en
Feedback
Amhara Revolution

Amhara Revolution

Open in Telegram

ይህቺ ገፅ 17/04/2016 ተከፈተች። መረጃ ያድርሱን @heyab8 ✅የተመሠረተችው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራን ሕዝብ ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ እና ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትሰራለች። ድል ለአፋብን💪

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Amhara Revolution

Channel Amhara Revolution (@minilik28) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 391 subscribers, ranking 4 046 in the Politics category and 2 516 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 391 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 287 over the last 30 days and by 9 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.98%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.60% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 738 views. Within the first day, a publication typically gains 1 420 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህቺ ገፅ 17/04/2016 ተከፈተች። መረጃ ያድርሱን @heyab8 ✅የተመሠረተችው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራን ሕዝብ ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ እና ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትሰራለች። ድል ለአፋብን💪

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Politics category.

13 391
Subscribers
+924 hours
+917 days
+28730 days
Posts Archive
ተጠናክሮ በቀጠለው ስቦ ማስከዳት ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቀሉ! በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮርን ስምንት የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት አባላት ሙሉ ት
+3
ተጠናክሮ በቀጠለው ስቦ ማስከዳት ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቀሉ! በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮርን ስምንት የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት አባላት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው ተቀላቅለዋል። መነሻቸውን በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ ብልባላ ከተማ 204ኛ ኮር በኮሎኔል አባቡ የምትመራው 38ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎች ስድስት አባላቱ ምቹ ቦታና ጊዜን ይጠብቁ የነበሩት የአማራን ህዝብ ግፍ ቆሞ ማየትና ተባባሪ መሆን የሰለቻቸው ለስለላ በተላኩበት እርስ በርስ በመተማመንና ቆራጥ ውሳኔ በመወሰን ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ/ም ፋኖን ተቀላቅለዋል። በሌላ አቅጣጫ ከ38ኛ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሬጅመንት አንድ መቶ መሪና አንድ ብሬን ተኳሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው 19ኛ ክፍለ ጦር ወደ ፋኖዎች ቤት ጎራ ያሉ ሲሆን ለመጡት ጥቁር እንግዶችም በአማራነት ባህልና እሴትም በእንክብካቤ ተይዘዋል። አባላቱም አንድ ጥቁር ስናይፐር፣ ሰባት ጥቁር ክላሽ፣ አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ 549 የክላሽ ተተኳሽ፣ ስድስት የእጅ ቦምብ በኮሩ ስር ለሚገኙ 19ኛና 30ኛ ክፍለ ጦር ፋኖዎች አበርክተዋል። ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ!

ሰሞኑን ኦፍላይን ስለነበርኩ ደጋ ዳሞት ስለተፈፀመው የጦር ሜዳ ጀብዱ አልሰምቸም ነበር:: በሰማሁ ጊዜ እጅጉን ተደስቻለሁ:: ወትሮም እኮ ዳሞት የጀግና ምድር ነው:: የመትረየስ ማራኪው የአባ ሻወል
ሰሞኑን ኦፍላይን ስለነበርኩ ደጋ ዳሞት ስለተፈፀመው የጦር ሜዳ ጀብዱ አልሰምቸም ነበር:: በሰማሁ ጊዜ እጅጉን ተደስቻለሁ:: ወትሮም እኮ ዳሞት የጀግና ምድር ነው:: የመትረየስ ማራኪው የአባ ሻወል ሀይሌ ምድር ነው:: አባ ሻወል ሀይሌ የጎራው ወጥ ቤት! መትረየሱን ጥዶ ሲሰራ አየሁት! ተብሎ ነበር:: ሻለቃ ዝናቡ የአባ ሻወልን ጀብዱ ደግሞታል:: ይህ ስራ የሻለቃ ዝናቡ ውጤት ነው ብንክደው ፈጣሪም ይቀየማል:: አንዳንዶች ለድሉ ቦታ መስጠት አቅቷቸው አስተዋልኩ:: በመሰረቱ የወንድም ድል እና ስኬት የሚያስከፋን ልንሆን አይገባም:: በበኩሌ እንኳን ኮሎኔል ለሚደመስስ ጀግና እውቅና ልነፍግ በጠላት ላይ ጥይት ተኩሶ ለሚረብሽ ሁሉ ክብር አለኝ:: የጀግናን ሀቅ አንክድም! @በላይነህ ተፈራ

አየር መቃዎሚያው ተመታ!/ተኳሾቹ ተገደሉ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ ዐምሐራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 71ኛ ክ/ጦር ስር የሚገኙት የ1ኛ ሙሐመድ ዳውድ ሬጅመንት አርበኞች ትናንት ሰኔ 21/2018 ዓ.ም በከላላ ግንባር በታላቅ የጦር ብቃት የጠላትን ኃይል በማፍረክረክ አንፀባራቂ ድል አስመዝግበዋል። በአየር መቃዎሚያና በሌሎች የሜካናይዝድ መሣሪያዎች ታጅቦ መነሻውን ከጊምባ ያደረገው የጠላት ኃይል፡ ንፁኋንን ለመጨፍጨፍ፣ ሃብት-ንብረት ለማውደምና ወረራ ለመፈፀም ወደ ሻፊ እና ባከት አከባቢዎች ለመንቀሳቀስ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም፡ በአርበኞቹ ልዩ የውጊያ ጥበብ ሁለትና ሦስት ቦታዎች ላይ ተቆርጦ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል። ትናንት አመሻሽ ድረስ በወሎ ቤተአማራ ቀጠና ከላላ ግንባር ሻፊና በባከት አከባቢዎች ላይ በተደረገው ተጋድሎ፡ የፋኖ አስደማሚ የፀረ ማጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ጥበብ ሲታየ፡ በአንፃሩ የጠላት ብልፅግና ኃይሎች ከወደ ፋኖ የተወሰደባቸውን እርምጃ የሚመክቱበት ፋታ አጥተው ተሽመድምደው የዋሉበት አውደ ውጊያ ተካሂዷል። አርበኞቹ ጠላትን በሁለት አቅጣጫ ማለትም በሻፊ እና በባከት በኩል ቆርጠው ቀጠናውን በመቆለፍ ከባድ እርምጃ ወስደውበታል። በአከባቢው በተለይ ጎራዳ ተብሎ በሚጠራው ቦታ፡ ጠላት በአየር መቃዎሚያ መሣሪያ ታግዞ ከወደ ፋኖ የተከፈተበትን የፀረ ማጥቃት እርምጃን ለመቋቋም ሙከራ ቢያደርግም፡ ነገር ግን ከጥቃቱ መክበድና ከአጥቂዎቹ ፍጥነት ጋር ተዳምሮ ጠላት ሙትና ቁስለኛውን አዝረክርኮ ለመሸሽ ተገድዷል። በዚህ ተጋድሎ ሙትና ቁስለኛ ከተደረጉ የጠላት እግረኛ ወታደሮች በተጨማሪ የአየር መቃዎሚያው አፈሙዝ በፋኖ ዲሽቃ ተመቶ በእሳት ሲጋይ፡ የአየር መቃዎሚያ ተኳሹና ረዳቶቹ ፋኖ ባካሄደው የዲሽቃና የብሬን ስብጥር ተኩስ ተገድለዋል። የ71ኛ አባናደው ክፍለጦር አርበኞች ከወሰዱት ከባድ የሆነ የፀረ ማጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ስልትን ከአንዳች አማራዊ ጀግንነትና ወኔ ጋር ያዋሃደ እርምጃ አንፃር የጠላት ከባባድ መሣሪያዎችና የሰው ኃይሉ ትርጉም ባጣበት በዚህ ተጋድሎ፡ 23 የአገዛዙ ወታደሮች ተደምስሰዋል፡ በርካታ ልዩ ልዩ  የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ወታደራዊ ቁሣቁሶች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል። አርበኞቹ ከሚያደርጉት የመደበኛ ውጊያ በተጨማሪ፡ የጠላት ኃይልን ስቦ ከመምታት ጀምሮ፡ በከባባድ የጦር መሣሪያዎች ሽፋን ታግዞ በሚንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም የቆረጣና የደፈጣ ጥቃት በመፈፀም የብልፅግናውን አገዛዝ አሽመድምደው በድል ጎዳና እየገሰገሱ ይገኛሉ። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! በአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሰኔ 22/ 2018 ዓ/ም

photo content
+1

አገዛዙ በአርበኛ ኢንጂነር ዘበነ በላይነህ ቤተሰቦች ላይ እስራትና ከባድ ድብደባ ፈፀመ! ​ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ ከአንኮበር ወረዳ የአፋብን ዕቅድና ስትራቴጅ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት የአርበኛ ኢንጂነር ዘበነ በላይነህ ቤተሰቦች በአገዛዙ ታስረው ማሰቃዬት እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተረጋግጧል። ​የፋኖን ወታደራዊ ክንድ መቋቋም ያቃተው የብልፅግና አገዛዝ ከዚህ ቀደም የጀግናውን አርበኛ ቤተሰቦች ንብረት ያወደመ ሲሆን፣ ዛሬ ደግሞ ንፁሃን እናቱንና መላው ቤተሰቡን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛል። ይህ የእስራትና የማንገላታት እርምጃ የአገዛዙን ተሸናፊነት የሚያሳይ እንጂ ትግሉ ላይ የሚያመጣው ምንም ዓይነት የውጤት ለውጥ እንደሌለ ይታወቃል። ​ጀግናው አርበኛ ኢንጂነር ዘበነ በላይነህ በአገዛዙ እየተፈጸመ ባለው በዚህ እኩይ ተግባር ምክንያት ይበልጥ የሚጠነክር እንጂ የሚዝል ክንድ እንደሌለውና ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ​በዚህ ግፍና በደል ሰለባ የሆኑትና በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር ውለው የሚገኙት የቤተሰቡ አባላት ዝርዝር የሚከተለው ነው፦ ▸እናት፦ ወይዘሮ ይማልዱ ሸዋን ታምሬ ▸ ​ወንድም፦ ምንዳ በላይነህ ▸ ​ወንድም፦ ሽመልስ በላይነህ ▸ ​አጎት፦ አቶ ሙላቱ በቀለ ​በአገዛዙ አማካኝነት በንፁሃን ዜጎችና በቤተሰብ አባላት ላይ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈፀም ይህ ዓይነቱ ግፍና ማንገላታት፣ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ከመቀስቀሱም በላይ የትግል ወኔን ይበልጥ እያጠናከረው እንደሚገኝ ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ምንጭ፦በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content

ጥብቅ መረጃ እናድርሳቹሁ‼✍ ይኸ መረጃ ከቀኘዎች የመጣ ነው አጠቃላይ አማራ ያለ አድማ ብተና ፖሊስና ሚኒሻ ወደ አንድ ማዕከል ማለትም ወደ መከላከያ ግዴታ ይገባሉ የሚል ቀጭን ትዕዛዝ ወርዱ ቅደሚያ ፖሊስ ላይ ይጀመር ተብሎ እንቅስቃሴ ጀምረዋል በአንድ ጣቢያ 20 ፖሊስ ወደ መከላከያ ይገባል ። ባህርዳር ያሉ የፖሊስ አባሎች ከፍተኛ ቅሬታ አቅርበዋል ቅሬታው 220ሺህ የቦታ ከፍለን የትም አንሔድም የሚል ነው ወደሽ ከተደፋሽ ቢረግጦሽ አይክፋሽ እነ ሆዱ ተጨማሪ ዝርዝር ስላለ በእኛ በኩል መጣን

አዲስ መረጃ!  አባት አርበኞች እና የፋኖ አመራሮች ወሳኝ ውይይት አካሄዱ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሃቤቴ አውራጃም ለአባት አርበኞች ኃይል ስለ ፖለቲካዊ ትጥቅ ትግሉ የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና ሰጥቷል። በሌላ በኩል፣ የሁለቱ ብርጌድ (የፋሲለደስ ክላስተር አማራ አምባ ብርጌድ እና የገነት ክላስተር ሸዋ ታጠቅ ብርጌድ) አባት አርበኞችና አመራሮች በህልውና ትግሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት አድርገዋል። የአማራ ህዝብን ህልውና ለማረጋገጥና የአገዛዙን ጥቃት ለመቀልበስ የተነገሩትን ዝርዝር መረጃዎች፣ የታሳሪ ቤተሰቦችን ሁኔታ እና የአርበኛ ዘመነ ካሴን ሙሉ መልዕክት አሁን በቪዲዮ ይዘንላችሁ ቀርበናል። 👇 ሙሉ ዜናውን በቪዲዮ ለመከታተል ሊንኩን ተጭነው ዩቲዩብ ቻናላችንን ይጎብኙ፡ https://youtu.be/6aXaxxtCbE4?si=cpBxpistJiMNCDJ4 መልሕዕ ልሳን አማራ

የሁለቱ ብርጌድ አባት አርበኞችና አመራሮች በህልውና ትግሉ ላይ ውይይት አካሄዱ።       ​ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር ራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ስር የተደራጁት የፋሲለደስ ክላስተር "አማራ አንባ" ብርጌድ እና የገነት ክላስተር "ሸዋ ታጠቅ" ብርጌድ አባት አርበኛ  አባላት ጋር ትናንት በ21/2018 ዓ.ም  ጥልቅ ወሳኝ  ውይይት ተካሄደ። በዚህ ወሳኝ መድረክ ላይ የአፋብን ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ ፊትአውራሪ ባዩ አለባቸው እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ፋኖ ዳዊት ቀፀላ እና ፋኖ አለማዬሁ ውሮ በተገኙበት የሰራዊቱን የውስጥ አደረጃጀት፣ ስነ-ልቦና እና የወደፊት የትግል አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ እና ጥልቅ ውይይት በማድረግ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል። ​በተለይም በአማራ ሕዝብ ላይ በአገዛዙ ቅጥረኞች አማካኝነት ዛሬም ድረስ እየደረሰ ያለውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋትና ጥቃት ለመቀልበስ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል። ውይይቱ ጥቃቶችን በመመከትና ራስን በመከላከል ላይ ብቻ መወሰን እንደሌለበት አጽንኦት የሰጠ ሲሆን፣ አደጋውን ከመነሻው ፈልቅቆ ለማጥፋት ቆርጦ መታገል ብቸኛውና የመጨረሻው አማራጭ መሆኑን በመስማማት የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። ​📌 ከፍተኛ አመራሮቹ ለሰራዊቱ ባደረጉት ንግግርና በሰጡት ማብራሪያ ፦ ▸ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ ግፎች፣ መፈናቀሎችና ጥቃቶች የአገዛዙ ስልታዊ እቅዶች አካል በመሆናቸው፣ ትግሉ ጥቃትን ከመከላከል ባለፈ የጥቃቱን ምንጭ ከመነሻው ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ የሚያስችል ጠንካራ ስራዎች ላይ ማተኮር አለበት። ▸ አገዛዙ ሃይማኖት፣ ፆታ እና ዕድሜ ሳይለይ አማራነት እንደ አንድ መጥፊያ ቀይ ካርድ ሆኖ በሕዝቡ ላይ  ጥቃት እያደረሰ ባለበት በአሁኑ ወቅት  መዘናጋትና መተኛት በፍጹም ሊኖር እንደማይገባ ተገልጿል። ▸በአሁኑ ሰዓት ያለው አገዛዝ ሕዝባዊ ቅቡልነትን ሙሉ በሙሉ ያጣ መሆኑንና "እንደቆሰለ ጅብ" በውስጣዊ የመበላላት ሂደት ውስጥ እንደሚገኝ በመረዳት ከትናንቱ ይልቅ ዛሬ በሁሉም መንገድ መተባበር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። ▸ በትግሉ ሂደት ውስጥ የጠላትን አጀንዳ ተሸክመው የውስጥ አንድነትን የሚያናጉና የሚያደፈርሱ "ከፉፉይ" አካላት ካሉ ለይቶ የማጥራት ሥራ በተደራጀ መልኩ በአስቸኳይ መሥራት ይገባል። ▸ በአሁኑ ዘመን በአማራ ሕዝብ ላይ ከፊት ለፊትም ሆነ በስውር በርካታ ዘመቻዎች ቢከፈቱም ሕዝቡ በፈተናዎች መካከል ነጥሮ የወጣ ጠንካራና ወጥ የሆነ አታጋይ መሪ ድርጅት ስላለው ያሸንፋል፣ ለዚህም በሁሉም መስክ መታገል ነገ በነፃነት የምንኖርባትን ሀገርና መንግስ መፍጠሪያ መንገድ በመሆኑ ህዝባችን በሚችለው ሁሉ ሊታገል ይገባል።ያሉ ሲሆን:- ​💬የሁለቱ ብርጌድ አባላት በበኩላቸው በትግሉ መዋቅር ውስጥ የታየውን መሻሻልና የወደፊት ዝግጁነታቸውን በታላቅ ቁጭትና ወታደራዊ ወኔ ሲገልጹ፦ትናንት የነበረብን የልጆቻችን የአንድነት ስጋት ዛሬ ሙሉ በሙሉ በመሪዎቻችን ብልሀት ተወግዷል። አሁን ላይ በበቂ ሁኔታ ወኔም ትጥቅም ታጥቀናል፣ ተደራጅተናል፣ እንዲሁም ሰልጥነናል። ድርጅታችን የሚያዘንን ማንኛውንም ትዕዛዝ በመቀበል እራሳችንን ከሞት፣ ታሪካችንን ደግሞ ከጥፋት ለመታደግ ዝግጁ ነን ብለዋል። ​አባላቱ አክለውም ያለፉትን መዋቅራዊ በደሎችና ግፎች የሚያስታውስ እና ከትናንት እስከዛሬ በአሩሲ፣ በደራና አካባቢው (በመላው አማራ ምድር) የተፈፀመውን እና አሁንም እየተፈፀመ ያለውን ጭፍጨፋ የሚገነዘብ ማንኛውም አማራ ትግሉን ከመደገፍ ውጭ አማራጭ እንደሌለውና ይህንን ታሪካዊ እውነታ የሚረሳ ካለ እርሱ ከወገን ሊቆጠር እንደማይገባው በቁርጠኝነት አስታውቀዋል።      ክብር ለትግሉ ሰማዕታት      ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን     ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

photo content
+3

ዘመነ ካሴን የሚጠላ የብአዴን ቅጥረኛ ብቻ ነው 💪🥷‼✍

“ለግብፅ መላላክን፥ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ መሽቆጥቆጥን፥ ለህወሃት መንበርከክን አብይና ቡድኑ እንጅ እኛ አያውቀውም።” የኔ እና የ80 ሚሊዮን አማራ ፕሬዚዳንት ክቡር አርበኛ ዘመነ ካሴ!

photo content

ከታች ምን ይላል 👇👇👇 ከኢትዮጵያዊያን ሃይሎች ጋር የጋራ መርፌ የመግዛት ተልዕኮ ቢኖረን እንኳ የአማራ ህዝብ በይፋ ሳያውቀው የምንጓዘው አንድም ስውር እርምጃ የለም። አርበኛ ዘመነ ካሴ💪💪🥷‼✍ የአፋብን ሊቀመንበር

አንዳንድ ነገሮች‼️ አለም ፊቱን ዞሮበት፥ ወይንም እንደፍጥርጥሩ ለእጣፋንታው ትቶት "ረስቶት" እያለ "መተን ቀብረነዋል" የተባለው የአማራ ህዝብ "መቃብር" ፈንቅሎ ብድግ አለ። ያለ አንዳች መካሪና ተቆርቋሪ፥ ያለ አንድ ሰው ሃሳብ አበዳሪ ከመከራው ተምሮ፥ ከራሱ መክሮ አማራ የራሱን አቢዮት ራሱ ፈጠረ።ሲነሳ በደነገጡት ጠላቶቹ ፊት ራሱን በፍጥነት አደራጅቶ የህልውና ትግሉን ጀመረ።እፍኝ የማትሞላ ተተኳሽ በመቶ ሽዎች ብር እየገዛ፥ ታጣቂም አስታጣቂም ራሱ ሆኖ ወደ ራሱ ግብ መገስገስ ቀጠለ። እነሆ ሶስት አመት አለፈው። ትልቁ ብሄራዊ ሃብት ሰው ነው። የሁሉም ነገር... የፖለቲካውም፥ የታንኩም፥የዲፕሎማሲውም ፥ የርእዮተ አለሙም ግርግር ማእከሉ፥ መቋጫው ሰው ነው። ለሰው ልጆች የተሻለ ነገር ለማምጣት የሚደረግ ነው። የራሱን ህዝብ በሰማይም በምድርም እሳት አሰማርቶ የሚያነድ ዘረፈጅ ሥርዐት ስለ ብሄራዊ ክብርና ሉአላዊነት የት ያውቃል? ስለ ሃገር ለማውራት ሞራሉስ ከየት ይገኛል?አንገቷ ላይ ቆሞ እያነደዳት ያለችን ሃገር እወዳታለሁ ሊለን ይሞክራል። የጥፋት ተልእኮ ይዞ ሃገር እያቃጠለ ሳያፍር ሌላውን ሃይል በተላላኪነት ሊከስ ይዳዳዋል። ለግብፅ መላላክን፥ ለፕሬዝዝዳንት ኢሳያስ መሽቆጥቆጥን፥ ለህወሃት መንበርከክን አብይና ቡድኑ እንጅ ፋኖ አያውቀውም። በኛ በኩል የአለም ጥቅሞች ሁሉ ተሰልፈው ቢመጡ፥ መዳፋችን ላይ ቢቀመጡ አንዲት ግራም የአማራን ህዝብ ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም። የአማራ ህዝብ ህልውና፥ ጥቅሙና ምኞቱ ለድርድር አይቀርቡም፥ "ቅዱስ" ናቸው። ቅዱሱን የሚነካም የሚያስነካም ማንም የለም።ነገር ግን ካለፉት ረጅም አመታትም ፥ከራሱ ከብልፅግና ስህተትና ውደቅትም ተምረን ከቀጠናዊና አለምአቀፋዊ ልውጥውጡ የማንም ወኪል ሳይሆኑ መጠቀምን እናውቅበታለን።በሊማሊሞ ገደል አናት በተወጠረ ገመድ ላይ አይናችን ታስረን እንኳን አመጣጥነን መራመድ እና ወደ ነገ መሻገር እንችላለን። ይህ መከራ ከእድሜው በላይ ያስተማረው ትግል ነው። ስለሆነም በፍፁም አንሳሳትም። ከኢትዮጲያውያን ሃይሎች ጋር በጋራ መርፌ የመግዛት ተልእኮ እንኳን ቢኖረን የአማራ ህዝብ በይፋ ሳያውቀው የምንጓዘው አንድም እንኳን ስውር እርምጃ የለም። ጠላት ግን ይጮሃል። "ይህን ውሃ ምን ያስጮኸዋል ቢሉት፥ በውስጡ ያለው ድንጋይ" ብሎ መለሰለት አሉ። በዚህ ወቅት ብልፅግና የተባለ የኩሬ ቦይን የሚያስጮሁት "ድንጋዮች" ሁለት ናቸው፦ 1)ፍርሃት። አብይ የቀጠናውና የሃገር ውስጥ ሃይሎች ከተባበሩ እድሜዬ በአንድ እጄ እጣቶች ልክ የተቆጠሩ ናቼው ብሎ ስለሚያምን ደንግጧል። እናም ድንገት ጥቂቶችን አደናግሬ የማምሻ እድሜ ባገኝ ብሎ ሌት ተቀን ይጮሃል።ከሞት የማያድን ጩኸት። 2)ጦርነት። በአብይ አህመድ ስሌት የአማራ፥ የትግራይ፥ የአፋርና ሌሎች ህዝቦች ገና በበቂ አልደቀቁም። ስለዚህ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ መድቀቅና መጥፋት አለባቼው። ይህ ይሆን ዘንድ ግን "ሰበብ " ያስፈልጋል። ስለሆነም አቅም አግኝቶ ነገ ወደ አንድ ተረኛ ህዝብ ቢተኩስ ለአለሙ የሚነግረው ሰበብ "ተባብረው ሊያጠፉኝ ሲሉ ራሴን ለመከላከል ጦርነት ከፈትሁ" ይሆናል ማለት ነው። ይኸው ነው። ይህ ትግል የአማራንና የሃገራችን ህልውናን የማረጋገጥ ትንቅንቅ ብቻ አይደለም፥ ቢያንስ ለሚቀጥሉት አምስት መቶ አመታት የጥይት ድምፅ የማይሰማ ትውልድ የመፍጠር ተልእኮም ነው። ብልፅግና ይወገዳል፥የአማራ ህልውና ይረጋገጣል። ኢትዮጲያ ለኢትዮጲያውያን የፍቅርና የደስታ ምድር ትሆናለች፥ ሰላም ትሆናለች። ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም! አዲስ ትውልድ ፥አዲስ አስተሳሰብ፥አዲስ ተስፋ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሰኔ-21/2018 ዓ. ም! አርበኛ ዘመነ ካሴ!

photo content
+1

የወቅቱን ትኩስ እና አጓጊ መረጃዎች ይዘንላችሁ ቀርበናል! በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰቱ ዋና ዋና ሁነቶችን በአጭሩ እና በማራኪ አቀራረብ እነሆ፡  የፋኖ ድንቅ ጀብዱ በአቡዬ ሜዳ የተራሮች ሁሉ ንጉስ በሆነው አቡዬ ሜዳ (እስቴጎማ ተራራ) ላይ የፋኖ ክፍለ ጦር አስደናቂ ጀብዱ ፈጽሟል! በደጋዳሞት ወረዳ ለተከታታይ ቀናት ሲደረግ የነበረው ትንቅንቅ በድል መጠናቀቁ ሲታወቅ፣ በሌላ በኩል ደግሞ በቡግና ወረዳ አይና ማርያም ከተማ በተካሄደ የኦፕሬሽን እርምጃ የ19ኛ ክፍለ ጦር በርካታ የአገዛዙን ሰራዊት አባላት እስከነ መሪያቸው ደምስሷል።  የአውሮፓ ህብረት እና አሜሪካ ስጋት የአውሮፓ ህብረት በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ወቅታዊ ውጥረት ላይ ያለውን ከፍተኛ ስጋት ገልጿል። ህብረቱ እና የአሜሪካ መንግስት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ መልኩ እንዲተገበርና ወገኖች ሁሉ ወደ ውይይት እንዲመለሱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።  የእስራኤል እና ሊባኖስ "ታሪካዊ ስምምነት" የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ከሊባኖስ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት ማዕቀፍ "ታሪካዊ ስኬት" ሲሉ አሞካሽተውታል። ይህ ስምምነት ለቀጠናው ሰላም አዲስ በር ይከፍታል ተብሏል።
 ሙሉውንና ዝርዝር መረጃውን ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን ሰብስክራይብ (Subscribe) በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! ቪዲዮውን ላይክ እና ሼር ማድረግ እንዳይረሱ!
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን! ?
? https://youtu.be/g-CAc7p3ylI?si=BJCRkKCbbsN-Z90K

የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፊያለው ደሴ ኮር አንበሳው ጋይንት ክ/ ጦር አስቻለው ደሴ ብርጌድ አዲስ ምልምል ኮማንዶ ሰልጣኞችን አስመረቀ! በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ የ206ኛ ከፊያለው ደሴ ኮር አመራሮች እና በስሩ ያሉ የክፍለጦር አመራሮች ጥሪ የተደረገላቸው የሃይማኖት አባቶች የሃገር ሽማግሌዎች ነገላ ከተማ በመገኘት አስመርቀዋል። በፕሮግራሙ ላይ የተጋበዙ የኮሩም የክ/ጦሩም መሪወች ተመራቂዎችን የእንኳን ደስ ያላችሁ መልክት የአስተላለፉ ሲሆን በፕሮግራሙ ተመራቂዎቹ የተለያዩ ወታደራዊ ትሪቶችን ያደረጉ ሲሆን ብርጌዱ ለተለያዩ መሪዎች ቀደም የተሰው መሪዎችን ፎቶ ስጦታ አበርክቶላቸዋል። በመጨረሻም ለአሰልጣኙ ማስተር ብሬ የአንበሳው ጋይንት ክ/ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ አስጊዶም ውበት አንድ እግር ታጣፊ ክላሽ በሽልማት አበርክቶለታል። የአፋብን ጎጠግ በላይ ዕዝ 206ኛ ከፊያለሁ ደሴ ኮር የአንበሳው ጋይንት ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

photo content
+5

የወቅቱን ትኩስ እና አጓጊ መረጃዎች ይዘንላችሁ ቀርበናል! በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰቱ ዋና ዋና ሁነቶችን በአጭሩ እና በማራኪ አቀራረብ እነሆ፡  የፋኖ ድንቅ ጀብዱ በአቡዬ ሜዳ የተራሮች ሁሉ ንጉስ በሆነው አቡዬ ሜዳ (እስቴጎማ ተራራ) ላይ የፋኖ ክፍለ ጦር አስደናቂ ጀብዱ ፈጽሟል! በደጋዳሞት ወረዳ ለተከታታይ ቀናት ሲደረግ የነበረው ትንቅንቅ በድል መጠናቀቁ ሲታወቅ፣ በሌላ በኩል ደግሞ በቡግና ወረዳ አይና ማርያም ከተማ በተካሄደ የኦፕሬሽን እርምጃ የ19ኛ ክፍለ ጦር በርካታ የአገዛዙን ሰራዊት አባላት እስከነ መሪያቸው ደምስሷል።  የአውሮፓ ህብረት እና አሜሪካ ስጋት የአውሮፓ ህብረት በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ወቅታዊ ውጥረት ላይ ያለውን ከፍተኛ ስጋት ገልጿል። ህብረቱ እና የአሜሪካ መንግስት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ መልኩ እንዲተገበርና ወገኖች ሁሉ ወደ ውይይት እንዲመለሱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።  የእስራኤል እና ሊባኖስ "ታሪካዊ ስምምነት" የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ከሊባኖስ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት ማዕቀፍ "ታሪካዊ ስኬት" ሲሉ አሞካሽተውታል። ይህ ስምምነት ለቀጠናው ሰላም አዲስ በር ይከፍታል ተብሏል።
 ሙሉውንና ዝርዝር መረጃውን ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን ሰብስክራይብ (Subscribe) በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! ቪዲዮውን ላይክ እና ሼር ማድረግ እንዳይረሱ!
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን! ?
? https://youtu.be/g-CAc7p3ylI?si=BJCRkKCbbsN-Z90K