Abu Hayder Aliy
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
379
مشترکین
+1624 ساعت
+177 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
Repost from شـبـاب السـلــفـــيـــيــن
ያል አግባቡ "ዋቂፋ የሚሉ ሰዎች አሉ።ታዳ ዋቂፋ የተባሉት እነማን ናቸው?
ዋቂፋዎችኮ ከጀህምያ የባሱ ናቸው ተብለዋል።ይህም ስያሜ የመጣው የአሏህን ቃል ቁርኣንን በተመለከተ ፉጡር ነው ወይም ፍጡር አይደለም እንልም ያሉትን ሰዎች የሚመለከት ነው።
አጨር ድምፅ ፋይል
ከሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ሸይኽ ኣደም"ሀፊዞሁሏህ
ይ ቀ ላ ቀ ሉ ይ ጠ ቀ ማ ሉ
🩵 T.ME/MULTEQA_SELEFIYIN
🩵 T.ME/MULTEQA_SELEFIYIN
+1
የአላህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም፡፡ አላህ በእርግጥ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡(❶❽)
ከለመናችሁትም ሁሉ የሰጣችሁ ነው፡፡ የአላህንም ጻጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም፡፡ ሰው በጣም በደለኛ ከሓዲ ነው፡፡(❸❹ )
ከተፈጠርን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ሙሉ ጊዜያችንን አላህን ሳናምፅ ብናመልከው እንድሁም ሙሉ አካላችን ከፀጉር እስከ-ጥፍር ምላስ ሆኖልን አላህን ብናመሰግን የአላህን ዉለታ አንከፍለዉም።
እስኪ ተመልከቱት ገና ሳንወለድ ጀምሮ እናታችን ሆድ ውስጥ ጠባቡን ቦታ እንዳይጠበን እንደፈለግን እንደንሆን ብሎ ከዱንያ የሰፋ አደረገልን ከዛም: ቀጥሎ እዛዉ እናታችን ሆድ ዉስጥ በዱንያ ያላገኘነዉን የተመጣጠነ ምግብ መገበን ከዛም: ሁላችንንም በእስልምና ፈጠረን ከዛም: በእስልምና እንድንፀና አደረገን ከዛም: ለሱ ታዛዥ አደረገን: ያረብ !ምነኛ ነዉ የታደልነዉ!!
ከዛም አካላችንን ሳያጓድልብን እዝህ አደረሰን የአላህ !ከዛም እራቁታችንን እንዳንሆን ያለበሰን ሳያልቅብን ሁሌም እያቀያየረ አለበሰን !ከዛ እንድም ቀን እንኳ እንዳይርበን ሁሌ እየመገበ እዝህ አደረሰን 'ከዛም ከምንፈራዉ ነገር እየጠበቀ :ከማይጠቅመን ነገር እያራቀ ለኛ እሚጠቅመንን ብቻ እያደረገለን እዝህ አደረሰን ! አኛ ግን በደለኞች ሁነን ለሱ እሚገባዉን ያክል አላመሰገነዉም አሱ እኛን ማብላት ማጠጣት ማልበስን ሳይሰለች እኛ ግን እሱን ማመስገንን ሰለቸን¡ የአላህ ! አላህ ይዘንልን ለሁላችንም እሱን አብዝተዉ ከሚያመሰግኑት ያድርገን 🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲
https://t.me/abu_haider_aliye
https://t.me/abu_haider_aliye
አሰላሙአለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካትሁ
አስደሳች ዜና
ታላቅ የሙሀደራ ፕሮግራም
እነሆ ዛሬ ማክሰኞ 11/9/2018 ፉሪ በሚገኘው ሰልሰቢል መስጅድ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ከሳኡዲ አረቢያ በመጡት ታላቁ ሸይኽ አቡ ኡመር ዶክተር አብዱረህማን የሚሰጠውን ቀልብ አርስ ምክር እንድትታደሙ ስንል በታላቅ ደስታ ጋብዘነዎታል ።አረበኛ መስማት ለሚከብዳችሁ ወንድም እና እህቶች በአማረኛ የሚተረጎም መሆኑን እናበስራለን።
በአካል ቦታው ላይ ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በቀጣዩ ሊንክ ገብታችሁ ላይቭ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን
https://t.me/yemesjidetewhidgebimasebasebiya
Repost from Huda Wave
ፈጥኖ የመለሰ! 🚀
ትክክለኛውን መልስ ያገኘ ሰው 'Add' የሚለውን በመጫን ብዙ ጠቃሚ ቻናሎችን ያገኛል።
➡️ ቻናል ለማሳደግ
ጥያቄ፦ በአስሩ (የዙል-ሒጃህ) ቀናት ከሚሰሩ መልካም ስራዎች ይልቅ አላህ ዘንድ ይበልጥ የተወደደ መልካም ስራ የሚሰራበት ሌላ ምንም ቀን የለም።
እኛ ሰዎች ስንባል በተፈጥሯችን ዚያዳን/ጭማሬ/ትርፍ ነገርን እንፈልጋለን ነገር ግን ብዙዎቻችን እምናሳዝነዉ እምንፈልገዉን ትርፍ ስንመለከት በዱንያ ትርፋማ መሆን ሆኖ እናገኘዋለን ደግሞ እሚገርመዉ እነኚህ በዱንያ የምንፈልጋቸዉ ትርፎች ስንሞት ለሌላ ሰዉ መሆናቸዉ ነዉ" ከዛም የለፋንበትን ትርፈ ዘመድ ተብየ ሁሉ እኔም ካልተካፈልኩ እያሉ ይሻሙበታል ። ሓቂቃ ዱንያ አላህ ዘንድ ርካሽ አታላይ አጭር መሆኗን እየረሳን ነዉ ቁርአንና ሓዲሦ የሚመክረን በአኼራ ትርፋማ እንድንሆን ነዉ ስለዚህ በመካሪያችን እነመከር !መጀመሪያ የታዘዝነዉን በመታዘዝ የተከለከልነዉንም በመከልከል እና ትርፍ ዒባዳዎችን :- ፆም :ቁርአን መቅራት : ሶደቃ መስጠት :ሱና ሶላት : ,,,,,,, የመሳሰሉትን በመስራት በአኼራ ትርፋማና የበላይ እንሆናለን በተለይም በነዚህ ቀኖቅች ከሰራናቸዉ ትርፋማ ያደርጉናል ከትርፍ ሁሉ በላጩ ትርፍ እራሳችንን ከቀብር ቅጣት ከጀሀነም እሳት ማትረፍ ነዉ።
https://t.me/abu_haider_aliye
https://t.me/abu_haider_aliye
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የዙል ሒጃ ስምንቱን ቀናት መፆም
~
ነብያችን ﷺ የዙልሒጃን አስር ቀናት አስመልክቶ እንዲህ ብለዋል፦
مَا مِنْ أَيَّامٍ الْعَمَلُ الصَّالِحُ فِيهِنَّ أَحَبُّ إِلَى اللَّهِ مِنْ هَذِهِ الأَيَّامِ الْعَشْرِ . فَقَالُوا : يَا رَسُولَ اللَّهِ ، وَلا الْجِهَادُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ؟ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : وَلا الْجِهَادُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ، إِلا رَجُلٌ خَرَجَ بِنَفْسِهِ وَمَالِهِ فَلَمْ يَرْجِعْ مِنْ ذَلِكَ بِشَيْءٍ
''በውስጣቸው መልካም ስራ ከሚፈፀምባቸው ቀናት ውስጥ ከነዚህ አስር ቀናት በላይ አላህ ዘንድ የተወደደ የለም።" "በአላህ መንገድ መታገልም ቢሆን?" ብለው ሲጠይቋቸው የአላህ መልእክተኛ ﷺ "በአላህ መንገድ መታገልም ቢሆን! በነፍሱም፣ በገንዘቡም ወጥቶ ከዚህ ውስጥ ምንም ያልተመለሰ ሰው ሲቀር" ብለው መለሱ። [አልቡኻሪይ፡ 969]
በዚህ መሰረት በነዚህ የተከበሩ ቀናት የተለያዩ ዒባዳዎችን መፈፀም በጣም ትልቅ ዋጋ ያለው ነው። ፆም ወደ አላህ መቃረቢያ ከሆኑ ዒባዳዎች ውስጥ አንዱ መሆኑ ግልፅ ነው። ከመሆኑም ጋር በያመቱ "የዙል ሒጃን አስር ቀናት መፆም ይቻላል ወይ?" የሚል ጥያቄ ሲነሳ ያጋጥማል። የግርታው መነሻ እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ "በነዚህ አስር ቀናት ውስጥ የአላህ መልእክተኛን ﷺ ፈፅሞ ፆመው አላየሁም" ማለቷ ነው። [ሙስሊም፡ 1179]
ይሄ ግን ግርታ ሊፈጥር የሚገባው አይደለም። እንደሚታወቀው የነብዩ ﷺ ሱና በሶስት መንገድ ይተላለፋል።
1- በቃላቸው
2- በተግባራቸው እና
3- ሌሎች ሲፈፅሙ አይተው የሚሰጡት ይሁንታ (ኢቅራር)።
የዙል ሒጃን ስምንት ቀናት መፆም ከነዚህ ውስጥ በቃላቸው የተላለፈው ሐዲሥ ውስጥ ይካተታል። ሐዲሡ አስተማማኝ፣ መልእክቱም ፆምን አካታች ነው። ከዚህ በኋላ የዓኢሻ ነብዩን ﷺ ሲፆሙ አለማየት የሳቸውን ጥቅል የቃል መልእክት ለመገደብ መነሻ መሆን የለበትም። ለዓኢሻ አለማየት የተለያዩ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ደግሞ የሚገድብ መረጃ እስከሌለ ድረስ በጥቅል ቃላዊ መረጃ የተገኘው በቂ ነው።
ስለዚህ ሌሎች መረጃዎች ደካማዎች (ዶዒፎች) ቢሆኑ እንኳ መግቢያ ላይ የተጠቀሰው ሐዲሥ በቂ ማስረጃ ነው።
ይሄ እንግዲህ ስምንቱን ቀናት በተመለከተ ነው።
* ዘጠነኛው ቀን የሁለት አመት ወንጀል እንደሚያሳብስ አስተማማኝ መረጃ መጥቶበታል። [ሙስሊም፡ 1162] ስለዚህ ብዥታ የሚነሳበት አይደለም።
* አስረኛው ቀን በአል ስለሆነ አይፆምም።
ወሏሁ አዕለም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
💰فضل عشر ذي الحجة وما يشرع فيها💰
🎙الشيخ صالح الفوزان حفظه الله
🎙الشيخ ابن عثيمين رحمه الله
🎙الشيخ ابن باز رحمه الله
🎙الشيخ صالح اللحيدان رحمه الله
🎙الشيخ محمد الجامي رحمه الله
🎙الشيخ ربيع المدخلي رحمه الله
🎙الشيخ عبيد الجابري رحمه الله
https://t.me/abu_haider_aliye
https://t.me/abu_haider_aliye
Repost from ስለ ቀልባችን
▣ በነዚህ በዙል ሂጃህ አስር ቀናት የሚሰሩ 128 ቀላልና ተወዳጅ መልካም ስራዎች!
t.me/Sle_qelbachn1
t.me/Sle_qelbachn1
እስኪ ይችን ጣፋች ነሲሓ ተጋበዙልኝ ስለነዚህ ዉድ ቀናቶች በገጥም መልኩ የቀረበች ምክር እስከ-አረፋ ጋብዣችኋለዉ አድምጧት ደስ ትላለች "
https://t.me/abu_haider_aliye
https://t.me/abu_haider_aliye
🛑 (ቁርኣንን በየቀኑ በሩብ በመከፋፈል በ8 ቀናት ውስጥ ማክተም)
በየቀኑ 30 ሩብ (Rub') — ይህ ማለት ሙሉው የሱረቱል በቀራህ እና የሱረቱ ኣሊ-ዒምራን ርዝማኔ ያህል ነው።
ይህ ክፍፍል (ተሕዚብ) ቁርኣንን በ 8 ቀናት ውስጥ ለማክተም የተዘጋጀ ሲሆን፥ በየቀኑ 30 ሙሉ ሩብ (Rub') ይነበባል። ይህም ከ 3 ጁዝእ ከ 6 ሩብ ጋር እኩል ነው — [ይኸውም ሙሉው የሱረቱል በቀራህ እና የሱረቱ ኣሊ-ዒምራን ርዝማኔ ያህል] ለየቀኑ።
እነዚህ የቀን መደበኛ ንባቦች (አውራዶች) በርዝማኔ ረገድ እርስ በርሳቸው የተቀራረቡ ናቸው፤ ይህ የተደረገው የንባብ መጠኑ (ብዛቱ) እና የሚወስደው ጊዜ በየቀኑ እኩል ወይም የተቀራረበ እንዲሆን ለሚፈልጉ ሰዎች ነው።
📊 📊 የንባብ መርሃ-ግብር ሰንጠረዥ (الجدول)
የቀኑ መደበኛ ንባብ (الورد) ከጅምሩ (من بداية) እስከ ፍጻሜው (إلى نهاية)
የመጀመሪያው ቀን ሩብ ቁጥር (1) | አል-ፋቲሓ፡ 1 ሩብ ቁጥር (30) | ኣሊ-ዒምራን፡ 200
ሁለተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (31) | አን-ኒሳእ፡ 1 ሩብ ቁጥር (60) | አል-አንዓም፡ 165
ሦስተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (61) | አል-አዕራፍ፡ 1 ሩብ ቁጥር (90) | ሁድ፡ 40
አራተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (91) | ሁድ፡ 41 ሩብ ቁጥር (120) | አል-ካህፍ፡ 74
አምስተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (121) | አል-ካህፍ፡ 75 ሩብ ቁጥር (150) | አሽ-ሹዐራእ፡ 227
ስድስተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (151) | አን-ነምል፡ 1 ሩብ ቁጥር (180) | አስ-ሷፋት፡ 144
ሰባተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (181) | አስ-ሷፋት፡ 145 ሩብ ቁጥር (210) | አን-ነጅም፡ 25
ስምንተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (211) | አን-ነጅም፡ 26 ሩብ ቁጥር (240) | አን-ናስ፡ 6ስምንተኛው ቀን ሩብ ቁጥር (211) አን-ነጅ26 /
🛑 غدا الإثنين أول أيام شهر ذي الحجة 🇸🇦
🛑 يوم الثلاثاء بعد القادم يوم عرفة 🇸🇦
🛑 يوم الأربعاء بعد القادم عيد الأضحى 🇸🇦
https://t.me/abu_haider_aliye
ነገ ኢንሻአላህ
🦋🦋 2 🦋🦋አጅር የሚያስገኙ የሱና ፆሞች የሚፆሙበት ቀን ነው
1ኛው የሰኞ ሱና ፆም ሲሆን
2ኛው ደግሞ 10ቱ የዙልሂጃ ፆም ቀናት መጀመሪያ ነው
ስለዚህ ለሁለቱም ኒያ እናድርግ
የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ
አሏህ ፆማችንን ይቀበለን
https://t.me/yemesjidetewhidgebimasebasebiya
እውቀትዎን ይፈትሹ! 🕌
"እውቀት ብርሃን ነው!" ዲንዎን እየተዝናኑ የሚማሩበትና እውቀትዎን የሚለኩበት ብቸኛ ቦታ!
❓ አስተማሪ ጥያቄዎች
✅ አስተማማኝ መልሶች
🏆 አሳታፊ ውድድሮች
አሁኑኑ ይቀላቀሉን፤ እውቀትዎን ያሳድጉ! 👇
Repost from N/a
📝 ማስታወሻ!
➖➖➖➖
በዛሬው ዕለት ሳዑዲ ዓረቢያ የዙል-ሒጃህ ወር ጨረቃ መታየት የምትከታተል በመሆኑ፣ የሚከተሉት ቀናቶች ይወሰናሉ፦
• የዙል-ሒጃህ ወር መጀመሪያ
• የዓረፋ ቀን መቼ እንደሚሆን
• የዒድ አል-አድሓ (የአረፋ በዓል) ዕለት
🔴 ዛሬ ትኩስና ወቅታዊ የሆኑ የዙል-ሒጃህ ወር መረጃዎችን ይዘንላችሁ እንቀርባለን። እስከዚያው ተከታተሉን!
=
ቻናሉን ለመቀላቀል፦
https://t.me/FuadKemal
https://t.me/FuadKemal
የግጥሙ ርዕስ ሁሉም ባዶ፣ሁሉም መና ፣ሁሉም ዜሮ
✅ሁሉም ባዶ✅
🌿ምን ቢለፋ ኸይርን ወዶ፣
🌿ቀኑን ቢፆም ለይሉንን ሰግዶ፣
🌿ሁሉን ቀድሞ ቢጓዝ ማልዶ፣
🌿ሀጅ ቢያደርግ መካ ሄዶ፣
🌿ያለ ተውሂድ ሁሉም ባዶ፣
✅ሁሉም መና✅
🌿ሌት ቀን ለፍቶ ምን ቢፀና፣
🌿ቢኖረውም ቅን ልቦና ፣
🌿ንያው አድጎ ምን ቢቀና ፣
🌿ቢደጋገም በምርቃና ፣
🌿ቢያሳምርው እንደገና፣
🌿ያለ ሱና ሁሉም መና፣
🌿ያለ ሱና ሁሉም መና፣
✅ሁሉም ዜሮ✅
🌿ሀብታም ቢሆን ዱንያው አምሮ፣
🌿ዶክተር ቢሆን ምድርን ዞሮ፣
🌿ቆንጆ ሴትጋ ቢኖር አብሮ ፣
🌿ልጆች ቢወልድ ትዳር ሰምሮ፣
🌿ንጉስ ቢሆን ምድርን ዞሮ፣
🌿ያለ ኢስላም ሁሉም ዜሮ፣
🌿ያለ ኢስላም ሁሉም ዜሮ፣
✍️ ابو شريح عمر بن إسماعيل
> " (ኡድሂያ) ማቅረብ የፈለገ ሰው የዙልሒጃ ወር ጨረቃ ከታየች ጀምሮ መሥዋዕቱን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩ፣ ከጥፍሩም ሆነ ከቆዳው ምንም ነገር ላለመውሰድ (ላይቆርጥ) ይደነገግለታል። ይህ የሆነው ቡኻሪን ሳይጨምር ሌሎች የሐዲስ ሊቃውንት (ጀማዓህ) ከአሥማእ ቢንት አቢ በክር — አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና — ባስተላለፉት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ስላሉ ነው፦ «የዙልሒጃን ጨረቃ ካያችሁና ከእናንተ መካከል አንዱ መሥዋዕት ማረድ ከፈለገ ከፀጉሩና ከጥፍሩ (መቁረጥ) ይቆጠብ።»
> በአቡ ዳውድ፣ በሙስሊምና በነሳኢይ ዘገባ ደግሞ ቃሉ እንዲህ ይላል፦ «የሚያርደው መሥዋዕት ያለው ሰው የዙልሒጃ ጨረቃ ከታየች መሥዋዕቱን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩም ሆነ ከጥፍሩ ምንም ነገር አያስወግድ።»
> ይህም (ከመቁረጥ የመቆጠብ ግዴታ) መሥዋዕቱን ራሱ በገዛ እጁ አረደውም ወይም ሌላ ሰውን እንዲያርድለት ቢወክልም ለሁለቱም እኩል ይሠራል፤ ነገር ግን መሥዋዕት የሚታረድለት (በቤተሰብ ውስጥ አባወራው ሲያርድለት አብሮ የሚካተተው) ሰው ይህንን ማድረግ አይደነገግለትም፤ ምክንያቱም በዚህ ዙሪያ የመጣ ምንም ማስረጃ የለምና። ይህ (ከፀጉርና ጥፍር መቆጠብ) ‘ኢሕራም’ (ለሐጅ ወይም ለዑምራ የሚደረግ ዕገዳ) ተብሎ አይጠራም። ‘ሙሕሪም’ (ኢሕራም ላይ ያለ ሰው) የሚባለውማ ለሐጅ፣ ለዑምራ ወይም ለሁለቱም ኢሕራም ያደረገው ሰው ብቻ ነው።"
> — *“ፈታዋ አል-ለጅናህ አድ-ዳኢማህ”* (ቅጽ 11፣ ገጽ 397-398) የተወሰደ።
>
إطعام الطعام شأنه عظيم لا تغفلوا عنه !
الشيخ علي بن غازي التويجري حفظه الله
"ምግብ ማብላት (ሰዎችን መመገብ) ነገሩ/ደረጃው ታላቅ ነው፤ ከእሱ እንዳትዘናጉ!"
— ሼኽ ዓሊ ቢን ጋዚ አል-ቱወይጅሪ (አላህ ይጠብቃቸው)
https://t.me/abu_haider_aliye
