en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 767
Subscribers
+3524 hours
+447 days
+5030 days
Posts Archive
+1
#ለአብይ #አህመድ እና #ለምስኪን #እናታቸው ሼር እያደረጋችሁ ከምርኮኞቹ በከፊል ጀባ ተብላችኋል! ቴሌግራም ሊንካችን ይወዳጁት!!https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

የምኒልክ 1ኛ ዕዝ በዋድላ ደላንታ ዳዉንት ግንባር በተደረገው ከባድ ዉጊያ የጠላትን አንድ ክፍለጦር በመደምሰስ በርካታ የአገዛዙን ሰራዊት እና መሳሪያዎችን መማረኩ ይታወቃል። ከተገኙ የመሳሪያ ምርኮዎች መካከል በከፊል የምስል ማስረጃዎችን አቅርበናል! ነገ ሙሉ የሰዉ እና ተጨማሪ የቁስ ምርኮ ምስሎችን እናጋራለን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!! ጷግሜ:-04/ 2018 ዓ/ም

የማንነት ሰንደቅ የሚኒልክ ትንፋሽ፦  አርበኛው እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ፅናት!! ​የዳግማዊ አፄ ሚኒልክ መናገሻ፣ የሀገር ሉዓላዊነትና የጀግንነት እምብርት የሆነችው ታሪካዊቷ የሸዋ ምድር፤ ዛሬም እንደ ትላንቱ የነፃነት ቀንበጦችና የቁርጥ ቀን ልጆች መፍለቂያ መሆኗን በተግባር እያስመሰከረች ትገኛለች። ታሪክና ሰንበር አድረገው በሳሏት፣ ፅናትና ክብር በታደለችው የሸዋ መንዝ እምብርት ውስጥ፣ የአማራን ሕዝብ ታሪካዊ ክብርና የማንነት ህልውና ለማስጠበቅ የተነሳው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምየው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ፤ የዚህ ዘመን የፋኖ እምቢተኝነት ሕያው ማህተም ሆኗል። ​ዛሬ በዱር በገደሉ፣ በጋራና በሸለቆው የሚሰማው የፋኖ የነፃነት ክንድ እና የምድር አንበሶች ተጋድሎ፤ የእነ አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ  የመርህ ፅናትና የስትራቴጂ ውጤት ነው። እናም ​እውነታው ግን ግልጽ ነው ለጊዜያዊ ሥልጣን ፍርፋሪና ለከርሳቸው ጥቅማጥቅም ሲሉ የሕዝባቸውን ሰላምና ክብር አሳልፈው የሰጡ፣ የጥፋትን አጀንዳ ተሸክመው የሚኳትኑ “ጥቁር ሆድ አደሮች” ይህንን አርበኛና እርሱ የሚመራውን የአማራ ልጅ ፋኖ እጅጉን አብዝተው ይጠሉታል።የፋኖ አይበገሬነቱን ያሳየው ይህ የአማራ ልጅ ጀግና በአማራ ህዝብ ላይ ክህደት፣ ባንዳነትና ሆድ አደርነት የፈፀሙትን የብልፅግና አሽከሮች የብአዴን ቅጠረኞች በየቀኑ የእግር እሳት ሆኖባቸዋልና! ​ነገር ግን ለማንነታቸውና ለታሪካቸው የሚቆረቆሩ እውነተኛ የአማራ ልጆች፣ የፋኖን የነፃነት ክንድና የአርበኛ ደሳለኝን አመራር አብዝተው በሚሳሱላቸው፣ በፍቅርና በኩራት በሞሉ ዓይኖቻቸው ይመለከቱታል። በደማቸውና በህይወታቸውም ይደግፉታል። ምክንያቱም ይህ ንቅናቄ የአማራ የቁርጥ ቀን ደራሽ፣ የሚኒልክ የታሪክ ትንፋሽና ከምንም ዓይነት ምድራዊ ሥልጣንና ማዕረግ ይልቅ “አማርነትን፣ ነፃነትንና የሕዝብን ክብር” ያስቀደመ የቁርጥ ቀን ታጋይ ኃይል ስለሆነ። ​ለጥላቶቹና ለባንዳዎች የሚገርመውና የሚያስደነግጠው እውነታ ግን ይህ ነው፤ አርበኛ ደሳለኝንና እርሱ የሚመራውን የፋኖን ስም አፍ አውጥቶ መሳደብና መዳፈር ቀርቶ፣ በሃሳብ እንኳ ነክቶ ማማት የማይታሰብ መሆኑ ነው። ​የፋኖ ፅናትና የአርበኛው መሪ ጥበብ የሸዋ ምድር ዛሬም እንዳልመከነች ሕያው ምስክር ነው። የዚህ ትልቁ ማረጋገጫ ደግሞ ጠላቶቹ ሊያጠፉትና ሊያሸብሩት ቢመኙም አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ  ዛሬም በሕይወትና በጤና በመስዋዕትነት ሜዳው ላይ በጽናት መቆሙ ነው! ዛሬም በዕድሜውና በጉልበቱ ሳይበገር  የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን ከፊት ሆኖ በመምራት ላይ ይገኛል። ​በቅርቡ በጦር ግንባሮች በተመዘገበው አስደናቂ የጀግንነት ውሎ፣ የአርበኛ ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሪዎችና የአሳምነው አናብስት ፋኖ በጠላት ምሽግ ላይ እንደ መብረቅ ተከስተው፣ የክህደትን ኃይል የነቀሉበትና ታሪክ ያደነቀው ወታደራዊ ድል አስመዝግበዋል። አርበኛ እንጅነር  ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ በቁርጥ ቀን ልጆቹ ጋር በመሆን፣ ወደ ሽዋ ምድር የዘመተውንና ንፁሃንን የሚጨፈጭፈውን የአብይ አህመድን ወራሪና አራዊት ሰራዊት እግር በእግር እየተከታተለ ድባቅ እየመታው ይገኛል። በነዛ አስፈሪ ጋራዎች ላይ የተሰማው የፋኖ ቀረርቶና ፉከራ፣ የጠላትን አጥር ሰብሮ የገባው አንበሳዊ ተወርዋሪነት፣ የሸዋን ምድር ወደማይደፈር የነፃነት አምባነት ቀይሮታል። ​ይህ የጦር ሜዳ ጀግንነት፣ የጠመንጃቸው ኃይልና የፅናት ማዕበል የማንነታችን ሰንደቅ ዓላማ በጀግኖቻችን ትከሻ ላይ ከፍ ብሎ ለዘላለም እንደሚወለብል ማረጋገጫ ነው። የፋኖ ጀግንነትና የአርበኛው ደሳለኝ ገድል የትውልዳችን የነፃነት አዋጅ ነው ታሪክ በደማቅ ቀለም እየፃፈ፣ ጠላት በሽብር የሚረበሽበት፣ ወዳጅ በኩራት አንገቱን የሚያቀናበት የዘመናችን እውነተኛው የድል ታሪክ እየሰራ ይገኛል። የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ፈጣሪ እንዲጠብቅህ እመኛለሁ። #Dave #Amhara

የአማራ ልጅ ፋኖ የጀግንነት የፅናት ተምሳሌት!! ​በነፃነት የመኖር ማንነቱና የታሪክ አደራው የተቀበለው ​የአማራ ልጅ ፋኖ ማለት የጥንካሬ፣ የኩራትና የታሪክ ምስክር ነው። ከቀደሙት አባቶች የተረከበውን የነፃነትና የክብር አደራ አንግቦ፣ የነገውን ብሩህ ተስፋ ለመቅረጽ የሚተጋ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። ስሙ የነፃነት ጥሪ፣ መገኘቱ ደግሞ የፍትህና የጽናት ጋሻ የሚገርመው የጀግንነት መገለጫ ​በፈተናዎች ውስጥ የማይናወጥ፣ በግርማ ሞገሱ ፈተናዎችን የሚያስደነግጥ ኃይል አለው። ​እንደ አለት የጠነከረ ጽናት ማዕበልና አውሎ ንፋስ የማይበግረው፣ ለእውነትና ለወገኑ እምነት የቆመ የቁርጥ ቀን ጀግና። ​የማይፈራ ልብ ለማንነቱና ለህዝቡ ክብር ሲል ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ወደኋላ የማይል።​የኩራት መገለጫ በአካሄዱ ግርማ ሞገስ፣ በንግግሩ ደግሞ እምነትና ተስፋ የሚታይበት እውነተኛ የክብር ምልክት። የሚያስደምመው ታላቅ ዓላማ ​የፋኖ ዓላማ ግልጽና መሠረተ-ጽኑ ነው፤ እሱም ፍትህ፣ እኩልነት፣ ማንነትና ዘላቂ ሰላም ማስፈን ነው። ዓላማችን የግፍ ቀንበርን ሰብሮ፣ በእኩልነትና በነፃነት የሚኖሩ፣ በአለማችን የተከበሩ ማህበረሰብ መገንባት ነው። ​ይህ ጉዞ ለራስ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልድ የሚተርፍ የፍትህና የክብር አሻራ ለመተው የሚደረግ የታሪክ ጉዞ ነው። የአማራ ልጅ ፋኖ የትላንት ታሪክ ኩራት፣ የዛሬ የጽናት መሠረት፣ የነገ የሰላምና የነፃነት ዋስትና የሆነው የአማራ ልጅ ፋኖ ብቻ ነው!! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ወታደራዊ እቅድና እስትራቴጂ ዋና መምሪያ መቶ አለቃ ልመነው ሻወል ደመቀ የቴሌግራም ሊንካችን ሸርና ጆይን በማድረግ ይወዳጁን፦ https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

እኛን የሚገልፀን አንድ ታላቅና የማይናወጥ እውነት አለ... ​እኛ የዚች ታሪካዊት ምድር ኩሩ የአማራ ልጆች ነን! በራሳችን ሰማይ ስር በፍቅር፣ በክብርና በሰላም መኖርን እንጂ፣ የሰውን ክፉ መመኘትም ሆነ የሌላውን ድንበር መድፈር በተፈጥሯችን የለም። ተፈጥሮ በውበት፣ በንጽሕናና በጽናት የሰራችን የእውነት ሕያው እንቁዎች ነን! ​​ክብራችንን የሚነካ፣ ማንነታችንን የሚደፍርና ሰላማችንን የሚያደፈርስ ማንኛውም እጅ ሲመጣ በጭራሽ አንታገስም! የፍቅራችንን ያህል ቁጣችን ታላቅ፣ የትዕግስታችንን ያህል እሳታችን የበረታ ነው! በታሪካችን ታይቶ በሚታወቅ ዳግማዊ ድልና የበላይነት እንጂ፣ በሽንፈት የሚባል ጥቁር ጥላ ማንነታችን ላይ እንዲያርፍ አንፈቅድም። ​ማንነታችን ንጹሕና የወርቅ ያህል የጠራ ነው፤ ጽናታችን ደግሞ ተራራ የሚያናውጥ፣ ከድንጋይ የጠነከረ ነው! የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላት #Dave #Amhara

ዶክተር ታደሰ 3

100 አለቃ ልመን 5

ሻለቃ ሞገስ 4

አርበኛ አበበ ሙላቱ መዝጊያ ንግግር 6

የፀሎት እና የመክፈቻ ንግግር

Repost from N/a
ኪነ_ጥበብ 4

Repost from N/a
ኪነ_ጥበብ 3

Repost from N/a
ኪነ_ጥበብ2