cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

FBC (Fana Broadcasting Corporate)

This is FBC's official Telegram channel. For more updates please visit www.fanabc.com

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
183 675
Suscriptores
+18424 horas
+6677 días
+3 38530 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ከዳያስፖራው 3 ቢሊየን ዶላር በሬሚታንስ ወደ ሀገር መላኩ ተገለጸ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከዳያስፖራው የሚገኘውን ሬሚታንስ ለማሳደግ በተደረገ ድጋፍና ክትትል 3 ቢሊየን ዶላር የሬሚታንስ ገቢ መገኘቱን የዳያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ በዳያስፖራ ዘርፍ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀም ላይ ከኢፌዴሪ ሚሲዮኖች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱም ባለፉት 9 ወራት ከ197 ሺህ በላይ የዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላትን ያሳተፈ ወቅታዊና ሀገራዊ የልማት ጉዳዮች የተዳሰሱባቸው ከ730… https://www.fanabc.com/archives/244452
Mostrar todo...
👍 16😁 3 1
ክልሉ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ926 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ926 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታወቀ። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ እሸቱ ጎዴቶ እንደገለጹት÷ የክልሉ የይቅርታ ቦርድ በይቅርታ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ መሰረት መስፈርቱን የሚያሟሉ ታራሚዎችን ከመንግስት፣ ከህዝብና ከታራሚ ጥቅም አኳያ ሲመረምር ቆይቷል። በተደረገው ምርመራም በአጠቃላይ የይቅርታ ጥያቄ ካቀረቡ 978 ታራሚዎች መካከል መስፈርቱን ያሟሉ 926 ታራሚዎች ጥያቄያቸው ለክልሉ መንግስት ቀርቦ የይቅርታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን ተናግረዋል።https://www.fanabc.com/archives/244441
Mostrar todo...
👍 16 6👏 3
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ሲምፖዚዬም በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ አካፈለች አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዶሚኒካን ሪፐብሊክ በተዘጋጀው የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ሉላዊ የአፈፃፀም ድጋፍ ሲምፖዚዬም ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ አካፍላለች፡፡ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ሲምፖዚዬም ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡ አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ÷ በሲምፖዚዬሙ የአቪዬሽን ዘርፉን በሚያሳድጉ እና በሚያዘምኑ ጉዳዮች ላይ… https://www.fanabc.com/archives/244439
Mostrar todo...
👍 4😁 3
በሻምፒየንስ ሊጉ ግማሽ ፍፃሜ ዶርትመንድና ፓሪስ ሴንት ጀርሜይን ይፋለማሉ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመኑ ቦርሺያ ዶርትመንድና የፈረንሳዩ ፓሪስ ሴንት ጀርሜይን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት ያካሂዳሉ፡፡ ጨዋታው ከምሽቱ 4 ሰዓት በዶርትመንድ ሜዳ ሲገናል ኤዱና ፓርከ የሚካሄድ ሲሆን÷ የመልሱ ጨዋታ ደግሞ በፓሪስ ፓርክ ደ ፕሪንስ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ትናንት ባየርን ሙኒክ እና ሪያል ማድሪድ በአሊያንዝ… https://www.fanabc.com/archives/244436
Mostrar todo...
👍 9 7👏 4
በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 46 በርሚል ነዳጅ ተያዘ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 46 በርሚል ነዳጅ መያዙን የሚዛን አማን ከተማ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር አዳነ አለማየሁ እንደገለጹት÷ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ ከተያዘው ነዳጅ ውስጥ 35 በርሚሉ ናፍታ ሲሆን 11 በርሚሉ ደግሞ ቤንዝል ነው፡፡ በተሽከርካሪ ተጭኖ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ በተያዘው ነዳጅ ላይ ምርመራ እየተደረገ… https://www.fanabc.com/archives/244433
Mostrar todo...
👍 19 5
ከ80 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለሚያደርግ የውሃ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሃዋሳ ከተማ ከ80 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የውሃ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል፡፡ አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ ተግባራዊ ከሚደረጉ ፕሮጀክቶች አንዱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ነው። ዛሬ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የፋራ ሂጠታ ንፁህ የመጠጥ… https://www.fanabc.com/archives/244428
Mostrar todo...
👍 17 4
ማስታወቂያ! እንኳን አደረሳችሁ! የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር 482/2013 የተቋቋመ ሲሆን፣ ዓላማውም ለገንዘብ አስቀማጮች የመድን ዋስትና ወይም ኢንሹራንስ ሽፋን በመስጠት ለፋይናንስ ዘርፉ ጤናማነት አስተዋጽኦ ማበርከት ነው፡፡ በዚህም መሠረት አይበለውና አንድ ባንክ ወይም ማይክሮፋይናንስ ተቋም ኪሳራ አጋጥሞት ለገንዘብ አስቀማጮች ገንዘባቸውን መመለስ ቢያቅተው፣ ፈንዱ ኪሳራ ያጋጠመውን እና የወደቀውን ባንክ ወይም ማይክሮፋይናንስ በመተካት ለእያንዳንዱ አስቀማጭ እስከ መቶ ሺህ ብር በፍጥነት የመመለስ ሃላፊነት አለው፡፡ ለገንዘብ አስቀማጮች የሚመለሰው ገንዘብም ከፋይናንስ ተቋማት የሚሰበሰብ ሲሆን፣ ለዚህም ሲባል እስካሁን ባለው ሁኔታ ከብር 4.6 ቢሊዮን በላይ አረቦን (premium) ተሰብስቧል፡፡ ፈንዱ የራሱን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግና ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት፣ በየጊዜው የሚሰበስበውን አረቦን በሕግ አግባቡ መሠረት በመንግስት ግመጃ ቤት ሰነድ ላይ ኢንቨስት እያደረገ ይገኛል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር +251115571597 እና +251115578534 መደወል ይቻላል፡፡
Mostrar todo...
👍 9 2
የሰራተኞችን መብትና ጥቅም የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል – ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱስትሪ ሰላምን የማረጋገጥ፣ ምርታማነትን የማሳደግ፣ የሥራ ላይ ደህንነትንና የሰራተኞችን ጥቅም የማስከበር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የዓለም የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ለ49 ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ135 ጊዜ “ለሠላምና ለኑሮ ውድነት መፍትሔ እንሻለን” በሚል መሪ ሐሳብ እየተከበረ ይገኛል። በአዲስ አበባ… https://www.fanabc.com/archives/244424
Mostrar todo...
👍 15 7😁 4👏 1😱 1
ስራ ፈጠራን በማበረታታት የኢኮኖሚ ነጻነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው – አቶ አደም ፋራህ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ስራ ፈጠራን በማበረታታትና የተረጂነት አመለካከትን በመቀየር የምግብ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ነጻነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኋላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እንደቀጠለ ነው። መድረኩ ሶስተኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን በዛሬው ዕለትም… https://www.fanabc.com/archives/244417
Mostrar todo...
👏 11👍 6💩 1
በቻይና በአውራ ጎዳና መደርመስ የ19 ሰዎች ህይወት አለፈ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና ለቀናት የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በጉዋንግዶንግ ግዛት በአውራ ጎዳና ላይ በደረሰ የመደርመስ አደጋ የ19 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል፡፡ በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች 30 ሰዎች ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው የተገለጸ ሲሆን ለህይወታቸው አስጊ ነገር እንደሌለም ተመላክቷል፡፡ የግዛቱ አስተዳደር 500 የሚሆኑ የድንገተኛ አደጋ ምላሽ ሰጪ ሰራተኞችን ማሰማራቱም… https://www.fanabc.com/archives/244413
Mostrar todo...
👍 13😱 3😢 3 2🥰 1