🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
تُعد قناة 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 168 مشتركاً، محتلاً المرتبة 7 298 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 776 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 168 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -26، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -9، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.34%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.29% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 597 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 496 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 28.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 04 سبتمبر | +5 | |||
| 03 سبتمبر | 0 | |||
| 02 سبتمبر | +4 | |||
| 01 سبتمبر | 0 |
| 2 | ✍
ላም=> ውሀ ትጠጣና ወተት ትሰጣለች:
እባብ=> ያንኑ ውሀ ትጠጣና መርዝ ትረጫለች!!
የጌታህ ስራ ተኣምር ነው!! | 1 144 |
| 3 | ✍
ሦሥት ነገሮች ድንገት ይመጣሉ፦
ሞት፣
ሪዝቅ እና
የቤት ኪራይ!! | 1 164 |
| 4 | ✍
የዐረቦች የአእምሮ ፍጥነት ግን ምን ጉድ ነው??……
ምን ሆነ መሰላችሁ??………
ከዕለታት በአንዱ ቀን አንድ ከሩቅ ሀገር የመጣ መንገደኛ ሓተም አል_ጣኢ ቤት በእንግድነት ይገባል። ከወትሮው የሓተም ባህሪ ፍጹም ተቃራኒ በሆነ መልኩ እንግዳው ምግብም ይሁን መጠጥ ሳይቀርብለት በባዶ ሆዱ ያድራል። ልክ ሊነጋጋ ሲል እንግዳው ማንም ሳያየው በዝግታ ይወጣና መንገዱን ይቀጥላል።
በድብቅ ሲከታተለው የነበረው ሓተም መጓጓዣው ላይ ይቀመጥና ፊቱን ተከናንቦ በሌላ መንገድ በማቋረጥ ከእንግዳው ፊት ይደርሳል።
የተለምዶ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ………
ሓተም:… "ወዴት ነው ምቴደው? አዳርህ የት ነበርክ?" አለው።
እንግዳው:… "አዳሬ ሓተም አል_ጣኢ ቤት ነው ያደርኩት።" አለው።
ሓተም:… "እና እንዴት ነበር?" አለው።
እንግዳው:… "በጣም አሪፍ ነበር። አርዶ ስጋ አበላኝ: ወተትም አጠጣኝ: መጓጓዣዬም ተንከባከበልኝ። አላህ ያክብረው" አለው።
ሓተም ፊቱን ገለጠና "ወደ ቤት ተመልሰን የዘረዘርካቸው ሁሉ ሳይደረግልህ ወዴትም አትሄድም" ብሎ መለሰውና ያማረ መስተንግዶ አደረገለት።
በመጨረሻም:…… "ለምን ስትል ነው ያልተደረገልህን ተደርጎልኛል ብለህ የዋሸኸው?" ሲለው;
"የውልህ፧ ሁሉም ሰዎች ስለ አንተ ደግነትና ቸርነት ነው የሚያወሩት። እኔ ስለ አንተ ክፋት ብናገር ሁሉም ሰው ውሸታም ብሎ ያነውረኛል እንጂ ህዝብ የሚያወድስህን ትቶ እኔ ያወገዝኩህን የሚቀበለኝ አይኖርም። ስለሆነም ለአንተ ብዬ ሳይሆን ለራሴ ክብር ስል ነው ውሸቱን የተናገርኩት!!" አለው። | 1 275 |
| 5 | ✍
አዲስ ንጋት...……
ከአላህ ጋ የሚደረግ ግንኙነት የሚታደስበት……
ልቦች ጌታቸው ላይ የነበራቸው ተስፋ የሚሞሉበት…
የዕለቱ ትልቁ ስኬት ማለት;
💫ቀንህን ለጌታህ ጥሪ ምላሽ በመስጠት ስትጀምረው ነው!!
💫የዕለቱ የመጀመሪያ ጉዞህ ወደ አላህ ቤት የምታደርገው ጉዞ ሲሆን ነው!!
💫የዕለቱ የመጀመሪያው ንግግርህ ከጌታህ ጋ የምታደርገው ንግግር ሲሆን ነው!!
ለልቡ ብርኃን፧ ለቀልቡ ሰኪና አጎናፅፎ, የሌሊትና የቀን መላኢካዎች በተጣዱበት, ውሎውን በሰላት የጀመረ ሰው ምንኛ የታደለ ነው??!!
🤲አላህ ይወፍቀን🤲 | 1 319 |
| 6 | ✍
በጠዋት ተነስተን ሻወራችን ወስደን
ከጥፍራችን ቆርጠን ጥርሳችን ቦርሸን፣
ጥምጣም ጀለቢያ ከነጫጩ ለብሰን
ሽቶ ተነስንሰን ተውበን አጊጠን፤
ጉዞ ወደ መስጂድ ሳይረፍድ በጠዋቱ
ቁርኣንና አዝካር በዝቶ ሰለዋቱ፤
ኹጥባ በፀጥታ ተቀምጠን አድምጠን
ጁሙዐችን በጀምዐ ለጌታችን ሰግደን፤
ፀሓይ እስክትገባ እስኪታይ ወጋገን
አላህን አብዝተን እንለምነዋለን!! | 1 309 |
| 7 | ✍
የዓለም ሚዛን ሲዛባ፤
ብልሽት ሜዳውን ሲቆጣጠር፤
የማህበረሰቡ አመለካከት ሲበለዝ፤
እውነት እንደ እንግዳ ተቆጥራ ታፍራለች።
ንፅህና እንደ ወንጀል ማሸማቀቂያ ይሆናል።
📖{أَخْرِجُوهُم مِّن قَرْيَتِكُمْ إِنَّهُمْ أُنَاسٌ يَتَطَهَّرُونَ}
{ከቀጠናችሁ አስወጧቸው: እነሱ የሚጥራሩ (ንፁህ) ሰዎች ናቸው።} | 1 392 |
| 8 | 🤲
ጁሙዐም አይደል?
📖﴿إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلّونَ عَلَى النَّبِيِّ يا أَيُّهَا الَّذينَ آمَنوا صَلّوا عَلَيهِ وَسَلِّموا تَسليمًا}
{አላህና መላኢካዎቹ በነቢዩ ላይ ሰለዋት (የአክብሮት ውዳሴና ዱዐ) ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት ዱዐን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡}
💫ከነብዩﷺ በተላለፈው……
🌙«أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشرا »
«ጁሙዐ ቀንና ጁሙዐ ሌሊት በእኔ ላይ ሰለዋት አብዙ። በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው በእሱ ላይ አላህ ዐስር ጊዜ ሰለዋት ያወርድበታል።»
🌙«من صلى علي مرة كتب الله له بها عشر حسنات»
«በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው አላህ ለእሱ በዚህ ምክንያት ዐስር ምንዳ ይፅፍለታል።»
🌙« من صلى علي من أمتي صلاة مخلصا من قلبه صلى الله عليه بها عشر صلوات ورفعه بها عشر درجات وكتب له بها عشر حسنات ومحا عنه عشر سيئات »
«ከኡመቶቼ ውስጥ ከቀልቡ ጥርት አድርጎ በእኔ ላይ ሰለዋት ያወረደ የሆነ ሰው; አላህ በእሷ ምክንያት ዐስር ሰለዋት ያወርድበታል፣ ዐስር ደረጃም ከፍ ያደርግለታል፣ ዐስር ምንዳም ይፅፍለታል፣ ዐስር ወንጀልም ያብስለታል።»
🌙« من صلى علي واحدة صلى الله عليه عشرا »
«በእኔ ላይ አንድ ሰለዋት ያወረደ በእሱ ላይ አላህ ዐስር ያወርድበታል።»
🤲اللهم صل على محمد وعلى آل محمد
كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد،
🤲اللهم بارك على محمد وعلى آل محمد
كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد.
ወደ መልካም ያመላከተ እንደ ሰሪው ነው!!
💎💎💎💎💎💎💎 | 1 519 |
| 9 | ✍
አላህ ያዘዘህ ነገር በመስራት ላይ ታገስ፤
አላህ ዕርም ያደረገውን በመተው ላይ ታገስ፤
አላህ ወስኖት በሚደርስብህ ሙሲባ ታገስ!!
መጨረሻ ላይ የምትሰማው ይህ ይሆናል፦
📖{سَلَامٌ عَلَيْكُم بِمَا صَبَرْتُمْ فَنِعْمَ عُقْبَى الدَّارِ} | 1 339 |
| 10 | 🕋 ልዩ የዑምራ ፓኬጅ✅
🎙በኡስታዝ አቡ አብድልመናን ኻሊድ መሪነት
ከተወዳጁ የለምለም ትራቭል✈️
ሁለት ጁመአዎችን በሁለቱ ሐረሞች
ልብህ በተውባ፣
ገላህ በዘምዘም፣
🚨ሩሕህም በሐረመይን ተረጋግቶ፤
ከዱንያ ጭንቀቶች ለጥቂት ቀናት ተላቀህ፣ የዱንያና የአኺራ ሐጃህን ለሰሚው እና ለአዛኙ ጌታህ የምታቀርብበት ውብ አጋጣሚ
የረሱልﷺ ማረፊያ የሆነችው መዲነቱል ሙነወራ ጨምሮ
➡️🎓የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ
➡️✈የደርሶ መልስ የአየር ትኬት
➡️ 🎓የባስ ትራንስፖርት
➡️💳አመታዊ የዑምራ ቪዛ
➡️🎓 የሆቴል ክፍያ
➡️🎁አጠቃላይ የዑምራ ጉዞውን ያካተተ ልዩ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል
ከመስከረም1⃣5⃣እስከ2⃣5⃣
Sept2⃣5⃣–Oct0⃣5⃣
ኢንሻአላህ ያማረ ቆይታ ይኖረናል
🫱ይህንን ዕድል ሳያስመልጡ አሁኑኑ ይደውሉ! ፈጥነው ይመዝገቡ📝
✈️ የለምለም ትራቭል—የትውልዱ ተስፋ!
🫱0911674580
🫱 0911683917
🫱 0922448888
አድራሻ📍ቤተል ሚና ሞል 2ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
✅Telegram:
https://t.me/Yelemlem_travel | 1 591 |
| 11 | ✍
ለእሱ ብረት አለዘብንለት!!………
📖{وَلَقَدْ ءَاتَيْنَا دَاوُۥدَ مِنَّا فَضْلًۭا ۖ يَٰجِبَالُ أَوِّبِى مَعَهُۥ وَٱلطَّيْرَ ۖ وَأَلَنَّا لَهُ ٱلْحَدِيدَ}
{ለዳውድም ከእኛ የሆነን ችሮታ በእርግጥ ሰጠነው፡፡ "ተራራዎችና በራሪዎችም ከእርሱ ጋር ውዳሴን መላልሱ" አልን። ብረትንም ለእሱ አለዘብንለት፡፡}
{ብረትን አለዘብንለት (አለሰለስንለት)}፦
ብረት በተፈጥሮው ደረቅና ጠንካራ ነው። ነገር ግን የአላህ ችሮታ በመጣ ጊዜ እንደ ቂጣ የለዘበ ለስላሳ ሆነ።
የሰው ልጅ በየትኛውም ዓይነት መልኩ ሊቆጣጠራቸውና ሊያዛቸው የማይቻሉት ግዑዝ ተራራዎች ጭምር ከዳኡድ ጋ አብረውት አላህን እንዲያጠሩ ተገሩ። በራሪ አዕዋፍትን ጭምር ዳኡድ አጅበው አምልኮ ይፈፅሙ ዘንድ ታዘዙ።
ዋናው ጉዳይ የነገሩን መጠንከር ላይ ሳይሆን; የነገሩ አስተናባሪ ላይ ነው።
በሕይወት ጉዞህ ብዙ ነገር ሊገጥምህ: ብዙ ልታስብ ትችላለህ;
ጉዳዩ እንደማይሳካ፣ በሮቹ እንደማይከፈቱ፣ መንገዱ እንደማይቃና፣ ሰዎቹም እንደማይለወጡ ተስፋ ቆርጠህ ታውቅ ይሆናል። ምክንያቱም፦
አንተ የሚታይህ የጉዳዩ ውስብስብነት ብቻ ነው፤ አላህ ግን እንዴት እንደሚገራው ያውቃል!!
ከችግሩ መውጫ መንገድ ስላልታየህ ብቻ: መፍትሔ የሌለው ችግር አድርገህ አትወስንበት።
በቻልክው አቅም ሁሉ ጥረት አድርግ፣ አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎች ሁሉ ውሰድ፣ ከአላህ ጋር ያለህን ግንኙነት አስተካክል። ከዚያም;
ከአቅምህ በላይ የሆነውን ነገር ምንም ለማይሳነው አላህ አደራ ስጥ።
አላህ ፈቃዱን ለመፈጸም የአንተን ዘዴዎች አያስፈልጉትም። ብቻ ግን ጥረት እንድታደርግ አዞሃል። እንዲሁም ተስፋህ ሙሉ ለሙሉ በጥረትህ ላይ እንዳታደርግ: በሰበብህ ላይ እንዳታስደግፍ አስጠንቅቆሃል።
ብዙ አንኳኩተህ ያልተከፈቱልህ በሮች አላህ ከፈለገ ያለምንም ሰበብ ሊከፈቱ ይችላሉ። ወይም ረዥም ጊዜ ከጠበከው በር ፈጽሞ ያዞርህና ወደ ሌላ በር ሊመራህ ይችላል።
ብዙ ደክመህ ያልሆነልህን: የእሱ ችሮታ በመጣ ጊዜ ያለ ምንም ሰበብ ሊያሳካው ይችላል። አልያም እሱን ያስረሳህና አንድም ቀን አእምሮህ ላይ ውል ወዳላለ ጉዳይ አስገብቶ ሊያስኬድህ ይችላል። አሊያም ቀደም ሲል የማይቻል መስሎህ የነበረውን ነገር ለማሸነፍ የሚያስችል ኃይል ሊሰጥህ ይችላል።
እውነተኛው መታደል ማለት፦
ሕይወት አንተ በምትፈልገው መልኩ ብቻ ስትሄድልህ ሳይሆን; ምንም እንኳ ፍላጎትህ ቢቃረንም ለአንተ የሚበጀውን አላህ ሲሰጥህ ነው።
ስለዚህ መንገዱ የሚከፈተው መቼ ነው?? እንዴት?? ከየት?? እና በመሣሠሉ ጥያቄዎች ራስህን አታስጨንቅ።
በጣም ብዙ ምክንያትና ረዥም ጊዜ ይፈልጋሉ ብለህ ያሰብካቸው ብዙ ጉዳዮች ነበሩ፤ የጌታህ ውሳኔ ሲሆን ግን እንዴት እንደሆነ እንኳ በማታውቀው መልኩ ተሳክተው ተፈፅመውልሃል።
እንዲከፈቱልህ ጓጉተህ ለረዥም ዘመናት ስታንኳኳቸው የነበሩ ብዙ በሮች ነበሩ፤ አላህ ለአንተ የመረጠው ግን አንተን ሙሉ ለሙሉ ከነዝያ በሮች በማራቅ ላይ ነበር።
የአቅምህን ጥረት እንድታደርግ እንጂ: እያንዳንዱ ሩጫህ ላይ ስኬት እንድታስመዘግብ አልተገደድክም። | 1 633 |
| 12 | 🕋
መካን መውደድ ዒባዳ መሆኑን ያውቀሉን?? | 1 822 |
| 13 | ✍
ጊዜ ወርቅ መሆኑን የሚገባህ እዚህ ጋ ነው………
📖{وَءَاخَرُونَ ٱعْتَرَفُوا۟ بِذُنُوبِهِمْ خَلَطُوا۟ عَمَلًۭا صَٰلِحًۭا وَءَاخَرَ سَيِّئًا عَسَى ٱللَّهُ أَن يَتُوبَ عَلَيْهِمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ غَفُورٌۭ رَّحِيمٌ}
{ሌሎችም በኃጢኣቶቻቸው ያመኑ: መልካም ሥራንና ሌላን መጥፎ ሥራ የቀላቀሉ አልሉ፡፡ አላህ ከእነሱ ጸጸታቸውን ሊቀበል ይከጀላል፡፡ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡}
[አል_ተውባ:¹⁰²]
📖{فَٱعْتَرَفُوا۟ بِذَنۢبِهِمْ فَسُحْقًۭا لِّأَصْحَٰبِ ٱلسَّعِيرِ}
{በኀጢኣታቸውም ያምናሉ ለእሳት ባልደረቦች (ከእዝነት) መራቅ ተገባቸው፡፡}
[አል_ሙልክ:¹¹]
ሁለቱም ቡድኖች በወንጀላቸው አምነዋል። የማመኛው ጊዜ መለያየት ግን ሁለቱ መሃል የፈጠረው ልዩነት ተመልከት፦
የመጀመሪያዎቹ፦
ከረሱልﷺ ጋ ዘመቻ ከመውጣት ወደ ኋላ ቀርተው: በስተመጨረሻም የሰሩትን ወንጀል አምነውና በወንጀላቸው የተፀፀቱ ሰሓቦች በተመለከተ የወረደ አንቀጽ ነው። ወንጀል ሰርተው ነበር: ዱንያ ላይ ሳሉ በወንጀላቸውን አምነው ተፀፀቱ። አላህ ሊምራቸው እንደ ሚከጀል አበሰራቸው። አላህ {ይከጀላል} ብሎ ካበሰረ ይሆናል ማለት ነው።
ሌላኞቹ፦
ጀሀነም የገቡ ሰዎች እዛ ውስጥ የሚሆኑት የስቃይ ሕይወት በተመለከተ የወረደ አንቀፅ ነው። እነርሱም በወንጀላቸው አምነዋል: ግን ማመን በማይጠቅምበት ጊዜ ነው።
አዎን ሁሉም መፀፀቱ አይቀርም;
ፀፀትህ ዋጋ የሚኖረው ግን ዛሬ ነው!! | 1 934 |
| 14 | 🕰 | 1 |
| 15 | ✍
እውነት ነው እኮ……………
በረሮ => አይጥ ትፈራለች
አይጥ => ድመት ትፈራለች
ድመት => ውሻ ትፈራለች
ውሻ => ወንድ ይፈራል
ወንድ => ሴት ይፈራል
ሴት => በረሮ ትፈራለች | 1 834 |
| 16 | ✍
አንዳንድ ስብራቶች;
ለአዲስ ሕይወት ጅማሪ ናቸው!! | 1 977 |
| 17 | ✍
ረሱልﷺ…………
📚«إنَّ أوَّلَ ما يُحاسَبُ به العبدُ يومَ القيامةِ من عملِه صلاتُه،
አንድ ባሪያ የቀቂያማ ዕለት ከስራዎቹ ሁሉ መጀመሪያ የሚጠየቀው ስለ ሰላቱ ነው:
فإن صلحت فقد أفلح وأنجح،
እሷ ከተስተካከለችለት በእርግጥም ድኗል ተሳክቶለታል፤
وإن فسدت فقد خاب وخسر
እሷ ከተባለሸት ከስሯል ጠፍቷል።» አሉ። | 1 851 |
| 18 | 🥰ልዩ የዑምራ ፓኬጅ
ከተወዳጁ የለምለም ትራቭል✈️
ልብህ መካን ናፍቆታል?
መዲናን በዓይንህ ለማየት ተመኝተሃል?
እንግዲያውስ… ይህ ጊዜህ ነው! 🤲
በሀገራችን በተለያዩ ምክንያቶች ለስራ ዝግ ሆነው የሚውሉ ቀናቶችን ከአረህማን እንግዶች አንዱ ሆነው በሐረመይን ያሳልፉ
ከመስከረም 1⃣4⃣_መስከረም2⃣4⃣
3⃣ቀናት በውቢቷ መዲና
7⃣ቀናት በተከበረችው መካ
✅ልዩ የዑምራ ፓኬጅ
🎙በኡስታዝ አቡ አብድልመናን ኻሊድ የሚመራ ፍሆናል
የልብህን ናፍቆት ወደ እውነተኛ ጉዞ ቀይር።
ምናልባት የምትጠብቀው ጊዜ ይህ ይሆናል!
አትዘግይ—አሁኑኑ 🖤ፈጥነህ ተመዝገብ!
🎓ሆቴሎቻችን እስታንዳርዳቸውን ጠብቀው🎈
ከሁለቱም ሐረሞች ቅርብ ርቀት ላይ ይገኛሉ
በአላህ ፈቃድ እጅግ ውብና ያማረ ቆይታ ይኖረናል።
☑ ስለመረጡን እናመሰግናለን
✈️ የለምለም ትራቭል
ምርጫ ብቻ ሳይሆን ብልጫም ነው!
📞 0911674580
📞 0922448888
📞0911683917
📍አድራሻ ቤተል ሚና ሞል — 2ኛ ፎቅ
https://t.me/Yelemlem_travel | 1 897 |
| 19 | ✍
ከደጋጎች አንዱ ለይል ተነስቶ ይሰግድና…………
አላህ ሆይ! እኔ ማለት፦
ያ…… ሰዎች የሚያውቁኝ ሷሊሕ ሳልሆን; አንተ የምታውቀኝ ወንጀለኛው ባሪያህ ነኝ፤ አደራህ ግርዶሽህ እንደትገልጥብኝ!!
ብሎ ያለቅስ ነበር።
ቦታ ከማንሰጣቸው ትላልቅ የአላህ ፀጋዎች አንዱ;
ድክመታችን, ዓይባችን, ወንጀላችን እንዳይታይ የሰተረበት ግርዶሹ ነው።
አንደኛችን ሲትሩ ተገልጦ ሙሉ ማንነታችን ሰዎች ቢመለከቱት; ይቅርና ሌላው ሰላምታ እንኳ የሚያቀርብልን እስከማይኖር ሁሉም ይጠየፈን ነበር። | 1 935 |
| 20 | ✍
ሸይጧን……………
ወደ ፊትና አልጎተትም ብትለው ሁላ; ፊትናው ወደ አንተ ይጎትተዋል!!
ኢማንህ ጨመርመር በሚልበት ጊዜ;
"ኣዑዙ_ቢላህ" ብለህ ስትሸሽ ተከታትለው ሲመጡብህ አልገጠመህም??!! | 1 832 |
