🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
El canal 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 12 204 suscriptores, ocupando la posición 7 404 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 761 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 12 204 suscriptores.
Según los últimos datos del 14 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 81, y en las últimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 28.87%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 14.01% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 521 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 709 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 49.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 15 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 15 julio | +9 | |||
| 14 julio | +3 | |||
| 13 julio | +1 | |||
| 12 julio | +3 | |||
| 11 julio | 0 | |||
| 10 julio | 0 | |||
| 09 julio | +7 | |||
| 08 julio | +3 | |||
| 07 julio | +8 | |||
| 06 julio | +8 | |||
| 05 julio | +9 | |||
| 04 julio | +13 | |||
| 03 julio | +1 | |||
| 02 julio | +8 | |||
| 01 julio | 0 |
| 2 | ✍
ኒቃብ.......
ዋጂብ ከሆነ => ድነሻል!!
ሱና ከሆነ => ማርከሻል!!
መጠበቂያ ከሆነ => ተከልለሻል!!
የተወደደ ከሆነም => አላህ ከወደደው ነገር መብቃቂያ የለሽም!! | 996 |
| 3 | ✍
የኢብኑ ጀውዚ ጥያቄ ዛሬም ድረስ ምላሽ አላገኘም;
🫵በጀሀነም ሰዎች ስራ ነው ጀነት ለመግባት የምታስበው??? | 1 098 |
| 4 | ✈️
ምዝገባው ሊጠናቀቅ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል!!
ዋናው ነገር......
አለመፍጠንህ ሳይሆን: አለመቅረትህ ነው!!
ብልሆች ተሽቀዳድመው ይመዘገባሉ: ዕድለኞቹ ግን ባለቀው ሰዓት ዕድላቸው በመጠቀም ይካተታሉ።
የምነግርህ ስለሌላ ሳይሆን;
ወደ አላህ 🕋ቤት በአብሮነት ለመጓዝ ስለተዘጋጀው የጉዞ ፕሮግራም ነው!!
የሕይወትህ ምርጡ ቀናቶች ለማየት በሑለቱ ሐረሞች አስር ቀናት ለመቆየት የተዘጋጀው የክረምት ልዩ የዑምራ ፓኬጅ ምዝገባው ሊጠናቀቅ ሁለት ቀናቶች ብቻ ቀርተውታል።
ከሁሉም ሙሓለፋዎች በጠራ መልኩ: እንግልትና መቸጋገር ሳያገኛችሁ: ለሁለቱም ሐረሞች ቅርብ በሆኑ ሆቴሎች እያረፋችሁ: የማይረሳና ምርጥ የዑምራ ስርዓታችሁ ማከናወን ትችሉ ዘንድ: የለምለም ትራቭል ልዩ የዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅቶላችኋል።
በቀጣዩ እሄዳለሁ አትበሉ፦
አላህ ካቆያችሁ በበረካው ትደግማላችሁ፤ የአላህ ውሳኔ ከቀደመ የማትፀፀቱበት ጉዞ ይሆናችኋል!!
ፓኬጁ የሚሆነው......
🗓ከሐምሌ_16 እስከ ሐምሌ_26 ነው;
የምዝገባው መዝገብ ከመዘጋቱ በፊት ዛሬውኑ ደውላችሁ ቦታ አስይዙ።
🤳 0911674580
🤳 0922448888 ለእናንተ ክፍት ናቸው።
ቤተል ሚና_ሞል ሁለተኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
✈️የለምለም ትራቭል የትውልዱ ተስፋ!!
👇
👉https://t.me/Yelemlem_travel | 1 352 |
| 5 | ✍
ምንም ነገር ላይ የሌለ ሰው; ቀስ በቀስ ሁሉም ዘንድ መረሳቱ አይቀሬ ነው!!
🫵መኖርህ ተረስቶ
መሞትህ ሳይታወቅ ተረስተህ እንዳትቀር፤
በዳዕዋው ሂደት ላይ
የድርሻህን ይዘህ ክፍተቶች በማጠር፤
አንተ የሞትክ ለታ
በሙስሊሞች መሃል ቀዳዳ ይፈጠር!! | 1 236 |
| 6 | 👆
ሁላችሁም አድምጣችሁ ሼር አድርጉት!!
በዕውቀትም ይሁን በገንዘብ የምትችሉትን ሁሉ ለማድረግ እያሰባችሁ ተዘጊጁ!! | 1 236 |
| 7 | ✅ የሀዲያው የዳዕዋ ጉዞ በተመለከተ የተሰጠ ማብራሪያ
👉ሁሉም ሰው ሊሰማውና ሊያዳምጠው የሚገባ የዳዕዋ ማብራሪያ ነው
👉በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ የህያ ኤሊያስ ቢን አወል
ማክሰኞ ከመግሪብ እሰከ ኢሻ
🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት
https://t.me/Abu_Yehya_ilyas_Awel/7874 | 888 |
| 8 | ✍
ወደ ሰፊው መቅበራ በአግራሞት እየተመለከተ......
"እዚህ ከተኙት: ከፊሉ ሟች ሲሆን ከፊሉ ሕያው ነው" አለ።
ሷሊሕ ልጆት ትቶ የሄደ ሰው ከመሬት ስር ቢተኛም ሕያው ነው፤ ከዚህ ሌላ የሆነው ግን ከሞተ በቃ ሞቷል ማለቱ ነው። | 1 322 |
| 9 | ✍
ስለ ሰሓባዎች እና ተከታዮቻቸው አላህ ሲናገር፦
📖{وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلْأَوَّلُونَ مِنَ ٱلْمُهَٰجِرِينَ وَٱلْأَنصَارِ وَٱلَّذِينَ ٱتَّبَعُوهُم بِإِحْسَٰنٍۢ رَّضِىَ ٱللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا۟ عَنْهُ وَأَعَدَّ لَهُمْ جَنَّٰتٍۢ تَجْرِى تَحْتَهَا ٱلْأَنْهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَآ أَبَدًۭا ۚ ذَٰلِكَ ٱلْفَوْزُ ٱلْعَظِيمُ}
{የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎቹ ከሙሃጂሮችና ከአንሷሮች እነዚያም በበጎ ሥራ የተከተሏቸው አላህ ከእነርሱ ወዷል እርሱም ወደዋል፡፡ በሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ጀነቶች በውስጣቸው ዘለዓለም ነዋሪዎች ሊሆኑ ለእነርሱ አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል ነው፡፡} ይላል።
[አል_ተውባ:¹⁰⁰]
ግልፅ በሆነ ቃሉ ለሰሓባዎች በልቁ ከዝያ በኋላ ለሚመጡት ሰሓቦችን በመልካም ከተከተሉ ስራቸው እንደሚወድላቸውና እነርሱም ከአላህ የሚሰጣቸውን ምንዳ እንደሚወዱ፤ በመጨረሻም የዘለዓለም መዘውተሪያዋ ጀነት እንደሚለግሳቸው ቃል ገባላቸው።
ሺዐዎች መጥተው........
ሰሓባዎችን አከፈሩ፤ የእነርሱ መንገድ የተከተሉ ሱንይ ሰለፍዮችም በማክፈር እያደኑ ይገድላሉ።
በዛሬው ዕለት ከሞት ለተረፉት ታላቁ ሸይህ አላህ ሐያታቸው እንዲያረዝመውና: የተሰዉት ልጃቸውና ባልደረባቸው አላህ የሸሂድነት ማዕረግ እንዲሰጣቸው እንማፀነዋለን!! | 1 647 |
| 10 | ✍
fire age ዓለምህን የምትቀጭበት ወይስ ዓለምን የምታንፅበት ዕድሜ???
መልካም ቀደምቶቻችን "fire age" ብለን "ዓለምን መቅጨት" በሚል ኋላ_ቀር አባባል የምናባክነው የዕድሜ ክፍል ላይ ሳሉ: ምን ዓይነት ተዓምር ሰርተው ዓለምን እንዴት እንዳነፁ የሚያሳዩ ከፊል ናሙናዎች እንመልከት።
1ኛ, ኡሳማ ቢን ዘይድ;
በ18 ዓመቱ የሙስሊሞች የጦር አበጋዝ (ጀነራል) ሆኖ መርቷል። እሱ የገጠመው ሰራዊት በምድር ላይ ከባድ የሚባለውን ጦር ሲሆን ዘመቻው ላይ እሱ መሪ ሲደረግ እንደ አቡ በክር እና ዑመር ያሉ ታላላቅ ሰሓባዎች ነበሩበት።
2ኛ, ዘይድ ቢን ሳቢት;
በ13 ዓመቱ ወሕይ መፃፍ ጀምሮ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ የሶሪያዊያን እና የየሁዳዎችን ቋንቋ በ17 ቀናት ብቻ ተምሮ በመሸምደድ የረሱልﷺ ተርጓሚ መሆን ችሏል።
3ኛ, ዙበይር ቢን ዓዋም;
በ15 ዓመቱ በእስልምና የመጀመሪያወ ሰይፍ የመዘዘው እሱ ነው። የነብዩﷺ ረዳት ተብሎም ይታወቅ ነበር።
4ኛ, ሙዓዝ ቢን ኣምር ቢን ጀሙህ እና ሙዐወዝ ቢን ዓፍራ;
ሙዓዝ የ13 ዓመት: ሙዐወዝ የ14 ዓመት ታዳጊ በነበሩበት: በበድር ዘመቻ ላይ የሙሽሪኮች ዋና መሪ የነበረው አቡጀህልን ገደሉ።
5ኛ, ዑታብ ቢን ኡሰይድ;
የ18 ዓመት ታዳጊ ሆኖ ነብዩﷺ መካ ላይ ሹመውታል።
6ኛ, ሰዒድ ቢን አቢ ወቃስ;
በ17 ዓመቱ በእስልምና የመጀመሪያውን ቀስት ያስወነጨፈው እሱ ነው።
7ኛ, አርቀም ቢን አቢ አርቀም;
በ16 ዓመቱ ቤቱ ለ13 ዓመታት የነብዩﷺ ማረፊያ እንዲሆን ሰጥቷል።
8ኛ, ጠልሓ ቢን ዑበይዲላህ;
በ16 ዓመቱ እስልምና ውስጥ የዐረቦች ቸር ተብሎ የተሰየመ ሲሆን በኡሑድ ዘመቻ እስከ ሞት ለመጋደል ለረሱልﷺ ቃል ገብቷል። በዚሁ ዘመቻ ረሱልﷺ ላይ የተወነጨፉ ቀስቶች በእጁ እየተከላከለላቸው ነበር: በዚህም ሰበብ እጁ ሽባ ሆናበታለች።
9ኛ, ኢማም ማሊክ ኢብኑ አነስ;
በ17 ዓመቱ የፈትዋ ወንበር ላይ ሲቀመጥ "የስደቷ ሀገር ኢማም" ተብሎ ተሰይሟል። "70 ያህል የመዲና ዑለማዎች “ለፈትዋ በቅተሃል” ብለው ከመሰከሩልኝ በኋላ ነው ለፈትዋ የተቀመጥኩት" ይላል።
10ኛ, መሐመድ ቢን ቃሲም;
በ17 ዓመቱ "ሲንድ" የተባለች ሀገር መክፈት የቻለ ሲሆን በዘመኑ ትላልቅ ከሚባሉ የጦር ጀነራሎች ውስጥ ተጠቃሽ ነበር።
እነዚህ ለናሙናነት እንጂ ያልተጠቀሱት በጣም በርካታ ናቸው። | 1 904 |
| 11 | 🤳
imagine........
ሁለት እርስ በእርስ የማይተዋወቁ ከስተመሮችህ በተመሣሣይ ሰዓት አንተጋ ቆመው የተለያየ ዕቃ እያሳየህ ስታስተናግዳቸው;
አጋጣሚ ሁለቱም የአንድ ብሄር ሰው ይሆኑና ማይገባህ መስሏቸው በቋንቋቸው እያወሩ...... አንዱ ለሌላው ስለአንተ ታማኝነት ሲነግረው የሚሰማህ የደስታ ስሜት........ ውስጥህ እኮ ነው የሚስቀው!!
እዘዙን.... ጠይቁን.... በታማኝነት እናገለግላችኋለን!!
እኛን ለማግኘት የመሰላል ምልክቱን ይጫኑ
👇👇👇
#⃣#⃣#⃣#⃣ ##### #⃣#⃣#⃣#⃣ | 1 871 |
| 12 | ✍
አንድ ወንድ ለአንዲት ሴት ሁሉም ነገር ሲያደርግላት ካየህ;
እሷ የሚወዳት ሴት እንደሆነች ዕወቅ፤
አንዲት ሴት ለአንድ ወንድ ሁሉም ነገር ስታደርግለት ካየህ;
እሷ እናቱ እንደሆነች ዕወቅ!! | 2 088 |
| 13 | ✍
የአካል ነውር በልብስ ይሸፈናል፤
የአስተሳሰብ ነውር በክርክር ይገለጣል!! | 2 126 |
| 14 | 🇸🇦
አለመቻልና አለመመቻቸት ሆኖ እንጂ.....
ሁሉም ሱንይ ሙወሒድ ቀሪ የዱንያ ዘመኑ በዚች🇸🇦 ሀገር እንዲሆን የሁል ጊዜ ምኞቱ ነው!!
🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦 | 2 222 |
| 15 | ✍
የወንጀል ምሳሌው ልብ ላይ ልክ እንደ መርዝ ነው: ባይገለው እንኳ አይቀሬ ያደክመዋል። የደከመ እንደሆነ በሽታዎች የመቋቋም አቅሙ ያጣል።
/ኢማም ኢብኑል ቀይም/
የልብ ዶክተር ተብሎ የተሰየመው ኢብኑ ሙባረክ እንዲህ ይላል....
رَأَيْتُ الذُّنُوبَ تُمِيتُ الْقُلُوبَب
وَقَدْ يُورِثُ الذُّلَّ إِدْمَانُهَا
وَتَرْكُ الذُّنُوبِ حَيَاةُ الْقُلُوبِ
وَخَيْرٌ لِنَفْسِكَ عِصْيَانُهَا | 2 123 |
| 16 | ✍
ለጓደኛው:... "እንትና ደስ አይለኝም" አለው።
"እሱ ሰውየ ለእኔም አይመቸኝም" አለውና;
"ማን ያውቃል አላህ ልባችን ላይ የሷሊሖች ውዴታ ፍቆብን ቢሆንስ?" አለው።
ሁሌም ራስን አሳንሶ ሌሎችን ማተልቅ የትላልቅ ሰዎች ባህሪ ነው!! | 2 294 |
| 17 | ✍
هربوا من الرقِّ الذي خُلقوا له
فبُلُوا برقِّ النفسِ والشيطانِ
/ኢብኑ ዕሰይሚን “ይህ ስንኝ በዓይን ውሀ ቢፃፍ ያንሰው ነበር” ይላል/ | 2 371 |
| 18 | ✍
ሳትወልድ ብላ ❌
ሳትወልድ ተኛ ✅ | 2 681 |
| 19 | ✍
ሁሉም ሟች ስርዓተ ቀብሩ ሲፈፀም በሚነገርለት ልክ ቢሆን ኖሮ;
ጀሀነም ባዶ ትሆን ነበር። ይላል
ሙት ብቻ........
ሁሉም ሰው መልካምነትህ ይናገራል፤ ወዳጅህም ይሁን ጠላትህ ሁሉም ዓፍው ይልሃል። | 2 745 |
| 20 | ✍
ሁለቱ ሙሲባዎች አምሳያ ተገኝቶላቸው አይታወቅም ይላል፦
የኣደም ልጅ ሲሞት......
ሀብቱን በአጠቃላይ ይወረሳል፤
ስለ አጠቃላይ ሀብቱ ይጠየቃል። | 2 653 |
