en
Feedback
ካራ አሎ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት Karalo

ካራ አሎ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት Karalo

Open in Telegram

ይህ ቻናል ታማኒና ወቅታዊ መልእክቶች ፣ሞደል ፈተናዎች ፣ ወርክሽቶች እንድሁም አስተማሪ መለዕክቶችን ያገኛሉ።

Show more
4 437
Subscribers
No data24 hours
+97 days
+2130 days
Posts Archive
Repost from Yeka Education
✔️በ2019 የትምህርት ዘመን በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ ✔️(ሀምሌ 9 /2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የትምህ
✔️በ2019 የትምህርት ዘመን በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ   ✔️(ሀምሌ 9 /2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የትምህርት ቢሮ እና የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ በጋራ በወጣው የተማሪ ቅበላ መመሪያ መሰረት ለሳይንስ ሼርድ ካምፓስ በ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ በ2019 ዓ.ም ለማስተማር ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ ✔️ስለሆነም የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተማሪዎች በሳይንስ ሼርድ ካምፓስ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡   ✅1.በ2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአማርኛ ወይም በአፋን ኦሮሞ ዘርፍ በመማር ላይ የነበሩ፤ ✔️2.በ2018 ዓ.ም በ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና አማካኝ ውጤት /Average/ 80% እና በላይ ያስመዘገቡ፤ ✅3.በ2018 ዓ.ም በ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት በአጠቃላይ ሳይንስ፤ በሒሳብ፤ በእንግሊዘኛ ትምህርት አይነቶች በእያንዳንዳቸው የፈተና ውጤት 80% እና በላይ ውጤት ያስመዘገቡ፤ ✅4.በ2018 ዓ.ም ከሚማሩበት ትምህርት ቤት ምንም ዓይነት የስነምግባር ግድፈት እንደሌለባቸው ደብዳቤ የሚያቀርቡ፤ ✅5.በትምህርት ቤታቸው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ ላይ መሳተፋቸውን ማስረጃ የሚያቀርቡ፤ ✅6.ተማሪዎች በ7ኛ ክፍል ውጤታቸው በአጠቃላይ ሳይንስ፤ በሒሳብ፤ በእንግሊዘኛ ትምህርት አይነቶች በእያንዳንዳቸው አማካኝ ውጤት 80% እና በላይ የሆነ፤ ✅7. በሳይንስ ሹርድ ካምፓስ በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ መቀጠል የሚገፈልጉ፤     ✔️የምዝገባ ቀን፡- ከሐምሌ 13 ቀን እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ፤      ለመመዝገብ ይህንን ሊንኩም ተጠቀሙ ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://bs.ministry.et ✅ የመግቢያ ፈተና ቀን 9ኛ ክፍል ለሚገቡ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን የፈተና ቦታና ሰዓት በቀጣይ በማስታወቂያ ይገለጻል፡፡      ማሳሰቢያ፡- በምዝገባና በፈተና ወቅት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የመጣ አይስተናገድም፡፡    🔠🔠🔠🔠 🔠🔠🔠 Our Channel ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76

✔️የትምህርት እድል ✅ለ6️⃣ኛእና8️⃣ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
✔️የትምህርት እድል ✅ለ6️⃣ኛእና8️⃣ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች

✅የትምህርት እድል ✅ለ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
+1
የትምህርት እድል ለ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች

ማስታወቂያ ለተማሪዎች በሙሉ ነገ እሮብ በ1/11/ 2018 ችግኝ ለመትከል የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ጠዋት 12:00 ስለሆነ መኪናው የሚንቀሳቀሰው በሰዓቱ እንድትገኙ ጥሪ እያስተላለፍን ችግኝ መትከል የሚፈልግ ተማሪ በሰዓቱ የተገኜ መሳተፍ የሚችል መሆኑን እናሳውቃለን።

ዘንድሮ ለተመዘገበው ውጤት ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ስራዉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱ ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሀ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ፣ የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተነድፎ በትኩረት መስራት መቻሉ ፣ የመማሪያና የማስተማሪያ ግብዓቶች መቅረባቸው እንዲሁም ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይም ከወላጆች ጋር በቅንጅት መሰራቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል:: በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ስርአቱ የብዝሀ ቋንቋ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞ እንደሁለተኛ ቋንቋ የተማሩ ተማሪዎች በትምህርት አይነቶቹ ፈተና መውሰዳቸውን ዶክተር ዘላለም አስታውሰው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል። https://aa6.ministry.et/#/result ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ተዘዋወሩ፡፡ (ሰኔ 29/2018 ዓ.ም) በአ
+2
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ተዘዋወሩ፡፡ (ሰኔ 29/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 97.48 % የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ አስታወቁ። ኃላፊው የ2018 የትምህርት ዓመት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን በማስመልከት ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በጋዜጣዊ መግለጫቸው በከተማ አስተዳደሩ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 84,257 ተማሪዎች መካከል 82,137 የሚሆኑ ተማሪዎች 50 በመቶ እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የትምህርት እርከን መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል። ኃላፊው አያይዘውም ዘንድሮ 97.48% የሚሆኑ ተማሪዎች 50 እና በላይ በማምጣት ወደ ዘጠነኛ ክፍል ያልፉበት ውጤት በ2017 ዓ.ም ከነበረው 95% አንጻር እድገት ማሳየቱን ገልጸው ውጤቱ እንዲመዘገብ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መምህራን ፣ የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለወላጆችና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

Repost from Yeka Education
⭐️ተማሪዎች ሆይ ለቀጣይ አመት አሁኑኑ ጥናት ጀምሩ መጽሀፍት ለማግኘት :- ✅የቅድመ 1ኛ መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3693?single ✅የቅድመ አንደኛ የእንግሊዘኛ መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/4609?singleየ1ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3716?singleየ2ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3709?singleየ3ኛ ክፍል  መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3702?singleየ4ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3685?singleየ5ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3678?singleየ6ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3670?singleየ7ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3659?single ➡️የ8ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3641?singleAfan Oromo Grade 3-8 text books ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3099?singleከ9ኛ-12ኛ ክፍል መጽሀፍ ለማግኘት ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3720

ከላይ ስማችሁ የተዘረዘራችሁ ተማሪዎች ነገ 2:30 ሰዓት ላይ ከወላጆቻችሁ ጋር የት/ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን ።

የምዝገባ ቦታ ካራአሎ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 3

Frame 1@2x.png2.84 MB

✔️የትምህርት እድል (ለ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች) ✅ለቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ✅ከት/ቤታቹህ መስፈርቱን የሚያሟሉ 1 ወንድ እና 1ሴት ተማሪ በቅጹ መሰረት አስከ ነገ አርብ 10:00 ድረስ ብቻ በሶፍት
+2
✔️የትምህርት እድል (ለ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች) ✅ለቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ✅ከት/ቤታቹህ መስፈርቱን የሚያሟሉ 1 ወንድ እና 1ሴት ተማሪ በቅጹ መሰረት አስከ ነገ አርብ 10:00 ድረስ ብቻ በሶፍት ኮፒ curriclum group ላይ ብቻ ላኩልን

Repost from Yeka Education
🔤🔤🔤🔤🔤➖8️⃣ ✔️ውጤት ለማየት 👇👇👇👇 https://aa.ministry.et/#/result 🔠🔠🔠🔠 🔤🔤🔤 ቻናላችን ይህ ነው ⬇️⬇️⬇️⬇️ ❤️❤️❤️❤️❤️ https://t.
🔤🔤🔤🔤🔤➖8️⃣ ✔️ውጤት ለማየት 👇👇👇👇 https://aa.ministry.et/#/result 🔠🔠🔠🔠 🔤🔤🔤 ቻናላችን ይህ ነው ⬇️⬇️⬇️⬇️ ❤️❤️❤️❤️❤️ https://t.me/dam76

👉ተማሪዎች ውጤታችሁን የማስፈንጠሪያዉን በመጫን መመልከት ትችላላችሁ Grade 8 Result https://aa.ministry.et/#/result

Repost from Yeka Education
✔️ የተፈታኞች መብትና ግዴታዎች ✔️ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት
✔️ የተፈታኞች መብትና ግዴታዎች ✔️ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና   ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። ✔️ ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። ✔️ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል ✔️ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። ✔️ ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ ✔️የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል ✔️ ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። ✔️ እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። ✔️ ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። ✔️ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም ✔️ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። ✔️ ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። ✔️ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። ✔️ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። ✔️ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። ✔️ ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። 🔤🔤🔤🔤🔤🔤 ⭐️ለተፈታኞች የተፈቀዱ እርሳስ የተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM) ADMISSION CARD ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ 🔤🔤🔤🔤🔤🔤 ለተፈታኞች የተከለከሉ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም ካልኩሌተር የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ሰዓት በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ ✔️የፈተና ኦረንቴሽን ቀ ➡️ ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል በ05/10/2018 ✔️ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ➡️ 6ኛ ክፍል ከሰኔ 8- 10 /2018 ዓ/ም ➡️8ኛ ክፍል ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ/ም ይሆናል 🥢https://t.me/dam76

Repost from Yeka Education
✔️ለ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈተኞች የትምህርት አይነትና ኮድ (ለአዲስ አበባ ተፈታኞች) ✔️የሚኒስትሪ ተፈታኞች ማድረግ የሚገባቸው 1ነገሮች ⭐️1.ለመልስ መስጫ ወረቀት እርሳስ ብቻ መ
✔️ለ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈተኞች የትምህርት አይነትና ኮድ (ለአዲስ አበባ ተፈታኞች) ✔️የሚኒስትሪ ተፈታኞች ማድረግ የሚገባቸው 1ነገሮች ⭐️1.ለመልስ መስጫ ወረቀት እርሳስ ብቻ መጠቀም ⭐️2.የት/ት አይነት መለያ ኮድን ቡክሌት ኮድ በትክክል ማጥቆር ⭐️3.ቡክሌት ኮድን በትክክል ማጥቆር ⭐️4.የመልስ ወረቀት ላይ በአግባቡ ማጥቆር ⭐️5.የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የጥያቄዎቸን ቅደም ተከተል ጠብቆ መስረት ⭐️6.ለአንድ ጥይቄ አንድ መልስ ብቻ ማጥቆር 🌟7.የመልስ ወረቀት ላይ ሌላ ነገር አለመጻፍ ✅8.በፈታኞች የሚሰጠንን መመሪያ ተግባራዊ ማደረግ ⭐️ ለሁሉም ተፈታኞች መልካም ፈተና 🔠🔠🔠🔠 🔠🔠🔠 Our Channel ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76