🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
کانال 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 114 مشترک است و جایگاه 7 540 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 777 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 114 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -24 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -2 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 27.07% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.17% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 280 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 596 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 38 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 15 ژوئن | 0 | |||
| 14 ژوئن | 0 | |||
| 13 ژوئن | +1 | |||
| 12 ژوئن | +7 | |||
| 11 ژوئن | +7 | |||
| 10 ژوئن | 0 | |||
| 09 ژوئن | +4 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | +2 | |||
| 05 ژوئن | +5 | |||
| 04 ژوئن | +1 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | +4 | |||
| 01 ژوئن | +2 |
| 2 | ✍
ኢማም ለተከታዮቹ የሚሸፍንላቸው ስድስት ነጥቦች!!
1ኛ, ከፋቲሓ በኋላ ያለው ቂርኣት;
የትኛውም ሰላት ላይ ፋቲሓ መቅራት በሁሉም ሰጋጅ ላይ ግዴታ ነው። ከፋቲሓ በኋላ ያለው ቂርኣት ግን ጀህር ላይ ከሆነ ማእሙም የኢማሙን ቂርኣት ያዳምጣል እንጂ በራሱ አይቀራም።
2ኛ, የማሟያ ሱጁድ;
ከኋላ የሚሰግደው ማእሙም ሰላቱ ላይ ሰላትን የማያፈርስ ስህተት ወይም መርሳት ቢያስገኝ ለብቻው የማሟያ ሱጁድ አያደርግም: የኢማሙ ሰላት ለእሱ ስህተት ያሟላለታል። ኢማሙ በራሱ የተሳሳተው ነገር ኖሮ ሱጁድ ከወረደ ግን ተከታዩ ምክንያቱ ባያውቅም ኢማሙን ተከትሎ ሱጁድ ያደርጋል።
3ኛ, የቲላዋ ሱጁድ;
ኢማሙ ሱጁድ የሚወረድበት አንቀጽ ቀርቶ ሱጁድ ከወረደ ማእሙም ተከትሎ ይወርዳል፤ ሳይወርድ ካለፈውም ተከታዩ ተነጥሎ ሱጁድ አያደርግም። እንዲሁም; ድምፅ ሳይወጣ በሚሰገድባቸው ሰላቶች ማእሙም ሱጁድ የሚወረድበት አንቀጽ ቢቀራ እንኳ ኢማሙን ትቶ ሱጁድ አያደርግም።
4ኛ, ሱትራ;
ኢማም ያደረገው ሱትራ ለሁሉም ማእሙሞች ይሆናል። ኢማም ተከትለህ እየሰገድክ አንዱ ከፊትህ ማለፍ ቢፈልግ መከልከል የለብህም: ምክንያቱም አንተ የምትወከለው በኢማምህ ሱትራ ነው።
5ኛ, የቁኑት ዱዐ;
የቁኑት ዱዐ በሚደረግባቸው ሰላቶች ላይ ማእሙም የኢማሙን ዱዐ እየሰማ "ኣሚን" ይላል እንጂ እሱ የራሱ ዱዐ አያደርግም።
6ኛ, "سمع الله لمن حمده " ማለት;
ከሩኩዕ በኋላ ኢማም "سمع الله لمن حمده" ሲል ማእሙም "ربنا ولك الحمد" ወይም መሰሎቹ ይላል እንጂ: ለብቻው እንደሚሰግድ ዓይነት "سمع الله لمن حمده" አይልም። | 1 701 |
| 3 | ✍
የመፈመስ ጉጉት ያለው ሰው
የአኼራ ጥፍጥና ሊያገኝ አይችልም!! | 1 730 |
| 4 | ✍
ስራ ቦታ ሴት ቀጥሮ ቀኑን ሙሉ ከእሷ ጋ የልብልቡን ሲያወራ ይውልና: ማታ መጥቶ ድካሙን ሲያራግፍብሽ;
የምር የሚስትነት ክብር ይሰማሻል ወይ?? | 2 062 |
| 5 | ✍
ልጄ አንባቢ እንዲሆን ምን ላድርግ?
ሲለው;
📖መጽሐፉ ለእሱ ከማስያዝህ በፊት ቀድመህ አንተ ያዘው። ልጆች የሚያንፀው ምክር ሳይሆን ተግባር ነው!!
አለው። | 2 123 |
| 6 | ✍
ከዝያ በኋላስ????
ثم ماذا؟؟؟؟؟؟؟؟
በሕይወታችን አንድ ቀን እንኳ ከራሳችን ጋ አውርተን ይህንን ጥያቄ እኛው ለእኛው ጠይቀን እናውቅ ይሆን?
"ከዝያ በኋላስ???" "ثم ماذا؟؟؟"
ነብዩ ሙሳﷺ አጀላቸው በደረሰ ጊዜ መለከል መውት ሩሓቸው ከጀሰዳቸው ሊለየው ሲመጣ እንደ ሌሎች ነብያቶች "በመኖርና በመሞት መሃል" አላስመረጣቸውም ነበር። በሰው ተመስሎ ሩሓቸው ሊነጥቃቸው ሰተት ብሎ ገባ። እሳቸውም ያንን ቂብጥይ እንኳ በአንድ ቡጢ መግደል የቻሉ ፈርጣማ እንጂ የዋዛ አልነበሩምና ሩሓቸው ሊወስድ የመጣውን መለክ በሞቀ ጥፊ አጮሉት። የጥፊው ክብደት የታወቀው መለከል መውት ዓይኑን እንደጠፋ ሲነገር ነበር።
የሙሳ ጥፊ ዓይኑን ያጠፋው መለከል መውት ወደ ጌታው በመመለስ «አላህዬ! ሞት ወደ ማይወድ ባሪያህ ልከኸኝ ይኸው ዓይኔን አጥፍቶልኝ ተመለስኩ» አለ።
ልዕለ ሀያሉ አላህ መለከል መውትና ሙሳ መሃል ስለሚከሰተው ነገር ገና መለኩ ወደ ሙሳ ከመላኩ በፊት አስቀድሞ ያውቃል። ይህንን ያደረገበትም ይሁን: ለሌሎች ነብያቶች በሚያስመርጠው መልኩ ለመሳ ሳያስመርጥ መላኩ የላከበት ትልቅ ጥበብና ምክንያት አለው።
አዎ.... ይህንን ክስተት የሰማ ያነበበ ሁሉ ሁል_ጊዜ ከራሱ ጋ "ከዝያ በኋላስ?? ثم ماذا؟؟" እያለ እንዲጠያየቅ አላህ ይፈልጋል።
ወደ ክስተቱ ስንመለስ......
መለከል መውት ወደ አላህ ሄዶ ሙሳ በጥፊ ብሎ ዓይኑን እንዳጠፋበት ሲነግረው: ተመልሶ እንዲሄድና ለሙሳ ሌላ አማራጭ እንዲያቀርብለት ነገረው።
«ወደ ሙሳ ተመለስና ዱንያ ላይ መቆየት የሚፈልግ ከሆነ መዳፉን በበሬ ቆዳ ላይ እንዲያሳርፍ ንገረው፤ መዳፉን ባረፈበት ፀጉር ልክ በያንዳንዱ ፀጉር አንድ አንድ ዓመት ይሰጠዋል» አለው። መለከል መውት ይህንን ተልዕኮ ይዞ ወደ ሙሳ በመመለስ ጌታው ያቀረበለትን ነገረው። በዚህ ጊዜ ሙሳ «ثم ماذا يا رب?« «ጌታዬ ሆይ ከዝያ በኋላስ?» አለ።
"እጄን ከበሬ ቆዳ ላይ አሳርፌ በነካሁት የፀጉር ብዛት ልክ የሆኑ ዓመታቶች ተጨምረውልኝ ከኖርኩ በኋላስ ምንድን ነው የሚጠብቀኝ??" ማለቱ ነው።
ጌታው ሲመልስለት «ثم الموت» «ከዝያማ ሞት ነው» አለው። ሙሳ «فالآن» «እንግዲያውስ አሁኑኑ ይሁንልኝ» አለ።
ሰው ነንና ብዙ እናስባለን: ብዙ እናቅዳለን። ያላገባው ስለወደፊት ትዳሩ፤ ያገባው ስለልጆቹ አስተዳደግና አያያዝ፤ የሚማረው ስለ ቀጣይ ሕይወቱ፤ ነጋዴው ቀጣይ ስለሚሰራው ቤትና ስለሚነዳው መኪና......፤ በጣም ብዙ ብዙ ነገሮች እናስባለን። ሀሳባችን ሲጎለብት ዕቅድ አውጥተን ጉዞ እንጀምራለን። ግና....... "ከዝያ በኋላስ??? የሚለው ጥያቄ ለምን እንረሳዋለን።
ዕቅድህ ሙሉ ባይሆን እንኳ በከፊል ተሳካ እንበል; ደረስክ... አገባህ... ወለድክ... ዳርክ... ቤት ሰራህ... መኪና ገዛህ... ምናምን... ምናምን;
ከዝያ በኋላ የሚጠብቅህ ምንድን ነው??????
ዕቅድህ ላይ ሞት ጨምርበት!! | 2 335 |
| 7 | خطبة الجمعة للشيخ حسين آل الشيخ 26 ذو الحجة 1447هـ
https://youtu.be/I8DuBgrsmUA | 1 957 |
| 8 | خطبة الجمعة للشيخ فيصل غزاوي 26 ذو الحجة 1447هـ
https://youtu.be/0NKy0jjPhg8 | 1 984 |
| 9 | ✍
መንግስት ለታርጋ ቅያሪ ያወጣው የዋጋ ተመን ስሰማ "መንግስት ጤና የለውም እንዴ?" ብዬ አብዮት ላስነሳ አስቤ ነበር፤
በኋላ ግን ባለ መኪናዎቹ ምንም ሳይመስላቸው እየከፈሉ: ተቃውሞ የምናሰማው ታክሲ ውስጥ በትርፍ የተቀመጥነው መሆናችን ስመለከት ነው እዚህ ሀገር ጤና ያለው ህዝብም ይሁን መንግስት እንደሌለ የተገለጠልኝ!! | 2 000 |
| 10 | ✍
«ከቀናቶቻችሁ በላጩ ቀን የጁሙዐ ቀን ነው፤
በእሱ ኣደም ተፈጥሮበታል, በዚሁ ቀን ሞቷል፤
በዚሁ ቀን ጥሩንባ ይነፋል, በዚሁ ቀን (ለቂያማ) ሁሉም ራሱን ስቶ ይወድቃል፤
በዚህ ቀን በእኔ ላይ ሰላት (ሰለዋት) ማውረድን አብዙ የእናንት ሰላት (ሰለዋት) ወደ እኔ ይቀርብልኛል።»
/ረሱልﷺ/ | 2 061 |
| 11 | ✍
የዕዝነት የፍትህ የሰላም ተምሳሌት፣
ከሰው ልጅ የላቁ የክብር ባልተቤት፤
ዛፉ እንደ ህፃን ያለቀሰላቸው፣
ግመል ስሞታውን የሚያሰማቸው፤
ድንጋይ ሰላምታውን ያቀረበላቸው፣
ስሞትን ሳወሳ ልቤ ይፈወሳል፤
ሀሳብ ጭንቁ ረስቶ ሰኪናን ይወርሳል!!
አላህ ይወፍቀኝ የእርሶን ጉርብትና፤
በተውሒድ አኑሮ ይውሰደኝ በሱና።
ሸፍዓዎት ያድለኝ አላህ በዕዝነቱ
ከሐውዶም ያጠጣኝ ያስገባኝ ጀነቱ።
ሰላትና ሰላም ይውረድ በሙሐመድ
በተከተላቸው ሱናቸውን በመውደድ‼️
🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙
📖{إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا}
🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙
| 2 185 |
| 12 | ✍
ጥበብና ዕውቀት ሲያብሩ!!....
ደሓክ ኢብኑ ሙዛሂም የተባለው ጋ የሚመላለስ አንድ ነሷራ ነበር። "ወደ እስልምና ለምን አትገባም?" ብሎ ሲጠይቀው;
"ለኸምር ያለኝ ፍቅር ነው ከመስለም የከለከለኝ" አለው።
"እሱማ አያሳስብህ: ሰልመህም ትጠጣለህ" አለው።
ነስራኒው ሰለመ። ከሰለመ በኋላ ደሓክ "አሁን ሰልመሃል: ኸምር ከጠጣህ ሓድ እናቆምብሃለን፤ ከተመለስክ ደግሞ በሙርተድ ሑክም እንገድልሃለን!!" አለው።
ሰውየው ግን ከሰለመ በኋላ እስልምናው አምሮለት ሷሊሕ ሰው ሆኖ ኖረ። | 2 098 |
| 13 | ✍
በዱንያም ይሁን በአኼራው መንገድ ላይ ክፉ እንቅፋት ማለት፦
አስተካካይ መስለው አጥፊዎች ናቸው!! | 2 288 |
| 14 | ✍
ሙሳﷺ በሕይወት ቢኖር; ከሙሐመድﷺ መንሓጅ ሌላ መከተል አይሰፋለትም ነበር።
ዒሳﷺ መጨረሻው ዘመን ላይ ወደ ምድር ሲወርድ; በሙሐመድﷺ መንሓጅ ነው የሚፈርደው።
አንድ ሰው ከረሱልﷺ መንሓጅ ውጪ ተከትሎ እንዴት ሊድን ይችላል??
ምክንያቱም፦
ከአላህ ጋ መገናኛ ብቸኛው መንገድ የነብዩ ሙሐመድﷺ መንገድ ነው!!
| 2 262 |
| 15 | 👆
ላጤያንስ እያነበባችሁ። | 2 429 |
| 16 | ✍
"ከማን ጋ ነህ?" ስትባል
የምታፍርበት ጓደኛ አትያዝ!! | 2 379 |
| 17 | 🕌
ስላቭ..... ስላቭ...... ስላቭ
እንኳን ደስ አላችሁ!! ለሦሥተኛው ፍሎር ስላቭ ደርሰናል!!
ከአላህ እገዛ በኋላ በወንድሞች ብርቱ ትብብር ተጀምሮ በሂደት ላይ ያለው ትልቁ የፉርቃን መስጂድ የግንባታ ፕሮጀክት ለሦሥተኛው ፍሎር ሙሌት ደርሰን ለዚህ ትልቅ የጀነት ድግስ ለሁሉም ጥሪያችን እናስተላልፋለን!!
የሁለተኛው ስላቭ ሲሞላ በወርሀ ረመዷን በጾመ አንጀታቸው ለሁለት ቀናት በትጋት ለፍተው ተኣምር ያሳዩ ወንድሞች;
አሁንም እንደተለመደው በፅኑ ልብና በብርቱው ክንዳቸው "ወዬ" ይሉ ዘንዳ እናት ፉርቃን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ
ሰኔ_6 እና ሰኔ_7
ከፈጅር ሰላት ጀምሮ የስላቭ ሙሌቱ ይጀመራል!!
ሁላችሁም በጊዜ ተገኝታችሁ የጀነቱ ቤታችሁ ግንባታ ታስፋፉ ዘንዳ በድጋሚ የአክብሮት ጥሪያችን እናስተላልፋለን!!
💪ወንድ ሁን..... በጊዜ ተገኝተህ እስከ ፍፃሜው ስራ!!
https://t.me/Al_Furqan_Islamic_Studio/20686?single | 1 888 |
| 18 | ✍
በሁሉም ዘመናት የነበሩ ሙሽሪኮች ነብይ በሚላክላቸው ጊዜ ለነብዮቻቸው ተኣምር አሳዩን ብለውው ይጠይቋቸው ነበር;
አንድም ቀን ግን በባጢል ስለሚያመልኳቸው ጣዖታት አንዲትም መረጃ ጠይቀው አያውቁም!! | 2 675 |
| 19 | - @ccdBot. | 2 538 |
| 20 | ✍
ልቡ ውስጥ እውነተኛ ኢማን ኖሮ 🕋ወደዚህ ቤት የማይናፍቅ ማን ይኖራል ከቶ????
🤲አላህዬ አደራህ🤲 | 2 332 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
