ፍሬ ሃይማኖት
Ir al canal en Telegram
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የአ/አ ሐገረ ሥብከት የመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረቦች ግጥማቸው ከነዜማ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያየት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot
Mostrar más1 825
Suscriptores
+124 horas
Sin datos7 días
+1130 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+18
en 0 canales
junio '26
+45
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+98
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+39
en 1 canales
Get PRO
marzo '26
+16
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+20
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+42
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+20
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+20
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+20
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+23
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+28
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+18
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+27
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+20
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+36
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+24
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+33
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+78
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+53
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+53
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+51
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+43
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+23
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+39
en 1 canales
Get PRO
junio '24
+38
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+22
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+27
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+30
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+28
en 1 canales
Get PRO
enero '24
+28
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+27
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+19
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+26
en 1 canales
Get PRO
septiembre '23
+23
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+21
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+24
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+32
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+23
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+37
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+16
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+23
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+27
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+33
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+48
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+33
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+31
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+24
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+18
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+23
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+19
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+23
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+26
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+29
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+41
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+73
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+83
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+99
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+56
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+35
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+50
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+38
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+58
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+41
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+65
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+96
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+2 101
en 0 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 14 julio | 0 | |||
| 13 julio | +2 | |||
| 12 julio | +1 | |||
| 11 julio | 0 | |||
| 10 julio | +1 | |||
| 09 julio | +3 | |||
| 08 julio | +3 | |||
| 07 julio | +1 | |||
| 06 julio | +2 | |||
| 05 julio | 0 | |||
| 04 julio | +1 | |||
| 03 julio | +3 | |||
| 02 julio | 0 | |||
| 01 julio | +1 |
Publicaciones del Canal
.
✝️ ታሪክ በዛሬዋ ዕለት ✝️
😭የቅዱስ ፓትርያርኩ በግፍ መገደል😭
በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ)
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ሰማዕት ሁለተኛው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ያን ፓትርያርክ ሲሆኑ በራሳችን ምድር(በኢትዮጵያ) በራሳችን አባቶች የተሾሙ የመጀመርያው ፓትርያርክ ናቸው። የተሾሙትም ግንቦት 1 ቀን 1963 ዓ.ም ሲሆን ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ እጅግ በርካታ ሥራዎችን እና አዳዲስ መዋቅሮችን ዘርግተው በመስራት ላይ ሳሉ ገና የወጠኗቸውን የቤተ ክርስቲያን ልማቶች ሳይፈጽሙ የካቲት 9 ቀን 1968ዓ.ም ከመንበረ ፕትርክናቸው ወርደው ለእስር ተዳረጉ።
ቅዱስ ፓትርያርኩ ከመንበራቸው የወረዱትም ሆነ ተላልፈው በመሰጠት የታሠሩት በወታደራዊው መንግስት ድፍረትን የተሞላ ተግባር ብቻ ሳይሆን መጽሐፍ "ለሰብዕ ጸሩ ሰብአ ቤቱ = ለሠው ጠላቱ ቤተ ሰቡ ነው" እንዲል።ቤተ ክሕነት ውስጥ በተሰገሰጉ የይሁዳ የግብር ልጆች አማካይነት ነው።
ኋላም እነዚሁ መሠሪዎች ቅዱስ ፓትርያርኩ በፋሽስት ደርግ ከመንበራቸው እንዲለቁ ከደረጉ በኋላ "መንግስት የወሰደውን እርምጃ ደግፈን ተስማምተናል ቀብለናልም" ሲሉ መግለጫ መስጠታቸው እጅግ በጣም አሳዛኝ ነበር።
እንዴት ተገደሉ???
ከየካቲት 9 ቀን 1968ዓ.ም እስከ ሐምሌ 7 ቀን 1971ዓ.ም(ለሶስት ዓመት ከአምስት ወራት) በእስር ቤት ተጣሉ።ቀኖና ቤተ ክርስቲያንም ተሽሮ እርሳቸው በሕይወት እያሉ ሌላ(ሶስተኛው ፓትርያርክ) በደርግ ትዕዛዝ ተሾሙ።በዚህ ረዥም ጊዜ ፓትርያርኳ ተዋርዶ ስቃይና መከራን ሲቀበል፤ ቤተ ክርስቲያን ለምን ይህ ይደረጋል? ብላ አለመጠየቋ፤የጎረምሶች ጥርቅም የነበረውን አዲሡን የደርግ መንግስት አባቶች መገሠጽ አለመቻላቸው...... አይደለም በጊዜው ለነበረና ድርጊቱን በቅርበት ለተመለከተ ሠው ቀርቶ ዛሬ ላይ ሆነን በታሪክ ለምንሰማ ሰዎች ልባችንን በኃዘን ፍላጻ እየወጋ ሲያደማው የሚኖር የእኩያን ሰይጣናዊ ሥራ ነው።
አሰቃቂው የግድያ ድርጊት፦
ሐምሌ 7 ቀን 1971 ዓ.ም በዚህኛው በኩል(በቤተ ክርስቲያን) የቅድስት ሥላሴ በዓል በመከበር ላይ ሲሆን
በዚያኛው በኩል ደግሞ(በእስር ቤት) ፓትርያርኩን ጨምሮ ሠላሳ ሶስት እስረኞች በሞት መልዕክተኞች ተጠሩ፣ተሰለፉ፣በተራቸው ገቡ።ወደ ጨለማው ቤት ውስጥም ተጨመሩ።
የተለያዩ የጨለማ ኮሪደሮች ባሉት የጨለማ ቤት ውስጥ ጥግ ላይ ያለው ሰው ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን "ና" አላቸው።ወደርሱ አተኩረው ሲራመዱ በጨለማው ኮሪደር ለግድያ ካሸመቁ ሰልጣኝ ኮማንዶዎች አንዱ ሳያስቡት በሲባጎ አነቃቸው።ኮማንዶው ሲባጎውን በሁለት እጆቹ ጠምጥሞ አጥብቆ በመያዝ በአንገታቸው ላይ ከአጠለቀ በኋላ ገመዱን በመሸረብና በማሳጠር በስተመጨረሻ በገመዱ እንደታነቁ የእንግላሊት ጀርባው ላይ አውጥቶ በአንገታቸው የገባውን ገመድ በእጁ እየጠቀለለ በማሳጠርና በማጥበቅ ትንፋሻቸውን ቋጨ።
አስከሬናቸውንም ጎትቶ ከሌሎች እስረኞች ጋር ሸራ አለበሰው።ማታ ሶስት ሰዓት ኖራ ተነስንሶባቸው ከሠላሳ ሶስቱ እስረኞች ጋር በጅምላ በአንድ ጉድጓድ ተቀበሩ።😭😭😭
አይ ኢትዮጵያ ‼️ የስንት ንጹሐን ደም ደመ ከልብ ሆኖብሽ ቀረ❓❓❓
ቅዱስነታቸውን ለዚህ ሁሉ ግፍና መከራ የዳረጋቸው "መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው ብላችኋል።እናንተም ሥራችሁን ሥሩ።እኔም ሥራዬን አሠራለው"።ብለው ቤተ ክርስቲያንን አለማስደፈራቸው ብቻ ነበር።እንጂ ሌላማ ምን ወንጀል ተገኝቶባቸው።
የሰማዕቱ ፓትርያርክ ረድኤትና በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።
ተጻፈ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ 5:00 ሰዓት
| 2 | "ኹለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይኽ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለኹ፡፡"
ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
ሐምሌ ፭ ፳፻፲፰ ዓ.ም. ጋብቻችኹን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችኹት
የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ፍሬ ሀይማኖት ሰንበት ት/ቤት ወንድማችን ልመንህ ገለጠ እና እህታችን ሜላት ንጉሴ የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችኹን ይባርክላችኹ፥ ያጣምራችኹ፥ ያዋሕዳችኹ 🙏
ስታገለግሉት የኖራችኹት ቅዱስ ሚካኤል በሕይወታችኹ ሞገስ ይኾናችኹ ዘንድ በፍቅርና በጤና ይባርካችኹ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው! | 341 |
| 3 | ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያውን ጉዞ ያደረገው ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ነው።
በዚህ ጉዞአቸው በጠቅላላ ወደ ፪፼ (ሁለት ሺህ) ኪሎ ሜትር የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል። ይህም ጉዞ የተከናወነው በ፵፮ ዓ.ም. አካባቢ ነው።
ሁለተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶ ዓ.ም. ገደማ ነው። በመጀመሪያው ጉዞ ማርቆስ አብሮ ተጉዞ ነበር። ነገር ግን ጵንፍልያ ከተማ ሲደርስ እናቱ ስለናፈቀችው መመለስ በመፈለጉ በርናባስ ወደ ኢየሩሳሌም ይዞት መጣ።
ስለዚህም በሁለተኛው ጉዞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲላስን ይዞ ወደ ኪልቂያ ሶርያ ሲጓዝ በርናባስ ደግሞ ማርቆስን አስከትሎ ወደ ቆጵሮስ ሄደ።
በዚህ ጉዞው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ግሪክ ደርሶአል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስን ያገኘው በዚሁ ጉዞው በልስጥራ ከተማ ነው።
ሦስተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶፬ ዓ.ም. ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከልዩ ልዩ ሀገሮች ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ዕርዳታ ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን በመያዝ ሦስተኛውን ጉዞ አጠናቅቆ ኢየሩሳሌም ገባ።
ነገር ግን ኢየሩሳሌም የገባበት ጊዜ የፋሲካ በዓል ስለነበር ከልዩ ልዩ ሀገሮች የተሰበሰቡ አይሁድ በከተማዋ ነበሩ።
እነዚህ በዝርወት የሚኖሩ አይሁድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን በየሀገራቸው በትምህርቱ የተነሣ ሲቃወሙት የነበሩ ናቸው።
እኒህ አይሁድ ቅዱስ ጳውሎስን በኢየሩሳሌም ሲያዩት ታላቅ ተቃውሞ አነሡበት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞ አነሡበት። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞአቸውን ለመግታት እንደ አይሁድ ሕግ በቤተ መቅደስ የመንጻት ሥርዓት መፈጸም ጀመረ።
ነገር ግን ከኤፌሶን የተከተለውን ጥሮፊሞስን ወደ መቅደስ ያስገባው ስለመሰላቸው ተቃውሞአቸው በረታ።
ከተማውንም አወኩት፤ ይህ ቅዱስ ጳውሎስን በ፶፰ ዓ.ም. ለሮም እሥር ዳረገው። ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ታስሮ ሮም ገባ።
በዚያም በቁም እሥር ለሁለት ዓመታት ያህል ወንጌልን ሰበከ። የሁለቱን ዓመት የቁም እሥር እንደጨረሰ ወደ ኔሮን ፍርድ ቤት ቀረበ።
ይህም በ፷ዎቹ ዓ.ም ነው። በፍርድ ቤቱ በተደረገው ምርመራ የሮሜን ሕግ የሚቃወም ምንም ወንጀል ስላልተገኘበት በነፃ ተለቀቀ፤
ከዚህ በኋላ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አራተኛውንና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ያልመዘገበውን ጉዞውን ያደረገው።
ይህ ጉዞው በመታሠሩ አዝነው ተክዘው የነበሩ ክርስቲያኖችን ለማጽናናት የጀመራቸውን ሥራዎች ፍጻሜ ለማየት የተደረገ ጉዞ ነው።
በመጨረሻ በ፷፬ ዓ.ም. ኔሮን በጥጋቡ የሮማ ከተማ ስትቃጠል ምን እንደምትመስል ማየት እፈልጋለሁ ብሎ አቃጠላት።
የሮም ሕዝብ በከተማው መቃጠል በማዘኑና በማመፁ ነገሩን ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ አሳበበ።
በዚህም የተነሣ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ መሰደድ፣ መሠየፍ፣ መታረድ እጣ ፈንታው ሆነ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኒቆጵልዮን ከተማ ሲያስተምር በ፷፭ ዓ.ም. ተይዞ ወደ ወኅኒ ገባ።
ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ፸፬ ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱን ተሰይፎ በ፷፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፭ ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ሁለት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ዐስራ አራት መልእክታትን ጽፈዋል።
የቅዱሳኑ ሐዋርያት ረድኤትና በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
ምንጭ፦
✔መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ ፭፤
✔መጽሐፍ ቅዱስ-ሐዲስ ኪዳን፣
✔ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ ቁጥር ፩፤ በማኅበረ ቅዱሳን | 298 |
| 4 | የሮም ሕዝብ በደረሰው አደጋ እጅጉን ተቆጣ። ኔሮንም በክርስቲያኖች አመካኘ። በዚህም የተነሣ በሮማ ከተማ ሁለት ዓይነት ወሬ መናፈስ ጀመረ።
የሮማ አማልክት በክርስቲያኖች ሃይማኖት ስለተቆጡ በከተማዋ እሳት አዘነቡባት የሚለው የመጀመሪያው ሲሆን ክርስቲያኖች ሆን ብለው ከተማዋን አቃጥለዋታል የሚለው ደግሞ ሁለተኛው ወሬ ነበር።
የከተማው መጋየት ያበሳጨው የሮማ ሕዝብ፣ ክርስቲያን የሆነውን ሁሉ እያወጣ መግደሉን ተያያዘው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሰዓት በእሥር ነበርና ተሠይፎ ዐረፈ። ይህን የሰሙት የአግቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች (የሮም ባለሟሎች ነበሩ) «ባይሆን አንተ ትረፍልን» ብለው በከተማዋ ግንብ በገመድ አሥረው በቅርጫት በማውረድ ቅፅረ ሮማን ለቅቆ እንዲወጣ አደረጉት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በኦፒየም ጎዳና ጉዞውን ቀጠለ። ሮማን ለቀቀ። እያዘገመ በሸመገለ ጉልበቱ ሲጓዝ አንድ ቀይ ጐልማሳ ወደ እርሱ ሲመጣ አየ።
እየቀረበ ሲመጣ ጌታችን መሆኑን ተረዳ። ወዲያው በፊቱ ተደፋና «ጌታዬ ወዴት እየተጓዝክ ነው?» አለና ጠየቀው። «ዳግም በሮም ልሰቀል» አለው።
በዚህ ሰዓት ቅዱስ ጴጥሮስ አዘነና እንደገና ወደ ሮማ ተመለሰ። የኔሮን ወታደሮች እየፈለጉት ነበር። «እነሆኝ ስቀሉኝ» አለ ቅዱስ ጴጥሮስ።
ያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ይዘው አሠሩት። ከጥቂት ቀናት በኋላም ሮማውያን የመስቀያውን እንጨት አቀረቡለት።
ያን ጊዜ «እኔ እንደ ጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም» በማለት ቁልቁል እንዲሰቅሉት ለመነ። ያለውንም አደረጉለት። ሐምሌ ፭ ቀን ፷፯ ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ።
፪. ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘሩ ከዕብራዊያን፣ ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው።
ጠርሴስ በንግድዋ የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት። በከተማዋ እስከ አምስት መቶ ሺህ የሚገመቱ ከየሀገሩ የተሰባሰቡ ሕዝቦች ነበሩባት።
ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነትን ይሰጡ ስለነበር፥ የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር። ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል።
ቅዱስ ጳውሎስ በ፲፭ ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሀገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀው የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ።
በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዓት እየተማረ እስከ ፴ ዓመቱ ቆየ። ገማልያል ፈሪሳዊ ስለነበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ተቀብሎታል። በ፴ ዓመቱ የአይሁድ ሸንጎ አካል ሆኖ ተቆጠረ።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ ሁኔታዎቹን ሁሉ ያውቃል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለሁለት ዓመታት በሠራበት ወቅት ለኦሪታዊ እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር።
እንዲያውም ሊቀዲያቆናት እስጢፋኖስን በማስተማሩ ምክንያት ተከሶ ለአይሁድ ሸንጎ በቀረበ ጊዜ የተከራከረው እርሱ ነበር።
በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው።
በ፴፪ ዓመት እድሜው ከኢየሩሳሌም ፪፻፳፫ (ሁለት መቶ ሃያ ሦስት) ኪ.ሜ. ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ አገኘ።
ከዚህም በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ።
ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና «ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ?» የሚለውን ድምፅ የሰማው።
ሐዋርያው ጳውሎስም «ጌታ ሆይ ማን ነህ?» ብሎ ጠየቀ። «አንተ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ። የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል» ሲል መድኃኒታችን ተናገረው።
ያን ጊዜም በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ «ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ?» ሲል ጠየቀ።
ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው። (የሐዋ. ፱፥፩)
የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም። እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ።
ለሦስት ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ።
በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራእይ ተገለጠለት።
ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና ሄዶ እንዲያጠምቀው አዘዘው። ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል።
አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል።
አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት የመጡ ናቸው።
ያን ስደት ያስነሣው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው።
በዚህ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ጳውሎስ ነበር።
ይህን የሚያውቀው ሐናንያ በቅድሚያ ከእግዚአብሔር ጋር መከራከር ጀምሮ ነበር። እግዚአብሔር አያውቀው ይመስል ስለ ቅዱስ ጳውሎስ ማስረዳት ጀመረ።
በመጨረሻ ግን «ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእሥራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና» በማለት እግዚአብሔር ሐናንያን ላከው።
ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረው በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሀገር መሄዱን ራሱ ተናግሮአል። (ገላ ፩፥፲፯)
ለ፫ ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየ በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ።
በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ።
ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰበክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት።
በዚህም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት።
ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ የገጠመው ሁለት ችግር ነበር። በቅድሚያ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሡ።
በሌላ በኲል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም።
በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኲል ወደ ትውልድ ሀገሩ ጠርሴስ ተመለሰ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለዘጠኝ ዓመታት ቆይቷል።
ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ።
ከኢየሩሳሌም የተሰደዱት ክርስቲያኖች የአንጾኪያን ሕዝብ ተግተው በማስተማራቸው ዝናው እስከ ኢየሩሳሌም ደረሰ።
በዚህም ምክንያት በኢየሩሳሌም የነበሩት አበው በርናባስን ወደ አንጾኪያ ላኩት።
በርናባስ የግሪክ ቋንቋ ችሎታ ያለውን፣ ከማንኛውም ሰው ጋር መግባብ የሚችለውን፣ ደግሞም እግዚአብሔር ለአሕዛብ ሐዋርያ እንዲሆን የመረጠውን ቅዱስ ጳውሎስን ከጠርሴስ በማምጣት በአንጾኪያ ሥራቸውን ጀመሩ።
በገላትያ መልእክቱ ምዕራፍ ፪ ላይ ራሱ እንደገለጠው ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ርዳታ ይዞ ወጣ።
በዚህም በአይሁድና በአሕዛብ መካከል የነበረውን መለያየት ክርስትና አንድ እንዳደረገው አስመሰክሯል። | 238 |
| 5 | ፩. ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተሳይዳ ነው።
የአባቱ ስም ዮና ይባላል። ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ሲሆን በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሳ ማሥገር ጀመረ።
ለደቀመዛሙርነት ሲመረጥ ዕድሜው ፶፭ ዓመት እንደነበረ ይነገራ፤ ወደ ጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው።
ቅዱስ ጴጥሮስ በርናባስና ወንጌላዊው ማርቆስ ቤተ ዘመድ ናቸው። የማርቆስ አባት አርስጦቡሎስና በርናባስ በእናት የሚገናኙ ወንድማማች ናቸው።
ቅዱስ ጴጥሮስ ያገባው የበርናባስና የአርስጦቡሎስን እኅት ስለነበር በጋብቻ ይዛመዳሉ።
ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡንና ታንኳውን እንዲሁም አባቱን እርግፍ አድርጐ ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው።
የቅዱስ ጴጥሮስ በመጀመሪያ ስሙን ስምዖን ብላ እናቱ የጠራችው በነገዷ ስም እንደሆነ ይነገራል።
በቂሳርያ ከተማ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ማን ትሉኛላችሁ?» ብሎ በጠየቀ ጊዜ «አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ» ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረውን ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን «አንተ ጴጥሮስ ነህ» ብሎታል ይህም በላቲን ቋንቋ ዐለት ማለት ነው፤ በአርማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል።
ቅዱስ ጴጥሮስ ከአዕማድ ወይንም የምሥጢር ሐዋርያት ከእነ ዮሐንስ እና ያዕቆብ ጋር የሚቆጠር ነው።
ከሐዋርያት ሁሉ ቀደም ቀደም የማለት ባሕርይ ነበረው። ጌታ በጥብርያዶስ ባሕር ላይ ሌሊት በእግሩ ሲመጣ ቢመለከት ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ በማለት ካስፈቀደ በኋላ ወደ ጌታ ለመምጣት መንገድ ጀምሮ በመሐል ቤት ጥርጣሬ ገባውና መስጠም ስለጀመረ ጌታችን «ያመንክ እንጂ ያላመንክ አትሁን» ብሎ ገስፆ ከመስጠም አድኖታል። (ማቴ ፲፬፥፳፪-፴፫)
በቅፍርናሆም ጉባኤ ጌታን ምሥጢረ ቁርባንን ሲያስተምር፣ አይሁድ ስላልገባቸው ወደ ኋላ አፈገፈጉ። ከደቀ መዛሙርቱም «ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ» በዚህን ጊዜ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁ?» ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው።
በዚህ ሰዓት «ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም የሕይወት ቃል አለህ። እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንክ እናምናለን» በማለት ሐዋርያትን ወክሎ የመለሰ እርሱ ነው። (ዮሐ ፮፥፷፮-፷፰)
ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር። ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለበት በመሆኑ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል። (ማቴ ፲፮፥፳፫)
በኋላም «ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም» ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር። ጌታችን «ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ» እያለው እንኳን «ከአንተ ጋር መሞት እንኳን የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም» በማለት የተናገረ ሰው ነው። (ማቴ ፳፮፥፴፬)
ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ የተናገረውን ቃል ለመጠበቅ ሞክሮ ነበር። ጌታ ዛሬ «የሰው ልጅ አሳልፎ ይሰጣል» ብሎ አስተምሮአቸው ነበርና መከላከያ ይሆነኛል ብሎ ሠይፍ ደብቆ ይዞ ነበር።
የሮም ጭፎሮችም ጌታን ለመያዝ ሲጠጉ የሊቀ ካህናቱን ባርያ (ማልኰስን) በሠይፍ ጆሮውን ቆረጠው። ጌታችን ግን ሞቱ በፍቃዱ ለድኅነተ ዓለም ነውና «ሠይፍህን ወደ ሰገባው» መልስ ሲል ገሠፀው።
ቅዱስ ጴጥሮስ የሚታወቅበት ሌላው ትልቁ ነገር ንስሐው ነው። ጌታው የነገረው መድረሱን፣ ቃል የገባለትን አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታ በተለያቸው ጊዜ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሳ ወደ ማሥገሩ ተሠማራ።
ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢክደው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን፤ ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለትም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት። (ዮሐ ፲፰፥፲)
ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው። አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው ዐውቆአልና «ትወደኛለህን?» ተብሎ ሲጠየቅ «አንተ ታውቃለህ» ነበረ መልሱ።
የራሱ ዕውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኅዳጌ በቀል (በቀልን የሚተው) ነውና ዛሬም እንደሚወደው፣ በንስሐ ተመልሶአልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐድልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጐቼን አሠማራ» በማለት አደራውን አስረከበው። ከዚያም በሞቱ እንደምን አድርጐ እግዚአብሔርን አንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማያት ዐረገ። (ዮሐ ፳፩፥፲፭-፲፯)
ቅዱስ ጴጥሮስ በአራቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ በተቀመጡት የሐዋርያት ዝርዝር ቀዳሚውን ሥፍራ ይዞ ይገኛል።
ይህም፦
፩. በሽምግልና አባትነቱ፣
፪. ጌታ በቂሳርያ በሰጠው ቃል ኪዳን፣
፫. የሐዋርያት አፈ ጉባዔ ሆኖ ይናገር ስለነበር፣
፬. በጥብርያዶስ ባሕር በተሰጠው ቃል መሠረት ነው።
በዚህም የተነሣ በይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ እንዲመረጥ ሐሳብ ያቀረበ እርሱ ነበር።
በበዓለ ሃምሳም ለደቀመዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ለተሰበሰቡት አይሁድ አፈ ጉባዔ ሆኖ ወንጌልን የሰበከ ፫፼ (ሦስት ሺህ) ምእመናንንም አሳምኖ የመጀመሪያዋን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም የመሠረተ እርሱ ነው። (የሐዋ. ፩፥፲፮-፳፫፣ ፪፥፲፬-፴)
አስቀድሞ ፈሪ የነበረውና በሊቀ ካህናት ቀያፋ ግቢ ጌታውን የካደው ቅዱስ ጴጥሮስ፣ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ካገኘ በኋላ ግን በአይሁድ ሸንጐ ድውይ ፈወስክ ተብሎ በተከሰሰ ጊዜ በድፍረት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መሰከረ።
ቆርነሌዎስን በማጥመቅ ወንጌልን ለአሕዛብ አስቀድሞ የሰበከው ሐዋርያ ነው። ይህ ሐዋርያ ልዑል እግዚአብሔር ባደለው ጸጋ ጥላው እንኳን ድውያንን ይፈውስ ነበር። የሐዋ ፭፥፲፭።
በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፲፭ ላይ በ፶ ዓ.ም. አካባቢ በኢየሩሳሌም በተደረገው የሐዋርያት ሲኖዶስ ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች ለቀረበው ጥያቄ የመጀመሪያውን መልስ የሰጠው እርሱ ነበር።
ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ መልክና ቁመና ጥንታዊያን መዛግብት እንደሚከተለው ያቀርቡታል። «ፊቱ ሰፋ ያለ ሲሆን ሪዛምና መካከለኛ ቁመት የነበረው ራሰ በራ ሰው ነው። በማናቸውም ነገር ፈጣንና ቀልጣፋ ነበር።»
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ መሠረት ቅዱስ ጴጥሮስ በፍልስጥኤም፣ በሶርያ፣ በጳንጦን፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በቢታንያ እና በሮሜ ሰብኳል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ አንድ ዓመት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ካስተማረ በኋላ የሮሜ ክርስቲያኖች እየበዙ ከመምጣታቸውም በላይ የክርስትናው ጉዞ እስከ ሮማ ባለሥልጣናት ደረሰ።
የኔሮን የቅርብ ባለሥልጣናት የሆኑት የአልቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች ወደ ክርስትናው ገቡ። በዚህን ጊዜ ኔሮን ንጉሠ ሮማ በቅንዓት ተነሣባቸው።
ኔሮን በሮም የነገሠው በ፶፬ ዓ.ም. ነው። በመንግሥቱ መጀመሪያ ደግ ሰው ነበረ። ነገር ግን በነገሠ በዓመቱ የጨካኝነት ዐመሉ ብቅ ማለት ጀመረ እና የአባቱን ልጅ አስገደለ።
በ፶፱ ዓ.ም. ደግሞ እናቱን በመርዝ ገደለ። በ፷፫ ዓ.ም. እያስተማረ ያሰደገውን መምህሩን ፣ በ፷፪ ዓ.ም. የልጅነት ሚስቱን አግታሺያን አስገደለ።
ከእርስዋ በኋላ ያገባትን ሚስቱንም ፓፒያን በርግጫ ብሎ ገደላት።
ኔሮን በ፷፬ ዓ.ም. እርሱ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤተ መንግሥቱ ተቀምጦ የሮማን ከተማ እሳት ለቀቀባት። | 169 |
| 6 | ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ
የቅዱሳን ሐዋርያት ታሪክ ገድልና ሥራ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በሙሉ አልሰፈረም።
አርባዕቱ ወንጌላት ሐዋርያት እንዴት እንደተጠሩና እስከ ዕርገት ድረስ የነበራቸውን ሁኔታ ሲጽፉ፤ ወንጌላዊው ሉቃስ ደግሞ የሐዋርያትን ታሪክ እስከ ፷ዎቹ መጀመሪያ ያለውን ጽፏል።
ከዚህ በመለስ ያለውን የሐዋርያት ታሪክ ለማወቅ ግን ዋናው ምንጩ የቤተ ክርስቲያን የታሪክ መጻሕፍት ናቸው።
የሐዋርያት ደቀመዛሙርት እነ ፓፒያስ፣ ፖሊካርፐስ፣ አግናጥዮስ፣ ቀሌምንጦስ ዘሮም ወዘተ. የአባቶቻቸውን ታሪክ ጽፈው አቆይተውልናል።
ከዚህ በኋላ ጊዜም በ፪ኛውና በ፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሱት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፍት እነ አውሳብዮስ፣ ሩፊኖስ፣ ጄሮም፣ ወዘተ. በትውፊት የተቀበሉትን መዝግበው አልፈዋል።
ቅዱሳን ሐዋርያት ገድላቸው የተጻፈላቸው፣ በዓላቸው የተከበረላቸው የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ናቸው።
በቤተ ክርስቲያናችን በሐምሌ ፭ ቀን በታላቅ ድምቀት በዓላቸው ከሚከበረው ሐዋርያት መካከል የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስና የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ ታሪክ እንደሚከተለው ነው። | 222 |
| 7 | በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩
አምላክ አሜን!!!
✝️ ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ✝️
በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ)
በየዓመቱ ሐምሌ 2 ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ ሐዋርያ የቅዱስ ታዴዎስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ይከበራል።ይህ ሐዋርያ ከአስራ ሁለቱ የጌታ ደቀ መዛሙርት መካከል አንዱ ሲሆን አገረ ስብከቱም ከኢየሩሳሌም ከተማ 150ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ሶርያ ነው።
ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያት እንደ አባት የሚታይ በመሆኑ ታዴዎስን ወደ አገረ ስብከቱ ለማድረስ አብሮት ተጉዞ ነበር።በከተማዋ አጠገብ ሲደርሱም አንድ ሽማግሌ ሲያርሱ አገኟቸውና ቅዱስ ጴጥሮስ ጠጋ ብሎ "እባክዎ የምንበላው ነገር ይስጡን?" በማለት ጠየቃቸው።ሽማግሌውም ደግ ስለነበሩ "ከቤቴ እስካመጣላችሁ ድረስ በሬዎቼን ጠብቁልኝ" ብለው ወደ መንደር ገቡ።
ሁለቱ ሐዋርያት የገበሬውን ደግነት ተመልክተው ታዴዎስ ጠምዶ ሲያርስ ቅዱስ ጴጥሮስ መዝራት ጀመረ።
እኒያ ገበሬም ከቤታቸው ምግቡን ይዘውላቸው ሲመለሱ የተዘራው እህል በአንድ ቀን በቅሎ አሽቶ ጠበቃቸው።ይህን ታላቅ ተአምር የተመለከቱት ገበሬም ባዩት ነገር ሁሉ እየተደነቁ ሁለቱን ሐዋርያት "እናንተ ከሰማይ የወረዳችሁ አማልክት ናችሁን?"ብለው ጠየቋቸው።እነርሱም የመጡበትን አገርና ምክንያት አስረዷቸው።ወንጌልንም ሰበኩላቸው።
ገበሬው በአድናቆት እሸቱን ታቅፈው ለሚስታቸው ሊያሳዩ ወደ ቤት ሮጡ።የከተማው ሰዎችም ነገሩ ገርሟቸው ከበቧቸው።እርሳቸውም ያዩትን እና የሰሙትን ሁሉ ተረኩላቸው።
ከዚህ በኋላ ቅዱስ ጴጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሠ።የከተማው መኳንንትም ነገሩን በሰሙ ጊዜ "ይህ ከአሥራ ሁለቱ አስማተኞች ወገን ሳይሆን አይቀርምና ወደ ከተማችን እንዳይገባ ምን እናድርግ?" ተባባሉ።
ከመካከላቸው አንዱ "እነዚህ አስራ ሁለቱ አስማተኞች ዝሙትን ይጸየፋሉና ዘማዊት ሴትን በከተማችን በር እናቁም"ብሎ ስለመከራቸው በከተማቸው መግቢያ በር ላይ የታወቀች ዘማዊት ሴትን ራቁቷን አድርገው አቆሟት።
ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ገጠር ገጠሩን ሲያስተምር ውሎ ወደ ማታ ወደ ከተማ ሲመጣ ያችን ዘማዊት ሴት በከተማው በር ቆማ አያት።የምታደርገው ድርጊት ሁሉ የሚያሰጠይፍ ነበርና ያን ጊዜ ወደ ልዑል እግዚአብሔር ጸለየ።በዚህ ሰዓት ወደ አየር ወጥታ ተንጠለጠለች።የአገሩም ሰዎች በሚያዩት ነገር እስኪገረሙ ድረስ ትጮህ ነበር።እርሱም ወደ ከተማ ገብቶ ወንጌልን መስበኩን ቀጠለ።ያችንም ሴት ከተንጠለጠለችበት አውርዶ አሳምኖ በማጥመቅ በቤቷ የክርስቲያኖችን ጉባዔ መስርቷል።
በከተማዋ ውስጥ እያስተማረ ለአያሌ ቀናት ሰነበተ።አንድ ቀን "ባዕለ ጸጋ መንግስተ ሰማያት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብታልፍ ይቀላል።" እያለ ሲያስተምር አንድ ባዕለ ጸጋ ሰማና በአጠገቡ ወደ ሚያልፉት ነጋድያን እያመለከተ "እስኪ የተናገርከውን አድርገህ አሳየኝ" በማለት ጠየቀው።
ሐዋርያው ታዴዎስም አንድ ብረት አንጣሪ ክርስቲያን ወዳጅ ነበረውና መርፌ ሠርቶ እንዲያመጣለት ላከበት።ያም ወዳጁ የጠቀመው መስሎት ቀዳዳውን አስፍቶ ሰጠው።ታዴዎስ ግን ቀዳዳው እንደሌላው መርፌ እንዲሆን አስደርጎ ስመ እግዚአብሔርንም ጠርቶ "ላመነ ሁሉ ይቻላል" ነውና ግመሏን በመርፌው ቀዳዳ አሾልኮ አሳየው።በዚህም የተነሳ በዙርያው የነበሩት ሁሉ በትምሕርቱ አመኑ።
ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ከሶርያ በኋላ በፐርሺያ አውራጃዎች ሲያስተምር ቆይቶ ሐምሌ ሁለት ቀን በሰማዕትነት አርፏል።
የቅዱስ ታዴዎስ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።አሜን።
ምንጭ፦"ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ" መጽሐፍ።
ወስብሃት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር።
አሜን። | 392 |
| 8 | Sin texto... | 520 |
| 9 | Sin texto... | 439 |
| 10 | በምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በተከበረው የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ በዓል ላይ፣ የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን በዝማሬያቸው ድባቡን አድምቀዋል። ይህ በዓል ዛሬ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፤ የቅዱስ ዮሐንስ በረከት ይደርብን። | 41 |
| 11 | በምስጋና የታጀበው የሰንበት ትምህርት ቤታችን የምርጫ ሂደት በሰላም ተጠናቀቀ!!
በዛሬው ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የሦስት ዓመት የሥራ ዘመን የሚያገለግሉ አዳዲስ የሥራ አመራር አባላትን በመምረጥ በታላቅ መንፈሳዊ ድባብ ጉባዔውን አካሂዷል።
በዚህም መሠረት፡-
· አሥር (10) የሥራ አመራር አባላት በምርጫ ተለይተዋል፤
· ከእነዚህ ውስጥ የሥራ አስፈጻሚ እና ፀሐፊ ተመርጠዋል፤
· ሦስት (3) የኦዲትና ኢንስፔክሽን ፣
· አንድ (1) የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ተወካይ ተመርጠዋል።
በመጨረሻም፣ ከአጥቢያችን ካህናት የተወከሉ ሁለት አባቶች እና ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ የመጡ ታዛቢዎች የተገኙበት የባረኩበትና የንግግር መድረክ ተካሂዷል። ጉባዔው በአባቶች ቡራኬና በጸሎት ተጠናቋል።
አዲሶቹን አገልጋዮች አምላክ በጥበቡ ይምራቸው፤ እኛም በጋራ በመቆም አብረን እናገልግል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ ወለወላዲቱ ድንግል፣ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን። | 541 |
| 12 | Sin texto... | 481 |
| 13 | በምስጋና የታጀበው የሰንበት ትምህርት ቤታችን የምርጫ ሂደት በሰላም ተጠናቀቀ!!
በዛሬው ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የሦስት ዓመት የሥራ ዘመን የሚያገለግሉ አዳዲስ የሥራ አመራር አባላትን በመምረጥ በታላቅ መንፈሳዊ ድባብ ጉባዔውን አካሂዷል።
በዚህም መሠረት፡-
· አሥር (10) የሥራ አመራር አባላት በምርጫ ተለይተዋል፤
· ከእነዚህ ውስጥ የሥራ አስፈጻሚ እና ፀሐፊ ተመርጠዋል፤
· ሦስት (3) የኦዲትና ኢንስፔክሽን ፣
· አንድ (1) የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ተወካይ ተመርጠዋል።
በመጨረሻም፣ ከአጥቢያችን ካህናት የተወከሉ ሁለት አባቶች እና ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ የመጡ ታዛቢዎች የተገኙበት የባረኩበትና የንግግር መድረክ ተካሂዷል። ጉባዔው በአባቶች ቡራኬና በጸሎት ተጠናቋል።
አዲሶቹን አገልጋዮች አምላክ በጥበቡ ይምራቸው፤ እኛም በጋራ በመቆም አብረን እናገልግል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ ወለወላዲቱ ድንግል፣ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን። | 76 |
| 14 | Sin texto... | 463 |
| 15 | "ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተሰቡ ላይ የሚሾመው ደግ ታማኝና ብልህ መጋቢ ማን ነው ?"
ሉቃስ 12÷42
አስመራጭ ኮሚቴ | 491 |
| 16 | ኑ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር አብረን እንስራ
አስመራጭ ኮሚቴ | 561 |
| 17 | ✝️ 12ተኛ ዙር የሥራ አመራር ምርጫ የጸሎት መርሐ ግብር ✝️
የተወዳችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤
ለ12ተኛ ዙር የሰንበት ት/ቤታችን የሥራ አመራር ምርጫ በተዘጋጀው የጸሎት መርሐ ግብር ላይ በመገኘት፤ ስለ ቤተክርስቲያናችን፣ ስለ ፍጹም ሃይማኖታችን፣ ስለ አንድነታችንና ስለ አገልግሎታችን እያሳሰብን፣ እስከዛሬ በቸርነቱ ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላክ ለቀጣዩ ዘመን የተሻለ ራእይ ያላቸውን አባላት እንዲሰጠን እንጸልያለን።
ሁላችሁም በፍቅር ተጋብዛችኋል!!
🗓 ቀን፦ 28/10/2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከጥዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ 📍 ቦታ፦ ደጀ ሰላም
✨ መ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ፍ/ሃ ሰ/ት/ቤት ✨ | 520 |
| 18 | ✝️ አንድነት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት!
የመካኒሳ ደብረገነት ቅዱስ ሚካኤል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፤
የሰንበት ትምህርት ቤታችን የ12ኛ ዙር የሥራ አመራር ምርጫን እና የጸሎት መርሐ ግብርን በታላቅ ድምቀት ለማከናወን ተዘጋጅተናል። በዚህ መንፈሳዊ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት የአገልግሎት አሻራችሁን እንድታኖሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
"የመጣነው ለመማር፣ የቆምነው ለማገልገል ነው!"
🗓 ቀን፡ 28/10/2018 🕒 ሰዓት፡ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ 📍 ቦታ፡ ደጀሰላም | 19 |
| 19 | 🚨 የሥራ ማስታወቂያ 🚨
የድርጅት ስም: የየረር አጠቃላይ ሆስፒታል (Yerer General Hospital)
የሥራ ቦታ: ጎሮ፣ አዲስ አበባ
የሥራ ዓይነት: ሙሉ ሰዓት (Full Time)
📌 የሥራ መደብ ዝርዝር
የሥራ መደብ: ነርስ (Nurse)
የትምህርት ደረጃ: በክሊኒካል ነርሲንግ (Clinical Nursing) የቢኤስሲ (BSc) ዲግሪ የተመረቁ።
የሥራ ልምድ: አግባብ ባለው የሙያ ዘርፍ 1 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ላት።
📞 ማመልከቻ እና አድራሻ
ለበለጠ መረጃ እና ለመመዝገብ ከዚህ በታች ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
ስልክ ቁጥር: +251911462331 | 544 |
| 20 | ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እኚህ ነበሩ። | 549 |
