዓመት ዓመት ታከብረዋለች። መጋቤ ብሉይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በተአምራቱ ዘወትር እንደሚጠብቀን ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ እንዲህ እያለ ይመሰክራል ፦ « የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የቀን እረኛ የሌሊት ጠባቂ ክንፎቹ የእሳት የሆነ ዘወትር የሚጠብቀን ቅዱስ ሚካኤል የእውነት የድንኳን ከተማ ነው። » በማለት ተናግሯል። በዚህ መሠረት ድንኳን ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር እንደሚከለሉበት ሁሉ #ቅዱስ_ሚካኤልም በቃል ኪዳኑም የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያድነናል ይታደገናል።

#እግዚአብሔርም በሰማያዊ ዜማ በምድራውያን ሰዎች ሊመሰገን በወደደ ጊዜ ቅዱስ ያሬድን ሦስት አዕዋፍ ግእዝ፣ ዕዝል እና አራራይ የሚባሉን የዜማ ስልቶች በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስተማረው ፡፡ ወደ ሰማ
#እግዚአብሔርም በሰማያዊ ዜማ በምድራውያን ሰዎች ሊመሰገን በወደደ ጊዜ ቅዱስ ያሬድን ሦስት አዕዋፍ ግእዝ፣ ዕዝል እና አራራይ የሚባሉን የዜማ ስልቶች በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስተማረው ፡፡ ወደ ሰማይም በመንፈስ ቅዱስ በመነጠቅ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ጣዕመ ዜማ ሲያመሰግኑ ሰምቶ ወደ ምድር ተመለሰ፡፡ ከዚያም በአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ከታቦተ ጽዮን ፊት ቆሞ አምላኩን እግዚአብሔርን ‹‹ በሰማያት የሰማሁት የመላእክት ምስጋና ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!›› በማለት በዜማው አመሰገነ ፡፡ ይህንንም በሰማያዊት ኢየሩሳሌም የሰማውን የመላእክትን ዜማ ለደቀ መዛሙርቶቹ አስተማረ ፡፡ ከ ቅ ዱ ስ : ያ ሬ ድ : በ ረ ከ ት : ረ ድ ኤ ት : ያ ሳ ት ፈ ን !!!

ልዑል ሰምራ ዳዊት ዘመራ በቤተ መቅደስ ተወክፍዋ ልዑል ወደዳት ዳዊትም ዘመረላት በቤተ መቅደስ ተቀበሏት መቅደሰ ኦሪት ዘቦዕኪ ኦ ማርያም እምነ፤ ወእሙ ለእግዚእነ፤ በሕፅነ ሐና ተማኅፀነ፤ ፈንዊዮ ለ
ልዑል ሰምራ ዳዊት ዘመራ በቤተ መቅደስ ተወክፍዋ ልዑል ወደዳት ዳዊትም ዘመረላት በቤተ መቅደስ ተቀበሏት መቅደሰ ኦሪት ዘቦዕኪ ኦ ማርያም እምነ፤ ወእሙ ለእግዚእነ፤ በሕፅነ ሐና ተማኅፀነ፤ ፈንዊዮ ለፋኑኤል ይዕቀብ ኪያነ፤ በረምኃ መስቀል ረጊዞ ሰይጣነ፤ ወደ ኦሪት መቅደስ የገባሽ የጌታችን እናቱ እናታችን ማርያም ሆይ አንቺን በታቀፈ በሃና ጭን ተማፅነናል፤ ሰይጣንን በመስቀል ጦር ወግቶ እኛን ይጠብቀን ዘንድ ፋኑኤልን ላኪልን። (ነግሥ ዘማኅሌት) በአታ ለማርያም 🙏 እንኳን አደረሳችሁ

ቅ ድ መ : ዓ ለ ም : የ ታ ሰ በ ች #መላእክት ቢታሰቡ ድንግል ማርያምን ከበው በእርስዋ መንበርነት የተገለጠውን ንጉሠ ነገሥት እግዚአ አጋእዝት ሊያመሰግኑ ነው። #ነቢያት ቢታሰቡ ትንቢታቸው በድ
ቅ ድ መ : ዓ ለ ም : የ ታ ሰ በ ች #መላእክት ቢታሰቡ ድንግል ማርያምን ከበው በእርስዋ መንበርነት የተገለጠውን ንጉሠ ነገሥት እግዚአ አጋእዝት ሊያመሰግኑ ነው። #ነቢያት ቢታሰቡ ትንቢታቸው በድንግል ማርያም ተፈጽሞ በእርስዋ ምክንያት መርገም ሊወገድላቸው ነው። #ሐዋርያት ቢታሰቡ በእመቤታችን ከብረው እርስዋ ያወጣችላቸውን ፀሐይ ለብሰው ለዓለም ብርሃን ሊሆኑ ነው። #ሰማዕታት ቢታሰቡ አክሊለ ሰማዕት ክርስቶስን ወልዳላቸው በእርሱ ስም አንበሳ ሊሰግድላቸው እሳት ሊቀዘቅዝላቸው ኃይል ሊያስታጥቃቸው ድል ሊነሡ ነው። #መነኮሳት ቢታሰቡ አክሊለ ሦክ ተቀዳጅቶ የምንኩስና ቆብን ከለሜዳ ለብሶ የምንኩስና ቀሚስን በበረሃ ጹሞ የበረሃው ውስጥ ከዋክብት እንዲሆኑ ገዳምን ባርኮ የሰጣቸውን ብርሃናቸው ጌታን ብትወልድላቸው ነው። ስለዚህ “ እመቤታችን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር” እንላለን።

በ ዓ ተ ፡ ግ ብ ጽ #ነገ_ግንቦት_24 ቀን እመቤታችን ከተወዳጅ ልጅዋ ጋር በስደት ግብጽ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው ። አበው የአበባን በዓል በአበባ ዘመን ብለው ማኅሌቱንም በዓሉን በወር
በ ዓ ተ ፡ ግ ብ ጽ #ነገ_ግንቦት_24 ቀን እመቤታችን ከተወዳጅ ልጅዋ ጋር በስደት ግብጽ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው ። አበው የአበባን በዓል በአበባ ዘመን ብለው ማኅሌቱንም በዓሉን በወርኃ ጽጌ በጥቅምት ቢወስዱትም ጥንተ መሠረቱ ግን ግንቦት 24 ቀን ነው ። እመቤታችን ቀጥኖ ከሚያመነምን ክፉ ዘመን ትሰውረን እፎይ ከምንልበት ዘመን በምልጃዋ ታድርሰን!

ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሰርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሰርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይ
ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሰርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሰርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይተው ያስገቡታል፡፡ እኛም እንዲኽ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ልቡናችንን በማንጻት፣ ልል ዘሊል ከመኾን በመራቅ፣ የክፋት እርሾን በማስወገድ፣ ከጾም ጋር አብረው የሚመጡትን የሚያጅቧትን መልካም ምግባራትንም ለመቀበል የልቡናችንን ውሳጤ በመክፈት የምግባር እናት፣ የማስተዋል እንዲኹሉም ለሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ልንቀበላት ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ይኽን ያደረግን እንደኾነ ታላቅ ሐሴት እናደርጋለን፤ ርሷም ቁስለ ነፍሳችንን ትፈውስልናለች፡፡ በሌላ አገላለጽ ብነግራችኹ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንኳን ለጾመ ሐዋርያት በሰላም አደረሳችሁ 🥰