ch
Feedback
ፍሬ ሃይማኖት

ፍሬ ሃይማኖት

前往频道在 Telegram

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የአ/አ ሐገረ ሥብከት የመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረቦች ግጥማቸው ከነዜማ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያየት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot

显示更多
1 848
订阅者
-124 小时
-27 天
+430 天

数据加载中...

吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+5
在0个频道中
八月 '26
+41
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+41
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+45
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+98
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+39
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+16
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+20
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+42
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+20
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+20
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+20
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+23
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+28
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+18
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+27
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+20
在1个频道中
Get PRO
四月 '25
+36
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+24
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+33
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+78
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+53
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+53
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+51
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+43
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+23
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+39
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+38
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+22
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+27
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+30
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+28
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+28
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+27
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+19
在1个频道中
Get PRO
十月 '23
+26
在1个频道中
Get PRO
九月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+21
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+24
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+32
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+37
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+16
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+11
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+27
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+33
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+48
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+33
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+31
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+24
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+18
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+23
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+19
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+23
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+26
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+29
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+41
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+73
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+83
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+99
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+56
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+35
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+50
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+38
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+58
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+41
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+65
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+96
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+2 101
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
04 九月0
03 九月+2
02 九月+2
01 九月+1
频道帖子
2
ጸሊ ኀበ አምላክ.m4a
207
3
没有文字...
208
4
ረዳኤ ምንዱባን.m4a
203
5
没有文字...
194
6
መራሄ ብርሀናት.m4a
195
7
没有文字...
190
8
没有文字...
191
9
+5
没有文字...
270
10
+4
没有文字...
51
11
ወለተ ማርያም(አባይነሽ ኮረሚ) ይህች ነበረች።
ወለተ ማርያም(አባይነሽ ኮረሚ) ይህች ነበረች።
361
12
    ‼️ ወልደ ሥላሴ ማለት የዚህ ጽሑፍ(ታሪክ) አዘጋጅ የወለተ ማርያም የልብ ወዳጅ(ወንድም) መሆኑን ልብ ይሏል።     መቼም በእነዚህ ሃያ ሶስት ዓመታት በርካታ አባላት ገብተው ወጥተዋል፤ መጥተው ሄደዋል።በሁሉም ጭንቅላት ውስጥ ግን አንድ ጥያቄ ያቃጭላል።"ወለተ ማርያም ማን ናት"❓ የሚል ጥያቄ።       ከእረፍቷ አስራ አንድ፣ከዛሬ ደግሞ ሠላሳ ሶስት ዓመታትን ወደ ኋላ ተጉዛችሁ ታሪክን ስታጠያይቁ ምላሹን ታገኙታላችሁ።    አባ ኢየሱስ ሞዓ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ  ገብታችሁ ቀደምት መጻሕፍትን ገለጥ ገለጥ ስታደርጉ ከዚያ ቁጭ ብላ ታገኟታላችሁ።       አብሮ አደግ ወንድም እህቶቿን፣የሥጋ ዘመዶቿን ጠጋ ስትሉ እርሷ በሁሉም ዘንድ እንደተወደደችና እንደተከበረች አለች።ወደፊትም ትኖራለች።ሠው ከዚህ ዓለም ቢያልፍም፣ ዐረፍተ ዘመን ቢገታውም መልካም ሥራው ከመቃብር በላይ ሕያው ሆኖ ይኖራል።ለዚህ ደግሞ ማረጋገጫ ምሥክራችን ወለተ ማርያም ናት።      ደብረ ገነት ስትቆረቆር፣ ፍሬ ሃይማኖት ስትመሠረት ገና በለጋ ዕድሜያቸው ሁሉ ነገራቸውን ከለገሡቱ አንዷ ናት።ነባር አባላት ልክ እንደ እናቶቻችን ከምንቆጥራቸውና በልዩነት ከምናከብራቸው ታላላቅ እህቶቻችን መካከል አንዷ ናት አባይ።       ታጋሽ፣ትሑት፣ሰው በልቶ የሚጠግብ የማይመስላት ደግ፣ ንፍገት ፈጽሞ የሌለባት ለጋስ፣ ጮክ ብላ ስትናገር አንድም ቀን ተሰምታ የማትታወቅ ከአሥራ ሁለቱ  የመጀመርያዎቹ  አመራሮች አንደኛዋና የልማት ክፍል ተወካይ ነበረች።        ሥራ ስትይዝም  ከመጀመርያው ደመወዟ ላይ አርባዕቱ  ወንጌል አንድምታውን ገዝታ  ለእናት የሰንበት ት/ቤቷ  በማበርከት፤ በዚህም ሳትገደብ በየጊዜው መጻሕፍትን እየገዛች በመለገስ በኋላ ምሥረታው ዕውን ለሆነው እና የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ሆኖ ለተገኘው ቤተ መጻሕፍት ግንባር ቀደሙን ሚና የተወጣች፣ በመልካም ሕይወቷም ምሣሌ በመሆን ብዙዎችን በቃል ያይደለ በተግባር የሰበከች አመለ ሸጋ፣ ድንቅ ልጅ ነበረች ወለተ ማርያም።      በነገራችን ላይ ቤተ መጻሕፍቱ ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩና የእርስዋ ኅልፈት በተመሳሳይ ወቅት ነበር ማለት ይቻላል።ልዩነቱ የሁለት ወራት ልዩነት(መቀዳደም) ብቻ ነበር።(ሰኔ 29 ቀን 1995ዓ.ም እና ነሐሴ 27 ቀን 1995ዓ.ም) ተወዳጆች ሆይ!!!       ሃያ ሶስት ዓመታትን በእግረ ኅሊና ወደ ኋላ  ይዘናችሁ ስንጓዝ ልክ በዛሬዋ ቀን ዕለተ ማክሰኞ ነሐሴ 27 ቀን 1995ዓ.ም ነበር በተወለደች በ28 ዓመቷ ታላቋ እህታችን ከዚህ ከሚያልፈው ወደ ማያልፈው፣ ድካም ከበዛበት ከወዲህኛው ዓለም ድካም ወደ ሌለባት ወደዚያችኛዋ አዲስ ዓለም የተሸጋገረችው። መቼም ቢሆን የማትረሳ ዕለት።      እኛም ጊዜያችን ደርሶ እስከምንከተላት ድረስ ቀኒቱንም(ነሐሴ 27ን) ሆነ ወለተ ማርያምን(አባይነሽ ኮረሚን)  ለአፍታ እንኳን ሳንዘነጋቸው በልቦናችን ታትመው ይኖራሉ።        የእህታችንን የወለተ ማርያምን ነፍስ በአጸደ ነፍስ ከደጋግ አባቶችና እናቶች አጠገብ በክብር ያሳርፍልን። ከቅዱሳኑ ኅብረት ይደምርልን። ኦ እግዚኦ አዕርፍ ለነፍሰ ዓመትከ ወለተ ማርያም። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን። ተጻፈ ነሐሴ 26 ቀን 2018ዓ.ም ከምሽቱ በ4:00 ሰዓት።
333
13
+1
没有文字...
292
14
.                ታሪክ በዛሬዋ ዕለት       (ነሐሴ 27 ቀን 1995ዓ.ም) ዝክረ ወለተ ማርያም(አባይነሽ ኮረሚ)       በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) ሰላም ለኩልክሙ ኦ ውሉደ ፍሬ ሃይማኖት       ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይኄሉ (የጻድቅ  መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል።) መዝ. 111፥6        ሴት ልጅ ወለተ ማርያም  ተብላ ስትጠራ ትርጉሙ  የማርያም ልጅ ማለት ሲሆን፤ ለወንድ ልጅ ደግሞ ወልደ ማርያም ተብሎ ይሰየማል።ትርጉሙ ያው  እንደ መጀመርያው ነው አይለወጥም የማርያም ልጅ ማለት ነው። ወደ ታሪኩ ስንመለስ፦ በስመ ጥምቀቷ(በክርስትና  ስሟ)  ወለተ ማርያም፣ በዓለም ስሟ ደግሞ አባይነሽ ኮረሚ ትባላለች። አባይነሽ ኮረሚ(ወለተ ማርያም)ማን ናት??? "ማን ያውራ የነበረ፤ ማን ያርዳ የቀበረ" እንዲሉ አበው ስለ መልካሟ እህታችን በጥቂቱ እናውጋችሁ።        ወደ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ውስጥ ስትዘልቁ ከመድረኩ  ላይ አንድ ቆየት ያለ ስዕለ አድኅኖ ተቀምጦ ታገኛላችሁ።አስተውሎ ለተመለከተው በዕዝነ ሥጋ ድምጹ አይሰማ እንጂ  ስዕሉ ይናገራል።በዕዝነ ልቡና(በልቡና ጆሮ) ግን የሚሰማ ብቻ ሳይሆን የሚደመጥ ድምጽን ያስተጋባል።እንዲህ ሲል፦      በሩን በእጁ እየቆረቆረ  "እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለኹ።ማንም ድምጼን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ እገባለሁ።ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ።እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል"። የዮሐ.ራእ. 3፥20        በአናቱ በኩል ያለው ጽሑፍ ደግሞ ምንም እንኳን ከጊዜው ርዝመት፣ከዕድሜው ብዛት የተነሳ ቢወይብም(ቢደበዝዝም)  "ይህ ስዕል በሥጋዊ እረፍት ለተለየችን ለወለተ ማርያም መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ከወልደ ሥላሴ ተበረከተ" ይላል።
312
15
没有文字...
312
16
✨ ታላቅ የምስራች! የደብራችን እንቁ ልጅ ተማሪ ኪሩቤል ካህሳይ በዝክረ ቂርቆስ ወህፃናት ውድድር 2ኛ ደረጃን አሸነፈ! ✨ በተለያዩ ደብራት መካከል ሲካሄድ የቆየው የዝክረ ቂርቆስ ወህፃናት የ2018
✨ ታላቅ የምስራች!  የደብራችን እንቁ ልጅ ተማሪ ኪሩቤል ካህሳይ በዝክረ ቂርቆስ ወህፃናት ውድድር 2ኛ ደረጃን አሸነፈ! ✨ በተለያዩ ደብራት መካከል ሲካሄድ የቆየው የዝክረ ቂርቆስ ወህፃናት የ2018 ዓ.ም የአንድነት የጥያቄ እና መልስ ውድድር ፍፃሜውን አግኝቷል። ትላንት ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት በተካሄደው የመጨረሻ ዙር፤ የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት በኮኮብ ተማሪው በኪሩቤል ካህሳይ አማካኝነት ድንቅ ብቃት አሳይቷል። በዚህ ጠንካራ እና አጓጊ ፉክክር ውስጥ ተማሪ ኪሩቤል ያስመዘገበው አስደናቂ ውጤት የሰንበት ትምህርት ቤታችንን እና የደብራችንን ስም ከፍ ያደረገ ታላቅ ኩራት ነው። ለዚህ አኩሪ ድል የበቃህ የደብራችን እንቁ ልጅ ተማሪ ኪሩቤል፣ የሰንበት ትምህርት ቤቱ መምህራን እና አጠቃላይ ምዕመናን እንኳን ደስ አላችሁ!
333
17
没有文字...
466
18
.                  ታሪክ በዛሬዋ ዕለት             ነሐሴ 23 ቀን 1968ዓ.ም ✝️ የመናኙ ፓትርያርክ የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ሲመት(ሹመት) ✝️           በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) በቀድሞ ስማቸው አባ መልአኩ  ወልደ ሚካኤል ይባላሉ።የተወለዱት መስከረም 10 ቀን 1910ዓ.ም በቀድሞው ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ሲሆን፦ ሶስተኛው የኡትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን የተሾሙት ልክ የዛሬ ሃምሳ ዓመት ነሐሴ 23 ቀን 1968ዓ.ም ነበር። ፍጹም መናኝ የነበሩት አባ መልአኩ(ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ቀደም ብለን እንዳየነው ምንም እንኳን የተወለዱትና ያደጉት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ቢሆንም ከ1926ዓ.ም ጀምሮ ወደ ደቡቡ የአገራችን ክፍል በመጓዝ በወላይታ ሶዶ እና አካባቢው በተለይም በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በተጋደሉበት  ታሪካዊው ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት  ገዳም በአታቸውን በማጽናት በጾም፣በጸሎት፣በስግደትና በትኅርምት ፈጣሪያቸውን በቅድስና ሕይወት ሲያገለግሉ ኖረዋል። ከ1940ዓ.ም ጀምሮም በአታቸውን በዚያው ገዳም አድርገው በመላው ወላይታ አውራጃ እየተዘዋወሩ በማስተማር(ሐዋርያዊ) ተልኳቸውን በማከናወን በርካታ ሕዝብን ካለማመን ወደ ማመን ከአሕዛብነት ወደ ክርስትና የመለሱ ሲሆን በእርሳቸው ትምሕርትም ከ300,000(ከሶስት መቶ ሺህ) በላይ ኢአማንያን አምነው እንደተጠመቁ የክርስቶስ ተከታዮችም እንደሆኑ ይነገራል። በተጨማሪም በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን አሰርተዋል።አያሌ ትምሕርት ቤቶችን አቋቁመዋል።የችግረኞች መርጃ ማዕከላትን መስርተዋል።በዚህ መልካም ሥራቸው የተነሳም  የድሆች አባት በመባል ይታወቃሉ። ቅዱስነታቸው በዚህ ዓይነት መልካም ሥራ ተሰማርተው ሳሉ ወታደራዊው መንግሥት ደርግ ንጉሣዊውን መንግስት በኃይል አስወግዶ በትረ መንግስቱን ጨበጠ።የስልጣን ኮርቻውም ላይ ተፈናጠጠ። ቀጥሎም  ሁለተኛው የቤ ተክርስቲያናችን ፓትርያርክ የነበሩትን ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን አላግባብ አሠራቸው።ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪም ሌላ ፓትርያርክ እንዲመረጥ አዘዘ። ራሱ ባቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ አማካይነትም ለፓትርያርክነት እንዲመረጡ የሚፈለጉ አባቶችን ከየክፍሉ በእጩነት እንዲጠቆሙ  ካደረገ በኋላ በስተመጨረሻም አባ መልአኩ ከሌሎቹ እጩዎች የበለጠ ድምጽ በማግኘት ተመርጠዋል። ባላሰቡትና ባልጠበቁት ሁኔታ ለዚህ ታላቅ ኃላፊነት እንደታጩ የሰሙት ቅዱስነታቸውም "መንበሩ ለእኔ አይገባም"  ብለው እንደተቃወሙ ይነገራል።በዚህም የተነሳ ቅዱስነታቸው ቤተ ክህነት ውስጥ በምትገኝ አንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ በጥበቃ(በዘበኛ) ይጠበቁ እንደነበር ይነገራል። ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በጣሰ መልኩ በደርግ አስገዳጅነት ሶስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነው  የተመረጡት አባ መልአኩ(አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ፓትርያርክ ሆነው ከመሾማቸው አስቀድሞ ሐምሌ 11 ቀን 1968ዓ.ም ብጹዕ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተብለው በመሰየም  መዓርገ ጵጵስናን ተቀበሉ። ከአንድ ወር በኋላም ነሐሴ 23 ቀን 1968ዓ.ም ሶስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን ተሾሙ። የቅዱስነታቸውን የአመራረጥ ሒደት የሰሙት የግብጽ ቤተ ክርስቲያን፣የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት፣ እንዲሁም የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት "አንድን ፓትርያርክ በኃይል ከመንበሩ አንስቶ ሌላ ፓትርያርክ መሾም አይገባም" ሲሉ በመቃወም ለሹመቱ ዕውቅና አንሰጥም በማለት የተቃውሞ መግለጫን አውጥተዋል። በእንዲህ ያለ አወዛጋቢ መንገድ የተመረጡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዚያ "ፈጣሪ የለም ተብሎ በተካደበት" እና የሰው ልጅ ደም እንደ ከረምት ጎርፍ ይፈስ በነበረበት አስቸጋሪ ወቅት በትዕግስትና በጥበብ ቤተ ክርስቲያንን ማሻገር የቻሉ አባት እንደነበሩ ብዙዎች ይመሰክሩላቸዋል። ፍጹም ባሕታዊና መናኝ የነበሩት ሶስተኛው ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ታላቋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ለ12(ለአስራ ሁለት) ዓመታት ከመሩ በኋላ ግንቦት 28 ቀን 1980ዓ.ም  ከዚህ ዓለም ድካም አርፈው  ግንቦት 30 ቀን 1980ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሥርዓተ ቀብራቸው በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ስርዓት ተፈጽሟል። ተጨማሪ‼️ ጥቂት ስለ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መንፈሳዊ ሕይወት እናክልላችሁና ታሪኩን እናጠቃልል። ☦️ ፓትርያርክ ሆነው ሳለ በባዶ እግራቸው ይሄዱ ነበር እንጂ ለእግራቸው መጫሚያ አልነበራቸውም(ጫማን አያደርጉም ነበር)። ☦️ አመጋገባቸውን በተመለከተም ከበሶና ከተቀቀለ ድንች በስተቀር ሌላ የምግብ ዓይነት ቀምሰው አያውቁም ይባላል። ☦️ መቼም ቢሆን መሬት እንጂ አልጋ ላይ ተኝተው እንደማያውቁ በቅርብ የሚያውቋቸው  ሁሉ ይመሰክሩላቸዋል። ☦️ እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሀገረ ሙላድ(የትውልድ ስፍራ) ቢኖራቸውም ተወልጄ ያደግኹበት ቦታ ይህ ነው ብለው ከመናገር ይልቅ በፍጹም ኢትዮጵያዊነታቸው ያምኑ ነበር።በተጨማሪም የሰውን ልጅ በሙሉ በአንድ ዐይን(እኩል) በመመልከት ብቃታቸው ብዙዎችን ሲያስገርሙ የኖሩ አባት ነበሩ። ☦️  ቅዱስነታቸው መላ ዘመናቸውን በጾም፣በጸሎትና በሰጊድ ያሳለፉ በመሆናቸው ምክንያት ባደረባቸው ሕመም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ስትለይ የሰውነታቸው ክብደት 25(ሃያ አምስት) ኪሎ ግራም ደርሶ እንደነበር ይነገራል። የቅዱስነታቸው ረድኤትና በረከት በሁላችነም ላይ ይደርብን። ምንጭ፦ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን መጽሐፍ። በዲያቆን መርሻ አለኸኝ  የተዘጋጀ። ፲፱፻፺፯(1997)ዓ.ም ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። ተጻፈ ነሐሴ 22 ቀን 2018ዓ.ም ረፋድ 5:00 ሰዓት።
533
19
+2
没有文字...
473
20
.            የአሸንዳ በዓል የአሸንዳ፣ አሸንድዬ፣ ሻደይ፣ ሶለል በዓል ከየት መጣነት(መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ)።        በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) ሰላም ለኩልክሙ ኦ ውሉደ ፍሬ ሃይማኖት ውድ ቤተሰቦቻችን እንደምን ከረማችሁ?     ስንቶቻችን የአሸንዳ በዓል ከባህላዊ ገጽታው  ባሻገር መጽሐፍ ቅዱሳዊና መንፈሳዊ እንደሆነ እናውቅ ይሆን??? በመጠኑ እናውጋችሁ። ይጠቅማችኋልና በማስተዋል አንብቡት።      ይህ በዓል ከጊዜ በኋላ ባህላዊ ገጽታው እየጎላ የመጣ ቢሆንም ቅሉ መሠረቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው።በነገራችን ላይ አሸንዳ በወንዝ ዳር የሚበቅል ቅጠለ ሰፊ ቄጤማ መሳይ የሣር ዓይነት ሲሆን ልጃ ገረዶች በበዓሉ ሰሞን ይህን የሣር ዓይነት አቀጣጥለው፤ እንደ ጉርድ ቀሚስ በወገባቸው ላይ አስረው ስለሚጫወቱ ነው በዓሉ አሸንዳ ተብሎ የተሰየመው።        በዓሉ በሰፊው የሚከበረው በትግራይ በተለይም በተምቤንና በእንደርታ ሲሆን በተጨማሪም በዋግሕምራ፣በላስታ፣በላሊበላና በሰሜን ጎንደር አካባቢዎችም ይከበራል።      የአሸንዳ ጨዋታ(በዓል) ታሪክ ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ በአገረ እሥራኤል ይዘወትር ነበር።መጠርያው ይኽ(አሸንዳ) የሚለው ባይሆንም ቅሉ የጥንት አሥራኤላውያን መንፈሳዊና ባህላዊ ዕሴታቸው ነበር።       አጀማመሩም እንዲህ ነው፦ በመጽሐፈ መሳፍንት ምዕ. 11 ከቁ.1-40 ላይ እንደተጻፈው ዮፍታሔ የተባለ የገለዓድ ልጅ ነበር።ይሁንና ዮፍታሔ የተወለደው ከገለዓድ ሕጋዊ ሚስት ሳይሆን ከሌላ አመንዝራ ሴት ስለነበር፤ ከሕጋዊ ሚስቱ የተወለዱ የገለዓድ ልጆች "የአባታችንን ሥልጣንም ሆነ ኃብት የመውረስ መብት የለህም"። በማለት ወንድማቸው ዮፍታሔን አባረሩት።      ከጊዜ በኋላ ግን በእሥራኤላውያን ላይ ጠላቶች ተነስተው የገለዓድ ልጆችን አሸነፏቸው። በዚህን ጊዜ የእሥራኤል የአገር ሽማግሌዎች ተሰባስበው ከመከሩ በኋላ ዮፍታሔን ለማምጣት ተስማሙ።ምክንያቱም ዮፍታሔ የጦር ሠውና ኃይለኛ ተዋጊ እንደሆነ ያውቁ ነበርና ነው። ሔደውም ጠላቶቻቸውን እንዲወጋላቸው ለመኑት።      ዮፍታሔም ጥያቄያቸውን የሚቀበለው ጠላቶቹን ድል ካደረገ በኋላ መስፍን(ገዥ) አድርገው የሚሾሙት ከሆነ ብቻ እንደሆነ ነገራቸው። ሽማግሌዎቹም በዚህ ተስማምተው ቃላቸውን እንደሚያከብሩ አረጋገጡለት።        ዮፍታሔም  እግዚአብሔር ከጎኑ እንዲቆምለት ከጸለየ በኋላ ጠላቶቹን ድል አድርጎ ሲመለስ ቀድሞ ከቤቱ ወጥቶ የሚቀበለውን መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ ተሳለ። ዮፍታሔ እንደተመኘው ጠላቶቹን ድል አድርጎ ወደ ቤቱ ተመለሰ።ከራሱ አብልጦ የሚወዳት ብቸኛ ሴት ልጅ ነበረችው።ከእርሷ ሌላ ሴትም ሆነ ወንድ ልጅ አልነበረውም።ይህች ብቸኛ ልጁ አባቷ በጦርነት ድል ማድረጉን ስትሰማ የዕድሜ እኩዮቿ የሆኑ ጓደኞቿን ሰብስባ ከበሮ ይዛ እየጨፈረች ልትቀበለው ወጣች።አባቷ ወደ ቤቱ በተቃረበበት ጊዜም እየሮጠች ሄዳ ተጠመጠመችበት።      በዚህን ጊዜ ዮፍታሔ ልጁን እንደታቀፈ ማልቀስ ጀመረ።በሁኔታው ግራ የተጋባችው ልጁ ለምን እንደሚያለቅስ ጠየቀችው።እርሱም ለእግዚአብሔር የተሳለውን ስዕለት ነገራት።እርሷ ግን አልደነገጠችም። ይልቁንም "አባቴ አትዘን በስዕለትህ መሠሰት ሰዋኝ።ከዚያ በፊት ግን አንድ ነገር ብቻ ፍቀድልኝ፤ ይኸውም ከባልንጀሮቼ ጋር ሆኜ በአገሬ ተራሮችና ሸንተረሮች እየዞርኩ ለድንግልናዬ ክብር እንዳለቅስ ለሁለት ወራት አሰናብተኝ"። አለችው።ፈቀደላትና ጓደኞቿን ይዛ ሄደች።     ከሁለት ወራት በኋላ ስትመለስ ዮፍታሔ በስዕለቱ መሠረት ብቸኛ ልጁን መስዋዕት አድርጎ አቀረባት። እዚህ ላይ ዮፍታሔ ልጁን መስዋዕት አድርጎ አቀረባት ሲባል፦  አረዳት ማለት ሳይሆን ዕድሜ ልኳን ባል ሳታገባ በድንግልና እንድትኖር አደረጋት ማለት ነው ብለው የጻፉ ጸሐፍያንም አሉ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እሥራኤላውያን ልጃ ገረዶች በየዓመቱ ለአራት ቀናት ለዮፍታሔ ልጅ መታሰቢያ  ሙሾ የማውጣት ሥርዓትን  እንደ  ልምድ አድርገው ያዙት።      እዚህ ላይ ባህሉ ወደ ኢትዮጵያ እንዴት ሊመጣ ቻለ? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። መልሱም ታቦተ ጽዮን ወደ ኢትዮጵያ ስትመጣ አስራ ሁለት ሺህ ቤተ እሥራኤላውያንም አብረው መጥተው ነበር። እነዚሁ እሥራኤላውያን አሁን ተምቤን እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ እንዲሰፍሩ ተደረገ።ከዚያን ጊዜ በኋላ እነዚህ እሥራኤላውያን "አውርስ" የተባለውን የጨዋታ ዓይነት ጨምሮ ለአሸንዳ መሠረት የሆነውን ልማድና አሠራር እንዲስፋፋ አደረጉ።         ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ከተስፋፋ በኋላም ኢትዮጵያውያን የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በዓሉ የደናግል በዓል በመሆኑ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል ጋር ተየይዞ እንዲከበር አደረጉ።በመሠረቱ አሸንዳ የልጃ ገረዶች በዓል ነው። በመሆኑም፦የዚህ በዓል ተሳታፊዎች የሚሆኑት ያላገቡና ደናግል ብቻ ናቸው።       ልጃ ገረዶቹ የአሸንዳ ሥነ ስርዓታቸውን ሲጀምሩም ሆነ ሲያጠናቅቁ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው የጋራ ጸሎት ያደርሳሉ። በአካባቢው የሌለ ካልሆነ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኑ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሆን አለበት። በአሸንዳ ሰሞን ልጃ ገረዶች ሙሉ ነጻነታቸው የተጠበቀ ነው።በአሸንዳ ወቅት ሌላው ቀርቶ አንዲት ልጃ ገረድ "የማርያም ልጅ እየተባለች" ነው የምትጠራው። በመሆኑም "የማርያምን ልጅ" መምታት ቀርቶ መገላመጥና መቆጣትም ነውር ነው። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ምንጭ፦ ኅብረ ብዕር መጽሐፍ። (መምሕር ካሕሣይ ገ/እግዚአብሔር)  ተጻፈ ነሐሴ 21ቀን 2018ዓ.ም ምሽት በ4:00 ሰዓት።
555