🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
Канал 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 12 227 подписчиков, занимая 7 374 место в категории Религия и духовность и 2 749 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 12 227 подписчиков.
Согласно последним данным от 20 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 110, а за последние 24 часа — -5, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.72%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 13.34% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 511 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 631 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 47.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 21 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 21 июля | +2 | |||
| 20 июля | +1 | |||
| 19 июля | +2 | |||
| 18 июля | +8 | |||
| 17 июля | +12 | |||
| 16 июля | +6 | |||
| 15 июля | +9 | |||
| 14 июля | +3 | |||
| 13 июля | +1 | |||
| 12 июля | +3 | |||
| 11 июля | 0 | |||
| 10 июля | 0 | |||
| 09 июля | +7 | |||
| 08 июля | +3 | |||
| 07 июля | +8 | |||
| 06 июля | +8 | |||
| 05 июля | +9 | |||
| 04 июля | +13 | |||
| 03 июля | +1 | |||
| 02 июля | +8 | |||
| 01 июля | 0 |
| 2 | ✍
የፉርቃን ዑስማኖች.... ታሪክ ለመድገም ተዘጋጁ!!
አንጋፋው ሰሐብይ ዑስማን ኢብኑ ዓፋን በእስልምና ዳዕዋ ላይ ካደረጋቸው ትላልቅ ልገሳዎች የተወሰኑትን እንመልከት፦
1ኛ, የመከራ ዘመቻው ሰራዊት ማስታጠቅ!!
ከሂጅራ 9ኛው ዓመት ላይ: ሙስሊሞች ወደ ተቡክ ሄደው ሩሞችን ለመግጠም ወስነዋል። ለዚህ ግዙፍ ዘመቻ የሚሆን ትጥቅና ቀለብ ማግኘት ግን እጅግ በጣም ከባድ ነበር። በጊዜው በነበረው የአቅም ማጠርና የአየሩ ግለት ምክንያት ዘመቻው "የመከራ ዘመቻ" ተብሎ ተሰየመ።ነብዩﷺ ለባልደረቦቻቸው ለዚህ ዘመቻ ግብኣት የሚሆን ስንቅና ትጥቅ እንዲያዋጡ ጥሪ አስተላለፉላቸው። በዚህ ጊዜ ዑስማን ኢብኑ ዓፋን;
950_ግመሎች ና 50_ፈረሶች እስከነ ሙሉ ትጥቃቸው አዘጋጅቶ አቀረበ። ከዚሁ በተጨማሪ በጥሬ 1000 ዲናር አብሮ አስረከበ።
2ኛ, ሩእማ የተባለችዋ የውሀ ምንጭ መግዛት!!
የአንድ አይሁዲ ንብረት የነበረችና ሙስሊሞች በየቀኑ እየከፈሉ ውሀውን ገዝተው የሚጠጡባት ምንጭ ነበረች። ዑስማን ኢብኑ ዓፋን ይህንን በተመለከተ ጊዜ ከአይሁዲው ሙሉ ምንጩ በመግዛት ሙስሊሞች በነፃ እየቀዱ እንዲጠቃቀሙበት ተወላቸው። [ስለዚህ ምንጭ መሳጭ ታሪክ በአላህ ፍቃድ ሌላ ጊዜ በሰፊው እናቀርብላችኋለን]
3ኛ, የነብዩﷺ መስጂድ ማስፋት!!
ሙስሊሞች በበዙና የረሱልﷺ መስጂድ እየጠበባቸው በሄደ ጊዜ: ዑስማን ኢብኑ ዓፋን ከመስጂዱ አጠገብ የነበረው መሬት በመግዛት ወደ መስጂዱ አካሎት መስጂዷ እንድትሰፋ ተደርጋለች።
4ኛ, ሙስሊም ባሮች ገዝቶ ነፃ ማድረግ!!
የእስልምና ዳዕዋ ጅማሪ ላይ እስልምና ተቀብለው በዓለቆቻቸው ስር ሲሰቃዩ የነበሩ በርካታ ሙስሊም ባሪያዎች በመግዛት ነፃነታቸው አውጆ ይለቃቸው ነበር።
5ኛ, በመሪነት ዘመኑ ያደረገው ልገሳ!!
እንደሚታወቀው ዑስማን ኢብኑ ዓፋን ሦሥተኛው የረሱልﷺ ምትክ በመሆን ኡማውን የመራ ሰው ነው። በዚህ ትልቅ ሀላፍትና ላይ ተቀምጦ ሙሉ ኡማ ሲያስተዳድር ከበይተል ማል አንድም ቀን የተፈቀደለትን ደሞዙ እንኳ ተቀብሎ አያውቅም። እንኳንስ ሊቀበል: በርካታ የተቸገሩ ሙስሊሞች ሲያገኝና አንዳንድ ጊዜ ሀገራዊ ጉዳዮች ለማስፈፀም ሁላ ከራሱ ከግል ንብረቱ ነበር ወጪ የሚያደርገው!!
ዑስማን ማለት፦
ዛሬ ላይ ያለነው ሁሉም ሰለፍዮች "ሰለፎቻችን" ብለን ከምንከተላቸው አርኣያዎቻችን ውስጥ አንዱ ነው።
ሰለፍይ ማለት፦
ሰለፎች በእምነታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ_ምግባራቸው፤ በዒባዳቸው፤ በሰደቃቸውና በአጠቃላይ የሕይወት መንገዳቸው የሚከተል ነው።
ውድ የፉርቃን ባለ_አደራዎች.......
ከአላህ በኋላ ምስጋና ለእናንተ ይሁንና ትናንትና በሚያፈስ ቆርቆሮ ታጥሮ የነበረው ፉርቃን "ስሙን በሚመጥን መልኩ" ተባብለን የጀመርነው ግዙፍ ፕሮጀክት ዛሬ ለምታዩት ደረጃ ደርሷል።
ሆኖም......
ሁሉ ነገሩ ተጠናቆ ግንባታው መሟላቱ የማይቀር እውነታ ቢሆንም;
ይህንን ውብ ታሪክ በእናንተ ቀለም ይፃፍ ዘንድ አላህ እድሉንም አደራውንም ሰጥቷችኋል።
🕌ፉርቃንን......
በጀመራችሁት መልኩ ጨርሳችሁ ለትውልድ ለማስረከብ ዝግጁ ናችሁ??? ወይስ የጀመራችሁት ሌላ መጥቶ ይጨርሰው???
ሁላችንም......
እንደጀመርነው ለመጨረስ ቃል በተገባባነው መሠረት
የመጪው እሁድ ሳምንት ሐምሌ_26ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በአላህ ፍቃድ ታሪክ ለመድገም እዛው መስጂደል ፉርቃን ላይ ልዩ የውይይትና የምክክር ፕሮግራም ይደረጋል።
"ትናንት ሰጥቻለሁ: ትናንት አውጥቻለሁ" ሳትል በተያዘው ቀጠሮ በጊዜ ተገኝተህ ልክ እንደ ዑስማን "እሱማ እኔ እሸፈነዋለሁ" እያልክ ጌታህንና ወንድሞችህን ለማስደሰት ከአሁኑ ተዘጋጅ!!
https://t.me/Al_Furqan_Islamic_Studio/20815
👆
👇
https://t.me/hamdquante/10796 | 1 077 |
| 3 | ✍
ሙገሳቸው አያስክርህ: ወቀሳቸውም አይስበርህ።
ምክንያቱም፦
📖{بَلِ الْإِنسَانُ عَلَى نَفْسِهِ بَصِيرَةٌ}
https://t.me/hamdquante/10794 | 1 306 |
| 4 | ✍
ጅብሪል ሆይ! እከሌን እወደዋለሁ ውደደው ይለዋል!!
ይህንን ብስራት አስተንትኑት እስኪ፦
«☝️አላህ ለአንድ ባሪያው ሲወደው ለጅብሪል ይጣራውና "እኔ እከሌን እወደዋለሁ ውደደው" ይለዋል፤ ጅብሪልም ይወደዋል። ጅብሪል ወደ ሰማይ ሰፋሪዎች ይጣራና "አላህ እከሌን ይወደዋል ውደዱት" ይላቸዋል፤ እነርሱም ይወዱታል። ከዝያም በምድር ላይ ተቀባይነት ይደረግለታል።»
ሀሳብ ጭንቀትህ ሰዎች እንዲወዱህ ሳይሆን; አላህ እንዲወድህ ይሁን። ኢሕላስህ ጠብቀህ: ስራህን አሳምረህ: ከአላህ ጋ እውነተኛ ሰው መሆን ስትጀምር ካላሰብከው ካልጠበከው ቦታ አላህ የሰዎች ልብ ይከፍትልሃል።
የአላህ ውዴታ ስታገኝ የሰዎች ውዴታ ይከተልሃል: የሰዎች ውዴታ ስትከተል ግን ከአላህም ከሰዎችም ዐይን ትወድቃለህ። ሁሉም ያለው አላህ ጋ ብቻ ነው: አላህ ዘንድ ያለው የሚገኘው አላህን በመታዘዝ ብቻ ነው!!
በግልፅ ከምታሳየው ቀድመህ; በድብቅ የምታደርገው ዒባዳህን አሳምር!!
https://t.me/hamdquante/10793 | 1 408 |
| 5 | ✍
ሰው አይቀየርም:
የለበሰውን ጭንብል ብቻ ነው የሚያወልቀው!!
https://t.me/hamdquante/10792 | 1 392 |
| 6 | ✍
እግሬ ይራመዳል ወገቤም ጤነኛ
እርጅና አልያዘኝ አይደለሁ በሽተኛ።
ጉልበቴ ሚዝለው ምርኩዝ ምደገፈው
ኪሴ እስኪሞላ ብሩን እስከ ማይ ነው።
/የሚሉ ይመስላል ብሩ ሲገኝ ምርኩዙ ተረሳ/
https://t.me/hamdquante/10791 | 1 755 |
| 7 | 📱
ስልክ መግዛት፣
ስልክ መሸጥ፣
ስልክ ማስጠገን
ወይም
ስልክ በስልክ መቀየር ከፈለጉ
ሁሉም አገልግሎቶች እኛጋ ማግኘት ይችላሉ!!
📞 0912356397
ወይም
@hamduquante
🛣ቦሌ ኤድናሞልጋ ሰልዋ ሞባይል!!
ተጨማሪ ዕቃዎች ለማየት👇👇👇
https://t.me/hamdumobile | 1 960 |
| 8 | ✍
እናታችን ዓኢሻ የቅጥፈቱ ዜና በተናፈሰባት ጊዜ ተክዛ በተቀመጠችበት አንዲት የአንሷር ሴት ገባች። ምንም ነገር ሳትናገር ከዓኢሻ ጋ ተቀምጣ ረዥም ሰዓት አላቀሰቻት።
ዓኢሻ "ያንን ውለታዋ መቼም አልረሳላትም" አለች።
ካዕብ ቢን ማሊክ ከተቡክ ዘመቻ ወደኋላ በመቅረቱ ብዙ ከተፈተነ በኋላ አላህ ተውበቱን ሲቀበለው በደስታ እየፈነጠዘ ወደ መስጂድ ገባ። ጠልሓ ልክ ካዕብን ሲያየው እየሮጠ ሄዶ አቅፎ ተጠመጠመበት።
ካዕብ ቢን ማሊክ "ለጠልሓ ያንን መቼም አልረሳለትም" አለ።
በስብራት ጊዜ የሚገኙ ማፅናኛዎች መቼም አይረሱም!! | 1 916 |
| 9 | ✍
ተረት የሚመስለው የታቢዒዩ እውነተኛ ታሪክ.....
የታሪኩ አስተላላፊ ዐብዱላህ ቢን ሙሐመድ እንዲህ ይተርከዋል፦
የድንበር ጥበቃ ስራ ላይ ሳለሁ ከዕለታት በአንዱ ቀን በግብፅ ድንበር በኩል ተራችን ሆነና ወደዝያ ሄድኩኝ። ወደ ባህር ዳርቻው ስደርስ ሜዳው ላይ አንዲት የድንኳን ጎጆ አየሁኝ። ጎጆዋ ውስጥ እጆቹና እግሮቹ የተቆረጡ፤ ማየትም መስማትም የሚቸግረው፤ ከአካሉ ምላሱን ብቻ ያልተያዘ አንድ ሰው አለባት። ሰውየው ያቺ ድንኳን ውስጥ ብቻውን ተቀምጦ.......
" አላህ ሆይ! ከፈጠርካቸው በርካታ ፍጥረታት አስበልጠህ ላጎናፀፍከኝ በርካታ ፀጋህዎችህን ማወደስ የሚችል ምስጋና እንዳመሰግንህ ወፍቀኝ!!" ሲል ሰማሁት።
በውስጤ "ይህ ሰው ስለየትኛው ፀጋው እንደሚያመሰግንማ መጠየቅ አለብኝ" ብዬ ቀርቤው ሰላምታ አቀረብኩለት።
" አላህ ሆይ! ከፈጠርካቸው በርካታ ፍጥረታት አስበልጠህ ላጎናፀፍከኝ በርካታ ፀጋህዎችህን ማወደስ የሚችል ምስጋና እንዳመሰግንህ ወፍቀኝ" "ስትል ሰምቼሃለሁ: ስለ የትኛው የተዋለለህ ውለታ ነው እንዲህ አብዝተህ የምታመሰግነው?? ከሌሎቹ አስበልጦ የሰጠህ ፀጋስ ምንድን ነው??" አልኩት።
"ጌታዬ ለእኔ ያደረገልኝን አትመለከትምን? ወላሂ! ከሰማይ እሳት ልኮ ብታቃጥለኝ፤ ተራራ ደርምሶብኝ ብታወድመኝ፤ ባህርን አዞ ብታሰምጠኝ፤ መሬትን አዞ ብትውጠኝ እንኳ ጌታዬ ለዋለልኝ ለዚች ምላሴ ውለታ ከምስጋና ሌላ ምጨምርለት አይኖረኝም!!" አለኝ።
"እንደው ከመጣህ አይቀር ግን: እንደምታየኝ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለሁት፤ ለራሴ ምንም መጥቀምም ይሁን መጉዳት አልችልም። አንድ ሰላት ሲደርስ ውዱእ የሚያስደርገኝ፤ ሲርበኝ የሚያበላኝ፤ ሲጠማኝ የሚያጠጣኝ ልጄ አብሮኝ ነበር። ወጥቶ ሳይመለስ ከቀረ ሦሥት ቀናት ሆነውታል። እስኪ እሱን አፈላልገህ አምጣልኝ" አለኝ።
በአላህ ይሁንብኝ! አንድም ሰው አንድን ሰው ለመርዳት ተንቀሳቅሶ አጅር አያገኝም: የአንተ ዓይነቱ ለመርዳት የሚንቀሳቀስ ሰው የተሻለ አጅር ቢያገኝ እንጂ!! ብዬው ፍለጋ ሄድኩኝ።
ከእሱ ወጥቼ ብዙም ሳልጓዝ ያ... የጠቀሰልኝን ልጅ ቋጥኞች መሃል ወድቆ: ስጋው አውሬዎች ተቆራምተውት አገኘሁት።
አሁን በምን ዓይነት ሁኔታ ወደ ሰውየው ተመልሼ ይህንን መርዶ እንዴት እንደምነግረው ግራ ገባኝ። በሀሳብ ተውጬ በመመለስ ላይ ሳለሁ.... የነብዩላህ አዩብ ታሪክ እያወሳሁ ሰውየውን ማሳበር እንዳለብኝ ታወሰኝ
ስደርስ ሰላምታዬን አቀረብኩለት። ሰላምታውን መለሰልኝ። "ባልደረባዬ አይደለህምን?" አለኝ። "ነኝ" አልኩት። "እና ጉዳዬ ከምን ደረሰ?" አለኝ።
"አላህ ዘንድ ከአንተና ከነብዩ አዩብ ማን የተከበረ ይመስልሃል?" አልኩት"በእርግጥም ነብዩ አዩብ ነው" አለኝ።
"አላህ ምን እንዳደረገው ታውቃለህን? በልጆቹ: በቤተሰቦቹ: በንብረቱ ሁሉ እንደፈተነው ታውቃለህን?" አልኩት። "አዎን አውቃለሁ" አለኝ።
"ታድያ ጌታው እንዴት ነው ያገኘው" አልኩት
"ታጋሽና አመስጋኝ ሆኖ አግኝቶታል" አለኝ።
"በዚህም አላበቃለትም: ከዘመዶቹ ከወዳጆቹ ሁሉ ነጥሎ ብቸኛ እስከሚያደርገው ድረስ" አልኩት። "በእርግጥም አው" አለኝ። "እና ጌታው እንዴት ነበር ያገኘው?" አልኩት።
"ታጋሽ እና አመስጋኝ ሆኖ አግኝቶታል!! አላህ ይዘንልህ ጉዳዩን አሳጥረህ ንገረኝ" አለኝ
"እንግዲያውስ... ያ እንድፈልግልህ የላከኝ ልጅህ ቋጥኞች መሃል ወድቆ ስጋውን አውሬዎች ተቆራምተውት አግኝቼዋለሁ። አላህ ምንዳህን ያተልቅልህ ሰብሩም ይወፍቅህ!!" አልኩት።
"ከልጆቼ አንድም እሱን አምፆ በጀሀነም የሚቀጣ ያልፈጠረብኝ አላህ ሙሉ ምስጋና ይድረሰው!! ኢናሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!" አለ። በዝያው ቅፅበት ትንፋሹ ተናንቆት ሲቅ...ሲቅ አለውና ላይመለስ አሸለበ!!
"ኢና ሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን" ካልኩኝ በኋላ የሰውየው ሁኔታ እኔም ላይ ከባድ ሙሲባ ሆነብኝ። ይህንን ሰው ትቼው ብሄድ ጀናዛው አውሬ ሊበላው ነው። አብሬው ብቆይ አልጠቅመው አልጎዳው፤ እንዲው ግራ ገብቶኝ በአንዲት ጨርቅ ሰውነቱን ሸፍኜለት ራስጌው ጋ ቁጭ ብዬ ማልቀስ ጀመርኩኝ።
በዚሁ መልኩ ተቀምጬ ሳለሁ ከየት እንደመጡ ሳላውቅ አራት ሰዎች ከበቡኝ። "ዐብደላህ ሆይ! ምን ሆነህ ነው?? ምን ገጥሞህ ነው??" አሉኝ። የሆነውን ሁሉ ዘረዘርኩላቸው። "እስኪ ፊቱን ክፈትልን ድንገት ካወቅነው" አሉኝ ከፈትኩላቸው።
ልክ ፊቱን ስከፍትላቸው.... ሁሉም ጀናዛው ላይ ተደፍተው ማልቀስ ጀመሩ። አንዱ ዓይኖቹ ይስማል፤ አንዱ እጁ ይስመዋል፤ "አላህ ዕርም ካደረጋቸው ነገሮች ተሰብራ የኖረች ዓይን: ሰዎች በተኙበት እየሰገደ ያደረ አካሉ....." እያሉ ይላቀሳሉ።
" እንደው አላህ ይዘንላችሁና ይህ ሰው ማን ነው??" አልኳቸው።
" ይህ እኮ.... የኢብኑ አባስ ባልደረባ : አላህንና መልእክተኛውን አብዝቶ ይወድ የነበረው;
👇
👉አቡ ቂላባ አል_ጁርሚ ነው!!" አሉኝ።
አጥበን፤ እኛጋ በነበረ ልብስ ከፍነን፤ ሰግደንበት ቀበርነው። እነርሱም ወደ ሐጃቸው ሄዱ: እኔም ወደ ጥበቃዬ ሄድኩኝ። ምሽቱ በጨላለመ ጊዜ ለማረፍ ጋደም ባልኩበት ያንን ሰው በህልሜ አየሁት።
ከጀነት ጨፌዎች አንዱ ጨፌ ላይ ሆኖ፤ ከጀነት አልባሳት ለብሶ.......
{سَلَٰمٌ عَلَيْكُم بِمَا صَبَرْتُمْ ۚ فَنِعْمَ عُقْبَى ٱلدَّارِ}
{"ሰላም በእናንተ ላይ ይሁን: (ይህ ምንዳ) በመታገሳችሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ሀገር ምንኛ ታምራለች" (ይሏቸዋል)፡፡} የሚለውን የቁርኣን አንቀጽ ሲቀራ ሰማሁት።
"ያ.... ባልደረባዬ አይደለህምን?" አልኩት። "አዎ ራሱ ነኝ" አለኝ። "ይህንን እንዴት ሆነልህ?" አልኩት;......
"ለአንድ ባሪያ አላህ ዘንድ የተፃፈለት ደረጃ አለው። ያንን ደረጃ የሚገኘው ግን፦
በሙሲባ ሰዓት በሚደረግ ሰብር፤ በድሎት ሰዓት በሚደረግ ምስጋና እና በድብቅም ይሁን በግልፅ ለአላህ በሚኖር ፍራቻ ነው" አለኝ።
ታሪኩ በበርካታ የታሪክ መዛግብት ላይ በስፋት ተዘግቦ የሚገኝ ነው። የአቡ ቂላባ እዝያ ዳርቻ ላይ ተነጥሎ የመኖር ምክንያት በሌሎች ዘገባዎች ላይ እንደመጣው፦
አቡ ቂላባ በዘመኑ በስራ ከነበሩ ትላልቅ ዑለማዎች፤ ዙሃዶችና ዑባዶች ውስጥ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነበር። ለየት ባለ መልኩ ስለ አሕካምና ስለ ሸሪዐ ህግ የበለጠ ዐዋቂ ነበር። ስለሆነም በዘመኑ የነበሩ መሪዎች በዳኝነት ሊሾሙት ሲፈልጉ እሱ ግን ሹመት ላይ ከመቀመጥ ይልቅ ተነጥሎ አላህን መገዛት መርጦ ወደ ሻም በድብቅ ተሰደደ። በመጨረሻም ባየነው መልኩ እዝያው ሞቶ እዝያው ተቀበረ።
🤲አላህ ማረፊያው የጀነት ጨፌ ያርግለት🤲
🤲ለእኛም ስራችን ቢያንስም ለእነርሱ ባለን ውዴታ ወደ እነርሱ አስጠግቶ በጀነት ያጎራብተን🤲 | 2 072 |
| 10 | 👇 | 1 915 |
| 11 | ✍
ኢማም ኢብኑ ጀውዚይ; አላህ ይዘንለት......
💫በእሱ ምክንያት ከሀያ ሺህ በላይ አይሁዳዎችና ክርስቲያኖች እስልምና ተቀብለዋል፤
💫በእሱ ምክንያት ከመቶ ሺህ በላይ ሰዎች ከስህተታቸው ተውበት አድርገዋል፤
💫ከሁለት ሺህ በላይ ኪታቦች እንደ ፃፈ ይወሳለታል።
ከመሆኑም ጋ፦
ለተማሪዎቹ "ጀነት ገብታችሁ ካላገኛችሁኝ; ጌታችን ሆይ! እከሌ የሚባል ባሪያህ ስለ አንተ ያወሳልን ነበር የት ነው ያለው?”
ብላችሁ ጠይቁልኝ" ይላቸዋል።
| 2 208 |
| 12 | ✍
"ለአንተ ብቻ ነው የምነግርህ" ብለው የሰው ሚስጥር የሚነግሩኝ ሰዎች;
ከማንም በበለጠ የምጠነቀቃቸው እነሱን ናቸው። | 2 014 |
| 13 | ✍
ወይ በተሻለ ተክቶልህ, አልያም ትክክለኛው ጊዜ አልደረሰም ሊሆን ይችላል እንጂ;
አላህን ለምነኸው የሚከለክልህ ነገር የለም!!
📖{وَآتَاكُم مِّن كُلِّ مَا سَأَلْتُمُوهُ…}
{የለመናችሁትን ሁሉ ሰጥቷችኋል…}
[ኢብራሂም:³⁴] | 2 147 |
| 14 | ✍
ወደ አኼራ ይዘህ የምትሄደው የሰበሰብከውን ሳይሆን የበተንከውን ነው!!
ወደ አካውንትህ የሆነ ብር ገብቶ ቁጥሩ ሲጨምርልህ ከምትደሰተው የበለጠ:
ከአካውንት ቀንሰህ መሳኪኖችና መሳጂዶች ላይ በበተንከው የምትደሰት ሁን!! | 2 169 |
| 15 | ✍
ኢብራሂምﷺ......
እሳቱ እንደሚበርድለት አያውቅም ነበር: ግን ጌታው እንደማይተወው እርግጠኛ ነበር!! | 2 126 |
| 16 | ✍
በቲንሽ ስራ ታላቅ ምንዳ!!.. የተረሳ ሱና ሊባልም ይችላል!!
አቡ ሁረይራ እንዲህ አስተላልፎታል፦
ነብዩﷺ ለቢላል «ቢላል ሆይ! ጀነት ውስጥ ከፊትለፊቴ የጫማህን ኮቴ ሰምቼልሃለሁ: እንደው ለዚህ ደረጃ ያደርሰኛል ብለህ የምትከጅለው እስልምና ውስጥ የሰራኸው ስራህ ንገረኝ» አሉት።
ቢላል ሲመልስላቸው፦
"እኔ እንኳ ይህን ያህል የምገምተው ስራ የለኝም: ብቻ ግን በቀንም ይሁን በማታ ዉዱእ አድርጌ አላውቅም =>በዝያ ውዱእ አላህ ያገራልኝን ያህል ብሰግድበት እንጂ" አላቸው።
/ኢማሙ ቡሓሪ በሰሒሓቸው ዘግበውታል/
ነብዩﷺ ለቢላል ግምቱን ባፀደቁለት መሠረት ጀነት ውስጥ ኮቴውን ረሱልﷺ እስከሚሰሙለት ድረስ ትልቅ ደረጃ ላይ ያደረሰው ከውዱእ በኋላ የሚሰግደው "ሱነተል ዉዱእ" የሚባለው የተረሳው ሱና ሰላቱ ነው። አንድ ሰው በየትኛውም ሰዓት ዉዱእ ቢያደርግ ቀጥታ በዛች ውዱእ "የዉዱእ ሰላት" መስገዱ ትልቅ ምንዳ የሚያስገኝለት የተተወ የተረሳ ሱና ነው። | 2 374 |
| 17 | ✍
ሁሉም እናት.......
ልጇ አባቱ ያገኛትን ዓይነት ሷሊሕ ሚስት ያገኛል የሚል ግምት የላትም!!
🤲ዕድሜና ጤና ለእናቶቻችን🤲 | 2 271 |
| 18 | ✍
ማንንም በዘመዱ ከማነወርህ በፊት.....
ለኑሕ አዛ የሆነ ልጅ፤
ለሉጥ ካፊር የሆነች ሚስት፤
ለኢብራሂም ሙሽሪክ የሆነ አባት፤
ለኣሲያ "እኔ ጌታችሁ ነኝ" የሚል ባል፤
ለሙሐመድﷺ "የእሳት አባት" የተባለ አጎት እንደነበራቸው አስታውስ። | 2 820 |
| 19 | 🤲
አልሃምዱሊላህ!!
🌧ክረምት የሚመስል አየር ደስ ሲል: አላህ ራሕመቱን ያስቀጥልልን!! | 2 649 |
| 20 | ✍
በጠዋት ተነስተን ሻወራችን ወስደን
ከጥፍራችን ቆርጠን ጥርሳችን ቦርሸን፣
ጥምጣም ጀለቢያ ከነጫጩ ለብሰን
ሽቶ ተነስንሰን ተውበን አጊጠን፤
ጉዞ ወደ መስጂድ ሳይረፍድ በጠዋቱ
ቁርኣንና አዝካር በዝቶ ሰለዋቱ፤
ኹጥባ በፀጥታ ተቀምጠን አድምጠን
ጁሙዐችን በጀምዐ ለጌታችን ሰግደን፤
ፀሓይ እስክትገባ እስኪታይ ወጋገን
አላህን አብዝተን እንለምነዋለን!! | 2 724 |
