አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE
#የኅብርቱዋናዓላማ ፩.መንፈሳዊ መጻሕፍትን በዓላማ፤በእቅድ እንድናነባቸው፤እንድናስነብባቸው በሕይወታችን ትርጉም እንዲኖራቸው ማድረግ። ፪.ከቤተሰቦቻችን፤ዘመዶቻችን፤ወዳጆቻችን ስላነበብናቸው መጻሕፍት እነሱም ስላነበቡት መጻሕፍት ውይይት የማድረግ ልምድን ማዳበር። ፫.አንባቢ ትውልድ መፍጠር። ለአስተያየትዎ @orthokiha ይጻፉ። https://t.me/BetMetsahfte Cross @dawitfikr
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE
Channel አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE (@betmetsahfte) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 17 861 subscribers, ranking 1 998 in the Books category and 1 934 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 17 861 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -116 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.33% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 3 773 views. Within the first day, a publication typically gains 1 489 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 28.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“#የኅብርቱዋናዓላማ
፩.መንፈሳዊ መጻሕፍትን በዓላማ፤በእቅድ እንድናነባቸው፤እንድናስነብባቸው በሕይወታችን ትርጉም እንዲኖራቸው ማድረግ።
፪.ከቤተሰቦቻችን፤ዘመዶቻችን፤ወዳጆቻችን ስላነበብናቸው መጻሕፍት እነሱም ስላነበቡት መጻሕፍት ውይይት የማድረግ ልምድን ማዳበር።
፫.አንባቢ ትውልድ መፍጠር። ለአስተያየትዎ @orthokiha ይጻፉ።
https://t.me/BetMetsahfte
Cross @dawit...”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Books category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | +1 | |||
| 05 September | +1 | |||
| 04 September | +1 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
| 2 | #ፍኖት_መንፈሳዊት እና #የትዳር_ወግ
#አሳታሚና_አከፋፋይ
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0925421700_ይውሰዱ! | 2 212 |
| 3 | በእግዚአብሔር ቸርነት ክርስቲያን ነኝ፤ በምግባሬ ግን ታላቅ ኀጢአተኛ፤ አጠራሬም ቤት አልባና የትሕትናን ምንጭ በመፈለግ ላይ ያለ ከርታታ፤ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወር የሚል ነው። ንብረቶቼ በጀርባዬ ያዘልሁት ደረቅ ዳቦ ያለው የከረጢት ቦርሳና በእቅፌ የያዝሁት መጽሐፍ ቅዱስ ናቸው፤ ይኸው ነው ያለኝ።
ከበዓለ ኀምሳ በኋላ በኻያ አራተኛው እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን በቅዳሴ ላይ ለመሳተፍ ኼድሁና ልክ [የቅዱስ ጳውሎስ] መልእክት እየተነበበ ሳለ ገባሁ። ንባቡ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች ከላከው የመጀመሪያ መልእክት የተወሰደ ሲሆን፥ ይህም “ሳታቋርጡ ጸልዩ” ይላል።
እነዚህም ቃላት በእኔ ላይ ጥልቅ ስሜት ፈጠሩብኝና እንዲህ ስል ዐሰብሁ፤ “አንድ ሰው ለሕይወት የሚያስፈልጉትን ነገሮች በመፈለግ ብዙውን ትኩረቱን በሚይዝበት በዚህ ዓለም ሳያቋርጥ እንዴት መጸለይ ይቻለዋል?” መጽሐፍ ቅዱሴን ከፍቼ ያለማቋረጥ መጸለይ እንዳለብን [፩ተሰ.፭፥፲፯] በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በመንፈስ መጸለይ አስፈላጊ እንደሆነ [ኤፌ.፮፥፲፰]፤ በሁሉም ቦታ በጸሎት እጅን በክብር ማንሣት እንደሚገባ [፩ጢሞ.፪፥፰] የሰማሁትን በገዛ ዐይኖቼ በትክክል ዐየሁ። ስለነዚህ ቃላት ደጋግሜ ተማርሁ፤ዐስብም ነበር፤ ነገር ግን ምንም መረዳት አልቻልሁም።
#ፍኖት_መንፈሳዊት
የሽፋን ዋጋ 550 ብር
#አሳታሚና_አከፋፋይ
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 2 533 |
| 4 | እንግዲህ ቡሩክ ጢሞቴዎስ ሆይ “አርእስተ ትምህርተ መለኮትን” ከፈጸምኩ በኋላ፥ አሁን አቅሜ በፈቀደ መጠን ወደ አስማተ መለኮት ትርጓሜ እሻገራለሁ። ኾኖም ግን፥ ልንጸናበት የሚገባን የቅዱሳት መጻሕፍት መርኅ አለ፤ ይኸውም ስለ እግዚአብሔር የኾነውን እውነት የምናጸናው በሰው ጥበብ ማባበያ ቃላት አይደለም፣ ይልቁንም በመንፈስ በተቃኘው በነገረ መለኮት መምህራን ኃይል ምስክርነት ነው።
በዚህ ኃይል ከማይገለጹ እና ከመታወቅ በላይ ከኾኑ እውነታዎችህ ጋር የማይገለጽ እና ከመታወቅ በላይ የኾነ ኅብረትን እናደርጋለን። ይኸውም ኅብረት የሚኾነው በውስጣችን ባሉ የአእምሮ እና የኅሊና ሕዋሳት በግብራቸው አንድ በኾኑበት መጠን ነው። ስለኾነም በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ እግዚአብሔር ከገለጠልን ሐሳብ በቀር ከፍጥረት ኹሉ በላይ ስለኾነውና ኅቡዕ ስለኾነው አምላክ ምንም ነገር መናገርም ኾነ ማሰብ በፍጹም አይፈቀድልንም። ስለዚህ ይህን “ልዕለ ባሕርያዊ ዕውቀት” ልንሰጠው የሚገባው ‘አግኖስያ’(አለማወቅ) ተብሎ ለሚጠራው ነው።
ሐዋርያውያን አበው ቅጽ 1 ገጽ 227 ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ በእንተ አስማተ መለኮት
#አሳታሚና_አከፋፋይ
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 2 044 |
| 5 | መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ፍቅረማርያም ባዘዘው #ለደብረ_ታቦር_4ቱ_ጉባኤ_ቤት ራሳቸው ያዘጋጁት #ሃይማኖተ_አበው 4ኮፒ ሰጥተውናል።እቅዳችን 100ኮፒ ነው 60ኮፒ ይቀረናል። 60ሰዎች ካጣን ግን አንድሰው እንዲሸፍነው እናስገድዳለን።
@orthokiha እዘዙ ከቤታችሁ ያሉትን አምጥታችሁ ስጡ።
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 2 294 |
| 6 | ለደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት መጻሕፍት ማሰባሰቡ እንደቀጠለ ነው።
ወለተ ሐና 26 መጻሕፍት ሁለት ወንድሞቻችን 4መጻሕፍት አዘውናል ወንድማችን 1 አንድ ወንድማችንም 7 መጻሕፍት ሰጥተውናል። 34 መጻሕፍት ደርሰናል።እቅዳችን መቶ ነው 66 መጻሕፍት ይቀራል አሁንም አምጡልን። ወይም @orthokiha እዘዙን። | 3 401 |
| 7 | #የትዳር_ወግ
#በትእዛዙ_ካሣ
#የገጽብዛት_316
#ዋጋ_400ብር
“ከሦስት ዓመት በፊት ዕድሜያቸው በሠላሳዎቹ ያሉ ባለጠጋ የሚባሉ ጥንዶች ለምክር ወደ እኔ ይመጣሉ፡፡ ከተጋቡ ገና ሁለት ዓመት አልሞላቸውም፡፡ ከጋብቻ በፊትም ብዙም አይተዋወቁም፡፡ ፍቅር ጠናብን ብለው በችኮላ ነው ሰርጉንም ያጣደፉት፡፡ ትዳር ጣፋጩንም መራራውንም አጣምራ የያዘች እንቆቅልሽ መሆኗንም አልተረዱትም ነበር፡፡ ጫጉላ ሽርሽሩ ሁሌም የሚቀጥል ሳይመስላቸው አልቀረም፡፡
“ሚስትም በተደጋጋሚ የምታነሣው ‘አያዳምጠኝም’ የሚል ነበር፡፡ ባል በቅሬታዋ ግራ ሳይጋባ አልቀረም፡፡ ‘ስትናገር እንኳን አቋርጫት አላውቅም፡፡ እርሷ ራሷ ምስክር ናት’ ይላል ደጋግሞ፡፡ ለካስ ነገሩ ሌላ ነው፡፡ ‘ስሜቴን አይረዳልኝም፤ ሲከፋኝ እንኳ ልብ አይለውም፡፡ ፍላጎቴን ለመረዳት ትዕግሥት የለውም፡፡ እያዋራሁት ዓይኑ ሌላ ቦታ ነው የሚያዬው፤ ጆሮው ቢሰማም ወደ ልቡ አይዘልቅም’ እያለች ሚስት ናዳውን አወረደችው፡፡
“‘እንዲያውም በሚገርም ሁኔታ ሲከፋኝ ከባለቤቴ ይልቅ ውሻችን መከፋቴን ዐውቃ ከጎኔ ተኮራምታ ትቀመጣለች፡፡ ሳለቅስ ቆይቼ ፊቴ ተለዋውጦ እርሱ ወደ ቤት ሲገባ እንኳ ምን እንደ ሆንኩ ስለማያስተውለው አይጠይቀኝም’ አለች….
“ያንጊዜ ነው ባል የባነነው፡፡ በእርግጥ አስተዋይ ሰው ነበረ፡፡ በሴትና በወንድ መካከል ያለውን የስሜትና የአረዳድ ልዩነት ለማስረዳት ስሞክር ነው ነገሩ የገባው፡፡ መፍትሔ ባይኖርህ እንኳ ሚስት ችግሯን ስትረዳላት መፍትሔ ያገኘች ያክል ይሰማታል፡፡ ሴት አዛኝ የመሆኗን ያህል ቶሎ መደሰትም ቶሎ መከፋም ያጋጥማታል፡፡ አንዳንድ ሴቶች ጠባያቸው እንደ ማዕበል ይወጣልም ይወርዳልም፡፡ ዋናው ቁም ነገሩ ማዳመጥ ማለት በሚስህ ጫማ ራስህን አድርገህ ስሜቷንም፣ ፍላጎቷንም፣ ነገሯንም በአጽንዖት መከታተልና ለብሶቷ ዕውቅና መስጠቱ ላይ ነው፡፡ ስትከፋ ስታባብላት ኀዘኗን ፈጥና ትረሳዋለች፡፡ ከማንም ይልቅ ተስፋ የምታደርገው አንተን ነውና የሚሉ ሐሳቦችን ተለዋወጥንና ተሰነባበትን” አለና ዶ/ር ኦባንግ በዝምታ ተዋጠ፡፡
የትዳር ወግ በትእዛዙ ካሣ፣ ገጽ. 177-178
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 2 948 |
| 8 | #የትዳር_ወግ
#በትእዛዙ_ካሣ
#የገጽብዛት_316
#ዋጋ_400ብር
“ከሦስት ዓመት በፊት ዕድሜያቸው በሠላሳዎቹ ያሉ ባለጠጋ የሚባሉ ጥንዶች ለምክር ወደ እኔ ይመጣሉ፡፡ ከተጋቡ ገና ሁለት ዓመት አልሞላቸውም፡፡ ከጋብቻ በፊትም ብዙም አይተዋወቁም፡፡ ፍቅር ጠናብን ብለው በችኮላ ነው ሰርጉንም ያጣደፉት፡፡ ትዳር ጣፋጩንም መራራውንም አጣምራ የያዘች እንቆቅልሽ መሆኗንም አልተረዱትም ነበር፡፡ ጫጉላ ሽርሽሩ ሁሌም የሚቀጥል ሳይመስላቸው አልቀረም፡፡
“ሚስትም በተደጋጋሚ የምታነሣው ‘አያዳምጠኝም’ የሚል ነበር፡፡ ባል በቅሬታዋ ግራ ሳይጋባ አልቀረም፡፡ ‘ስትናገር እንኳን አቋርጫት አላውቅም፡፡ እርሷ ራሷ ምስክር ናት’ ይላል ደጋግሞ፡፡ ለካስ ነገሩ ሌላ ነው፡፡ ‘ስሜቴን አይረዳልኝም፤ ሲከፋኝ እንኳ ልብ አይለውም፡፡ ፍላጎቴን ለመረዳት ትዕግሥት የለውም፡፡ እያዋራሁት ዓይኑ ሌላ ቦታ ነው የሚያዬው፤ ጆሮው ቢሰማም ወደ ልቡ አይዘልቅም’ እያለች ሚስት ናዳውን አወረደችው፡፡
“‘እንዲያውም በሚገርም ሁኔታ ሲከፋኝ ከባለቤቴ ይልቅ ውሻችን መከፋቴን ዐውቃ ከጎኔ ተኮራምታ ትቀመጣለች፡፡ ሳለቅስ ቆይቼ ፊቴ ተለዋውጦ እርሱ ወደ ቤት ሲገባ እንኳ ምን እንደ ሆንኩ ስለማያስተውለው አይጠይቀኝም’ አለች….
“ያንጊዜ ነው ባል የባነነው፡፡ በእርግጥ አስተዋይ ሰው ነበረ፡፡ በሴትና በወንድ መካከል ያለውን የስሜትና የአረዳድ ልዩነት ለማስረዳት ስሞክር ነው ነገሩ የገባው፡፡ መፍትሔ ባይኖርህ እንኳ ሚስት ችግሯን ስትረዳላት መፍትሔ ያገኘች ያክል ይሰማታል፡፡ ሴት አዛኝ የመሆኗን ያህል ቶሎ መደሰትም ቶሎ መከፋም ያጋጥማታል፡፡ አንዳንድ ሴቶች ጠባያቸው እንደ ማዕበል ይወጣልም ይወርዳልም፡፡ ዋናው ቁም ነገሩ ማዳመጥ ማለት በሚስህ ጫማ ራስህን አድርገህ ስሜቷንም፣ ፍላጎቷንም፣ ነገሯንም በአጽንዖት መከታተልና ለብሶቷ ዕውቅና መስጠቱ ላይ ነው፡፡ ስትከፋ ስታባብላት ኀዘኗን ፈጥና ትረሳዋለች፡፡ ከማንም ይልቅ ተስፋ የምታደርገው አንተን ነውና የሚሉ ሐሳቦችን ተለዋወጥንና ተሰነባበትን” አለና ዶ/ር ኦባንግ በዝምታ ተዋጠ፡፡
የትዳር ወግ በትእዛዙ ካሣ፣ ገጽ. 177-178
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 1 |
| 9 | ስለ ደራሲው
ትእዛዙ ይሁኔ ካሣ በዓለም አቀፍና በተቋማዊ የአመራር፣ የፋይናንስና የፕላኒንግ መስኮች ከሦስት አሥርት ዓመታት በላይ ያካበቱት ሰፊ ልምድ ያላቸው ደራሲና አሰልጣኝ ናቸው። የሙያ ጉዟቸው በአሜሪካ መቀመጫውን ካደረገ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ተቋም እንዲሁም ፣ በኢትዮጵያ ቀደምት በሆኑ የግል ዘርፍ ውስጥ የነበራቸውን ከፍተኛ የአመራር ሚና፣ እንዲሁም በአገሪቱ ትልቁ ባንክ ተግባራዊ የሥራ ልምዶች ያቀናጀ ነው።
በጠንካራ የትምህርት መሠረትና በብዙ ዘርፎች ባላቸው ጥልቅ ተሞክሮ የታነፁት ደራሲው፣ እነዚህ ሦስት መጽሐፍትን ለ አንባቢያን አቅርበውልናል።
አዲሶቹ በእንግሊዘኛ የቀረቡ መጽሐፍቶቻቸው «Why Strategy Fails: Eleven Gaps Between Ambition and Results» እና «The Silent Soul»፣ ቀደም ሲል ካተሟቸውና ከፍተኛ አድናቆትን ካተረፉት «ቅን መሪ» እና «ባለ ራዕይ መሪ» ከተሰኙት ድንቅ መጻሕፍቶቻቸው ፣እንዲሁም በአሁኑ ወቅት በገበያ ላይ ከሚገኙት «የትዳር ወግ» ከተሰኘው በጣም ተወዳጅ ከሆነው የአማርኛ ሥራቸው ጋር በአንድነት ለአንባቢዎች የቀረበ የላቀ የዕውቀት ገጸ-በረከት ነው።
#የትዳር_ወግ የፊታችን ሰኞ ይወጣል።የሽፋን ዋጋው 650 ብር ነው።ቀድመው ለሚከፍሉ ደንበኞቻችን ታላቅ ቅናሽ አድርገናል።
የትዳር ወግ የተሰኘ መጽሐፍ ለመውሰድ 500 ብር ብቻ ቀድማችሁ ክፈሉ።2ቱ እንግሊጣ መጻሕፍትም ከኅትመት ሊወጡ ሲሉ ቅናሹ እናሳውቃለን።
CBE
1000499547629
KIFLOM H AND/OR YILEMA TSEGAYE
Screenshot @orthokiha ላይ ላኩልን።
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 2 824 |
| 10 | ስሜን አትጥቀስ ያሉኝ አንድ አባት አንገብጋቢ ችግር ላይ ላለው ገዳም ጤፍ ገዝተህ አስፈጭተህ ስጥልኝ ብለው 256ሺ ብር አስገብተውልኝ።በዛሬ ቀን ለደብረ መንኩል አቡነ መድኅንየ እግዚእ ገዳም አበምኔቱ በተገኙበት 19 ኩንታል ጤፍ በ13,500 ብር ሲሳብ 256,500 ብር ከፍለን 19 ኩንታል ጤፍ አስረክበናል።
ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን። | 3 394 |
| 11 | #የልዳው_ኮከብ የልጆች መጽሐፍ 2ኛ ዕትም በስርጭት ላይ ነን!
አዘጋጅ ፡- ዶክተር ብሩክታዊት ተስፋይ
የሽፋን ዋጋ፡- 300 ብር
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 3 227 |
| 12 | የዓመቱ ታላቅ ቅናሽ አድርገን መጻሕፍት ለእናንተ ልናቅርብ ነው።ለመች ይሁንላችሁ? የቀኑ ምርጫ በእናንተ ይወሰናል። | 3 423 |
| 13 | አርጋኖን መጻሕፍት መደብር የዓመቱ የመጻሕፍት ሽያጭ ቅናሽ አያደርግም ወይ? አዎ ያደርጋል።ዓመት ሙሉ ቅናሽ እንዳረግን ነው።የቅናሽ ቅናሽ ደግሞ በቅርቡ እያሰብን ነው።መቼ? በእናንተ ምርጫ ይወሰናል? የዓመቱ የቅናሽ ቅናሽ መች እናዘጋጅላችሁ? | 1 |
| 14 | No text... | 5 405 |
| 15 | እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ለትንሣኤ ማርያም! የእሷ መነሳት የትንሣኤ ጉባኤ ተስፋችን ነውና።
ጽሑፉ የላከልኝ የአብአለ ነው።
ለደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት አንድ ሰው ማጣቴ ግን እጅግ ገርሞኛል ከኪሳችሁ ብር ባታወጡም እቤታችሁ ያለ መጽሐፍ መስጠት እንዴት አቃታችሁ? አንብባችሁ ቁጭ ያደረጋችሁት ለጉባኤ ቤት ተማሪዎች ለንባብ ይጠቅማል ግን የላችሁም አንድ አንድ መጽሐፍ እንስጥ። @orthokiha እዘዙ ወይም መጽሐፉ አርጋኖን መጥታችሁ ስጡ።
መልካም አሸንዳ፤ሸደይ፤ሳሎልያ፤ማርያ! | 4 168 |
| 16 | የደብረ ታቦር መድኃኒዓለም የ4ቱ ጉባኤ ምስክር ቤት መጻሕፍት እንድናሰባስብ መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ ባለፈው በአካል መደብራችን መጥተው ደብዳቤ ሰጥተውናል።ያለፉ ሳምንታት ለአርዕስተ አበው ጉባኤ ቤት እየተሰበሰበ ስለነበር ትንሽ ጠብቁን ብለን እስካሁን አቆይተነዋል።የሱባኤው መዝግያ በበረከት እናድርገው።
Challenge እያስጀመርን ነው።
አንድ መጽሐፍ ለጉባኤ ቤት ስትሰጡ እኛም አንድ ተጨማሪ እንሰጣለን።የምንፈልገው የሰው ብዛት 100 ሰዎች ነው።በድምሩ 200 መጻሕፍት ይሆናሉ።
ኑ ለታላቁ የቤተ-ክርስትያን ዩኒቨርስቲ መጻሕፍት እንስጥ።
@orthokiha ለደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት አለሁኝ በሉኝ።
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 4 362 |
| 17 | መልካም ዜና!
እነዚህ ዓለም አቀፍ መንፈሳዊ መጻሕፍት ከእናንተው #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር በአማርኛ በሊቃውንት አስገርጉሞ በቅርቡ ያቀርብላችኃል።
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ! | 4 373 |
| 18 | በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የተሰናዳው #የብርሃን_እናት የተሰኘው መጽሐፍ 14ኛ ዕትም በማከፋፈል ላይ ነን!
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውንዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ | 3 934 |
| 19 | ፖሊካርፐስም ወደ ሜዳው ሲገባ "ፖሊካርፐስ ሆይ በርታ ፤ ጽኑ ኹን! " የሚል ቃል ከሰማይ መጣ ተናጋሪውን ያየው ማንም የለም ፤ ነገር ግን በዚያ የነበሩት ወንድሞች ድምፁን ሰሙ ።
በመጨረሻም ወደ ፊት ሲያቀርቡት ሀገር ገዢው ፖሊካርፐስ እርሱ መኾኑን ጠየቀው ፤ እርሱም መኾኑን ሲያምን ሃይማኖቱን እንዲክድ ሊያግባባው እየሞከረ እንዲህ አለው "ለሽምግልናህ እዘን ደግሞም እነርሱ እንደሚያደርጉት ኹሉ በቄሳር መልካም እድል ማል ፤ ሐሳብህንም ለውጥና 'አምላክ የሌላቸው ይጥፉ' በል " አለው ። ያንጊዜም ፖሊካርፐስ በመሰብሰቢያው የነበሩትን ዓመፀኞች አረማውያን ኹሉ በእርጋታ ተመለከተ ፤ በእጁም እነርሱን አመለከተ ቃተተም ወደ ሰማይም ቀና ብሎ "አምላክ የሌላቸው ይጥፉ ! " አለ ።
ከዚያም ሀገረ ገዢው እየገፋፋው "ማል ፤ እኔም ነጻ አወጣሃለሁ ፤ ክርስቶስን ስደብ " አለው ። ፖሊካርፐስም "ሰማንያ ስድስት ዓመት አገልግዬዋለሁ ፤ እርሱም ከቶ ምንም አልበደለኝም ። ታዲያ ንጉሤንና መድኃኒቴን እንዴት ልሰድብ እችላለሁ ? " ብሎ መለሰለት ።
ዜና ስምዑ ለቅዱስ ፖሊካርፐስ ፤ ሐዋርያውያን አበው ገጽ 127
@orthokiha ይዘዙ!
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0925421700_ይደውሉ! | 4 913 |
| 20 | የሐዋርያውያን አበው መጽሐፍ ዳሰሳ.docx | 8 230 |
