🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
کانال 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 188 مشترک است و جایگاه 7 397 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 756 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 188 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 05 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 68 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 9 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.34% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.70% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 089 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 670 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 40 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 05 ژوئیه | +9 | |||
| 04 ژوئیه | +13 | |||
| 03 ژوئیه | +1 | |||
| 02 ژوئیه | +8 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | 🕋
ቢደጋገም የማይሰለች ሰበር ዜና!!
የሁል ጊዜ ተወዳጅ እና ተመራጭ የሆነው የለምለም ትራቭል ልዩ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅቶ ምዝገባው ተጀምሯል።
የአላህ ዕዝነት ይበልጥ በሚከጀልበት በክረምቱ ወቅት; ከሚወርደው በረካ እና ዕዝነት የተሻለውን ለመውሰድ የክረምቱ መግቢያ በአላህ ቤት ትቀበሉ ዘንዳ ዕድሉን ተጠቀሙበት።
የዑምራ ጉዞው የሚሆነው በአላህ ፍቃድ ከሐምሌ16 እስከ ሐምሌ26
ወይም ከJuly23 እስከ August2 ይሆናል።
ረሱልﷺ ሕያው ሆነው የተሰደዱባትና ሲሞቱም የተቀበሩባት መዲነቱል ሙነወራ ጨምሮ የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ ያካተተው ፓኬጃችን ላይ ፈጥነው በመመዝገብ የማይረሳና ትክክለኛ ዑምራ ታደርጉ ዘንድ ትራቭላችን በአክብሮት ይጋብዛችኋል።
ፓኬጁ የሚያካትተው፦
የተረጋገጠ የዑምራ ቪዛ፤
የደርሶ መልስ የአየር ትኬት፤
እስከ መመለሻው ቀን ሆቴል፤
የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ፤
የመንቀሳቀሻ የባስ ትራንስፖርት ይገኙበታል።
✈️የለምለም ትራቭል.... የትውልዱ ተስፋ!!
🤳 0911674580
🤳 0922448888
🤳 0911683917
🏢ቤተል ሚና ሞል 2ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
👇 👇 👇 👇 👇 👇 👇
https://t.me/Yelemlem_travel | 325 |
| 3 | ✍
ሁለተኛ እንዳገቡ ብዙ ወንድሞች ነግረውህ ሊሆን ይችላል;
ሦሥተኛ ወይም አራተኛ እንዳገባ የነገረህ ግን አንድም ሰው የለም። ካለም በጣም ጥቂት ነው።
ምክንያቱም፦
ሐበሻ መከራ መከራውን እንጂ ሲደላው መንገር አይወድም። | 1 832 |
| 4 | ✍
ያልቸኮለ ብቻ ያንብበው!!
በበፊቱ ጊዜ.......
አንድ ሰው ንግዱ ቢከስርበት; ዘመድ አዝማድ: ተሰብስቦ ሁሉም የየአቅሙን በማድረግ የከሰረው አካል በቶሎ እንዲያገግም እርዳታ ይደረግለት ነበር።
አንድ ሰው ሙሲባ ደርሶበት ቢጎዳ; ጎረቤቶቹ ተሰባስበው ከማፅናናት በተጨማሪ ለሙሲባው መካሻ የሚሆን ነገር በማቅረብ ቁስሉን አክመው ቀዳዳውን ይሸፍኑለት ነበር።
አንድ ሰው ከባድ ጉዳይ ቢገጥመው; ወዳጆቹና ጓደኞቹ ተጠራርተው ጉዳዩን እንደጉዳያቸው በማየት ሁሉም የድርሻው ተካፍሎ ሸክሙን ያቀሉለት ነበር።
አሁን ላይ ግን......
አንዱ ችግር ደርሶበት ወደ ዘመዶቹ ቢመለከት; እነርሱ ላይ የደረሰው ችግር ከእሱው የከፋ ሆኖ ያገኘዋል፤
ደክሞ አቅም አጥቶ የጎረቤቶቹ እገዛ ፍለጋ ቢወጣ; ከእሱ ብሰው የደከሙ ሆነው ያገኛቸዋል፤
ሀሳቡን የሚጋራው: አድምጦ አቅጣጫ የሚያሳየው ጓደኛው ቢፈልግ; ጓደኛው ካለበት ውጥረት አንፃር የእሱው ቀላል እንደሆነ አምኖ ይመለሳል።
ይህ ብቻም አይደለም፨
በበፊቱ ጊዜ........
የሆነ ከበድ ያለ ህመም ታመህ ከሆነ; ሌላ ከባድ ህመም የሚገጥምህ ከብዙ ዓመታት በኋላ ነበር፤
ኪሳራ ቢደርስብህም; ቀጣይ ዓመታቶች በተሻለ ትበለፅጋለህ እንጂ ዳግም ሌላ ኪሳራ ማየትህ የተለመደ አልነበረም።
እንደውም "እከሌ ከሰረ" ማለት እንደ ሰበር ዜና ከስንት አንዴ የሚሰማ ዐረፍተነገር ነበር።
አሁን ላይ ግን.......
ከታመምክ; ቀድሞ የጀመረህ የቱ እንደነበር እስከምትረሳው ድረስ ህመሞቹ ይደራረቡብሃል፤
አንዴ መስመር ስተህ ኪሳራ ከቀመስክ; መኖር እስክትጠላ ድረስ ይከታተልብብሃል።
ዋሸሁ እንዴ??????
ያለነው ኣኺሩ ዘማን ላይ አይደለ??......
እንደ ጨለማ የተደራረቡ ፈተናዎች የሚመጡት "ዳዕዋ" ላይ ብቻ ሳይሆን: ፐርሰናል ላይፍ ላይም መሆኑን ተገንዝባችሁ ሸሪዓዊ መጠበቂያዎች እንድቲዙ ነው።
አላህ በግዴታነት የደነገጋቸው ዒባዳዎች ከመፈፀም በተጨማሪ;
የጠዋትና የማታ አዝካር በቋሚነት መያዝ ከሁሉም ፈተና ለመጠበቅ ሰበብ ከሚሆኑ ትላልቅ ምሽጎች አንዱ ነው።
🤲ድብቅም ይሁን ግልፅ ከሆኑ ፊትናዎች ሁሉ አላህ ይጠብቀን!! | 2 091 |
| 5 | ✍
የበፊቶቹ.....
ለወር ለሁለት ወር ሳይገናኙ ቆይተው ሲገናኙ; "እንዴት ነህ? ቤተሰብ እንዴት ነው?" ከማለት ሌላ ዝርዝር አይጠያየቁም ነበር። ሆኖም አንዱ ለሌላው ግማሽ ሀብቱ ቢጠይቀው ሳያመነታ ይሰጠዋል።
አሁን ላይ ግን......
ለአንድ ቀን ለሁለት ቀን ሳይገናኙ ቆይተው ሲገናኙ; ቤታቸው ውስጥ ስላለችዋ ዶሮ ሳይቀር ይጠያየቃሉ። አንደኛው ለሌላው የሳንቲም ስባሪ ቢጠይቀው ግን ሞቱን ይመርጣል እንጂ አውጥቶ አይሰጠውም። | 2 003 |
| 6 | ✍
ጥቂት ቀናቶች ናቸው የቀሩት; ቀጠሯችን ጀነት ነው!!
እያሉ ይፅናኑ ነበር። | 2 137 |
| 7 | ✍
ለመኖር ስንደክም: መኖራችን ያበቃል!! | 2 122 |
| 8 | ✍
ቢያለቅስ ዓይኔ በናፍቆት
ቢቆራረጥሎት አንጀቴ:
ልቤ ጠቋቁሯል በወንጀል
እንጃልኝ እርሶን ማየቴ!!
ካልደረሰልኝ ረሕማን
የዕዝነት በሩን ከፋፍቶ
የለኝም እኔስ መዳኛ
ተከምሯል ወንጀሌ በዝቶ!! | 2 426 |
| 9 | ✍
እሷ ራሷ እሷን አትፈልጋትም: እንዴት አንተ ትፈልጋታለህ???
እሷ.... የራሷን መልክ ስለማትፈልገው በሜካፕ ትሸፍነዋለች፤
እሷ.... የራሷን ፀጉር ስለማትፈልገው ፈረስ_hair ትተክልበታለች፤
እሷ.... የራሷን ቅንድብ ስለማትፈልገው ቀብታ ትደብቀዋለች፤
እሷ.... የራሷን ጥፍር ስለማትፈልገው ሌላ ቁስ ትቀጥልበታለች፤
እሷ.... የራሷን (ስሙን የማልጠቅሰው ነገሯ) ስለማትፈልገው ስፖንጅ ወጥራ ትቀይረዋለች።
እሷ ማለት እኮ፦
በሁለቱም እጆችህ ከፍ አርገህ እንደ አንሶላ ብታራግፋት.... የተቀጣጠሉ ነገሮቿ ሁሉ ይረግፉና ሌላ ፍጥረት መስላ የምትታይህ ስውር ሰው ናት!!
በራሷ አፍራ... ራሷን ደብቃ... በዚህ ልክ ራሷን ጠልታ የምትኖር ሴት ላይ;
ልቡ ተማርኮ... ራሱን ስቶ... እየተቁለጨለጨ የሚጃጃል ወንድ "ወንድ" ይባላል ወይ??? | 2 522 |
| 10 | ✍
በአሁን ሰዓት "ወቅቱን ያልጠበቀ ወንጀል" ማለት ኩራት ነው፦
ኩራት (በራስ መደነቅ)፦
ሊመጣ የሚችለው አንድ ሰው ከሌሎቹ የተሻለ ሲሰራ፤ ከሌሎቹ የተሻለ ሲጥራራ፤ ከሌሎቹ የበለጠ.... እና በተለያዩ ነገሮች ከሌሎቹ ተሽሎ ሲገኝ ነበር።
አሁን ላይ ያለው ተጨባጭ ያስተዋለ ግን;
አንዱ ከሌላው የበለጠ ሲሳነፍ፤ ከሌላው የበለጠ ሲግማማ፤ ከሌላው የበለጠ ሲወርድና ሲወድቅ እንጂ የተሻለ ሆኖ የሚገኝ ማየት ብርቅ ሆኗል።
አንተ ከእሱ የሻልክ እንደሆንክ የምታየው አካል;
እሱ ከአንተ ስለ ባሰ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።
አንተ ከእሱ የበለጠ ጥንቁቅ እንደሆንክ የምታየው አካል;
እሱ ከአንተ የበለጠ ስለተጃጃለና ስለደከረተ እንጂ አንተ ጥንቁቅ ሆነህ አይደለም።
በቀን አንድ ገፅ እንኳ ዊርድ የለህም; የጀምዐ ሰላት መስገድ ያቃተው ስታይ ከእሱ እንደተሻልክ ይሰማሃል።
እውታው ግን፦
እሱ ከአንተ ብሶ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።
ዓይንህ እንኳ መቆጣጠር አቅቶህ ከሄደች ከመጣችዋ ጋ ይኳትናል; ከአጅነብይ ጋ ተጨባብጦ የሚያወራ ስታይ ከእሱ እንደተሻልክ የሰማሃል።
እውነታው ግን፦
እሱ ከአንተ ብሶ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።
ከጌታህ ጋ በሚስጥር ያስቀመጥካት አንዲትም የተደበቀች መልካም ስራ የለህም; ሱሪው እየጎተተ ጺሙን የሚልጭ ሰው ስታይ ከእሱ የተሻልክ ይመስልሃል።
እውነታው ግን፦
እሱ ከአንተ ብሶ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።
ስድስት ሰባት ዓመታት ሁሉ ከአንዲት ሚስት ጋ ብቻ እየኖርክ ነው; ትራሱን ታቅፎ የሚተኛው ላጤ ስታይ ከእሱ የተሻልክ ይመስልሃል።
እውነታው ግን፦
እሱ ከአንተ ብሶ ነው እንጂ አንተም እንደ እኩዮችህ "ሁለት... ሦሥት... አራት" መደርደር ነበረብህ።
ሲጠቃለል......
በዚህ ዘመን አንዱ ከሌላው የሚብስ እንጂ: አንዱ ከሌላው የሚሻል ማግኘት ሩቅ ነገር ሆኗል።
ደካማ ሆነህ ሳለ;
ጭራሽ የዘቀጡትን እያየህ ራስህን የምታጥራራ ከሆነ =>ከድክመትህ ባሻገር ጅህልናህም እያሳየህ ነውና ተቆጠብ!!
| 2 423 |
| 11 | ✍
"ሞትህን.... ሞተህ አትጠብቀው"
/ከታክሲ ጥቅሶች/
የወደዳችሁት ካለ አካፍሉን👇 | 2 304 |
| 12 | ✍
በየቤቱ ገብተህ መከራውን ብታይ፣
ብሶቱን ብትሰማ ያለበትን ስቃይ፤
ይገባህ ነበረ ያለህበት ፀጋ፣
ታመሰግን ነበር ሲመሽም ሲነጋ!!
በየቤቱ ሕይወት ከብዷቸው: ሞት አስፈርቷቸው: በመኖርና ባለ መኖር መሃል ሆነው በስቃይ ላይ ያሉት ሁሉ 🤲አላህ ፈረጃውን ያቅርብላቸው። | 2 649 |
| 13 | ✍
"ሁለት ጊዜ ሐጅ አድርጌያለሁ" እንደማይባለው ሁሉ;
"ሁለት ሚስት ነው ያለኝ" ተብሎ አይነገርም፤ ሁለቱም ትላልቅ ዒባዳዎች ናቸው!! | 2 539 |
| 14 | ✍
ዓሊም ይኑር!!
አንዱ ለኢማሙ አሕመድ "በህልሜ ጀነት ውስጥ አይቼሃለሁ" አለው።
ኢማሙ ሲመልሱለት፦
"ህልም ለሙእሚን ታስደስተዋለች እንጂ አታስተኛውም። አንተ ለእኔ ያልከኝ ነገር ለእንትናም ይታይለት ነበር: እሱ ግን አሁን ላይ የኸዋሪጆች አመለካከት አራማጅ ሆኗል።" አለው። | 2 849 |
| 15 | ✍
ይህ ከባድ ነው!!
"አንድም ባሪያ ከወንጀሉ ወደ አላህ ተውበት አያደርግም....
☝️አላህ የተውበቱን እውነተኛነት ሊፈትነው የወንጀሉ መንገድ ቢያመቻችለት ቢያገራለት እንጂ።"
/ኢማሙ ሺንቂጢ/ | 2 872 |
| 16 | 👆
የልሙጦች መከራ ቀላል ነው ኣ የሚመስላችሁ!! | 2 988 |
| 17 | ✍
የጠመሙ ሰዎች ቢሆኑ እንኳ;
ሲዋረዱ ብታይ ለነገው ራስህ ፈርተህ ልትተናነስ እንጂ ልትሳለቅ አይገባህም!!
ጁበይር ኢብኑ ኑፈይር ይባላል የሚነግረን👇
"ቁብሩስ የተባለችዋ ግዛት ድል አድርገን በከፈትናት ጊዜ የቀጠናዋ ነዋሪዎች ከፊሉ ከከፊሉ ጋ ሆነው በደረሰባቸው ሽንፈት ይላቀሳሉ። አቡ ደርዳዠም ለብቻው ተነጥሎ ተቀምጦ ሲያለቅስ አየሁት።
ወደሱ ሄጄ……
"አቡ ደርዳ ሆይ! ዛሬ አላህ ኢስላምና ሙስሊሞችን የበላይ ባደረገበት በደስታችን ቀን ምንድን ነው ያስለቀሰህ? " አልኩት
ሲመልስልኝ………
"ጁበይር ሆይ! እንደው ፍጥረታት የአላህን ትዕዛዝ በሚተዉ ጊዜ ምን ያህል አላህ ዘንድ የተዋረዱ ናቸው?"
ይኸውልህ ተመልከት……
"እነዚህ እኮ ንግስና የነበራቸው ሀያል እና አሸናፊ ህዝቦች ነበሩ:
የአላህን ትዕዛዝ በተዉ ጊዜ እንዲህ እንደ ምታያቸው ሆኑ። አለኝ" ይላል።
ማስተዋሉን ይስጠን!! | 3 222 |
| 18 | ✍
ባል ውጭ አድሮ ይመጣል። ሚስት ፊቷ ተቀያየረ።
ባል:... "ምነው ውዴ ሐራም ይሰራል ብለሽ ጠርጥረሽኝ ነው?” ሲላት;
ሚስት:.... "በሐራምማ አልጠረጥርህም ግን ሐላሉን እንዳትሰራ ፈርቼ ነው።" | 2 960 |
| 19 | ✍
ፈጅር እና ፈረጅ መንታ ናቸው ይላሉ፦
ከጨለማ ወደ ብርሃን እና ከመከራ ወደ እረፍት።
አላህ የምትፈረጁበት ፈጅር ያድርግላችሁ። | 3 190 |
| 20 | ✍
የሰለፎች ብልጠት እኮ የሌለ ነው!!
አንደኛቸው የሆነ ነገር አልሞ አልሳካ ሲለው አላህ ያንን ነገር ለሆነ ወንድሙ እንዲሰጠው ዱዐ ያደርግለታል: ያኔ መላኢካ "ለአንተም እንደዛው" ብሎ ይመልስለታል። | 3 173 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
