🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
تُعد قناة 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 199 مشتركاً، محتلاً المرتبة 7 412 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 766 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 199 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 81، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 28.37%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.71% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 461 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 672 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 47.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 13 يوليو | +1 | |||
| 12 يوليو | +3 | |||
| 11 يوليو | 0 | |||
| 10 يوليو | 0 | |||
| 09 يوليو | +7 | |||
| 08 يوليو | +3 | |||
| 07 يوليو | +8 | |||
| 06 يوليو | +8 | |||
| 05 يوليو | +9 | |||
| 04 يوليو | +13 | |||
| 03 يوليو | +1 | |||
| 02 يوليو | +8 | |||
| 01 يوليو | 0 |
| 2 | 🇸🇦
አለመቻልና አለመመቻቸት ሆኖ እንጂ.....
ሁሉም ሱንይ ሙወሒድ ቀሪ የዱንያ ዘመኑ በዚች🇸🇦 ሀገር እንዲሆን የሁል ጊዜ ምኞቱ ነው!!
🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦 | 448 |
| 3 | ✍
የወንጀል ምሳሌው ልብ ላይ ልክ እንደ መርዝ ነው: ባይገለው እንኳ አይቀሬ ያደክመዋል። የደከመ እንደሆነ በሽታዎች የመቋቋም አቅሙ ያጣል።
/ኢማም ኢብኑል ቀይም/
የልብ ዶክተር ተብሎ የተሰየመው ኢብኑ ሙባረክ እንዲህ ይላል....
رَأَيْتُ الذُّنُوبَ تُمِيتُ الْقُلُوبَب
وَقَدْ يُورِثُ الذُّلَّ إِدْمَانُهَا
وَتَرْكُ الذُّنُوبِ حَيَاةُ الْقُلُوبِ
وَخَيْرٌ لِنَفْسِكَ عِصْيَانُهَا | 502 |
| 4 | ✍
ለጓደኛው:... "እንትና ደስ አይለኝም" አለው።
"እሱ ሰውየ ለእኔም አይመቸኝም" አለውና;
"ማን ያውቃል አላህ ልባችን ላይ የሷሊሖች ውዴታ ፍቆብን ቢሆንስ?" አለው።
ሁሌም ራስን አሳንሶ ሌሎችን ማተልቅ የትላልቅ ሰዎች ባህሪ ነው!! | 1 326 |
| 5 | ✍
هربوا من الرقِّ الذي خُلقوا له
فبُلُوا برقِّ النفسِ والشيطانِ
/ኢብኑ ዕሰይሚን “ይህ ስንኝ በዓይን ውሀ ቢፃፍ ያንሰው ነበር” ይላል/ | 1 441 |
| 6 | ✍
ሳትወልድ ብላ ❌
ሳትወልድ ተኛ ✅ | 2 079 |
| 7 | ✍
ሁሉም ሟች ስርዓተ ቀብሩ ሲፈፀም በሚነገርለት ልክ ቢሆን ኖሮ;
ጀሀነም ባዶ ትሆን ነበር። ይላል
ሙት ብቻ........
ሁሉም ሰው መልካምነትህ ይናገራል፤ ወዳጅህም ይሁን ጠላትህ ሁሉም ዓፍው ይልሃል። | 2 201 |
| 8 | ✍
ሁለቱ ሙሲባዎች አምሳያ ተገኝቶላቸው አይታወቅም ይላል፦
የኣደም ልጅ ሲሞት......
ሀብቱን በአጠቃላይ ይወረሳል፤
ስለ አጠቃላይ ሀብቱ ይጠየቃል። | 2 111 |
| 9 | ✍
አንዱ ለዑመር ኢብኑል ኸጣብ;
"ከአንተ የተሻለ ኸይረኛ ሰው አይቼ አላውቅም" አለው፤
ዑመር.... "አቡ በክርን አይተኸዋልን?" ሲለው; "አላየሁትም" አለው፤
ዑመር.... "“አዎን” ብትለኝ ኖሮ እገርፍህ ነበር" አለው። | 2 250 |
| 10 | ✍
ኧረ ወይኔ ሞትኩት.......
የመስጂዱ ሙከየፍ ይበላሽና ጀምዐው በሙቀት ይታፈናል። ሙሓደራ ሲያደርግ የነበረው ኡስታዝ;
"ምእመናን ሆይ! ይህ ሙቀት እንዲህ የጨነቃችሁ እስኪ ጀሀነምን አስታውሱ" አለ።
ከመሃል አንዱ ብድግ ብሎ.......
"ኡስታዝ ሆይ! ሙከየፉን አሰርታችሁ ለምን ጀነት አታስታውሱንም??" | 2 342 |
| 11 | ✍
አላህ ለሁሉም ነገሮች የሚገኙበት ሰበብ እና የሚወገዱበት ኣፋት አድርጎላቸዋል።
የአላህ ፀጋ መገኛና መዘውተሪያ ሰበቡ አላህን መታዘዝ ሲሆን
ፀጋዎች የሚወገዱበት ኣፋት አላህን ማመፅ ነው።
/ኢብኑል ቀይም/ | 2 302 |
| 12 | ✍
በስራህ ተመሣሣይ ሲመነዳህ.....
ሺዐዎች አላህ በቁርኣን ያጠራት እናታችን ዓኢሻን በዝሙት ወነጀሉ:
እነርሱ ግን አላህ ሐራም ያደረገውን ሙትዐ በመፍቀድ ሴቶቻቸው በዝሙት እየተጨማለቁ ይኖራሉ!! | 2 247 |
| 13 | ✍
ረዣዥሞች መፎካከሪያ እንደሆኑ ምነው እስከዛሬ ሳትነግሩን??
ቀይሰር የሩም ንጉስ እነርሱ ዘንድ ከነበሩት ሁሉ ረዥሙ ሰው ይመርጥና ወደ ሙዓዊያ ይልከዋል። ለሙዓዊያም "እሱን የሚስተካከል ሰው ካላችሁ አሳየኝ" ብሎ ይፎካከረዋል።
ሙዓዊያ ወደ ቀይስ ኢብኑ ዑባዳ ያስልክና "መጥተህ ከሩማዊው ጎን ቆመህ ተለካካው" ይለዋል። ቀይስ ኢብኑ ዑባዳ ከርዝመቱ የተነሳ "ፈረስ በሚጋልብበት ጊዜ እግሮቹ መሬት ይደርሱ" ነበር ይባላል።
ቀይስ ግን......
"ለዚህ ካፊር ከጎኑ የምቆምለት ያህልማ ክብር የለውም: ባይሆን ይህንን ሲርዋሌ ወስዳችሁ አስለኩት" ብሎ ሲርዋሉን ሰጣቸው።
የቀይስ ሲርዋል ሩሚው ላይ ሲለካ አፍንጫው ጋ ደረሰ። ያኔ ቦታው ላይ የነበሩ ሰሓባዎችም ሌሎች ሰዎችም ተሳሳቁ።
/አልቢዳያ ወልኒሃያ/ | 2 383 |
| 14 | 👆
የዛሬ አራት ዓመት የተፃፈ👇
🤲ሽንፈት ለ ሞሮኮ🤲
⚽
✍️ለምን⁉️
በዓለም ዋንጫው የኳስ ውድድር ላይ አንዲት ሀገር አሸናፊ ከሆነች እዛ ሀገር ላይ ምን ይከሰታል❓ ብለን ካየን……
✍️አንደኛ;
ሀገሪቷ ላይ እግር ኳስ ይነግሳል። ስለሆነም በዚህ ውድድር ላይ አሸናፊ የሆኑ ተጫዋቾች ከፍተኛ የሆነ ዝናና በርከት ያለ ሽልማት ይቸራሉ።
💫የእነዚህ ተጨዋቾች ዝናና ሽልማት እያየና እያደነቀ ያደገ ትውልድ ነገም እሱ አድጎ የኳስ ተጫዋች ለመሆን ይጥራል እንጂ ቁርኣንና ሓዲስ ተምሮ እስልምና የመርዳት ሞራል አይኖረውም‼️
✍️ሁለተኛ;
እነርሱ ያስገኙትን ድል እንዲቀጥል ተብሎ ተተኪ ተጫዋቾች እንዲተኩና እንዲጫወቱ ድጋፍና ቅስቀሳ ይደረጋል።
💫 ይህም በአንዲት ሙስሊም ሀገር ላይ ውርደት ይዞ የሚመጣ ተግባር ነው። ምክንያቱም፦
👇
👉በዛች ሀገር ላይ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ትውልዶች በየ ሚዲያው የሚያዩትና የሚሰሙት ስለ ኳስ ተጫዋቾች ዝና ስለ ሆነ እነርሱም ነገ አድገው ይህንን ደረጃ ላይ መድረስን ነው የሚመኙት።
በዚህም ምክንያት ቁርኣንና ሓዲስ የሚማር ትውልድ ይጠፋል ወይም ይደክማል። እስልምና ተምሮ በእስልምና ታንፆ አድጎ ሀገር የሚረከብ ትውልድ ከሌለ ይህ ሀገር የውርደት ካባ መልበሱ የተረጋገጠ ይሆናል‼️
✍️ሶስተኛ;
ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ያስመዘገበችው ድል ጠብቆ ለማስቀጠል በሚል ለእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በርከት ያለ ገንዘብ ተመድቦለት እንዲንቀሳቀስ ይደረጋል።
💫በዚህም ተግባር የዜጎች ሐቅ የሆነው የሀገር ሀብት አላህ በማይወደውና አላህን በሚታመፅበት ተግባር ላይ እንዲውል ይደረጋል። ይህም በሀገሪቷ ላይ የአላህ ቁጣ እንዲወርድ አንድ ሰበብ ነው‼️
✍️አራተኛ;
በሀገሪቷ ላይ ያሉ ሚዲያዎችም ይሁን አጠቃላይ መገናኛዎች ዘገባቸውና ቅስቀሳቸው ስለ ኳስ ይሆናል።
💫በዚህም ምክንያት አብዘሃኛው ቤቶች ላይ የሚደመጠው ቁርኣንና ሓዲስ ሳይሆን የኳስ ዜና ይሆናል።
✍️አምስተኛ;
አንዲት ሀገር የኳስ ውድድር ላይ ካሸነፈች የሀገሪቷ ደጋፊዎች ይጨፍራሉ፣ ይዘፍናሉ፣ ይጮሃሉ። የኳስ ውድድሩ እንደ አለም ዋንጫ ትልቅ ግምት የሚሰጡት ከሆነ በሀገሪቷ ላይ ለተገኘው ድል ተብሎ የሚደረገው ጭፈራና ዘፈን የበለጠ ያየለ ይሆናል።
💫ጭፈራ፣ ዘፈንም ይሁን ጩኸት የሸይጣንና የመሰሎቹ እንጂ የሙስሊሞች መገለጫ አይደሉም።
✍️እኛ እንደ ሙስሊምነታችን……
በየትኛውም የሙስሊም ሀገር ላይ እንዲህ ዓይነት የአላህ ቁጣ የሚያስፈርድ አመፅ እንዲስፋፋ ስለ ማንፈልግ ሞሮኮ በዚህ ውድድር ላይ ሽንፈት ተላብሳ እንድትመለስ እንመኛለን‼️‼️
🤲ሀገራችን ኢትዮጵያም ለእንደዚህ ያሉ ውድድሮች አላህ መቼም እንዳያበቃት እንማፀነዋለን‼️
👌የተጠቀሱ ነጥቦች የማይከሰቱ ከሆኑ ወይም
መከሰታቸው የአላህ ቁጣ የማያስከትል ከሆነ መሞገት ትችላለህ፤
ስሜትህ ስላልገጠመ ብቻ የምትቃረን ከሆነ ግን ከግብዞቹ አንዱ ለመሆንህ ምልክት ነው‼️‼️
🤲አላህ
ሸር ሸርነቱን አውቀው ከሚርቁትና
ኸይር ኸይርነቱን አውቀው ከሚከተሉት ያድርገን‼️‼️
| 2 390 |
| 15 | ✍
ወደ አላህ ይበልጥ እንድትቀርብ፣ ቀንና ማታ ቁርኣን እንድትቀራ፣ እጆችህ🤲 በዱዐ እንድትዘረጋቸው፣ የጠዋትና የማታ አዝካር እንድትጠባበቅ ያደረገህ ህመም ብትታመመው እንኳ;
አንተ ህመምተኛ ሳትሆን በትልቅ ፀጋ የምትጠቃቀም ተመራጭ የአላህ ባሪያ ነህ።
በበሽታ ተይዞ ህመም ላይ ያለው ማለት......
ያ.... አላህ የዓፊያ ፀጋ ውሎለት በሙሉ ጤንነቱ ለአላህ መሰባበር አቅቶት በወንጀልና በኩራት የሚንበላቀቀው: እሱ ነው በከባድና አስፈሪ በሽታ የተያዘው!! | 2 340 |
| 16 | ✍
መንገድ ላይ ጃን_ጥላ ይዘው የሚሄዱ ወንዶች ሳይ;
ስለ ተዓዱድ ሲወራ ከሴቶች በላይ እየደነገጡ "አይቻልም" ላለማለት "እስኪ አንዷም በስርዓት ላስተዳድር" እያሉ የሚሸሹ ወንሴቶች ናቸው ትዝ የሚሉኝ። | 2 547 |
| 17 | ✍
መቼም የማይተውህ የሁልጊዜ መከታ
☝️አላህ ብቻ ነው!!
وكل فوق التراب تراب!! | 3 017 |
| 18 | ✍
ሸይጧን አንድም ሰው ላይ ተስፋ አይቆርጥም;
በሴት ልጅ በኩል ቢመጣው እንጂ። | 2 822 |
| 19 | ✍
እግር ኳስ አይመለክም ነው የምትሉኝ???....
ሰሞኑ የገጠመኝን ላካፍላችሁ......
ሳምንቱን አንድ "ትልቅ" በሚባል ሆስፒታል ነበር ያሳለፍኩት። እኛ በነበርንበት ሩም አብሮን የነበረው ታማሚ ህመሙ ቲንሽ አስደንጋጭና ከባድ የሚባል ዓይነት ነበር። ዕድሜው ከ60_70ዎች የሚገመት ሲሆን እንደማንኛውም ሰው ወጥቶ በመግባት ላይ ሳለ "ሆዴን.... እግሬን... እያመመኝ ነው" እያለ ቀለል ያለ ህመም እንደታመመ ለራሱ አምኖ ለቤተሰቦቹም ይናገራል። እየዋለ ሲያድር ግን ህመሙ እረፍት ሲነሳው ነበር "ለመታየት" በሚል ወደ ሆስፒታሉ ያመራው። ሆስፒታል ደርሶ ምናምኑ ሲመረመር ግን ከገመተው ፍጹም ተቃራኒ ሆነ; የያዘው በሽታ ሳይታወቀው ብዙ ነገሩ አድክሞታልና እግሩ መቆረጥ እንዳለበት ተነገረው።
ሙሉ አካሉን ይዞ ከሚሞት አንድ እግሩን አጥቶ መኖር ይመርጥና የቀኝ እግሩ ከጉልበቱ በላይ ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ተቆርጦ ይወጣለታል።
ይህ ክስተት ከቤተሰብ አልፉ ጎረቤቶቹ: ወዳጅ ዘመዶቹ ሁሉ ያስደነገጠ ነበር። በመሆኑም በዕድሜ የሚቀራረቡት ጓደኞቹን ጨምሮ ሊጠይቀው የሚመጣ ሰው ሁሉ እያለቀሰ ነበር ገብቶ የሚወጣው። እሱም ከእግሩ መቆረጥ በተጨማሪ ህመሙ በራሱ ይከባብደው ስለነበር ሊጠይቀው የሚመጣ ሰው የማየትና የማውራት ፍላጎት ብዙም አልነበረውም። በመስኮት መስታወት ሰው እንዳያይ ሁላ በመጋረጃ ይጋረድለት ነበር። ይህ ሁሉ የሚያደርገው የህመሙ ክብደት ነበር።
እናላችሁ.......
በዚህ ልክ ታምሞ ሰው ማየትም ይሁን ማውራት የሚያስጠላው ሰውዬ ልክ ሲመሻሽ ሁሌም ቀጣዩን ጥያቄ ይጠይቃል;
"የዓለም ዋንጫው ከምን ደረሰ?? ማን አለፈ?? ማን ተሰናበተ??" ሊያስታምመው ያደረው ቤተሰብ ስለኳስ የሚያውቅ ከሆነ ዘርዝሮ ያስረዳዋል።
በዚህም አያበቃም........
"ዛሬ ማን ከማን ጋ ይጫወታል?" ብሎ እስከነ ሰዓቱ ይጠይቅና አብሮት ለሚያድረው አስታማሚ ፓኬጅ አስሞልቶ ሌሊት የኳስ ጨዋታው እንዲከፈትለት ይጠይቃል። በኢንተርኔት ተከፍቶ ማሳየት ካልተቻለ በሬድዮ ይከፈትለትና እያዳመጠ ይከታተላል።
ነገሩ ቀልድ አይምሰላችሁ........
እነዚህ ሰዎች ኳስ የሚያዩትም ይሁን የሚከታተሉት "ለመዝናኛነት" ብቻ አንደለም። የተደረገባቸው ግዴታ ይመስል እሱን ካላዩ ካላደመጡ ህሊናቸው ሊረጋጋላቸው አይችልም ነው።
በተለመደው እኮ.......
አንድ ሰው የከፋ ህመም ወይም ጭንቀት ላይ ሲሆን ሙስሊም ከሆነ ቁርኣን ክርስቲያን ከሆነ መዝሙር ነበር የሚከፍተው። "ልቤ የሚረጋጋው በዚህ ነው" ብሎ ስለሚያምን። የኳስ ሱሰኞች ልብ የሚረጋጋው ግን የሚደግፉት ቡድን ሲያዩ ወይም ስለሱ ሲሰሙ ነው።
እንደው አታስዋሹኝና.........
ከእነዚህ ሱሰኞች አንዱ ቡድኑ ግጥሚያ ባለው ቀን እናቱ ብትሞት ሽንት ቤት ገብቶ ስልኩን ከፍቶ ውጤቱ የማይከታተል ይመስላችኋል???? ምን አልባት ይህንን ፅሁፍ ከሚያነቡት ውስጥም ተመሣሣይ ነገር የገጠመው ሊኖር ይችላል።
በመከራው ዕለት ከስቃይ መዳን የሚችለው {ንፁህ ቀልብ} ይዞ የመጣ ብቻ ነውና ....
ትኩረት ለልባችን እላለሁ!! | 3 073 |
| 20 | ✍
እና ኳስ አያመልኩም ነው የምትሉኝ???......
1ኛ, እነሱ የሚደግፉት ቡድን የሚደግፍ ሰው የልብ ወዳጃቸው ሲሆን; እነሱ የሚደግፉት ቡድን የሚጠላ ሰው የአባታቸው ገዳይ ዓይነት ጥላቻ ይጠሉታል።
2ኛ, አለባበሳቸው፣ አረማመዳቸው፣ ሁሉም አክሽናቸው እነሱ በሚወዱት ተጫዋች ስታይል ለማድረግ ሁሌም ይጥራሉ።
3ኛ, የቤት ኪራይ አልፎባቸው ድብርትና ጭንቀት ላይ ሆነው እንኳ የሚደግፉት ቡድን ካሸነፈ ምንም ሐጃ የሌለበት ሰው ዓይነት በደስታ ይፈነጥዛሉ።
4ኛ, የሰላት ወቅት ጨምሮ የትኛውም ሐጃ ቢኖርባቸው የሚደግፉት ቡድን ጨዋታ ካለው ሁሉም ነገር ትተው ጨዋታውን መከታተል ያስቀድማሉ።
5ኛ, ሰላት ላይ ጨምሮ ሲተኙና ሲነሱም ይሁን... እንዲሁም በህልማቸው ሁላ የሚያስቡትና የሚጨነቁት ስለሚደግፉት ቡድን ጨዋታና አጨዋወት ነው።
⚫️በጃሂሊያ ዘመን ሳለን.......
"ኳስ ለምን ታያላችሁ?" ስንባል "ለመዝናናት" ነበር የምንለው፤
አሁን ግን ኳስ መዝናኛ ሳይሆን ያልታወቀበት ጣዖት ሆኗል።
🫵ሙስሊም ወንድሜ ሆይ.......
መውደድና መጥላት ለአላህ ብቻ ተብሎ የሚደረግ ትልቅ የአምልኮ ስርዓት ነው። በማወቅም ይሁን በጅህልና ከአላህ ውጪ ላለ ነገር (ለኳስ) ብለህ የምትወድና የምትጠላ ከሆነ ተቀበልክም አልተቀበልክም አምልኮህን ለሌላ እየሰጠህ ነው። ሌሎቹም እንደዛው።
ቀልድም ይሁን ጨዋታ የማይጠቅምበት አስፈሪ ለሆነው ቀንህ የምትሰበስበውን እያሰብክ ኑር!! | 3 316 |
