2 772
Subscribers
-124 hours
+387 days
+12930 days
Posts Archive
04/01/2019
ለውድ ወላጆች አሳዳጊዎች
ዛሬ መስከረም 4 ሰኞ እና ነገ መስከረም 5 ማክሰኞ የትምህርት ጊዜያቸው ግማሽ ቀን መሆኑን እየገለፅን 6:30 ላይ ልጆቻችሁን መውሰድ ትችላላችሁ
ከ መስከረም 6 እረቡ ጀምሮ ግን ሙሉ ቀን መሆኑን እናሳስባለን፡፡
ት/ቤቱ
04/01/2019
ለውድ ወላጆች አሳዳጊዎች
ዛሬ መስከረም 4 ሰኞ እና ነገ መስከረም 5 ማክሰኞ የትምህርት ጊዜያቸው ግማሽ ቀን መሆኑን እየገለፅን
ከ መስከረም 6 እረቡ ጀምሮ ግን ሙሉ ቀን መሆኑን እናሳስባለን፡፡
ት/ቤቱ
ለልደታ ማርያም ልጃገረዶች ትምህርት ቤት ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ !!!
ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 04/01/2019 ዓ.ም (ሰኞ) መሆኑን እያሳወቅን📅፣ በዕለቱ ከወረዳ፣ ከክፍለ ከተማ እና ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የተዋቀሩ የሱፐርቪዥን ቡድኖች ልዩ ክትትል ስለሚያደርጉ 👀 "First Day - First Class ትምህርት ስለሚጀምር በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እንገልጻለን📚።በተጨማሪም የተማሪዎችን ስነ-ተግሣጽ ወይም የስነ ምግባር ደንቦችን አንድታውቁ ከወዲሁ እናሳውቃለን📢። የስነምግባር ደንቦች
ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ሥነ ምግባር ለመቆጣጠር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ Nov 20, 2025 3 min read ህዳር 11 2018 📄
ሴት ተማሪዎች የጥፍር ፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም መቀባት፣ ቅንድብ መቀንደብና መኳኳል፣ አላስፈላጊ ጌጣ ጌጦችን አድርጎ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ የሚከለክል መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጀ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ሥነ ምግባር ለመቆጣጠር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ማንኛውም ተማሪዎች ከተፈጥሮ ጸጉራቸው በስተቀር አርቴፊሻል ፀጉር መቀጠል አይችሉም ተብሏል፡፡ ከዚህ ባለፈም በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ በዓላት በተለይም እንደ ክሬዚ ዴይ፣ ኦልድ ዴይ፣ ቤቢ ዴይ፣ ቶማቶ ዴይ፣ ከለር ዴይ፣ ቫላንታይን ዴይ እና ሌሎችም የበዓል ቀናቶች ተብለው የሚከበሩ በዓላት ማክበር በመመሪያው ተከልክሏል🚫፡፡
በትምህርት ቤት የደንብ ልብስ በተገቢ መንገድ መልሰብ ሲል ባወጣው መመሪያ ስር ሴቶች ጉርድ ቀሚስ ከባት በታች የሆነ ቁመት ያለው ለብሶ መገኘት አለባቸው ተብሏል፡፡
ከደንብ ልብስ ውጪ ቢሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን አለባበስ መልበስ ይጠበቅባቸዋል ይላል ረቂቅ መመሪያው፡፡
ትምህርት ቤት ውስጥ መፈፀም የተከለከሉ ድርጊቶች ብሎ ከዘረዘራቸው መካከል ደግሞ የትምህርት ቤቱን መምህራን፣ የትምህርት አመራር፣ ሠራተኞችና ሌሎች የትምህርት ማህበረሰብ አካላትን መዝለፍ፣ መስደብ፣ ማንቋሸሽና አካላዊ ጥቃት መፈጸም ቅጣት የሚያስከትል ተግባር ነው ተብሏል፡፡
ተንቀሳቃሽ ስልክ 📲 ወይም ሞባይል እና የሙዚቃ ማዳመጫ 🎧 መሣሪያዎችን ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይዞ መገኘት ረቂቅ መመሪያው ከልክሏል።🚫
በቃል፣ በምልክትም ሆነ በጽሑፍ ፀያፍ ነገሮችን መግለፅ፤ ጨዋነት የጎደላቸውን እንዲሁም ሐይማኖታዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ምስሎችና ጽሑፎች በትምህርት ቤት ውስጥ ይዞ መገኘትና ማሰራጨት አይፈቀድም፡፡
በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ የማንኛውንም ዓይነት የኃይማኖት አምልኮ ሥርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማካሄድ ይከለክላል፡፡
ማንኛውም ተማሪ አገራዊ እሴት ያልሆኑና መጤ የሆኑ ነገሮችን በሰውነት ላይ ምልክት ማድረግ፤ ከአገራዊ እሴት ጋር የሚቃረኑ አሉታዊ መጤ ምልክቶችን በሰውነት ላይ መነቀስ፣ ማሳየት፣ ማድረግ፣ መጠቀም ፍፁም የተከለከለ ነው ብሏል ረቂቅ መመሪያው፡፡
ከ9 እስከ 12ተኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች አንድ ተማሪ በሥነ-ምግባር ጉድለት እጅ ከፍንጅ ከተያዘና የመማር ማስተማሩን ሂደት የሚያውክ ሆኖ ከተገኘ ውሳኔ እስኪሰጠው ከትምህርት ቤት ሊታገድ እንደሚችልም በመመሪያው ሰፍሯል፡፡
ተማሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት አጥፍተው ሲገኙ በተለይም ከ7 እስከ 12ተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች እስከ 1 ዓመት ድረስ እንደ ጥፋቱ መጠን ታይቶ ከትምህርት ሊታገዱ ይችላልም ሲል ረቂቅ መመርያው አስቀምጧልከሰላምታ ጋር🙏፣ የትምህርት ቤቱ ሃላፊ ሲስተር ሺና
Repost from NGCS PARENTS GRADE 1-8
የልደታ ማርያም ልጃገረዶች ትምህርት ቤት ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 04/01/2019 ዓ.ም (ሰኞ) መሆኑን እያሳወቅን፣ በዕለቱ ከወረዳ፣ ከክፍለ ከተማ እና ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የተዋቀሩ የሱፐርቪዥን ቡድኖች ልዩ ክትትል ስለሚያደርጉ "First Day - First Class ትምህርት ስለሚጀምር በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እንገልጻለን።በተጨማሪም የተማሪዎችን ስነ-ተግሣጽ ወይም የስነ ምግባር ደንቦችን አንድታውቁ ከወዲሁ እናሳውቃለን።
የስነምግባር ደንቦች
ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ሥነ ምግባር ለመቆጣጠር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያNov 20, 20253 min readህዳር 11 2018
ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም መቀባት፣ ቅንድብ መቀንደብና መኳኳል፣ አላስፈላጊ ጌጣ ጌጦችን አድርጎ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ የሚከለክል መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጀ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ሥነ ምግባር ለመቆጣጠር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ማንኛውም ተማሪዎች ከተፈጥሮ ጸጉራቸው በስተቀር አርቴፊሻል ፀጉር መቀጠል አይችሉም ተብሏል፡፡
ከዚህ ባለፈም በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ በዓላት በተለይም እንደ ክሬዚ ዴይ፣ ኦልድ ዴይ፣ ቤቢ ዴይ፣ ቶማቶ ዴይ፣ ከለር ዴይ፣ ቫላንታይን ዴይ እና ሌሎችም የበዓል ቀናቶች ተብለው የሚከበሩ በዓላት ማክበር በመመሪያው ተከልክሏል፡፡
በትምህርት ቤት የደንብ ልብስ በተገቢ መንገድ መልሰብ ሲል ባወጣው መመሪያ ስር ሴቶች ጉርድ ቀሚስ ከባት በታች የሆነ ቁመት ያለው ለብሶ መገኘት አለባቸው ተብሏል፡፡
ከደንብ ልብስ ውጪ ቢሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን አለባበስ መልበስ ይጠበቅባቸዋል ይላል ረቂቅ መመሪያው፡፡
ትምህርት ቤት ውስጥ መፈፀም የተከለከሉ ድርጊቶች ብሎ ከዘረዘራቸው መካከል ደግሞ የትምህርት ቤቱን መምህራን፣ የትምህርት አመራር፣ ሠራተኞችና ሌሎች የትምህርት ማህበረሰብ አካላትን መዝለፍ፣ መስደብ፣ ማንቋሸሽና አካላዊ ጥቃት መፈጸም ቅጣት የሚያስከትል ተግባር ነው ተብሏል፡፡
ተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም ሞባይል እና የሙዚቃ ማዳመጫ መሣሪያዎችን ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይዞ መገኘት ረቂቅ መመሪያው ከልክሏል፡፡በቃል፣ በምልክትም ሆነ በጽሑፍ ፀያፍ ነገሮችን መግለፅ፤ ጨዋነት የጎደላቸውን እንዲሁም ሐይማኖታዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ምስሎችና ጽሑፎች በትምህርት ቤት ውስጥ ይዞ መገኘትና ማሰራጨት አይፈቀድም፡፡
በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ የማንኛውንም ዓይነት የኃይማኖት አምልኮ ሥርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማካሄድ ይከለክላል፡፡
ማንኛውም ተማሪ አገራዊ እሴት ያልሆኑና መጤ የሆኑ ነገሮችን በሰውነት ላይ ምልክት ማድረግ፤ ከአገራዊ እሴት ጋር የሚቃረኑ አሉታዊ መጤ ምልክቶችን በሰውነት ላይ መነቀስ፣ ማሳየት፣ ማድረግ፣ መጠቀም ፍፁም የተከለከለ ነው ብሏል ረቂቅ መመሪያው፡፡
ከ9 እስከ 12ተኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች አንድ ተማሪ በሥነ-ምግባር ጉድለት እጅ ከፍንጅ ከተያዘና የመማር ማስተማሩን ሂደት የሚያውክ ሆኖ ከተገኘ ውሳኔ እስኪሰጠው ከትምህርት ቤት ሊታገድ እንደሚችልም በመመሪያው ሰፍሯል፡፡
ተማሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት አጥፍተው ሲገኙ በተለይም ከ7 እስከ 12ተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች እስከ 1 ዓመት ድረስ እንደ ጥፋቱ መጠን ታይቶ ከትምህርት ሊታገዱ ይችላልም ሲል ረቂቅ መመርያው አስቀምጧል
ከሰላምታ ጋር፣
የትምህርት ቤቱ ሃላፊ ሲስተር ሺና
ውድ ተማሪዎች እና ወላጆች፣
👕 የዩኒፎርም ማልበሻ መርሃግብር፦
· ሰኞ፣ ማክሰኞ እና ረቡዕ — ሹራብ ሸሚዝ ከጉርድ ጋር
· ሐሙስ እና አርብ — ቲሸርት፣ ሹራብ እና ጉርድ
⚠️ ተማሪዎች ሁሉም ደንቦቹን በደንብ እንዲያውቁ እና እንዲከተሉ፣ ወላጆችም ልጆቻቸውን በደንብ እንዲከታተሉ በአጽንዖት እናሳስባለን።
ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን።
ትምህርት ቤቱ
4/13/2018
ለውድ ወላጆች አሳዳጊዎች በሙሉ
በመጀመሪያ ለ2019 ዓ.ም በሰላም እንኳን አደረሳችሁ እያለን የመጪው ዓመት የሰላም የደስታ እንዲሆንላችሁ እየተመኘን ከዛሬ ጰጉሜ 4 ከ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ እሁድ መስከረም 3 2019 ድረሰ ት/ቤቱ ዝግ ይሆናል፡፡
ሰኞ መስከረም 4 2019ዓ.ም መደበኛ ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እየገለፅን ለግማሽቀን ትምህርት ብቻ ሲሆን ከማክሰኞ ጀምሮ መደበኛ ሙሉ ቀን ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እናሳስባለን ፡፡
ት/ቤቱ
ቅዳሜ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በድጋሚ የተሠጠ አስቸኳይ ማሣሠቢያ በመጪው አዲስ ዓመት 2019ዓ.ም ልጆቻችሁን የ 12 ኛ ክፍል (የ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና(ማትሪክ) ለምታስፈትኑ ወላጆች እንዲሁም አሳዳጊዎች በሙሉ።
በዚህ እያገባደድን ባለው 2018ዓ.ም ጀምሮ ከትምህርት ሚኒስቴር በተዋረድም ከ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች በወረደው መመሪያ መሠረት 12ኛ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ የሚመጡ ተመዝጋቢ ተማሪዎች በሙሉ የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ስለተደነገገ እስከ አሁን ፋይዳ መታወቂያ ያላወጣችሁ ትምህርት ቤት ሳይከፈት በዚህ በቀረው ጊዜ ለልጆቻችሁ ፋይዳ መታወቂያ አውጥታችሁ ዝግጁ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እያሳሰብን ትምህርት ቤቱ በሚከፈትበት ጊዜ ፎቶ ኮፒውን ከየክፍላቸው እየዞርን የምንሰበስብ መሆኑን እየገለፅን በ ፋይዳ መታወቂያው ላይ የሚሰፍሩት የልጆቻችሁ መረጃዎች
ስም፣የአባት ስም፣ የአያት ስም (ስፔሊንግ)
የትውልድ ዘመን፣ፃታ ወ.ዘ.ተ በትክክል መስፈራቸውን አረጋግጣችሁ እንድትቀበሉ እናሳስባለን። ከዚህ በተጨማሪ የ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመፈተን የ 8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት እና ከ 9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የነበራችሁን አጠቃላይ የትምህርት አቀባበላችሁን የሚያሳይ ትራንስክሪፕት ማቅረብ ስላለባችሁ በተለይ ከሌላ ትምህርት ቤት ወደ ልደታ ማርያም ልጃገረዶች ትምህርት የመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ ከላይ የተጠየቁትን የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ከነበራችሁበት ትምህርት ቤት ተቀብላችሁ ለቢሮ ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን ። ይህ የ2019 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በምንጀምርበት ጊዜ ከተመዝጋቢ ተማሪዎች መረጃ አለመሟላት ጋር በተያያዘ ከሚገጥሙን ችግሮች እንደሚያላቅቀን በማሰብ ስለሆነ ይህንን ዛሬ ነገ ሳትሉ ተግባራዊ እንድታደርጉ አበክረን እናሳስባለን ።
ትምህርት ቤቱ
ማስታወቂያ 📢
የ 2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
Ø የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን። 📝
Ø ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ ⚠️፡-
v የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር 🏛️
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል።
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፣ የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና በብቃት የሚያልፉ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድሉ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የ Presidential Scholarship Program ዕድሉ ተጠቃሚዎች፣ ዩኒቨርሲቲው ባሉት ሰባት ኮሌጆች እና የሕግ ትምህርት ቤት ስር ባሉ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ይመደባሉ።
ነጻ የትምህርት ዕድሉ ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ ድጋፍና የስልጠና ዕድሎችን ያስገኛል፡፡
በዚህ የትምህርት ዕድል በወጥነት ተጠቃሚ ለመሆን፣ የዕድሉ ተጠቃሚዎች በየሴሚስተሩ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም የዕድሉ ተጠቃሚዎች በተመደቡበት የትምህርት ዘርፍ መቀጠል ይኖርባቸዋል።
የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች በቀጣይነት ዩኒቨርሲቲው የድኅረ-ምረቃ (Masters እና PhD) የትምህርት ዕድል ያገኛሉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 👇
https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements
@tikvahuniversity
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል።
ውጤት ለማየት ፦
👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
