en
Feedback
ሰሌዳ | Seleda

ሰሌዳ | Seleda

Open in Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ሰሌዳ | Seleda

Channel ሰሌዳ | Seleda (@seledadotio) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 52 908 subscribers, ranking 4 966 in the News & Media category and 627 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 52 908 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 81 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 18.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 14.93% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 9 969 views. Within the first day, a publication typically gains 7 902 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 69.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

52 908
Subscribers
-224 hours
-1067 days
+8130 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+17
in 10 channels
August '26
+519
in 20 channels
Get PRO
July '26
+279
in 23 channels
Get PRO
June '26
+204
in 25 channels
Get PRO
May '26
+401
in 24 channels
Get PRO
April '26
+697
in 30 channels
Get PRO
March '26
+1 203
in 27 channels
Get PRO
February '26
+86
in 22 channels
Get PRO
January '26
+343
in 27 channels
Get PRO
December '25
+1 705
in 19 channels
Get PRO
November '25
+291
in 19 channels
Get PRO
October '25
+1 240
in 25 channels
Get PRO
September '25
+2 465
in 22 channels
Get PRO
August '25
+1 010
in 18 channels
Get PRO
July '25
+1 063
in 21 channels
Get PRO
June '25
+1 852
in 23 channels
Get PRO
May '25
+155
in 14 channels
Get PRO
April '25
+161
in 14 channels
Get PRO
March '25
+302
in 10 channels
Get PRO
February '25
+25
in 9 channels
Get PRO
January '25
+32
in 1 channels
Get PRO
December '24
+151
in 2 channels
Get PRO
November '24
+220
in 1 channels
Get PRO
October '24
+381
in 5 channels
Get PRO
September '24
+429
in 8 channels
Get PRO
August '24
+789
in 7 channels
Get PRO
July '24
+380
in 6 channels
Get PRO
June '24
+130
in 9 channels
Get PRO
May '24
+388
in 6 channels
Get PRO
April '24
+631
in 3 channels
Get PRO
March '24
+676
in 5 channels
Get PRO
February '24
+408
in 7 channels
Get PRO
January '24
+409
in 4 channels
Get PRO
December '23
+370
in 7 channels
Get PRO
November '23
+62
in 7 channels
Get PRO
October '23
+97
in 2 channels
Get PRO
September '23
+105
in 0 channels
Get PRO
August '23
+42
in 0 channels
Get PRO
July '23
+47
in 0 channels
Get PRO
June '23
+69
in 0 channels
Get PRO
May '23
+67
in 0 channels
Get PRO
April '23
+23
in 0 channels
Get PRO
March '23
+22
in 0 channels
Get PRO
February '23
+29
in 0 channels
Get PRO
January '23
+32
in 0 channels
Get PRO
December '22
+2
in 0 channels
Get PRO
November '22
+2
in 0 channels
Get PRO
October '22
+4
in 0 channels
Get PRO
September '22
+62
in 0 channels
Get PRO
August '22
+58
in 0 channels
Get PRO
July '22
+29
in 0 channels
Get PRO
June '22
+56
in 0 channels
Get PRO
May '22
+24
in 0 channels
Get PRO
April '22
+1 295
in 0 channels
Get PRO
March '22
+14 593
in 0 channels
Get PRO
February '22
+1 248
in 0 channels
Get PRO
January '22
+3 354
in 0 channels
Get PRO
December '21
+10
in 0 channels
Get PRO
November '21
+120
in 0 channels
Get PRO
October '21
+18
in 0 channels
Get PRO
September '21
+1 060
in 0 channels
Get PRO
August '21
+1 878
in 0 channels
Get PRO
July '21
+3 486
in 0 channels
Get PRO
June '21
+2 099
in 0 channels
Get PRO
May '21
+3 766
in 0 channels
Get PRO
April '21
+3 994
in 0 channels
Get PRO
March '21
+124
in 0 channels
Get PRO
February '21
+2 523
in 0 channels
Get PRO
January '21
+169
in 0 channels
Get PRO
December '20
+109 570
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September+2
06 September+2
05 September0
04 September+1
03 September+10
02 September0
01 September+2
Channel Posts
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለ840 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ የይቅርታ መስፈርቱን ላሟሉ 840 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለ840 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ የይቅርታ መስፈርቱን ላሟሉ 840 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንዳስታወቁት ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩ ሲሆን በሕግ የተደነገጉ የይቅርታ መስፈርቶችን ማሟላታቸው በክልሉ የይቅርታ ቦርድ ተጣርቶ ቀርቧል። ታራሚዎቹ በመደበኛ የይቅርታ ሕግ እና ተጨማሪ መስፈርቶች መሠረት ይቅርታ የሚያስገኙ ሁኔታዎችን ያሟሉ መሆናቸውም ተገልጿል። ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል 56ቱ ሴቶች ሲሆኑ 784 ቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው።ታራሚዎቹ በማረሚያ ቤት የቆዩ ፣የጤና ችግር የነበረባቸው ፣በዕድሜ የገፉ፣ እንዲሁም ከተፈረደባቸው የእስራት ጊዜ አንድ ሦስተኛ ወይም ከግማሽ በላይ የሆነውን የቅጣት ጊዜ ያጠናቀቁ መሆናቸው ታውቋል። የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል ሊክሱ ይገባል ተብሏል። ማኅበረሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በጥፋታቸው ተፀፅተውና ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት ወደ መልካም እና አምራች ኑሮ እንዲመለሱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

2
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅ከጠዋቱ 2፡00-9፡30 👉ግብፅ ኤምባሲ፣ 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ ፣ የካቲት 12 ሆስፒታል፣ ኤፍቢ ግቢ፣ ናይጄሪያ ኤምባሲ፣ 20 ቀበሌ ፣ አፍንጮ በር ፣ ቀጨኔ ጉቶ ሜዳ ፣ ቤላ ኮሪያ ሰፈር ( ቤላ 05 ) ፣ ጃንሜዳ ፣ ጃንሜዳ መከላከያ እና አካባቢው 👉አለምባንክ ፣ ኢንዲያና ት/ቤት አካባቢ ፣ ታፍ ማደያ ፣ አቃቂ ብሩህ ተስፋ ት/ቤት ፣ ኮፊ ሲቲ ድረስ እና አካባቢው ✅ከጠዋቱ 4፡00-9፡00 👉ፉሪ ፣ አለምገና ፣ ሰበታ ፣ዲማ ፣ ሜታ ፣ ክሬቸር ፣ ኪዳነ ምህረት 👉 ሜታ አካባቢ ፣ ሰበታ ከተማ ፣ አለምገና ሚካኤል አካባቢ ፣ ገዳም ሰፈር ፣ ዳለቲ ኢንዱስትሪ ፣ ዳለቲ ቄራ ፣ ገዳምባ ፣ አለምገና ኢንዱስትሪ እና አካባቢው 👉ዓለምገና፣ዳለቲ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል ፡፡ ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
334
3
ያለባህር በር ውጤታማ አንሆንም‼️ ያለ ባሕር በር ባለቤትነት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ውጤታማ አገር መሆን አይቻልም - የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ዋና ሥራ አስፈጻሚ። ታከለ ኡማ፣ "የባሕር በር ባለ
ያለባህር በር ውጤታማ አንሆንም‼️ ያለ ባሕር በር ባለቤትነት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ውጤታማ አገር መሆን አይቻልም - የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ዋና ሥራ አስፈጻሚ። ታከለ ኡማ፣ "የባሕር በር ባለቤትነትን ካላሳካን፣ የፈለግነውን ቴክኖሎጂ ብናለማ፣ የፈለግነውን ያህል መርከብ፣ ባቡር እና የጭነትተሸከርካሪዎችን ብንገዛ ውጤታማ አገር  አንሆንም፡፡"ሲሉ ተደምጠዋል።
2 294
4
በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ ሞባይሎችን የገዙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ . በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በተለይም ሞባይሎችን የገዙና የተቀበሉ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ም
በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ ሞባይሎችን የገዙ ግለሰቦች  በቁጥጥር ስር ዋሉ . በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን  በተለይም ሞባይሎችን የገዙና የተቀበሉ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የቦንጋ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል። የቦንጋ ከተማ ወጣቶች ያለአግባብ እየታሰሩ ነው በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጾች የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑንና ዓላማውም ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በህግ እንዳይጠየቁ ለማድረግ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት በከተማው የስርቆት ወንጀል ተፈጽሞ የተሰረቁ ሞባይሎችን የሚገዙ፣ የሞባይል ይለፍ ቃል የሚጠልፉ እና ከህገወጥ የስርቆት ተግባር ፈጻሚዎች ጋር ግንኙነት ያላቸው አምስት ግለሰቦች በመረጃ እንዲለዮ ተደርጓል። በሞባይል ጥገና ስራ የተሰማሩ አራት ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።አንደኛው ተጠርጣሪ መሰወሩ የተገለፀ ሲሆን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ በክትትል ላይ ይገኛል ሲሉ ኢንስፔክተሩ ጨምረው ገልፀዋል።ተጠርጣሪዎቹ የተሰረቁ ሞባይሎችን የይለፍ ቃል በመክፈትና በውስጣቸው ያሉ መረጃዎችን በማጥፋት ገንዘብ ሲቀበሉ እንደነበር ተነግሯል። ፖሊስ በተጨማሪም የተሰረቁ ዕቃዎችን የሚገዙ፣ የሚረከቡና የሚያጓጉዙ ግለሰቦች እንዲሁም ባለሦስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎች በመኖራቸው ህብረተሰቡ እነዚህን ሕገወጥ ተግባራት ለመከላከልና ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ከፖሊስ ጋር እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
2 302
5
ህውሓት የአባሳንጆን የሸምግልና ጥረት ገለልተኝነት እና ተጨባጭ ይዘት ይጎለዋል ሲል ተቸ ህውሃት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን አባሳንጆ በትግራይ ሰላም ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረት የተቸ
ህውሓት የአባሳንጆን የሸምግልና ጥረት ገለልተኝነት እና ተጨባጭ ይዘት ይጎለዋል ሲል ተቸ ህውሃት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን አባሳንጆ በትግራይ ሰላም ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረት የተቸ ሲሆን፣ አሸማጋይነታቸው «ገለልተኝነት፣ ተጨባጭ ሀሳብ» እና ወደ ትርጉም ያለው ውይይት የሚያመራ ግልጽ መንገድ የጎደለው ነው ሲል ከሰሰ። ህውሃት ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ለሰላማዊ ውይይት ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፣ የኦሉሴጉን አባሳንጆ የሰላም ጥረት ከፌደራል መንግሥት ተፅዕኖ ነፃ ስለመሆኑ ጥያቄ አንስቷል። ድርጅቱ ማንኛውም የሰላም ሂደት ወገንተኛ ባልሆነ እና በገለልተኛ አሸማጋይ ሊመራ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል። መግለጫው አባሳንጆ በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል ውይይት ለማመቻቸት ቀደም ሲል ያደረጓቸውን ጥረቶች ተቃውሟል። ኦሉሴጉን አባሳንጆ ሰኔ 2018 ዓ.ም. በትግራይ ያደረጉትን ጉብኝት እና በአንድ ወይም በሁለት ሳምንታት ውስጥ ለመመለስ ገብተውት የነበረውን ቃል በማስታወስ፣ ሆኖም ከሁለት ወራት በኋላ መመለሳቸውን ጠቁሟል። @Seledadotio @Seledadotio
2 785
6
በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ:: በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክቷል።
በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ:: በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክቷል። በጥናቱ መሰረት ከ15 እስከ 24 በሚሆን የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ወጣቶች የሱስ ተጠቂ መሆናቸዉ ተረጋግጧል ሲሉ በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር አስካለማሪያም ቢክስ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ። እንደ ዶክተር አስካለማሪያም ገለፃ በወጣቶች ዘንድ የአልኮል ተጠቃሚነት ሱስ ከፍተኛዉን ድርሻ ይይዛል ። ሲጓራ እና ጫትን ጨምሮ ለማስታገሻነት በጥንቃቄ የሚወሰዱ መድኃኒቶችን ወጣቶች ለሱስ እንደሚጠቀሙበት ተገልጿል ። ወጣቶች ራሳቸዉን ከሱስ ለመጠበቅ እርስ በእርስ መረዳዳት ፣ጊዜያቸዉን ትርጉም ባላቸዉ ነገሮች ላይ ማሳለፍ ፣ስፖርት መስራት እና በሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ መሳተፍ እንዳለባቸዉ ተነግሯል።የሱስ ተጠቂነት የሚያስከትለው ጫና ቀላል አለመሆኑን የሚያስረዱት ስፔሻሊስቷ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ለራሳቸዉ ቅድሚያ በመስጠት ህክምና ማድረግ እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል ። ሱስ በአካል እንዲሁም በአእምሮ ላይ የሚያሳድረዉን ተፅዕኖ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተገንዝቦ ከመፈረጅ ይልቅ በዙሪያው ያሉ የሱስ ተጠቂዎች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርበታል ተብሏል ።
4 004
7
የዶናልድ ትራምፕ አዲስ የፀጉር ቀለም በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆነ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በኒው ጄርሲ አውሮፕላን ማረፊያ ከፕሬዝዳንታዊው አውሮፕላን ኤር ፎርስ ዋን ሲወር
የዶናልድ ትራምፕ አዲስ የፀጉር ቀለም በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆነ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በኒው ጄርሲ አውሮፕላን ማረፊያ ከፕሬዝዳንታዊው አውሮፕላን ኤር ፎርስ ዋን ሲወርዱ የታዩበት አዲስ ገጽታ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ​በፎቶዎቹ ላይ የፕሬዝዳንቱ ፀጉር ከተለመደው ቢጫ ቀለም ይልቅ ወደ ቡናማነት ያደላ ጠቆር ያለ ሆኖ በመታየቱ በርካታ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ልዩ ልዩ ግምቶችንና ቀልዶችን ሲሰነዝሩ ውለዋል። አንዳንዶች "ትራምፕ አሁን ጠይም ሆነዋል" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ ከታዋቂው ተዋናይ ብራድ ፒት ጋር አወዳድረውታል። ​ትራምፕ የዊግ ጥያቄን ቀደም ብለው አስተባብለው የነበረ ቢሆንም፣ የፀጉራቸው ቀለምና ቅርጽ በአጭር ጊዜ ውስጥ መለዋወጥ የህዝቡን ትኩረት መሳቡ አልቀረም። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ፀጉራቸው ቀለል ያለና ወፍራም ሆኖ መታየቱ ይታወሳል።
5 491
8
ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ። ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በ
ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ። ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በወጣ በሦስተኛው ቀን በድጋሚ በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው አቶ ያሬድ ገብረሚካኤል የተባለው ግለሰብ መሆኑ የአክሱም ከተማ ፖሊስ  አስታውቋል። የማዕከላዊ ዞን ዓቃቤ ሕግ ቢሮ እንዳስታወቀው ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ያለችን እህቱን ለመጠየቅ የመጓጓዣ ገንዘብ እንደሌለው በመግለጽ በዓድዋ ከተማ ቀይ መስቀል ማህበር አምቡላንስ ተሳፍሮ በመጓዝ ላይ በነበረበት ወቅት ነው። ግለሰቡ በተሳፈረበት አምቡላንስ ውስጥ ተቀምጦ የነበረውን የተሽከርካሪውን ቁልፍ ሰርቆ ከተሰወረ በኋላ በጸጥታ አካላት በተደረገ ክትትል በአክሱም ከተማ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።የአክሱም ከተማ ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዉን እጅ ከፍንጅ ይዞ በቁጥጥር ስር በማዋሉ አስፈላጊውን ማጣራት በማጠናቀቅ መዝገቡን ለዓቃቤ ሕግ አቅርቧል። ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤትም ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቀረበበትን የሰነድ እና የሰው ማስረጃ መርምሮ ግለሰቡ በተከሰሰበት የስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ6 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
6 973
9
"በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ ካልሆኑ ተማሪ አንመድብም" - ትምህርት ሚኒስቴር ​በትግራይ ክልል በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ግቢ ውስጥ የሚገኙ ታጣቂዎችና
"በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ ካልሆኑ ተማሪ አንመድብም" - ትምህርት ሚኒስቴር ​በትግራይ ክልል በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ግቢ ውስጥ የሚገኙ ታጣቂዎችና የወታደራዊ ኃይሎች እንቅስቃሴ በአስቸኳይ እንዲነሱ ትምህርት ሚኒስቴር ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ። ​🔹 ዋና ዋና ነጥቦች፦ ​የተተላለፈው ማሳሰቢያ፦ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለመቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች በላኩት ደብዳቤ፣ የዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢዎች ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲደረጉ አሳስበዋል። ​የተማሪዎች ደህንነት፦ በካምፓሶቹ ውስጥ የወታደራዊ ኃይሎችና የትጥቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸው የተማሪዎችን ደህንነትና ሰላማዊ የመማር-ማስተማር ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥል ሚኒስቴሩ ገልጻል። ​የሚኒስቴሩ ማስጠንቀቂያ፦ የዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢዎች ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው ካልተረጋገጠ ሚኒስቴሩ ወደ ተቋማቱ ተማሪዎችን እንደማይመድብ አስታውቋል። ​ @Seledadotio @Seledadotio
7 243
10
🌼🌻🌼ለአዲሱ አመት አጭር ጊዜ የሚቆይ ትልቅ Discount🌼🌻🌼 ውበት እና ምቾት ያላቸው ኮምፈርቶች እናንተ በመረጣችሁት ከለር 🎨፣ እንደ አልጋዎቻችሁ ስፋት 📏 (በተለያዩ ሜትሮች) እንዲ
🌼🌻🌼ለአዲሱ አመት አጭር ጊዜ የሚቆይ ትልቅ Discount🌼🌻🌼   ውበት እና ምቾት ያላቸው ኮምፈርቶች እናንተ በመረጣችሁት ከለር 🎨፣ እንደ አልጋዎቻችሁ ስፋት 📏 (በተለያዩ ሜትሮች) እንዲሁም የተለያዩ የዋጋ አማራጮች 💰 አሟልተን አስገብተናል። ምቾትና ጥራታቸው በገበያው ላይ ካሉት ኮምፈርቶች ሁሉ በግልጽ የሚታይ ልዩነት  አሏቸው። ነጻ ዴሊቨሪ 🚚📦 በአዲስ አበባ 🌆 የምትገኙ ደንበኞቻችን ባላችሁበት በነጻ  እናደርሳለን። በክፍለሀገር 🌍 የምትገኙ �ደንበኞቻችን ደግሞ አዲስ በጀመርነው የስርጭት አገልግሎት 🚛ዴሊቨሪ እናደርጋለን። በፍጥነት ይደውሉ! 📞⚡️ 📞 ስልክ: 0910975512 https://t.me/joinkelalshopping
6 617
11
የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ከጀሞ ፒያሳ የፈጣን አውቶቡስ መስመር ግንባታን በልዩ ትኩረት እየከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ የአአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ
የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ከጀሞ ፒያሳ የፈጣን አውቶቡስ  መስመር ግንባታን በልዩ ትኩረት እየከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ የአአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳኛቸዉ ሽፈራዉ ከጣቢያችን ኢትዮ ኤፍ ኤም  ጋር በነበራቸው ቆይታ ከፍተኛ የትራንስፖርት ፍላጎትና የአቅርቦት አለመመጣጠን ለመፍታት የከተማ አስተዳደሩ የጀሞ-ፒያሳ የፈጣን አውቶቡስ  መስመር ግንባታን በልዩ ትኩረት እየከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ይህ 15 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ፕሮጀክት አውቶቡሶች ብቻ የሚጓዙበት የተለየ መስመር የሚኖረው ይሆናል ብለዋል። ወደ አገልግሎት ሲገባ በአንድ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝብ የማጓጓዝ አቅም ስለሚኖረው፣ በአካባቢው የሚታየውን የታክሲ ሰልፍ በእጅጉ እንደሚያቃልል ይጠበቃል። የትራንስፖርት ቢሮው እንደገለጸው፣ ፕሮጀክቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የክትትል ስርዓት የሚኖረው ሲሆን፣ አውቶቡሶቹ የሚመጡበትን ሰዓት ተሳፋሪዎች አስቀድመው እንዲያውቁ የሚያስችል አሰራርም ይኖረዋል ብለዋል። ይህ የትራንስፖርት ስርዓት በሌሎች የከተማዋ ዋና ዋና መስመሮች ላይም ተሞክሮው እንዲሰፋ እቅድ ተይዞለታል ተብሏል።
6 744
12
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁሉም መሥሪያ ቤቶች፣ ቢሮዎች እና የመንግሥት ተቋማት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ያላቸውን የገቢ እና የወጪ ሂሳቦች ዘግተው ወደ ስኬት ባንክ እንዲያዛውሩ ትዕዛዝ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁሉም መሥሪያ ቤቶች፣ ቢሮዎች እና የመንግሥት ተቋማት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ያላቸውን የገቢ እና የወጪ ሂሳቦች ዘግተው ወደ ስኬት ባንክ እንዲያዛውሩ ትዕዛዝ አስተላለፈ ​ከተማ አስተዳደሩ 50 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ባለው በዚህ ባንክ ውስጥ ሂሳብ እንዲከፍቱ ከተወሰነባቸው መካከል 180,078 የከተማዋ ሰራተኞች ይገኙበታል። አስተዳደሩ ለአዲሱ የበጀት ዓመት 502 ቢሊዮን ብር የገቢ ግብ የያዘ ሲሆን፣ ይህ ትልቅ የገንዘብ እንቅስቃሴ ወደ ስኬት ባንክ መዞሩ የባንኩን አቅም በእጅጉ ያሳድገዋል ተብሎ ይገመታል። ​ነገር ግን ከብድር፣ ከእርዳታ እና ከስጦታ ጋር የተያያዙ የሂሳብ ቁጥሮች አሁንም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስር ሆነው እንደሚቀጥሉ ታውቋል። ይህ ውሳኔ የከተማዋን የፋይናንስ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የመቀየር አቅም ያለው ነው:: @Seledadotio @Seledadotio
6 925
13
የአሜሪካ ፍርድ ቤት ለኢትዮጵያ እና ለሌሎች ሀገራት የዲቪ-2026 አመልካቾች ተስፋ ሰጪ ውሳኔ አስተላለፈ የካሊፎርኒያ ክልላዊ ፍርድ ቤት ዳኛ ኤድዋርድ ዳቪላ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚስቴር በዲቪ አመልካቾች ላይ ተጥለው የነበሩ የቪዛ እገዳዎችን የሚያነሳ ውሳኔ ማስተላለፋቸውን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ የ48 ሀገራት አመልካቾች የቪዛ ሂደታቸውን እንዲቀጥሉ መንገድ መከፈቱ ተገለጸ። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚስቴር ቀደም ሲል ጥሎት የነበረውን እገዳ ያነሳ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን፣ አመልካቾች እስከ መስከረም 20 ቀን 2019 ዓ.ም በሚጠናቀቀው የዲቪ-2026 ፕሮግራም ገደብ ውስጥ ሰነዶቻቸውን ማቅረብ እና የተያዙላቸውን ቃለ-መጠይቆች መከታተል እንደሚችሉ አስታውቋል። ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ እድል ይዞ የመጣ ሲሆን፣ ከ49 የአፍሪካ ሀገራት የተመረጡ እና ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ 53 ሺህ 939 ሰዎች በDV-2026 ተመዝግበው ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከል ግብፅ በ5,527 ከፍተኛውን ቁጥር ስትይዝ፣ አልጄሪያ በ5,457፣ ሱዳን በ5,226፣ ኬንያ በ3,949 እንዲሁም ኢትዮጵያ በ3,287 አመልካቾች ቀጣዩን ደረጃ በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ። ባለፉት አምስት ዓመታት ከ50 ሺህ በላይ ስደተኞችን ወደ አሜሪካ የላኩ እንደ ናይጄሪያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ያሉ ሀገራት በዚህ ፕሮግራም ውስጥ አልተካተቱም። በአለም አቀፍ ደረጃ ከ20.8 ሚሊዮን በላይ ብቁ ተወዳዳሪዎች መካከል 129,516 ሰዎች ለዲቪ-2026 የተመረጡ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ በየዓመቱ እስከ 55 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የአሜሪካ ቋሚ መኖሪያ ቪዛ ይሰጣል። @Seledadotio @Seledadotio
7 243
14
🌼🌼🌼🌼 በግ በኪሎ 🌼🌼🌼🌼 👉 0982 - 89 89 40 የበዓል ገበያ ድካም ቀረ! በስጋቸው ጣዕም እና ጥራት የሚታወቁትን እውነተኛ #የደብረብርሃን በግና ፍየሎች በኪሎ መዝነን ባሉበት
🌼🌼🌼🌼 በግ በኪሎ 🌼🌼🌼🌼          👉  0982 - 89 89 40    የበዓል ገበያ ድካም ቀረ! በስጋቸው ጣዕም እና ጥራት የሚታወቁትን እውነተኛ #የደብረብርሃን በግና ፍየሎች በኪሎ መዝነን ባሉበት እናቀርባለን። ፈጥነዉ ይደዉሉ☎️📞 0982 - 89 89 40
7 146
15
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው! ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚ
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው! ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ አልበም ሊያሰራጩ መሆኑን ገልጸዋል። ፖለቲከኛው አዲስ የከፈቱትን የዩቲዩብ ገጽ ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሳወቁት የሙዚቃ አልበሙን ያዘጋጁት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ነው። እንደሚታወሰው ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ አልበሙን ካሰራጨ በኋላ የፈጠረውን ተጽእኖ ተከትሎ አቶ ልደቱ በወቅቱ፣ "የመንፈስ ቅናት አደረብኝ" ሲሉ ገልጸው ነበር።
8 544
16
አርሰናል 3ኛ ተከታታይ ድሉን አሳካ በሦስተኛ ሳምንት እጅግ ተጠባቂው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል ቼልሲን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በኢምሬትስ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት 3
አርሰናል 3ኛ ተከታታይ ድሉን አሳካ በሦስተኛ ሳምንት እጅግ ተጠባቂው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል ቼልሲን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በኢምሬትስ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ካይ ሃቨርትዝ እና ማርቲን ኦዴጋርድ አስቆጥረዋል። ቼልሲን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ሞርጋን ሮጀርስ ከመረብ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በሊጉ ያደረጋቸውን ተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አድርጓል። የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በሊጉ ከተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ድል በኋላ ሽንፈት አስተናግዷል። አስቀድሞ በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ ከኤቨርተን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት መለያየቱ ይታወቃል።
8 487
17
26 ስልክና 34 ሺህ ብር የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️ በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች አደረጃጀት ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት 26 ስልክ እና 34,000 ብር የ
26 ስልክና 34 ሺህ ብር የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️ በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር  የወጣቶች አደረጃጀት ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት 26 ስልክ እና 34,000 ብር የሰረቀን ግለሠብ በቁጥጥር ስር አውለዋል። ‎
8 498
18
አሳዛኝ ዜና‼️ ከአድስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በሸኖ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አልፏል! 18 የሚደርሱ ቆስለዋል። ሸኖ — በሸኖ ከ+2
አሳዛኝ ዜና‼️ ከአድስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በሸኖ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አልፏል! 18 የሚደርሱ ቆስለዋል። ሸኖ — በሸኖ ከተማ አስተዳደር ኦንቱ ቀበሌ፣ «አዳ ሀሮ» ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፣ በ18 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው የትራፊክ ደህንነት ክፍሎች አስታወቁ። የሸኖ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አብዲሳ መርጋ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ 3-A04933 አ.አ የሆነ ‘ባስ ኤፍኤም’ የህዝብ ማጓጓዣ ተሽከርካሪ ከሚፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከሩ ምክንያት ነው ብለዋል። በአደጋው ሕይወታቸው ካለፉት 6 ሰዎች መካከል 2 ወንዶች እና 4 ሴቶች እንደሚገኙበት ታውቋል። በተጨማሪም ጉዳት ከደረሰባቸው 18 ተጓዦች (12 ወንዶች እና 6 ሴቶች) ውስጥ 13ቱ ከባድ እና መካከለኛ አደጋ የገጠማቸው ሲሆን፣ አምስቱ ደግሞ ቀላል ጉዳት አስተናግደዋል። የሟቾች አስከሬን በህብረተሰቡና በትራፊክ ፖሊስ አባላት ትብብር ወደ ሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን፣ ተጎጂዎችም በዚሁ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ለተሻለ ህክምና ወደ ሌሎች ከፍተኛ ሆስፒታሎች የተላኩ ሲሆን፣ አነስተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ጉዟቸውን ወደ ደብረ ብርሃን እና አዲስ አበባ መቀጠላቸው ተገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio
9 022
19
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅ከጠዋቱ 2፡00-9፡30 👉ጎፋ ካምፕ ፣ ሀዋርያው ቸርች ፣ ኪዳነምህረት ቤተ ክርስቲያን፣ መካኒሳ አረቄ ፋብሪካ መብራት ፣ ቆሬ አደባባይ ፣ አሚጎ ኮንዶሚንየም በከፊል፣ ፋና ት/ቤት እና አካባቢው፣ 👉ኮዬ 05 ፕሮጀክት 16 በከፊል፣ ፕሮጀክት 12 ፣ ፕሮጀክት 17  እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡ ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት @Seledadotio @Seledadotio
8 290
20
ቢኒያም ሽብሬ ከማስተር ሀገረሰላም አርባ (ቦንጆ) ጋር በ Ethio Fight ይፋለማሉ! ከ16 ቀን በኋላ በጉጉት በሚጠበቀው የ Ethio Fight የትግል ውድድር ላይ፣ ቢኒያም ሽብሬ ከሌላኛው ጠንካ+1
ቢኒያም ሽብሬ ከማስተር ሀገረሰላም አርባ (ቦንጆ) ጋር በ Ethio Fight ይፋለማሉ! ከ16 ቀን በኋላ በጉጉት በሚጠበቀው የ Ethio Fight የትግል ውድድር ላይ፣ ቢኒያም ሽብሬ ከሌላኛው ጠንካራ ተፎካካሪ ማስተር ሀገረሰላም አርባ (በቅፅል ስሙ "ቦንጆ") ጋር እንደሚፋለም ታውቋል። ከአሜሪካ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ የገባው ቢኒያም ሽብሬ በአሁኑ ሰዓት ደማቅ አቀባበል እየተደረገለት የሚገኝ ሲሆን፣ የትውልድ አካባቢው የፈረንሳይ ሌጋሲዮን ወጣቶችም ለተፎካካሪው ልዩ የድጋፍ እና የአቀባበል ስነ-ስርዓት አዘጋጅተውለታል። ሁለቱ ጠንካራ ስፖርተኞች የሚያደርጉት ይህ ታላቅ ፍልሚያ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ግምትና ትኩረት አግኝቷል። ይህንን ታላቅ ውድድር ጉርሻ ፔጅ በስፋት ሽፋን መስጠት ይጀምራል። መልካም እድል ከወዲሁ ለሁሉም ተፋላሚዎች @Seledadotio @Seledadotio
8 464