en
Feedback
ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

Open in Telegram

This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ “ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።” — 2ኛ ቆሮ 11፥28

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

Channel ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ (@yaregalabegaz) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 39 947 subscribers, ranking 1 545 in the Religion & Spirituality category and 862 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 39 947 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 657 over the last 30 days and by 32 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.58%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.23% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 8 221 views. Within the first day, a publication typically gains 3 289 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 67.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ “ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።” — 2ኛ ቆሮ 11፥28

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

39 947
Subscribers
+3224 hours
+1597 days
+65730 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+174
in 3 channels
August '26
+862
in 7 channels
Get PRO
July '26
+901
in 8 channels
Get PRO
June '26
+892
in 3 channels
Get PRO
May '26
+710
in 2 channels
Get PRO
April '26
+736
in 10 channels
Get PRO
March '26
+245
in 5 channels
Get PRO
February '26
+251
in 2 channels
Get PRO
January '26
+251
in 4 channels
Get PRO
December '25
+664
in 13 channels
Get PRO
November '25
+445
in 7 channels
Get PRO
October '25
+272
in 1 channels
Get PRO
September '25
+304
in 3 channels
Get PRO
August '25
+558
in 5 channels
Get PRO
July '25
+416
in 8 channels
Get PRO
June '25
+390
in 9 channels
Get PRO
May '25
+670
in 11 channels
Get PRO
April '25
+958
in 24 channels
Get PRO
March '25
+913
in 4 channels
Get PRO
February '25
+1 379
in 13 channels
Get PRO
January '25
+2 598
in 6 channels
Get PRO
December '24
+3 626
in 18 channels
Get PRO
November '24
+2 971
in 19 channels
Get PRO
October '24
+2 315
in 12 channels
Get PRO
September '24
+1 485
in 7 channels
Get PRO
August '24
+1 832
in 5 channels
Get PRO
July '24
+2 275
in 16 channels
Get PRO
June '24
+1 233
in 10 channels
Get PRO
May '24
+1 907
in 10 channels
Get PRO
April '24
+2 135
in 14 channels
Get PRO
March '24
+2 637
in 10 channels
Get PRO
February '24
+1 859
in 5 channels
Get PRO
January '24
+1 100
in 8 channels
Get PRO
December '23
+833
in 3 channels
Get PRO
November '23
+256
in 1 channels
Get PRO
October '23
+153
in 1 channels
Get PRO
September '23
+271
in 0 channels
Get PRO
August '23
+156
in 0 channels
Get PRO
July '23
+240
in 0 channels
Get PRO
June '23
+281
in 0 channels
Get PRO
May '23
+463
in 0 channels
Get PRO
April '23
+202
in 0 channels
Get PRO
March '23
+134
in 0 channels
Get PRO
February '23
+239
in 0 channels
Get PRO
January '23
+186
in 0 channels
Get PRO
December '22
+104
in 0 channels
Get PRO
November '22
+96
in 0 channels
Get PRO
October '22
+71
in 0 channels
Get PRO
September '22
+60
in 0 channels
Get PRO
August '22
+85
in 0 channels
Get PRO
July '22
+104
in 0 channels
Get PRO
June '22
+109
in 0 channels
Get PRO
May '22
+100
in 0 channels
Get PRO
April '22
+115
in 0 channels
Get PRO
March '22
+124
in 0 channels
Get PRO
February '22
+809
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
08 September+4
07 September+32
06 September+26
05 September+26
04 September+17
03 September+37
02 September+19
01 September+13
Channel Posts
በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል በወርኀ ጳጉሜን ከሚታሰቡ እና ከሚከበሩ በዓላት መካከል በየዓመቱ ጳጕሜን ፫ ቀን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በዓሉ የሚከበርባቸው ምክንያቶችም ሁለት ናቸው፤ እነርሱም አንደኛው በዓለ ሢመቱን ምክንያት በማድረግ ሲኾን፣ ሁለተኛው ደግሞ ቅዳሴ ቤቱ ነው፡፡ ‹ሩፋኤል› የሚለው የስሙ ትርጓሜ ‹ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ› ማለት ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ያለ ማቋረጥ ፈጣሪያቸው ልዑል እግዚአብሔርን ከሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነው፡፡ ‹‹ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ›› እንዲል (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡ የሰው ልጆች ከተያዙበት የኀጢአት ቍስል ይፈወሱ ዘንድ በአማላጅነቱና በጸሎቱ የማይለይ መልአክ ነው፡፡ ‹‹በበሽታ ዅሉ ላይ በሰው ልጆችም ቍስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው›› በማለት ሄኖክ ከእግዚአብሔር መልአክ ያገኘውን የምስክርነት ቃል ጽፏል (ሄኖክ ፲፥፲፫)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል በሰውነታችን ላይ የሚወጣውን ደዌም ኾነ ቍስል ይፈውስ ዘንድ ከልዑል እግዚአብሔር ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ‹‹በሰው ቍስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው›› እንዳለ ሄኖክ፡፡ ለቈሰሉ ፈውስን የሚያሰጣቸው፤ ላረገዙ ሴቶች ረዳታቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሴት በፀነሰችበት ወቅት ቅዱስ ሩፋኤል አይለያትም፡፡ ሕፃኑ (ኗ በማኅፀን እያለ (ች) ተሥዕሎተ መልክዕ (በሥላሴ አርአያ መልኩ /ኳ/ መሳል) ከጀመረበት ቀን አንሥቶ እስከሚወለድበት ቀን ድረስ ቅዱስ ሩፋኤል በጥበቃው አይለያቸውም፡፡ በመውለጃቸው ቀን ሴቶች ከሚደርስባቸው ጭንቀትና ሕመም ስሙን ጠርተው ይማጸኑታል፡፡ ፈታሔ ማኅፀን ነውና ቅዱስ ሩፋኤልም ጭንቀታቸውን ያቀልላቸዋል፡፡(ሄኖክ ፮፥፫) አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ቢያሰቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል (ጦቢት ፫፥፰-፲፯)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ‹‹ዳግመኛም እግዚአብሔር ሩፋኤልን፣ አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጨለማ ውስጥ ጣለው አለው›› ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሄኖክ ፫፥፭-፯)፡፡ ለቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መሥራትን፣ የምንዝር ጌጥ ማጌጥን፣ መቀንደብን ያስተማረ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ እየቀጣ በረቂቅ አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ይኸው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው (ሄኖክ ፪፥፲፰)፡፡ የጦቢትን ልጁ ጦቢያን በሰው አምሳል ተገልጦ ከተራዳው በኋላ ወደ ሰማይ በሚያርግበት ጊዜ ራሱን ሲገልጥ ‹‹የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ አላቸው›› (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡ በቅዱስ ሩፋኤል ተራዳዒነት ከተደረጉ ተአምራት መካከል በእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት በታነጸች ቤተ ክርስቲያኑ ያደረገው ተአምር አንደኛው ነው፡፡ በመጽሐፈ ስንክሳር እና በድርሳነ ሩፋኤል እንደ ተጻፈው ብዙ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጠች፤ ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና፡፡ የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ዓሣ አንበሪው ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው፡፡ ምእመናኑም ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔር በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ ‹‹እግዚአብሔር አዝዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጥ ጸጥ ብለህ ቁም!›› ባለው ጊዜ አንበሪው ጸጥ ብሎ ቆሟል፡፡ በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገልጠዋል፡፡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆኗል፤ የቅዱስ ሩፋኤል ተራዳዒነት አይለየን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር

2
https://youtube.com/shorts/dJhyx7h9srQ?si=FCEPJ8oEI1PnzzbS
3 205
3
በብሕትውናው ቦታ ፈጽሞ እንዳይለቅ ከመሬት በላይ ቤት ሠርቶ እንዳይኖር፣ ፀጉሩን እንዳይላጭ፣ ጥፍሩንም እንዳይቆረጥ ሚስትም እንዳያገባ ሥርዓት ሠርቶለታል፡፡ በመላከ እግዚአብሔር እየተረዳ ምግቡን መላእክት እየመገቡት እስከ አብርሃም ድረስ በፍጹም ብሕትውና ለማንም ሳይገልጥ ኑሮአል፡፡ አብርሃም የወንድሙ ልጅ ሎጥን ያስጨንቁና ንብረቱን የዘረፉ አምስቱን ነገሥታት ኮሎዶጎሞርን ድል ነሥቶ ሲመለስ የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ በዘመኑ የሚፈጸም መሆኑንና አለመሆኑን ለማወቅ ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቆ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ግን ምሳሌውን ካህኑ መልከጼዴቅን ከተሰወረበት ቦታ ሄዶ እንዲመለከት ፈቀደለት፡፡ አብርሃምም የዮርዳኖስን ወንዝ ተሻግሮ ኅብስተ አኮቴት ጽዋ በረከት ይዞ ወደ ማዕከለ ምድር ቀራንዮ ሄደ፤ መልከጼዴቅም ተገልጦለት ‹‹አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሴት አደረገ፤ አየም ደስም አለው ….›› እንዳለው ጌታችን (መልከጼዴቅ የእግዚአብሔር ወልድ የመድኅን ዓለም ክርስቶስ) ምሳሌ ነበር፡፡ (ዮሐ.፰፥፶፰) ለዚህ ነው ጌታችን ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ አየም ማለቱ) አብርሃም ኅብስት አኮቴት ጽዋ በረከት ለመልከጼዴቅ የሰጠው፤ (ዘፍ.፲፬፥፲፰) ትውልድ ከእርሱ የማይቆጠር ግን አብርሃም ዐሥራትን አውጥቶ ሰጥቶታል፤ የአብርሃምንም መሥዋዕት አስታኮቶለታል፤ አብርሃምንም ባርኮታል፤ የጌታችን ምሳሌ የሆነው የኦሪቱ ሊቀ ካህን መልከጼዴቅን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዕለት ታስበዋለች፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም ሊቀ ካህን የመልከጼዴቅ ጸሎት ይጠብቀን፤ አሜን!!! ጾመ ዮዲት በወርኃ ጳጉሜን ምእመናን በፈቃዳቸው ይጾሙባታል፤ መጪው ዘመን እንዲባረክ፣ ስለ ቀደመው ኃጢአት እያዘኑ በጾም በጸሎት ፈጣሪን እየተማጸኑ ያሳልፏታል፤ ይህቺ ወቅት በመጽሐፈ ዮዲት ተመዝግቦ እንደምናነበው ሆሎፎርኒስ የተባለ የናቡከደነጾር ቢትወደድ የእስራኤልን ልጆች ምንጭ ይዞ ሕዝቡን ባስጨነቀ ጊዜ ተስፋ ቆርጠው ለጠላት ምርኮ እንግባ አሉ፤እግዚአብሔርን የምትፈራ በጾም በጸሎት ተወስና የምትኖር ዮዲት የተባለች ደገኛ ሴት ከመሪዎቿ መካከል ተገኝታ ለጠላት እጅ እንዳይሰጡ ከእነርሱ የስንፍናን ንግግር እንዲያርቁ ተማጸነች፡፡ አባቶቻቸውን ከጠላት የታደገ ድንቅ ተአምራት ማድረግ ወደሚቻለው እግዚአብሔር በጾም በጸሎት ለአምስት ቀን እንዲማጸኑ አሳሰበች፤ ከአባቶች ምርቃት ተቀብላ አገልጋይዋን አስከትላ ከጠላት መንደር ተጓዘች፡፡ እግዚአብሔር ግርማ ሞገስ ሆናት፤ ለቀናት በጾም በጸሎት ተወስና አብራ ከሆሎፎርኒስ ጋር ተቀመጠች፤ በአንድ ሌሊት አብዝቶ ጠጥቶ እንቅልፍ ጥሎት ሳለ ወደ ፈጣሪዋ እንዲህ ጸለች፤ ‹‹አቤቱ የመላእክት ፈጣሪ በዚህች ሰዓት ኢየሩሳሌም ከፍ ከፍ ትል ዘንድ መከራችንን አይተህ በእኔ እጅ ይቅርታን አደርግ፤ እስራኤልን ከኃሣር የምታነሣበት ጊዜው ደርሷልና …›› (መጽሐፈ ዮዲት ፲፫፥፬-፭) ከዚያም የራሱን ሰይፍ አንሥታ ቸብቸቦውን ቆርጣ ወደ ሕዝቦቿ ተመለሰች፤ የናቡከደነጾር ጭፍሮች የመሪያቸው የሆሎፎርኒስን መሞት ሲመለከቱ ሸሹ፤ ዮዲትና ሕዝቧ በእግዚአብሔር ኃይል አስጨናቂ ጠላቶቻቸውን ድል አደረጉ፡፡ ዮዲት በመልካም ምግባሯ፣ በጾም ጸሎቷ ሰው በጠፋበት ዕለት ለወገኖቿ ሰው ሆና ተገኘች፤ በመልካም ጊዜ የጾሙት የጸለዩት ጸሎት በችግር ወቅት የመፍትሔ አካል እንደሚሆን ዮዲት አስተማረች፤ ተስፋ የቆረጠ ሕዝቧን ተስፋ ሰጠች፡፡ የወገኖቿን አስጨናቂ አስወግዳ ለተጨነቀች ነፍሳቸው ሰላም (የዕረፍት) ማግኘት ምክንያት ሆነቻቸው፡፡ ምእመናን በዚህ ይህ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ፣ የዮዲትን የእምነት ጽናት፣ የጾም ጸሎትን ጥቅም ተረድተው ስለ ግል ሕይወታቸው፣ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ አገር ፍቅር ሰላም ብለው በፈቃዳቸው ወርኃ ጳጉሜን በጾም በጸሎት ያሳልፋሉ፤ የሕይወት ኃሣር ይወገድ፣ ጥላቻ ከሕዝብ ይራቅ መጪው አዲስ ዓመት ይባረክ፤ የተዘራው ዘር ለፍሬ እንዲሆን ጠላት ዲያብሎስ ያፍር ዘንድ ይማጸናሉ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!!!
7 214
4
ወርኃ ጳጉሜን ዕለተ ምርያ ወርኃ ጳጉሜን በዓመቱ መጨረሻ የምትገኝ በአገራችን ኢትዮጵያ እንደ ዐሥራ ሦስተኛው ወር የምትቆጠር ናት፤ ወርኃ ጳጉሜን አምስት ቀናት ያሏት ስትሆን በአራት ዓመት አንድ ጊዜ በዘመነ ሉቃስ መውጫ በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ ያለው ስድስት ቀን ይሆናል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላታቸው ጳጉሜን እንዲህ ይተረጉሟታል፤ ጳጉሜን ማለት ጭማሪ ተውሳክ፣ አምስት ቀን፣ ከሩብ፣ ከዐውደ ወር ተርፎ በዓመቱ መጨረሻ የተጨመረ ስለሆነ ትርፍ ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ ፱፻፭) በወርኃ ጳጉሜን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተከብረው (ታስበው የሚውሉ በዓላት አሉ፤ በሌላ ስያሜም ዕለተ ምርያ (የመዳን ወር ) ትባላለች፤ ምርያ ማለት ከቀን ወደ ቀን የሚያሻግር፣ አንድም ዕለተ ኅሪት ዕለተ መድኃኒት ማለት ነው፤ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ ፮፻፰) ምእመናን በዚህች ወቅት ጸበል ይጠበሉባታል (ይጠመቁበታል)፡፡ ሊቀ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ጳጉሜን ሦስት ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው በዓላት አንዱ የሊቀ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል በዓል ነው፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በዚህች ዕለት ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ይከበራል፡፡ በድርሳነ ቅዱስ ሩፋኤል እና በወርኃ ጳጉሜን ሦስት ቀን የሚነበበው ስንክሳርና የተጻፉት ድርሳናት እንዲህ ያስተምሩናል፤ አንዲት ክርስቲያን ሴት በቅዱስ ሩፋኤል ሰም በባሕር መካከል ባለች ደሴት ቤተ ክርስቲያን አሳነጸች፤ ሊቀ ጳጳሱ አባ ቴዎፍሎስ በዚህች ዕለት ቅዳሴ ቤቱን አከበረ፤ ከደሴቲቱ ሥር የነበረ ግዙፍ ዓሣአንበሪም ባሕሩን ባናወጠው ጊዜ በደሴቲቱ የታነጸቸውን ቤተ ክርስቲያኗን ሊያፈርስ ደረሰ፤ በውስጧም ለበዓል ተሰብስበው የነበሩ ምእመናን በጸሎት ወደ ቅዱስ ሩፋኤል ተማጸኑ፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤልም ከእግዚአብሔር ተልኮ መጣ፤ ሕዝቡን ታደገ፤ ከደሴቲቱ ሥር ያለውንም ግዙፍ ዓሣአንበሪው እንዳይንቀሳቀስ በጦር ወጋው፤ ‹‹እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም!›› አለው፤ ጸጥ ብሎም ቆመ፡፡ ሕዝቡም ከባሕሩ ከመስጠም፣ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኒቱም ከመፍረስ ተረፉ፤ ቅዱስ ሩፋኤል ይህን ድንቅ ተአምር አድርጎ፣ ከፈጣሪው አማልዶ፣ ለጠሩት ፈጥኖ የደረሰበትን ይህን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓመቱ መጨረሻ ባለችው ወርኃ ጳጉሜን በሦስተኛ ቀን በድምቀት ታከብሯለች፡፡ (ስንክሳር ዘወርኃ ጳጉሜን ሦስት ቀን) በዚህች ዕለት ከሚከበሩ በዓላት ሌላኛው በመጽሐፍ ቅዱስ በመጽሐፈ ጦቢት እንደተጻፈው ቅዱስ ሩፋኤል በመልካም ምግባሩ፣ በምጽዋት ሥራው ለሚታወቀው ለጦቢት በችግሩ ጊዜ በሰው አምሳል ተገልጦ፣ እንደ ሠራተኛ ተቀጥሮ በማገልገለል ልጁ ጦቢያን ከዓሣአንባሪ ፣ ሣራ የተባለችን ሴት ያሠቃያት ከነበረው ርኩስ መንፈስ፣ ጦቢትን ከዓይን ሕመሙ የፈወሰበት የቅዱስ ሩፋኤል ተራዳኢነት፣ የጦቢት መልካም ምግባር፣ የእግዚአብሔር ቸርነት የተገለጠበት መታሰቢያም በዓል ነው፡፡ (መጽሐፈ ጦቢት አንድምታው መግቢያ) ይህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የተሾመበት መታሰቢያውም ነው፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ጸሎት ይጠብቀን፤ አሜን!!! ዕለተ ምጽአት ወርኃ ጳጉሜን የዕለተ ምጽአት መታሰቢያም ናት፤ እግዚአብሔር ለፍርድ ወደዚህ ምድር የሚመጣበት ወቅት መታሰቢያ ነው፤ ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ተናገረ፤ ከፀሐይም መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ምድርን ጠራት፤ ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝምም አይልም ….›› በማለት እንደተናገረው ጌታችንም በደብረ ዘይት ተራራ ለደቀ መዛሙርቱ ዳግመኛ ለፍርድ እንደሚመጣ በገለጸው መሠረት ወደዚህ ምድር ለጻድቃን ሊፈርድላቸው፣ በኃጥአን ሊፈርድባቸው ይመጣል፤ (መዝ. ፵፱፥፩-፫) ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቼ እንደሚመጣ ዓመቱንና ዕለቲቱን በግልጽ ባይነግረንም ዳግመኛ ግን እንደሚመጣ ነግሮናል፤ ‹‹…ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፤ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና፡፡›› (ማቴ.፳፬፥፵፬) ቅዱስት ቤተ ክርስቲያንም የዕለተ ምጽአቱን መታሰቢያ በዐቢይ ጾም እኩለ ሳምንት ላይና በወርኃ ጳጉሜን ሦስተኛው ቀን ታከብራለች፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታት ጸሎት ላይ ‹‹ለምጽአትከ ከዋላ እስከነ ዘመን ወዕድሜ፣ ለመለኮትከ ዘአልቦ ፍጻሜ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላከ ሱላሜ፤ አመጣጥህ በኋለኛው ዘመን የሆነ ለአገዛዝህ ፍጻሜ የሌለህ ኢየሱስ ክርስቶስ የፍቅር አምላክ ነህ›› በማለት እንደተናገረው ለዘመኑ ፍጻሜ የሌለው የፍቅር አምላክ ፈጣሪያችን ዳግመኛ ይመጣል፡፡ (ስብሐተ ፍቁር) ሐዋርው ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ ‹‹ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋው ቃል አይዘገይም፤ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል›› ብሎናልና፡፡ (፪ኛ ጴጥ.፫፥፱) ጌታ ስለ ተስፋው ቃል አይዘገይምና ሕይወታችንን በንስሐ አንጽተን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን ተዘጋጅተን ልንጠብቀው ይገባል፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ‹‹…ኑ እናንተ የአባቴ ቡሩካን…›› ከሚላቸው ወገን ይደምረን! ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ አሜን!!! ርኆተ ሰማይ ይህች ዕለት ርኆተ ሰማይ (የሰማይ መስኮቶች የሚከፈቱባት)፣ ሊቃውንቱ የሰማይ ደጆች ተከፍተው የምእመናን ጸሎት የሚያርጉበት በዓመት አራት ጊዜያት እንዳሉ ይገልጻል፤ ታዲያ የመጀመሪያው ዕለት ጳጉሜን ሦስት ቀን በመሆኑ ይህች ዕለት ርኆተ ሰማይ ትባላለች፡፡ የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የምእመናንን ጸሎት ለእግዚአብሔር የሚያሳርግበት ዕለትም መታሰቢያ ነው፡፡ የእግዚአብሔር የምሕረት ደጆች የሚከፈቱባት ዕለት መታሰቢያ ናት ርኆተ ሰማይ ! አባቶችና እናቶች በትውፊት በዚህች ዕለት ዝናም ሲዘንብ በእምነት የቤታቸውን ዕቃ (ሌማቱን፣የቡሆዕቃ…) ከሰማይ በሚወርደው ዝናመ ምሕረት እንዲባረክላቸው ከውጭ አውጥተው ያስመቱታል፤ ምእመናን በዚህች ዕለት በሚዘንብ ዝናብ ይጠመቁበታል፤ በርኆተ ሰማይም በጳጉሜን ሦስት ቀን!!! የኦሪቱ ሊቀ ካህን የመልከጼዴቅ መታሰቢያ በዚህች ዕለት የጌታችን ምሳሌ የሆነው የኦሪቱ ሊቀ ካህን የመልከጼዴቅ መታሰቢያ ነው፤ መልከ ጼዲቅ ማለት ንጉሠ ጽድቅ ንጉሠ ሰላም ማለት ነው፡፡ ከተማዋም በእርሱ ኢየሩሳሌም/የሰላም ከተማ /ተብላለች፡፡ መልከ ጼዲቅ የእስራኤል እምብርት /ዋና ከተማ/ ኢየሩሳሌምን ያቀና ከካም ወገን የሆኑት የኖኅ የልጅ ልጅ ነው፡፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለኖኅና ለልጁ ለሴም ከካም ወገን የተለየ የተባረከ ልጅ እንደሚወለድና አጽመ አዳምን ይጠብቅ ዘንድ የተመረጠ መሆኑን ነግሮት ስለነበር ሴም በታዘዘው መሠረት ወደ ማዕከለ ምድር ቀራንዮ ወስዶ አጽመ አዳምን እንዲጠብቅ በእግዚአብሔር የተመረጠ መሆኑን ነግሮት በክህነቱ መፈጸም ስለሚገባው/በኑሮው ስለሚገልጠው/ ሥርዐት ሠርቶለታል፡፡ በክህነቱ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ እንዲያመሰግን የእንስሳት መሥዋዕት እንዳይሠዋ መሥዋዕቱ ንጹሕ ስንዴና ወይን እንዲሆን በእጁም ደም እንዳያፈስ ነግሮታል፡፡
5 976
5
ቅዳሜ ይጠብቁን https://youtu.be/En5-U3WVxlE?si=pQLHC2P_Yk3HMqEq
163
6
"የተጠራነው እንድንቀደስ ነው" #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
"የተጠራነው እንድንቀደስ ነው" #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
5 654
7
መታገል #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
መታገል #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
7 609
8
No text...
9 304
9
ጌታን ሲከተሉት የነበሩ አይሁድ "ከሰማይ የወረደ እውነተኛ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" የሚለውን የጌታ ቃል በሁለት ምክንያት ለመቀበል ተቸግረው ነበር። ለጊዜው ፍላጎታቸው ምድራዊውን ምግብ አበርክቶ የሚያበላቸው ሰው ነው፡፡ ሁለተኛው እንዴት ሥጋውን ለመብልነት ሊሰጣቸው እንደሚችል ማሰብ አልቻሉም። በዚህ ትምህርቱ " እንዴት ልንከተው እንችላለን" ብለውም ጥለውት ሄዱ። ይኼንን የወንጌል ክፍል ለማየት ሞክረናል። አድምጡት https://youtu.be/Dt2XogkyzFk?si=m15uIes48_xP5kNO
8 989
10
የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው:: ሙት አንስተዋል፤ ድውያንን ፈውሰዋል፤ አጋንንትን አሳደዋል፤ እሳትን ጨብጠዋል፤ በክንፍ በረዋል፤ ደመናን ዙፋን አድርገዋል፤ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መስርተዋል፤ በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕፃናት አብረው ኑረዋል፤ በዘመናቸው ሰይጣን ታስሯልና:: ዕረፍት ጻድቅ፣ ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው፣ መከራን በብዙ ተቀብለው፣ እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው በተወለዱ በ፺፱ ዓመት: ከስምንት ወር ከ አንድ ቀናቸው ነሐሴ ፳፬ ቀን በ፲፻፫፻፮ ዓ.ም ዐርፈዋል:: ጌታችን፣ ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል፤ ፲ ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል:: የጻደቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ በረከታቸው ይደርብን፤ አሜን፡፡ ምንጭ፡- ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
10 125
11
በዓለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አምላካችን እግዚአብሔር ለነቢዩ ኤርምያስ “በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ፤ ከማኅፀን ሳትወጣ ቀድሸሃለሁ” በማለት እንደተናገረ የገናናው ጻድቅ የአባታችን ተክለ ሃይማኖት ዜና ሕይወቱን እንዘክራለን፡፡ (ኤር.፩፥፭) ልደት ደጋጎቹ ካህኑ ጸጋ ዘአብና እግዚእኃረያ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፡፡ እነርሱም እንደሌሎች ቅዱሳን እናት እና አባቶቻቸው ልጅ አተው ኖረዋል፡፡ እንደነ አብረሃም እና ሣራ፣ እንደ እነ ዘካርያስ እና ኤልሳቤጥ ማለት ነው። እግዚኃርያም ሁል ጊዜም ወደ ቤተ እግዚአብሔር ታመለክት ነበር። ከዕለታት አንዲት ቀን መላኩ ተግልጾ ልጅ እንደሚወልዱ ነገራቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በመጋቢት ፳፬ ቀን ፲፻፪፻፮ ዓ.ም ተፀንሰው በሸዋ ክፍለ ሀገር በጽላለሽ ወይም በዞረሬ አካባቢ ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብ እና ከእናታቸው ከእግዚኃርያ በታኅሣሥ ፳፬ ቀን በታኅሣሥ ፳፬ ቀን በ፲፻፪፻፯ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ሲወለዱም ሥላሴን “ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ” ብለው አመስገነዋል። ጻድቁ በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጿል፤ ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል:: አባታችን ተክለ ሃይማኖት ክርስትና ወይም የሥላሴን ልጅነት ሲቀበሉ አባቱ ጸጋ ዘአብ ሲቀድስ ያመሰግን ነበር፡፡ እናቱም ደግሞ “አንተ ልጅ አሁን ጡጥ ጥባ እንጂ” እያለች ትሞግተው ነበር። የካህን ልጅ ካህን እንዲሉ ገና ሲወለድ ጀምሮ “ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ምስጋና ስለጀመረ አባት እና እናቱ እጅግ ተደሰቱ፡፡ ዕድገት ጻድቃኖች የቅዱሱ ወላጆች እግዚአብሔር ለሰጣቸው የተመረጠ ልጅ የመጀመሪያ ያወጡላቸው “ፍሥሃ ጽዮን” የሚል ስም ነው:: በዚህም ስያሜ አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይም ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያትና ሐዲሳትን) ተምረዋል:: ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል:: መጠራት ከዕለታት በአንዱ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑት በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ:: በመቀጠልም የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ፤ “ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: ከአሁን በኋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ” ብሎትም በግርማ ዐረገ:: ጻድቁ ተክለ ሃይማኖትም ጊዜ አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: አገልግሎት ጻድቁ አባት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: አባታችን በኢትዮጵያ በረሃዎች ወንዞች ሸንተረሮች እና አውራጃዎች እየተዘዋወሩ በልዩ ልዩ አምልኮ የነበረውን ሕዝብ የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥት አስተምረው እና አጥምቀው የክርስቶስን መንግሥት እንዲወርሱ ያደረጉ ታልቅ ጻድቅ ናቸው። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ፲ ሽህ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮዽያ ሁለት መልክ ነበራት:: አንደኛ ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽእኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዶ እና በባዕድ አምልኮ ተጠምዶም ነበር:: ሁለተኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: ግማሹ ሀገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን እንዲሁመ መሳፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: አባታችን ተክለ ሃይማኖት በዚህ ዓለም ላይ ወንጌልን መሰረት አድርገው የሐዋርያትን ሥራ ፈለግ በመከተል ብዙ ተጋድላዋል። ለሀገራችን ለኢትዮጵያ በዚህ ዓለም ብዙ ደክመዋል።፡ ለዚህም ነው በአንድ ወቅት አባታችን “ወለእመ ጠፋአ ማሕቶት አልቦ ዘየሐቱ ሎቱ ዘእንበለ ዘይከድኖ ጽልመት፤ መብራት ቢጠፋፋ የሚያበራለት የለም፤ ጨለማ ከሚወርሰው በቀር።” ለአቃቤ ሥርያኒ መኑ ይፌውስ ለአመኢያመረ ፈውሰ ለእረሱ ከማሁ ኮነት ነፍስዬ በላዕሌየ ቀሰምኩ ባዕዳነ ወለሳህዩኩ ለልየ ሰረይኩ፤ አሕዛበ ወደወይኩ ለልየ አብራይኩ ለዓለም ወጸለምኩ ለእርስየ፤ ባለ መድኃኒትንስ ማንን ይፈውሰዋል፤ ከእራሱ የሚድንበት ካላወቀ ነፍሴ በእኔ ላይ እንዲሁ ሆነች፤ ሌሎችን ግን አጣፈጥኩ፤ ለእራሴ ግን አልጫ ሆንኩ፤ ሕሙማንን ፈወስኩ፤ ለእራሴ ግን ድውይ ሆንኩኝ፤ ለዓለም አበራሁ፤ ለእራሴ ግን ጨለምኩ” በማለት እንደተናገሩ ገድላቸው ይጠቅሳል። ይህ የሚያመለክተው አባታችን ተክለ ሃይማኖት ረኃቡን፣ ጥሙን፣ መካራ ሥቃዩን ታግሠው በጾም እና በጸሎት እንዲሁም በስግደት ተጋድሎ በማድረግ በየተራረው እየዞሩ በዚህች በመራረው ዓለም ጣፋጭ ወንጌልን በማስማር ኢትዮጵያን ያጣፈጡ እንደሆኑ ነው፡፡ ሥራቸውም በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለዓለም እንዳበራ የተመሠከላቸው ነው፡፡ ገዳማዊ ሕይወት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በሦስት ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል:፡ እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ፲፪ ዓመታት፣ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለሰባት ዓመታት፣ በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለሰባት ዓመታት፣ በአጠቃላይ ለ፳፮ ዓመታት አገልግለዋል:: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ፳፪ ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም ስድስት ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለሰባት ዓመታት ጸልየዋል:: ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እስራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ፣ እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከፅንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር:: ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ፣ በቤተ መቅደስ ብሥራቱን፣ በቤተ ልሔም ልደቱን ፣በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን ፣በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ፣በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው:: በዚያም የብርሃን ዐይን ተቀብለው ስድስት ክንፍ አብቅለው፣ የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው፣ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው፣ ከ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው ፣ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -“ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ” ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: ተአምራት
9 156
12
ታላቅ የምሥራች የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ሮሜ ሰዎች በዮሐንስ አፈወርቅ በመምህር ሽመልስ መርጊያ ተተርጉሞ ጀምሮ ገበያ ላይ ውሏል። በሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር ታገኙታላችሁ።+2
ታላቅ የምሥራች የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ሮሜ ሰዎች በዮሐንስ አፈወርቅ በመምህር ሽመልስ መርጊያ ተተርጉሞ ጀምሮ ገበያ ላይ ውሏል። በሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር ታገኙታላችሁ።
9 430
13
https://youtu.be/5VGAbdNmosU?si=M31d3BkqFlTD-tiS
7 622
14
https://youtu.be/jCaa_Q-auC4?si=HUJmQ49Sqcmx5H9a
7 301
15
No text...
7 916
16
‎📖 መማር እንሻለን - የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ‎ማኅበራዊ ቀውሶች የብዙ ሕፃናትን የትምህርት ጉዞ አግድመውታል። የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት እነዚህን ሕፃናት
‎📖 መማር እንሻለን - የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ‎ማኅበራዊ ቀውሶች የብዙ ሕፃናትን የትምህርት ጉዞ አግድመውታል። የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት እነዚህን ሕፃናት ለመደገፍ ሰፊ የንቅናቄ ዘመቻ ጀምሯል። ‎🔹 ዓላማ፦ ሕፃናቱ በትምህርት መሣሪያ እጥረት ሳይስተጓጎሉ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ። ‎🔹 መዋጮ፦ የአንድ ተማሪ ዓመታዊ ቁሳቁስ ወጪ 3,300 ብር ቢሆንም፣ ማንኛውም ሰው የቻለውን ያህል (አንድ ደብተርም ቢሆን) ማበርከት ይችላል። ‎🏦 የባንክ መረጃዎች፦ ‎CBE: 1000309803648 ‎Ahadu: 0025393810901 ‎Abyssinia: 23375458 ‎Wegagen: 083731610101 ‎📍 የመቀበያ ቦታ፦ አምስት ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ 1ኛ ወለል
8 854
17
No text...
9 353
18
https://vt.tiktok.com/ZSVQxEynb/
93
19
📚#መድሎተ_ጽድቅ እነኾ ቅጽ ፪ ለ6ኛ ጊዜ ታትሟል 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ
📚#መድሎተ_ጽድቅ እነኾ ቅጽ ፪ ለ6ኛ ጊዜ ታትሟል     📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623
10 234
20
ከክርስትና በፊት የነበረው አረማዊው ዓለም (pagan world) ድሆች ፣ ሕሙማን እና አካል ጉዳተኞች በአማልክቱ የተረገሙ እንደሆኑና ርኅራኄ እንደማይገባቸው ያምን ነበር። ለእነዚህ የተገለሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች መራራት ለአረማዊው ዐለም እንግዳ የሆነ፣ የክርስትና ግን መሠረታዊ ተፈጥሮ ነበር። ክርስቲያኖችም ከአረማውያኑ የሚለዩበት ልዩ መታወቂያቸው ይህ ለተቸገሩትና ልዩ ልዩ ደዌ ለጸናባቸው ሰዎች የሚያሳዩት ፍቅር ርኅራኄና እንክብካቤ ነበር። በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ለነበሩ ክርስቲያኖች ምጽዋት እንደ አማራጭ በጎ ስራ (virtue)  የሚደረግ አልነበረም። ይልቁንም ክርስቲያን ያደረጋቸው መሠረታዊ ማንነታቸው እንጂ። በዛሬው ቆይታችን ይህንን የጥንቷ ቤተክርስቲያን ስለነዳያን የነበራትን አቢዮታዊ አቋም ፣ ዛሬ ካለው መረዳትና ልምምድ ጋር በስፋት ለማነጻጸር ሞክረናል። መልካም ቆይታ። https://youtu.be/cy9mYo1cFw0?si=3FKQyHXn4yO_Nnvj
9 363