cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ሰሌዳ | Seleda

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! @seleda_support ለማንኛውም አይነት ጥያቄ

Ko'proq ko'rsatish
Advertising posts
50 534Obunachilar
+524 soatlar
-207 kunlar
+25930 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

በኮሪደር ልማት 1 ሺህ 135 ሰዎች አሁንም ምትክ ቤት ወይም ቦታ አለማግኘታቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ ተናገሩ🤔 👉🏼 ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸዉ አንድም ሰው ቤት ሳይሰጠው ተነስቶ ሌላ ቦታ የገባ ሰው የለም ብለዋል በትናንትናው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ጥያቄ ካቀረቡ የምክር ቤት አባላት መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ፤ ከኮሪደር ልማት ተነሺዎች መካከል “1,135 ሰዎች አሁንም ምትክ ቤት ወይም ቦታ አለማግኘታቸውን” በማንሳት ጥያቄ አቅርበዋል። “1,135 ሰው ማለት ቀላል አይደለም። በዚህ ወቅት፣ በዚህ የኑሮ ውድነት፣ በዚህ ጊዜ ተረጋግቶ የሚኖርበት አጋጣሚ ካልተፈጠረ፤ የሚሰራውን ስራ ሁሉ በዜሮ ድምር የሚያባዛ ነው የሚሆነውና እርሱ ለምን ግምት ውስጥ አልገባም?” ሲሉ መጠየቃቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር አስነብቧል። የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በ90 ቀናት እንዲጠናቀቅ እቅድ እንደተያዘለት በመጥቀስም፤ “የግድ በዚህ ሶስት ወር ውስጥ ስራ ማለቅ አለበት ወይ?” ሲሉ ተጨማሪ ጥያቄ አስከትለዋል። “በጊዜ ተለክቶ ስራ መሰራት አለበት፤ ልክ ነው። አምናም የ90 ቀን እቅድ ተብሎ ውጤታማ ስራዎች ተሰርተዋል። ሁልጊዜ ግን በዚህ መልክ በዘመቻ መሰራት አለበት ወይ? የሚል ጥያቄ ይስነሳል” ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ “ነገሮች በተረጋጋ እና በታቀደ መልኩ እንዲሄዱ ለማድረግ መሰራት የለበትም ወይ?” ሲሉ አስተያየት አዘል ጥያቄ ማንሳታቸውን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ የምክር ቤት አባሉ ከጠቀሷቸው የልማት ተነሺዎች ውስጥ “አንድም ሰው ቤት ሳይሰጠው ተነስቶ ሌላ ቦታ የገባ ሰው የለም። በተለይ የመንግስት ቤት ተከራይ፣ የቀበሌ፣ የኪራይ ቤቶች፣ የቤተክህነት ጭምር ማለት ነው” ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ የልማት ተነሺዎችን በዚህ መልኩ የማስተናገድ አካሄድ ሲከተል “ለመጀመሪያ ጊዜ” መሆኑንም ጠቁመዋል። ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😢 5👎 2👏 1
ከ18 ሺህ በላይ የውጭ ዜጎችን ከሀገር ተባረዋል የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ በአገር ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ18 ሺህ በላይ የውጭ አገር ዜጎችን ከአገር ማባረሩን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት ባቀረበው ሪፖርት ገልጧል። ከአገር ከተባረሩት መካከል፣ ለሌሎች የውጭ ዜጎች ሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ አዘጋጅተው በገንዘብ ሲሸጡ የነበሩ እንደሚገኙበት ተቋሙ ገልጧል። በኢንቨስትመንት ፍቃድ ወደ አገሪቱ የገቡ የውጭ ዜጎች ለበርካታ ዓመታት በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሳታፊ ኾነው እንደተገኙም ተቋሙ ጠቅሷል።(ዋዜማ)
Hammasini ko'rsatish...
👍 13
ለ28 አመት ታጥፎ የኖረውን ግለሰብ ያዳነው የህክምና ጥበብ👏 ሊ ኋ ይባላል፡፡ ቻይናዊ ነው፡፡ ታዲያ ሊ አንኪሎሲንግ ስፖንዲላይትስ (Ankylosing spondylitis) በተሰኘ የአጥንት በሽታ ለ28 አመታት ፊቱን ከጉልበቱ ላይ ማንሳት ሳይችል እንደታጠፈ ኖሯል፡፡ የሊኋ የጀርባ አጥንቶች በጣም ስለታጠፉ መቀመጥም ሆነ መነሳት ወይንም ጋደም ማለት ባለመቻሉ 28 የስቃይ አመታትን አሳልፏል፡፡ ይህ እጥፋቱም የቻይናዊውን ቁመት ወደ 90 ሳንቲ ሜትር አውርዶት ነበር፡፡ ታዲያ እ.ኤ.አ በ2018 ህክምና ሊደረግለት ቢሞከርም ቀዶ ጥገናው እጅግ አደገኛ ስለነበር ሐኪሞቹ ሊሰሩለት አልመረጡም ነበር፡፡ በጊዜ ሂደት ግን ሊኋን ለማዳን ቆርጠው ተነሱ፡፡ በዛ ላይ ኋ ቀና ካልተደረገና በልቡና ሳንባው ላይ ያለውን ጫና መቀነስ ካልተቻለ ሕይወቱ አስጊ ወደ ሆነ ደረጃ በመሸጋገሩ ህክምናው የግድ ሆነ፡፡ በመሆኑም በቻይና ሸንዘን ዩኒቨርስቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የአጥንትና መገጣጠሚያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ፕሮፌሰር ዌይረንን ጨምሮ ሌሎች የሕክምና ቡድን አባላት ሊን ቀጥ አድርጎ የሚያራምደውን ህክምና ጀመሩ፡፡ ህክምናው የግለሰቡን ታጥፈው የነበሩትን የጀርባ አጥንቶ አንድ በአንድ እየሰበሩና ድጋሚ ቀጥ አድርጎ የመገጣጠም ስራ ነበር፡፡ በዚህም ከአራት ዙር አስቸጋሪ ቀዶ ጥገናዎች በኋላ የተሳካ ስራ መስራት ችለዋል፡፡ የእግሩ አጥንቶችም እንደዚሁ ተሰብረው መልሰው መጠገን ቻሉ፡፡ ሆስፒታሉ የቀዶ ጥገናውን ክብደት ሲገልጽ የኤቨረስት ተራራን እንደመውጣት ነበር ነው ያለው፡፡ በዚህም ሊ በድንቅ የህክምና ጥበብ ከ28 አመት በኋላ ቀጥ ብሎ መቆምና መራመድ ችሏል፡፡ Via አዲስ ዋልታ
Hammasini ko'rsatish...
👏 111👍 33 4😱 2
አምና የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ተመልሷል 🔥 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ አንድን እየመራ የሚገኘው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ኦሮሚያ ፖሊስ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አምስት ጨዋታዎች እየቀሩት ከወዲሁ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ማደግ ችሏል። ባለፈው አመት ወደ ታችኛው ሊግ የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከአንድ አመት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሪቱ ትልቅ ሊግ መመለሱን ማረጋገጥ ችሏል። ምንጭ :- የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን
Hammasini ko'rsatish...
👍 26
"የስፖርት ውርርድ / የቤቲንግ ቤቶች ሊታገዱ ይገባል" ሲል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር አሳሰበ። ሚኒስቴሩ ዛሬ የ9 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለተ/ም/ቤት አቅርቦ ነበር። በዚህ ወቅት ፤ " የወጣቶች ሱሰኝነት በሀገር ደረጃ እየተባባሰ መጥቷል ፤ በተለይ አሉታዊ መጤ ልማዶች እና አደንዛዥ ዕጽ እንደ ሀገር እየተስፋፋ መጥቷል " ሲል ገልጿል። ይህም ብዙ ወጣቶችን እያሳጣን ነው ሲል አስረድቷል። ወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ላይ ተግዳሮት እየፈጠረ ከሚገኘው አንዱ የስፖርት ውርርድ እንደሆነ ያመለከተው ሚኒስቴሩ " የስፖርት ውርርድ ለሀገሪቱ ከሚያስገባው ገቢ አኳያ ብቻ መታየት የለበትም " ብሏል። " ' ስፖርት ቤቲንግ ' ላይ ያሉት፣ ካሁን በፊት የወጡት መመሪያዎች፣ ደንቦች፤ ጥናትን መሰረት አድርገው ሊታገዱ ይገባል " ሲል ገልጿል። ፓርላማውም በዚህ ረገድ እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል። " ገቢ አንድ ነገር ነው። ሀገር ገቢ ማግኘት አለባት " ያለው መ/ቤቱ ነገር ግን ፦ ➡️ በወጣቶቹ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያስከተለ ስለሆነ፣ ➡️ ብዙ ወጣቶች እያሳጣ ስለሆነ፣ ➡️ ብዙ ቤተሰብም #እየፈረሰ ስለሆነ ሊታገድ እንደሚገባ ገልጿል። በህ/ተ/ም/ቤት የጤና ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፤ " ብሔራዊ ሎተሪ ከገቢ ጋር አይቶታል። በዚህም በኩል ደግሞ ሌላ ችግር እየፈጠረ ነው " ያለ ሲሆን " ተማሪዎች ዩኒፎርማቸውን እያወለቁ የስፖርት ውርርድ ቤት ይገባሉ። ስለዚህ መቼ ያጥኑ። አእምሮአቸው ሊጎዳ ስለሚችል ጥንቃቄ ተደርጎ መሰራት አለበት " ብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፖርት ውርርድ ላይ በተሰማሩ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ በቅርቡ የወሰደውን እርምጃ " ጥሩ ስራ " ሲል አወድሷል። በሌሎች አካባቢዎች በተሞክሮ ሊወሰድ ይገባል ሲል ጠቁሟል። የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴርም ፤ ከስፖርት ውርርድ ጋር በተያያዘ ያለውን የወጣቶች ሁኔታ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ አድርጎ እንዲያየው እና ጠንካራ ክትትል እንዲያደርግ መክሯል። ከዚህ ቀደምም የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የስፖርት ውርርድ / ቤቲንግ / ' #ቁማር ' ነው ብሎ እንደሚያምን ገልጾ እንዲታገድ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን ፤ " ቤቲንግ " ' #ጨዋታ ' እንጂ ' ቁማር ' ነው ብሎ እንደማያምን ገልጾ ነበር። ቤቲንግ አትራፊና ብዙ ወጣቶች ስራ እንዲያገኙ ያደረገና በከፍተኛ ሁኔታ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ የሚያደርግ መሆኑንም አስረድቶ ነበር። በስርዓት እንዲመራም መመሪያዎች ወጥተውለት እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ " እኛ ጨዋታውን አቅርበናል ተጫዋቹ ደግሞ በኃላፊነት መጫወት አለበት " ሲል ነበር የመለሰው። via - tikvahethiopia
Hammasini ko'rsatish...
👍 38👎 16 1
የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች በፍተሻ ኬላዎች አላግባብ ከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍሉ እየተጠየቁ ነው ተባለ ለአገር አጠቃላይ የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ ዋነኛ መሆኑ የሚነገርለት የትራንስፖርቱ ዘርፍ በርካታ ፈተናዎች እንደተጋረጡበት ያስታወቀው የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ማህበር ነው፡፡ የማህበሩ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ዘውዴ ከዚህ ቀደም የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች እገታ፤ ዝርፊያ፤ ግድያ እና ሌሎች ጥቃቶችም ሲደርስባቸው እንደነበር ገልጸው፤ አሁን ላይ ግን በአንጻራዊነት መሻሻሎች እንዳሉ ጠቁመዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሁን ላይ አሽከርካሪዎች በሚያቀኑባቸው አከባቢዎች ባሉ የፍተሻ ኬላዎች አላግባብ እንዲከፍሉ የሚጠየቁት ገንዘብ ከፍተኛ መሆኑን እና ይህም በዘርፉ ላይ ችግር እየፈጠረ እንዳለ ተናግረዋል፡፡ ስራ አስኪያጁ እንደሚሉት ከሆነ ተሸከርካሪዎች በሚንቀሳቀሱባቸው ኬላዎች ከ5ሺህ እስከ 30 ሺህ የሚደርስ ገንዘብ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው፡፡ ዘርፉ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የተለያዩ ፈተናዎች እንደተጋረጡበት ማህበሩ ያስታወቀ ሲሆን፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በበኩሉ በአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለማስቆም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራው ነው ማለቱ የሚታወቅ ነው፡፡(መናኸሪያ ሬዲዮ)
Hammasini ko'rsatish...
👍 22 2
የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በተለያዩ ዘርፎች የሚሰጠው ድጋፍ ለኢትዮጵያ እድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ያለው ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በተለያዩ ዘርፎች የሚሰጠው ጠቃሚ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ያለው ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "ዛሬ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ሱዝማን እና ቡድናቸውን በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል" ሲሉ ገልጸዋል። የቢል እና ጌትስ ፋውንዴሽን በግብርና፣ ጤና፣ በስርዓተ ምግብ፣ በአካታች የፋይናንስ ስርዓት እና በሌሎች ዘርፎች የሚሰጠው ጠቃሚ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ይህን ትብብር በማላቅ እና በአዳዲስ ዘርፎች በመተባበር እንሰራለን ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ።
Hammasini ko'rsatish...
👎 33👍 18 3🤔 1
ራይድ በኤሌክትሪክ መኪና የታገዘ የትራንስፖርት አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ ራይድ የአረንጓዴ ትራንስፖርት አገልግሎት አካል የሆነውን የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎትን ማስጀመሩን በዛሬው እለት በአድዋ ሙዚየም የተለያዩ ተቋማት ሚንስትሮች፣ የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የዓለም አቀፍ እና የአህጉራዊ ድርጅት ተወካዮች፣ አምባሳደሮች እና ዘርፉን ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ የሚገኙ ግለሰቦች በተገኙበት ገልጿል፡፡ የራይድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሳምራዊት ፍቅሩ የራይድ የትራንስፖርት ዘርፉ ወደ ኤሌክትሪክ መኪኖች የሚያደርገዉን ሽግግር በይፋ በሚጀመርበት በዚህ ቀን እንደገለጹት በሀገራችን የአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፉን ለማስፋት እየተደረገ ያለዉን ርብርብ ራይድ በርካታ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ወደ አገልግሎት በማስገባት ከቴከኖሎጂው ፈር ቀዳጆች ተርታ ተቀምጧል ብለዋል ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በሞባይል መተግበሪያ እና በጥሪ ማዕከል አማካኝነት ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት በማቅረብ ላይ የሚገኘዉ ራይድ የኤሌክትሪከ መኪኖች ወደመገልገል መሸጋገሩ የተገለፀ ሲሆን ይህ አግልግሎቱ "የራይድ ራዕይ 2030” አንዱ (RIDE'S 3G, Vision 2030) ማስጀመሪያ ጭምር መሆኑም ተነግሯል። እነዚህ የተስላ ብራንድ የሆኑት ከ150 በላይ የኤሌክትሪክ መኪኖች ወደ አገልግሎት የሚገቡበት የመጀመሪያ ዙር የራይድ የአረንጓዴ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ተቋማት እና የመኪና አስመጪዎች ተሳትፈውበታል ተብሏል ። ራይድ በአሁን ሰአት ከ400 በላይ ለሆኑ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 85 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው። (በድሬቲዩብ ሪፖርተር)
Hammasini ko'rsatish...
👍 25👎 4 1
የአገር ውስጥ በረራ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው እንደገለጹት እየተጠናቀቀ ባለው በጀት አመት የአገር ውስጥ ተጓጓዦች ቁጥር 3.5 ሚሊየን ይደርሳል፡፡ ይህ መጠን ከ2015 በጀት አመት አንጻር የ34.6 በመቶ ጭማሪ የሚኖረው ነው፡፡ በቀደመው አመት በአገር ውስጥ በረራ የተስተናገዱት ተሳፋሪዎች 2.6 ሚሊየን እንደነበሩ አቶ መስፍን አስታውሰዋል፡፡ አየር መንገዱ እየሰፋ ያለውን የደንበኞች ቁጥር ታሳቢ በማድረግ የቦሌ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ አሁን በአመት ማስተናገድ ከሚችለው 25 ሚሊየን መንገደኞች ከ4 እጥፍ በላይ ማስተናገድ የሚችል አየር ማረፊያ እና ማስተናገጃ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፡፡ ሆኖም ይህ ማእከል የአለም አቀፍ እና በተወሰነ መልኩ የጭነት ማስተናገጃ ሆኖ የሚሰናዳ መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል፡፡ የቦሌ አየር ማረፊያ እያደገ የመጣውን የአገር ውስጥ በረራ በማሰተናገድ ይቀጥላል ያሉት አቶ መስፍን ; የጥገና እና የጭነት ማእከሉም በቦሌ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ አየር መንገዱ ለአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ የአየር መንገዶች የጥገና አገልግሎት እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ ስራ ለማስፋት ተጨማሪ የመለዋወጫ ማስቀመጫ እና የጥገና ማእከል እየሰራ ሲሆን እስከመጪው ታህሳስ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል:: በተመሳሳይ እጅግ ዘመናዊ የጭነት ማእከል የገነባው አየር መንገዱ ዋነኛ የችነት ማእከሉን በቦሌ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቀው፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ 40 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገነባው አዲስ የአየርመንገድ ከተማ ከቦሌ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ ጋር በፈጣን ባቡር እንደሚገናኝ ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡(Capital)
Hammasini ko'rsatish...
👍 28😁 12👎 4