en
Feedback
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Open in Telegram

« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Channel 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 (@https_asselefya1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 265 subscribers, ranking 6 132 in the Religion & Spirituality category and 2 370 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 265 subscribers.

According to the latest data from 08 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -2 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 16.75%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.90% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 390 views. Within the first day, a publication typically gains 1 269 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 265
Subscribers
-524 hours
-67 days
-230 days
Posts Archive
🔖አንተ ሙስሊም ወንድምህ ሲወድቅና ሳይሳካለት ሲቀር የምትደሰት ከሆነ ዉጤታማ ሲሆንና ሲሳካለትየምታዝንና የምትመቀኝ ከሆነ "እወቅ ትልቅ ችግር እንዳጋጠመህ ራስህን መርምር ኢማንህ የጎደለ መሆኑን አ
🔖አንተ ሙስሊም ወንድምህ ሲወድቅና ሳይሳካለት ሲቀር የምትደሰት ከሆነ ዉጤታማ ሲሆንና ሲሳካለትየምታዝንና የምትመቀኝ ከሆነ "እወቅ ትልቅ ችግር እንዳጋጠመህ ራስህን መርምር ኢማንህ የጎደለ መሆኑን አስተዉል በአንተ ላየ በጣም ይፈራል። ምክኒያቱም የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ስላሉ:–~"ከናንተ አንድኛችሁ አላመነም (አያምንም) ለራሱ የሚወደዉን ለወንድሙ እስካል ወደደ ድረስ " ~ t.me/https_Asselfya

ማንም እናንተን ተደግፎ እንዲቆም ምርኩዝ አትሁኑለት። ይልቁኑ በራሱ እንዲቆም መንገዱን አመላክቱት። ለሰዎች በራሳቸው መቆም እንዲችሉ ማስተማር እንጂ ምርኩዛቸው መሆን አይጠግናቸውም፣አይጠቅማቸውም።! እናንተ ስትሄዱስ? እንዳዲስ መኖር እንዲጠፋቸው ነው? ብዙ ጊዜ መንገድ ሊያመላክተን ከሚጥር የበለጠ፣ እድሜ ዘመናችን ሙሉ ተደግፈነው እንድንቆም የሚያደርገንን እንመርጣለን። (ለምን?) እንድንቆም መንገዱን ሳያመላክተን ምርኩዝ የሆነን ሁሉ አልጠቀመንም።ሁሉም መልካምነቶች መልካም አይደሉም።አንዳንድ መልካምነቶችን ፈትሹ።ቢያንስ ምርኩዙ የወደቀ ለት በመንገዱ ላይ የሚኖር ይኖራልና ሰዎች በራሳቸው እንዲቆሙ መልካም መንገዶችን ማመላከት ምርኩዛቸው ከመሆን ይበልጣል። =t.me/AbuSufiyan_Albenan

_أتأمرون_الناس_بالبر_وتنسون_أنفسكم_تلاوة_قديمة_للشيخ_د_سعود_الشريم.mp35.00 MB

🔖«እህቴ» ሁላችንም ጎዶሎዎችና ድሆች ነን !! ~ በዚህች አለም ላይ የተብቃቃና ፍፁም የሆነ ከጉድለት የጠራ ሰው መጠበቅ ከንቱ ምኞት ነው።ምክንያቱም አላህ እንዲህ ይላል፦«እናንተ ሰዎች ሆይ!እናንተ {ሁል ጊዜ}ወደ አላህ ከጃዮች ናችሁ።እርሱ ተብቃቂው  ምስጉኑ ነው።» ~ ከብዙ ጥቂት የማይባለው በዚህች አለም ድህነትን ይፈራል። በእጅጉ ደግሞ እኛ ሴቶች ድህነትን እንፈራለን ችግርን በመቋቋም ላይ ደካሞችም ነን በችግር በፍጥነት ተጠቂዎችና ደካማ ፍጥረቶች ነን።በተቃራኒው ደግሞ አባካኝና ገንዘብን በዳዮችም እኛው ነን። ~ መናገር ወደ ፈለኩት ሳልፍ ደግሞ እህቴ፦ በድህነት ፍራቻ መልካም ትዳርን አታርቂ ከድህነት ማምለጫ ያማረ አቋራጭ መንገድ ቢኖር ትዳር ነው። አላህም እንዲህ ይላል፦«ከናንተም ትዳር የሌላቸውን አጋቡ ከወንዶች ባሮቻችሁና ከሴቶች ባሮቻችሁም ለጋብቻ ብቁ የኾኑትን {አጋቡ}#ድኾች ቢኾኑ አላህም ስጦታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።» ~ብልህነት መለያሽ አድርጊው አንዳንዶቻችን አላህ ይዘንልንና ልክ ትዳር የሚያጨው ሰው ሲመጣ በዚህች ምድር ስንፈልገው የነበረውን #ጠላታችንን ያገኘነው ይመሰል ቡጭቅጭቅ እናደርገዋለን። ~እህቴ የታለ እዝነት? ሰውዬው አይቀጥል ችግር አይወጣ ችግር ለሰው የተደረገው በእኔ ለምን ይቅር ባይነትና በዙሪያ ያሉት ሰዎች ያንን ይህንን እያሉ ይገፋፋሉ እኛ መነዳትግን ምን አዘናጋሽ? ነገ እሱ ሲራብ ምትራቢው አንቺ ነሽ፣ሲበርደው ሚበርድሽ አንቺ ነሽ፣ሲቸገር የምትቸገሪው አንቺ ነሽ አላሰፈላጊ ወጪ ዛሬ የምታስተፊው ዛሬ ብታዛኝለት ነገ ቤትሽ ታገኝዋለሽ። ~ብልህ ሴት ከጅምሩ አሰተዋይና ለእሱ ያላትን ርህራሄ እንዲሁም ተቆርቋሪነት የምታሳይ ናት! ~ ጋብች ልዩ ታዐምራቶች ውስጥም እርካታናፍቅር እዝነትም ነው።አላህ እንዲህ ይላል፦ «ለእናንተም ከነፍሶቻችሁ {ከጎሶቻችሁ}ሚስቶችን ወደ እነሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፣በመካከላችሁም ፍቅርንና እዝነትን ማድረጉ አሰደናቂ ምልክቶቹ ነው።» ~ እናማ በዚህ ጋብቻ መፈለግ ያለብሽ በመልካም ነገር መበረታትበኢባዳ መጠንከር፣ጥሩ ተተኪ ዘሮች ማግኘት ይሁን። ነብያቶች ምትክን ፍለጋ አላህን እጅጉኑ ይማፀኑ ነበርነብዩላሂ ዘከሪያ እንዲህ ነበር ያሉት «ጌታዬ ሆይ!ከአንተ ዘንድ መልካም ዘርን ለኔ ስጠኝ አንተ ጸሎትን ሰሚ ነህና» ~ ያ!አላህ «ጌታችን ሆይ! ከሚስቶቻችንና ከዘሮቻችን ለዓይኖች መርጊያን ለእኛ ሰጠን።አላህን ለሚፈሩም መሪ አድርገን» አሚን! منقول = t.me/https_Asselefya1

يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي «ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡ =

~ አላማሽ ግብ እስኪመታ ድረስ  ትግልሽን በሚስጥር ጠብቂ ! =

ለሌሎች መልካም አድርጊ  ያን ስታደርጊ ግን ከማንም ጥቅም ሙገሳ ፈልገሽ አይሁን  ለአላህ ብለሽ ብቻ አድርጊ።  ባላሰብሺዉ መንገድ ተመልሶ ይጠቅምሻል ያ  በጎ ያደረግሺዉ ስራሽ ። =

_إن_الله_لا_يغير_ما_بقوم_حتى_يغيروا_ما_بأنفسهم_تلاوة_قديمة_ألشيخ.m4a11.46 MB

ይቅርታ… እጅግ ምርጥ ነገር!  ነገር ግን ዘግይቶ ሲመጣ ባዶ ነው።  የተሳሳትክ ሰው ሆይ! ስታጠፋ ለይቅርታህ "የስምምነት ህግ"ን አስታውስ። ደም ፈሶ ካለቀ በኋላ መጥረግ ከባድ ነው። ፀሀይ መውጫዋን ለውጣ ስትመጣ ወደ ጌታህ መመለስም አይቻልም። t.me/abdu_rheman_aman

~ጅራፍ ራሱን መቶ ራሱ ይጮሀል! ልክ እንደዚሁ የአንዳንድ ሰዎች ባህሪ እንዲህ ናቸዉ! =

~እንባዋ ትልቁ የፍቅር መግለጫዋ ነው። ስታለቅስ ከአይኖቿ የወረዱት እያንዳንዱ የእንባ ዘለላ የልቧ ቃላቶች ናቸው። ጊዜህን ስለሰጠኸኝ፣ በውሸት ሳቄ ከመሳቅ ይልቅ የምር እንባዬን ሳነባ ሊሰማኝ የሚችለውን እፎይታ ሽተህ ስላዳመጥከኝ አመሰግንሀለሁ ማለቷ ነው። ሰው ሳቁን የሚያጅብለት ሳይሆን እንዲያለቅስ የሚፈቅድለትን ነው ለማግኘት የሚቸገረው። ጥልቅ ህመም የዋጡት፣ የሚሰብራቸው በሞላበት ላለመውደቅ እየታገሉ የሚኖሩት የሚያነቡት እንባ፣ እንባ ብቻ አይደለም! የፍቅርና የአክብሮት መግለጫም ነው። እንባዋን ስታሳየኝ እንደምታምነኝ ገባኝ። አቅም ካጡት ቃላቶቿ የበለጠ ሀያዕ ያለው እንባዋ ብዙውን ይናገራል።እንባዋ የልቧ ነው። ሳቋ ግን የፊቷ ባርያ ከሆነ ሰንብቷል። ከመሳቅ ይልቅ ለማልቀስ አቅም ይጠይቃል። እንባ ወጪ ወራጁ የሚያየው ተራ ሳቅ አይደለም። እንባ ለወጪ ወራጁ የሚቀርብ የውሸት ፈገግታ ሳይሆን ላመኑት የሚገለጥ ውበት ነው። ☞የደበቀውን እንባ ያሳያችሁን ሰው ማክበር አይጥፋችሁ። እቴዋ ሰላም ለልብሽ! =t.me/AbuSufiyan_Albenan

ምናልባትም "እድል"… በምናገኛቸው ውብ ነገሮች አይለካም… ባልደረሱብን  መጥፎ ነገሮች እንጂ… ጤናህን አቅልለህ አትመልከት… ለመተንፈስ ሌላ መሳሪያ ሚፈልጉ፣ መመልከት የማይችሉና አልጋ ላይ አመታትን ያሳለፉ ፍጡራንም አሉ። … ምንም ባይኖርህም… እጅግ ትልቅ ፀጋ ላይ ነህ…አመስግን። t.me/abdu_rheman_aman

~ የፍቅርን አቅም ማየት ከፈለግክ ኡመሩል ፋሩቅ የረሱሉላህ ﷺ ህልፈት የተነገራቸው ጊዜ የሆኑትን ልብ በል፣ ~ የሚወዱትን ዳግም ሊያዩት እንደማይችሉ ሲያውቁ ያለውን ሀዘን መቃኘት ከፈለግክ፤ ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ረሱሉላህን ሲሰናበት ያለውን አስተውል። ~ ንፁህ ፍቅር ትዝታው ከባድ እንደሆነ ለማየት ቢላል ኢብኑ ረባህ ወደ መዲና ተመልሶ መጥቶ አዛን ሲል ስለነበረው ክስተት መርምር። ~ ልብ እጅግ የሚመኘውን ንፁህ ፍቅር ሲያገኝ ትንሽ ማየት ከፈለግክ «አላህ ሆይ ለኔና ለሙሀመድ ብቻ ምህረት አድርግ፣ ሌሎቹን ግን ቅጣቸው » ስላለው አዕራብይ ሁኔታ አስብ። ~ ፍቅር ልቦችን እንደሚያናግር ማወቅ ከፈለግክ ስለ ረሱሉላህ ሲወራ የአማኞችን ፊት ተመልከት።…ﷺ ﷺ =t.me/AbuSufiyan_Albenan

ሃብት እና ትዳር ~ ለትዳር ሃብት ያለውን ወይም ያላትን መምረጥ ምንም የሚያስወቅስ ነገር የለውም። የሚያስወቅሰው ሃብትን ብቻ በማየት የማይሆን ሰው ማግባት ነው። "ባለ ዲኗን ምረጥ" የሚለው ሐዲሥ መልእክቱ ከዚህ አንፃር የሚታይ ነው። ስለዚህ ሴቷ ተውሒድ ያለው፣ ሶላት የሚሰግድ፣ አላህን የሚፈራ እስከሆነ ድረስ ሃብት ያለውን ብትመርጥ ጥሩ ውሳኔ ነው የወሰነችው። ሃብት አይታ ሄደች ተብላ የምትወቀስበት ምንም አይነት ውሃ የሚያነሳ ምክንያት የለም። ወንዱም ላይ ተመሳሳይ ነገር ማለት ይቻላል። የእውነት ትዳር ፈላጊ እስከሆነ ድረስ ገንዘቤን ፈልጎ ሊሆን ይችላል የመጣው እያልሽ አትመልሺ። ወይም ከገባሽ በኋላ ትዳርሽን በአጉል ስሜት አትበጥብጪ። ሃብትሽ ለትዳርሽ ፈተና አይሁንብሽ። ትዳር ጌጥ ነው። ትዳር መከበሪያ ነው። ትዳር ዱንያ ብቻ ሳይሆን ዲንም ነው። እንዲያውም አላህ ሃብት ሰጥቶሽ ከሆነ ሁነኛ ሰው አፈላልገሽ ጥሩ ትዳር ለመመስረት ተጠቀሚበት። "በሃብቷ ልትጫነኝ ትፈልጋለች" የሚል ስሜት አድሮበት ሳይሳቀቅ ቤቴ ብሎ ዘና ብሎ በርትቶ ስራ ላይ እንዲሰማራ አድርጊው። የኸዲጃን - ረዲየላሁ ዐንሃ - ታሪክ አስታውሺ። በሃብታቸው ጥሩ ትዳር የመሰረቱ ብልጥ ሴቶችን እናውቃለን። ሃብታቸው ፈተና ሆኖባቸው ምን የመሰለ ትዳራቸውን አፍርሰው የተፀፀቱ ሴቶችንም እናውቃለን። በሌላ በኩል ከገንዘብ ውጭ ለትዳር ቦታ የሌለው፣ ስግብግብ ወንድም ያጋጥማል። ሰው እንደ አገዳ ተነክሶ አይለይም። አስተውሎ፣ ሰው አማክሮ ዲኑ እና ስነ ምግባሩ ያማረ የሆነውን መምረጥ፣ ዱዓእ ማድረግ፣ በአላህ ላይ መውወከል፣ በራስ በኩል ያለን ኃላፊነት እስከ ጥግ መወጣት ለዘላቂ ትዳር ሁነኛ ሰበቦች ናቸው። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor