en
Feedback
🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️

🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️

Open in Telegram

ቻናሉ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያጋራል። አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል። ጠበቃ ካሊድ ከበደ እና ጠበቃ አማረ እሸቱ በማንኛዉም የፌዴራል እና የክልል ፍ/ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ ስልክ- 0935439820 💌- khalidbinkebe@gmail.com 0919311915 -💌 amareeshetu423@gmail.com አደራሻ:- ቆቦ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ደሴ እና አዲስ አበባ

Show more
2 274
Subscribers
+224 hours
+307 days
+8830 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
July '26
July '26
+78
in 0 channels
June '26
+93
in 1 channels
Get PRO
May '26
+72
in 2 channels
Get PRO
April '26
+68
in 2 channels
Get PRO
March '26
+62
in 5 channels
Get PRO
February '26
+53
in 0 channels
Get PRO
January '26
+37
in 1 channels
Get PRO
December '25
+67
in 3 channels
Get PRO
November '25
+53
in 3 channels
Get PRO
October '25
+60
in 1 channels
Get PRO
September '25
+46
in 2 channels
Get PRO
August '25
+50
in 1 channels
Get PRO
July '25
+41
in 1 channels
Get PRO
June '25
+31
in 1 channels
Get PRO
May '25
+66
in 3 channels
Get PRO
April '25
+66
in 1 channels
Get PRO
March '25
+68
in 0 channels
Get PRO
February '25
+99
in 3 channels
Get PRO
January '25
+131
in 3 channels
Get PRO
December '24
+131
in 2 channels
Get PRO
November '24
+37
in 0 channels
Get PRO
October '24
+33
in 0 channels
Get PRO
September '24
+38
in 0 channels
Get PRO
August '24
+25
in 0 channels
Get PRO
July '24
+21
in 0 channels
Get PRO
June '24
+10
in 0 channels
Get PRO
May '24
+11
in 0 channels
Get PRO
April '24
+21
in 1 channels
Get PRO
March '24
+59
in 3 channels
Get PRO
February '24
+10
in 1 channels
Get PRO
January '24
+120
in 0 channels
Get PRO
December '23
+25
in 1 channels
Get PRO
November '23
+21
in 0 channels
Get PRO
October '23
+20
in 0 channels
Get PRO
September '23
+8
in 0 channels
Get PRO
August '23
+10
in 0 channels
Get PRO
July '23
+29
in 0 channels
Get PRO
June '23
+49
in 0 channels
Get PRO
May '23
+62
in 0 channels
Get PRO
April '23
+24
in 0 channels
Get PRO
March '23
+169
in 0 channels
Get PRO
February '23
+61
in 0 channels
Get PRO
January '23
+108
in 0 channels
Get PRO
December '22
+18
in 0 channels
Get PRO
November '22
+64
in 0 channels
Get PRO
October '22
+7
in 0 channels
Get PRO
September '22
+5
in 0 channels
Get PRO
August '22
+11
in 0 channels
Get PRO
July '22
+10
in 0 channels
Get PRO
June '22
+24
in 0 channels
Get PRO
May '22
+45
in 0 channels
Get PRO
April '22
+13
in 0 channels
Get PRO
March '22
+36
in 0 channels
Get PRO
February '22
+146
in 0 channels
Get PRO
January '22
+16
in 0 channels
Get PRO
December '21
+15
in 0 channels
Get PRO
November '21
+9
in 0 channels
Get PRO
October '21
+10
in 0 channels
Get PRO
September '21
+13
in 0 channels
Get PRO
August '21
+10
in 0 channels
Get PRO
July '21
+27
in 0 channels
Get PRO
June '21
+26
in 0 channels
Get PRO
May '21
+42
in 0 channels
Get PRO
April '21
+19
in 0 channels
Get PRO
March '21
+534
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
20 July+5
19 July+4
18 July+4
17 July+5
16 July+1
15 July+6
14 July+11
13 July+6
12 July+1
11 July0
10 July+2
09 July+4
08 July+6
07 July+2
06 July+2
05 July+4
04 July0
03 July+4
02 July+4
01 July+7
Channel Posts
የፎረንሲክ ምርመራና የሚቀርብበት ጊዜ = ፊርማው የተከሳሽ ነው ወይስ አይደለም የሚለው መረጋገጥ ያለበት ተከሳሽ መከላከያ ምስክር ካሰማ በሗላ ነው ወይስ ተከላከል አትከላከል ከመባሉ በፊት? =ተከሳሽ
+8
የፎረንሲክ ምርመራና የሚቀርብበት ጊዜ = ፊርማው የተከሳሽ ነው ወይስ አይደለም የሚለው መረጋገጥ ያለበት ተከሳሽ መከላከያ ምስክር ካሰማ በሗላ ነው ወይስ ተከላከል አትከላከል ከመባሉ በፊት? =ተከሳሽ ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅቷል በሚል ተጠያቂ ለማድረግ የተከሳሽ ፊርማ ናሙና የሚወሰደው በአዲስ እንዲፈርም በማድረግ ነው ወይስ አሁን ቀደም በተለያየ ሰነዶች የፈረማቸውን ፊርማዎች በማሰባሰብ ነው የሚሉትን ጥያቄዎች በሚመልስ መልኩ ሰበር የሰጠውን የህግ ትርጉም:- የሰበር ውሳኔ:- ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት በኩል ፊርማው የተከሳሽ ነው ወይስ አይደለም የሚለው በፎረንሲክ ምርመራ እንዲረጋገጥ የሚደረገው ተከሳሽ ተከላከል ከመባሉ በፊት እንጅ ተከላከል ተብሎ መከላከያ ምስክር ካሰማ በሗላ ድጋሜ የማስተባበል እድል በማያገኝበት ደረጃ የፊርማ ፎረንሲክ ምርመራ ውጤት እንዲመጣ በማድረግ ተጠያቂ ማድረግ ተገቢ ስላልሆነ ውድቅ ተደርጉል፣ የፊርማ ናሙና የሚወሰደው ከዚህ በፊት ከተለያየ ሰነድ የፈረማቸውን ሰነዶች በማሰባሰብ እንጅ በአዲስ እንዲፈርም የሚደረግበት የህግ አግባብ የለም በሚል ውሳኔ ሰጥቶበታል። ሙሉ ይዘቱን ከውሳኔ ማየት ይቻላል።

2
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ሕግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ (በየጉዳዮች የተደራጀ ልዩ እትም) ታትሞ ወጥቷል። ‎ ‎ይህንን ህትመት 4 ኪሎ በሚገኘው በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ዋና መስሪያ ቤት እንዲሁም ልደታ ፍርድ ቤት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በሚገኘው የብርሃንና ሰላም ሽያጭ መደብር የሚያገኙ ሲሆን ሶፍት ኮፒውን እዚሁ አያይዘናል። የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ 👉ዌብ ሳይት ↠ https://www.fsc.gov.et/ 👉ፌስቡክ ↠ https://web.facebook.com/FSCEthiopia 👉ትዊተር (ኤክስ) ↠ https://x.com/federalsupreme1 ሊንክድኢን ↠ https://tinyurl.com/supereme-court-of-ethiopia 👉ቴሌግራም ↠ https://t.me/fscethiopiaPR 👉ዋትስአፕ ↠ https://tinyurl.com/fscethiopia 👉ዩቲዩብ ↠ https://www.youtube.com/@fscethiopia 👉ቲክቶክ ↠ https://tiktok.com/@federal.supreme.court
485
3
👉ለወሮታ ክፍያ መሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጥ በማስፈለጉ የሕገወጥ ዕቃዎች መረጃ አሰጣጥ ፣ አያያዝ ፣ አመዘጋገብ እና የወሮታ ክፍያዎችን ለመወሰን መመሪያ ቁጥር78/2004 ተሻሽሎ መውጣቱን የመመሪያው መቅድም (preamble) ያመለክታል፡፡ 👉ጥቆማ በተለያዬ መንገድ ሊቀርብ የሚችል መሆኑን ፣ ጠቋሚው የወሮታ መቀበያ ቅፅ የመሙላት ግዴታ ያለበት መሆኑ ፣ የቅጹ ዋና ቅጅ ለጠቋሚው የሚሰጥ መሆኑን ፣ የጥቆማ ምዝገባው ምስጢራዊነቱን የጠበቀ መሆን እንዳለበት ፣ የጠቋሚ የምስጥር መለያ ጠቋሚው የሚለይበት እና ጠቋሚው ከባለሥልጣኑ ጋር ለሚያደርገው ማንኛውም ግንኙነት የተለየ የሚስጥር መለያ ቁጥር ለእያንዳንዱ ጠቋሚ የሚሰጥ መሆኑን ፣ ጠቋሚው የወሮታ ከፍያ ጥያቄን በሚያቀርብበት ወቅት የወሮታ መቀበያ ቅፅ ዋና ቅጅ የማቅረብ ግዴታ ያለበት መሆኑ ከመመሪያው ቁጥር 6, 7(1),7(2), 8(1), 9, 10 እና 16(3) ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል፡፡ 👉በተያዘው ጉዳይ አመልካች የወሮታ ክፍያ ጥያቄ ያቀረበው የወሮታ መቀበያ ቅፅ ሞልቶ የቅጹን ዋና ቅጅ አቅርቦ አለመሆኑ በፍሬ ነገር ደረጃ ተረጋግጧል፡፡ 👉ተጠሪ የወሮታ ክፍያውን ለመጠየቅ አስቀድሞ የወሮታ መቀበያ ቅፅ ሞልቶ በመያዝ በሕጉ የተመለከተውን ቅድመ ሁኔታ አሟልቶ ጠቋሚ መሆኑ የሚለይበትን የወሮታ መቀበያ ቅፅ የማቅረብ ግዴታውን ሳይወጣ የቀረጥ ነፃ መብት ከተፈቀደለት ዓለማ ውጭ ጥቅም ላይ መዋሉን ጥቆማ ስለሰጠ ዕቃው ወደ ሀገር ውስጥ በገባ ጊዜ ሊከፈል ይገባ የነገረውን ቀረጥና ታክስ 20% የጠቋሚ እንዲከፈለው ያቀረበው ክስ የሕግ ድጋፍ ያለው አይደለም፡፡ 👉የሰበር መዝገብ ቁጥር 214138 ሚያዚያ 24 ቀን 2014 ዓ/ም
727
4
አንድ ክስ ከዚህ ቀደም በእርቅ ተዘግቶ የነበረ መሆኑ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባይነሳም እንኳ፣ በፍሬ ነገር ክርክር ወቅት መነሳቱ እስካልቀረ ድረስ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን እንደ መጀመሪያ ደረጃ መ+3
አንድ ክስ ከዚህ ቀደም በእርቅ ተዘግቶ የነበረ መሆኑ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባይነሳም እንኳ፣ በፍሬ ነገር ክርክር ወቅት መነሳቱ እስካልቀረ ድረስ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ቆጥሮ ቀድሞ እልባት ሊሰጠው ይገባል ። ሰ/መ/ቁ 222041፣ ጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ.ም
770
5
👉በአገራችን የማይንቀሳቀስ ንብረት በሕዝቡ ዘንድ ካለዉ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የተነሳ የፍትሐ ብሔር ሕጋችንና የፍትሐ ብሔር ፍትህ አስተዳደሩ በአጠቃላይ ለዜጎች የማይንቀሳቀስ የንብረት መብት ልዩ ጥበቃ ያደርጋል፡፡ 👉ከዚህ አንጻር ከዘረጋዉ የጥበቃ ሥርዓት ዉሰጥ አንዱ በፍትሐ ብሔር ሕጉ የተለያዩ አናቅጽ የማይንቀሳቀስ ንብረት ለማስተላለፍ የሚደረጉ ዉሎች መከተል ያለባቸዉ ፎርማሊቲዎች እና ስለ ምዝገባ የተደነገገዉ ነዉ፡፡ (አንቀጽ 1553-1646 እንዲሁም 1723፣ 2878 እና 3052 ይመለከቷል)፡፡ 👉እነዚህ ድንጋጌዎች የየራሳቸዉ የሆኑ ዓላማዎች ያላቸዉ ቢሆንም፤ አጠቃላይ ዓላማቸዉ ግን ለማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ልዩ ጥበቃ በመስጠት እነዚህን ንብረቶች በተመለከተ ባለይዞታዉ መብቱን ሲያገኝ ወይም ንብረቱ በሆነ ምክንያት ወደ ሌላ ሦስተኛ ወገን በሚያስተላልፍበት ወቅት የመመዝገብ ስልጣን በተሰጠዉ መንግስታዊ አካል ካልተመዘገበ ሕግ ፊት የሚጸና መብት እንዳይኖረዉ በማድረግ ዜጎች በዚህ ግዙፍነት ባለዉ ንብረት ላይ ያላቸዉን መብት ከፍላጎታቸዉ ዉጪ በሆነ መንገድ እንዳያጡ ጥበቃ ለመስጠት፤ ብሎም ንብረቱ ወይም ንብረቱን የሚመለከቱ መብቶች በዉል ሊተላለፉ የሚችሉ መሆን ያለመሆኑንም በማጣራት የዉሉን ሕጋዊነት ለማረጋገጥ ጭምር ስለመሆኑ ከየድንጋጌዎቹ ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበዉ ነዉ፡፡ 👉የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ ከሚከናወኑት ሕጋዉያን ተግባራት ጋር በተያያዘ ምዝገባ ወይም ዉሉ በሚመለከተዉ አካል ዘንድ እንዲረጋገጥ የግድ ከሚልባቸዉ ዉስጥም አንዱ በፍትሐ ብሔር ሕጉ አንቀጽ 1723(1) ስር የተመለከተዉ ድንጋጌ ሲሆን፣ በዚህ ድንጋጌ መሠረትየማይንቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ የሚደረጉ ዉሎች በጽሑፍና ዉል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠዉ አካል ፊት መሆን አለበት፡፡ 👉 ሕግ አዉጪዉ ይህ እንዲሆን የፈለገበት ምክንያትም ዉሉ በተዋዋዮች መካከል ስለመደረጉ ለማረጋገጥ (certainty in transactions) ስለመሆኑ በዙሪያዉ ከተፃፉት አንዳንድ ጽሑፎች መገንዘብ የሚቻል ሲሆን፤ ይህ ሰበር ችሎትም በሰ/መ/ቁጥር 36887 ላይ በሰጠዉ የህግ ትርጉም በዚህ ድንጋጌ መሠረት የሚከናወን የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ምዝገባ ዓላማ በተዋዋይ ወገኖች መካከል ዉል መኖሩን ለማስረዳት ስለመሆኑ ወስኗል፡፡ 👉ከላይ እንደተመለከተዉ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገዉ ፎርማሊቲ በተዋዋዮች መካከል በፀና አኳኋን የተደረገ ዉል መኖሩን ለማረጋገጥና በዋናነት የተዋዋዮቹን መብት ለመጠበቅ የተደነገገ ሲሆን በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2878 እና በሌሎች ከላይ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች የተመለከተዉ ምዝገባ (Registration) ደግሞ ተዋዋዮች የማይነቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ለማስተላለፍ ወይም ባንድ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የአላባ ጥቅም መብት ወይም የመያዣ ወይም የሌላ አገልግሎት መብት ለመቋቋም ወይም በድንጋጌዎቹ ላይ የተመለከቱትን ሌሎች መብቶችን ለመመስረት ዉል በመዋዋላቸዉ የሦስተኛ ወገኖች መብትና ጥቅም እንዳይነካ ለሦስተኛ ወገኖች ጥበቃ ለማድረግ ነው። 👉 በመሆኑም ዉሉ በማዘጋጃ ቤት በሚገኝ ማህደር ዉስጥ ስለሚገኝእንደተመዘገበ ይቆጠራል ብለዉ ያቀረቡት ክርክርም ቢሆን ይሕ ተግባር ተፈጽሞ ቢሆን እንኳን በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገዉን የፎርም ስርዓት የሚተካ ካለመሆኑም በላይ ይህ ተፈጸመ ያሉት ስርዓት የተዋዋዮቹን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የተዘረጋ ስርዓት አይደለም። 👉የሰ/መ/ቁ፡-199400 ቀን፡ 03/02/2014ዓ.ም
1 173
6
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞችን አዋጅ ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር 309/2018
746
7
👉ቼክ ተላላፊ የገንዘብ ሠነድ በመሆኑና በዋስትናነት አይሰጥም በሚል በሕግ የተደነገገ ክልከላ ባለመኖሩ በመርህ ደረጃ ቼክ ለዋስትና ሊሰጥ ይችላል፡፡ 👉ሆኖም በሰበር መዝገብ ቁጥር 166392 ላይ በቀን 26/08/2012 ዓ/ም በተሰጠ ዉሳኔ ላይ በመርህ ደረጃ አግባብነት ያለዉ የፍ/ብ/ህጉና የንግድ ህጉ ለቼክ የሰጡት ዋና ዓላማ ለመያዣነት እንዲያገለግል ነዉ ባይባልም እንደማንኛዉም ሊተላለፉ እንደሚችሉ ሰነዶች በመያዣነት ወይም በዋስትና ሊሰጥ እንደሚችልና ይህ በሚሆንበት ጊዜ ግን በንግድ ህጉና በፍ/ብ/ህጉ ላይ በተቀመጡት ግልፅ ድንጋጌዎች መመራት ይኖርበታል (የን/ህ/ቁ 950 ና ፍ/ብ/ህ/ቁ. 2866)። 👉በተለይ የመያዣ ዉል ስምምነት በሚደረግ ጊዜ ዉሉ መከተል ስላለበት ፎርም በተመለከተም በግልፅ የተደነገገ ስለመሆኑ ከን/ህጉ ቁ. 952 እና የፍ/ብ/ህጉ ቁ. 2828 መመልከት ይቻላል። 👉 የመያዣ ወይም የዋስትና ዉል ህጉ በፅሑፍ በሰነድ ካልተደረጉ በህግ ፊት ዋጋ የላቸዉም (ፈራሽ ናቸዉ) በማለት ከደነገጋቸዉ ጥቂት የዉል ዓይነተች ዉስጥ አንዱ ስለመሆኑ ግልፅ ነዉ (የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1725(ሀ)፤ 1922(1-3)፣ 2828(1-2))። ሌላዉ ደግሞ የመያዣዉ ስምምነት ለምን ግዴታ እንደተደረገ፣ የግዴታዉ መጠን (ከፍተኛ የገንዘብ ወሰን) በጥንቃቄ ግልፅ መደረግ እንዳለበትናስምምነቱ የተደረገበት ቀን በግልፅ ልቀመጥ እንደሚገባ ህጉ የግድ ይላል (የፍ/ብ/ህ/አንቀጽ 2828 (1-2)፣ 2864-2866ና የን/ህ/ቁ. 952)። እነዚህ የህጉ አስገዳጅ ድንጋጌዎች ካልተሟሉ የመያዣ ስምምነት ዉል አለ ማለት አይቻልም። 👉 ስለሆነም ቼኩ የተሰጠዉ ለዋስትና ዓላማ እንደሆነ ተገልጾ በጽሁፍ የዋስትና ዉል ስምምነት ካልተደረገ በስተቀር ቼክ ለዋስትና አላማ ተሰጥቷል በሚል የሚቀርብ ክርክር ተቀባይነት እንደሌለዉ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡ 👉ተጠሪ ቼኩን የሠጡት የዕቁብ ዕጣ ሲወጣላቸው ለዋስትና ዓላማ ከሆነ ይሕ ስለመሆኑ በጸሁፍ የተደረገ የመያዣ ውል (pledge) በማቅረብ ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 👉የሰ/መ/ቁ. 201980 ቀን ፡- ህዳር 27 ቀን 2014 ዓ/ም
1 373
8
👉 በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 94 መሠረት ጋብቻ መኖሩን ማስረዳት የሚቻለው በጋብቻ የምስክር ወረቀት መሆኑ የተደነገገ ሲሆን የምስክር ወረቀቱ በሌለ ጊዜ የትዳር ሁኔታ መኖርን በማስረዳት ጋብቻ እንዳለ ማረጋገጥ እንደሚቻል ከሕጉ አንቀጽ 96 እና 97 ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ 👉ነገር ግን በተያዘው ጉዳይ አመልካችና ተጠሪ ፎቶ ግራፍ ተነስተዋል የተጠሪ እህትም እራት ጋብዘዋል መባሉ በህጉ በሚታወቁት ጋብቻዎች ሥርዓት ጋብቻ ተፈጽሟል የሚያሰኝ አይደለም፡፡ 👉በዚህ መልኩም የትዳር ሁኔታ መኖሩን አሳይተዋል ሊባልም አይችልም፡፡ 👉ከመነሻውም የአሁን ተጠሪ አስቀድመው ካቀረቡት አቤቱታና በዚህ ፍርድ ቤት ከሰጡት መልስ መገንዘብ የሚቻለው እራሳቸው ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበራቸው ግንኙነት ጋብቻ የፈፀሙ ባልና ሚስት ሳይሆን እንደባልና ሚስት ግንኙነት መሆኑን እንደሚቆጥሩት እና የተጠሪ ቤተሰቦችም ባልና ሚስት ናቸው በማለት ያልተቀበላቸው እንደነበር የሚያሳይ ነው። 👉 ይህ አይነቱ ሁኔታ ደግሞ በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 96 መሠረት በመካከላቸው የትዳር ሁኔታ መኖሩን የሚያስገነዝብ አይደለም፡፡ በቤተሰብ ህጉ በአንቀጽ 97/1/ መሠረትም ግምት መውሰድ የሚቻልበት አይደለም። 👉 የሰ/መ/ቁ. 246124 ጥቅምት 6 ቀን 2015
1 172
9
👉በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጋችን ከቁጥር 467 እስከ 479 ስር በተደነገገዉ መሰረት ገንዘብ የሌለዉና ለማግኘት የማይችል ማንኛዉም ደኃ ሰዉ ለሚያቀርበዉ ክስ የሚያስፈልገዉን የዳኝነት ገንዘብ በሙሉም ሆነ በከፊል ለመክፈል የማይችል መሆኑን ገልጾ አቤቱታዉን ካቀረበና ይህንኑ በተዘረጋዉ ስርዓት መሰረት በማስረጃ ካስረዳ በሙሉ ወይም በከፊል ዳኝነት ሳይከፍል የክስ መዝገቡ እንዲከፈትለትና በነጻ እንዲከራከር ሊፈቀድለት እንደሚገባ ተደንግጓል፡፡ 👉ሕጉ እነዚህ ድንጋዎች የደነገገበት ዋነኛ ዓላማ ለዳኝነት የሚከፈል ገንዘብ በሙሉም ሆነ በከፊል መክፍል ባለመቻላቸዉ ብቻ ሰዎች በፍርድ ሊወሰን የሚገባን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ወይም ለሌላ በሕግ የዳኝነት ሥልጣን ለተሰጠዉ አካል አቅርበዉ ፍርድ ወይም ዉሳኔ በማግኘት መብትና ጥቅሞቻቸዉን ሳያስከብሩ እንዳይቀሩ የመፍትሔ ሥርዓት በመዘርጋት ለሰዎች ፍትህ የማግኘት መብት ጥበቃ ለማድረግ ነዉ፡፡ 👉በመሆኑም በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕግ ቁጥር 467/1 ስር“…ገንዘብ የሌለዉና ለማግኘት የማይችል… “ ተብሎ የተገለጸዉ ሕጉ ለማሳካት የፈለገዉን የሰዎች ፍትህ የማግኘት መብት በሚያስጠብቅ መልኩ በጠባቡ መተርጎም አለበት፡፡ 👉ምክንያቱም ይህ የሕጉ አገላለጽ በሰፊዉ የሚተረጎም ከሆነ ሰዎች በእጃቸዉ ላይ የሌለን ገንዘብ በፍርድ ቤት አስወስነዉና አስፈጽመዉ ወይም በሌላ አካኋን በእጃቸዉ አስገብተዉ ለሚያቀርቡት ክስ የሚያስፈልገዉን ዳኝነት አግኝተዉ የዳኝነት ገንዘብ እስከሚከፍሉ ድረስ ክስ የማቅረብ መብታቸዉ በይርጋና በመሰል ምክንያቶች ሊታገድ ስለሚችል እንዲሁም የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸዉም ሊጣበብ ስለሚችል በአሁኑ ጊዜ ገንዘብ የሌለዉ መሆኑ እስከተረጋገጠ ድረስ ለወደፊት ገንዘብ የሚያገኝበት እድል በመኖሩ ብቻ የዳኝነት ገንዘብ ሳይከፍል በነጻ መዝገብ እንዲከፈትለት ያቀረበዉ አቤቱታ ተቀባይነት ሊያጣ አይገባም፡፡ 👉በተጨማሪም የዳኝነት ገንዘብ ሳይከፈል በነጻ መዝገብ ከተከፈተ በኋላ መዝገቡን ያስከፈተዉ ሰዉ ገንዘብ በሚያገኝበት በማንኛዉም ጊዜ የዳኝነት ገንዘብ እንዲከፍል የሚደረግብትን ሥርዓት የሥነ ሥርዓት ሕጉ ስለዘረጋ በተጠቀሰዉ መሰረት የሕጉ አገላለጽ በጠባቡቢተረጎም የሚደርስ የማይተካ ጉዳት የለም። 👉የሠ/መ/ቁጥር 188406 መስከረም 27 ቀን 2013ዓ/ም
1 151
10
👉የሕፃናትን ቀለብ አስመልክቶ ቀለብ እንዲከፍል የተወሰነበት ሰው በየጊዜው እንዲከፍል የተወሰነበትን የቀለብ ገንዘብ ጊዜው ደርሶ ካልከፈለና ለወደፊቱም የማይከፍል ሲመስል የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረቱ ተከብሮ ለቀለብ ክፍያ እንዲውል ማድረጉ የሕፃናትን መብት ከማስከበር አኳያ ተገቢ ከመሆኑም በላይ ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 45819 የመክፈያ ጊዜው ገና ለሆነው የቀለብ ገንዘብ አከፋፈል ጭምር የቀለብ ከፋዩን ንብረት አስከብሮ መያዝ እንደሚቻል ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ 👉ሆኖም የሚታገደው ወይም የሚከበረው ገንዘብ ከዕዳው ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይገባዋል፡፡ ተመጣጣኝ ካልሆነ የተከበረውን ንብረት ወይም ገንዘብ በከፊል ከዕገዳ ነፃ በማድረግ ማመጣጠን ተገቢ ይሆናል፡፡ 👉የሰ/መ ቁ፡-237498 ቀን፡-05/02/2016ዓ/ም
1 164
11
👉ከክርከሩ እንደሚያሳዉ የጠየቁት ክፍያ የትርፍ ሰዓት፣የበዓላትና የሳምንት የእረፍት ቀናት የሰሩበት በተጨማሪነትም የአልጋ አበል ታስቦ እንዲከፈላቸዉ ነዉ፡፡ 👉አመልካች አጥብቆ የሚከራከረዉ እነዚህ ከፍያዎች ለመክፈል የሚያስችል የሥራ ትእዛዝ አልሰጠሁም፤የዉል ግዴታም የለም በማለት ነዉ፡: 👉በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ እንደተመለከተዉ የትርፍ ሰዓት፤የሳምንት የእረፍት ቀናት እና የበዓል ቀናት ስራ ለመስራት ሰራተኛዉ የሚገደደዉ በህግ በተመለከቱ ዉስን ምክንያቶች ስለመሆኑና በአሰሪዉ ትእዛዝ መሰጠቱ መረጋገጥ እንዳለበት ህጉ ያስገነዝባል፡፡ 👉አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 66-72ያሉት ድንጋጌዎች ይመለከታል፡፡ከዚህ መገንዘብ እንደሚቻለዉ ሰራተኛዉም እነዚህን ክፍያዎች ሊጠይቅ የሚችለዉ እና አሰሪዉም ከፍያዉን ለመክፈል የሚገደደዉ ስራዉ በአሰሪዉ እዉቅና እና በተሰጠዉ የስራ ትእዛዝ መሰረት መስራቱን ሰራተኛዉ ማስረዳት ከቻለ ነዉ፡፡ 👉የትርፍ ሰኣት፣የበዓል ቀናትና የሳምንት እረፍት ጊዜ ጋር የተያያዙ ክፍያዎች በባህርያቸዉ ሰራተኛዉ እንደመብት የሚጠይቀዉ ሳይሆን ለስራዉ መልካም አካሄድ አስፈላጊ መሆኑ በአሰሪዉ ታምኖበት ትእዛዝ ሲሰጥ እና ሰራተኛዉም ተስማምቶ በተሰጠዉ ትእዛዝ መሰረት መስራቱ ሲረጋገጥ የሚፈጸም መሆኑ ነዉ፡: 👉የሰ/መ/ቁ፡-206765 ቀን፡-30/03/2014ዓ/ም
1 029
12
👉በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 231(1) መሠረት በክስ አቤቱታው የተገለጸው የማያስከስስ መሆን መሆን አለመሆኑን ፍርድ ቤቱ የመመርመር ኃላፊነት አለበት፡፡ 👉የክስ ምክንያት ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ ግዴታ መኖሩን፣ የተጠየቀው ዳኝነት በፍርድ ቤት የሚዳኝ መሆን አለመሆኑን እና በክሱ ዝርዝር ውስጥ የተመለከቱት ጉዳዮች ቢረጋገጡ የተጠየቀውን ዳኝነት ለከሳሽ ለመወሰን ህግ የሚፈቅድ መሆን አለመሆኑን መመርመርን የሚጠይቅ ነው፡፡ 👍ይህም የክስ ምክንያት የሌለው ጉዳይ የሚለው በዋነኛነት ዳኝነቱን ለመጠየቅ ከህግ የመነጨ ግንኙነት እያለው ግን በፍርድ ቤት ሊዳኙ የማይችሉ ጉዳችን (non-justiciable matters) ፍርድ ቤት አከራክሮ ሊፈጸም የሚችል ውሳኔ ሊሰጥባቸው የማይችሉ በመሆናቸውና ከሳሽ ወገን ክሱን ሲያቀርብ የጠቀሰው ወይም የገለጸው የክሱ መሰረት የሆነው ምክንያት በህግ የክስ መሰረት ሊሆን የማይችል ከሆነ የማያስከስስ ነው ተብሎ ክሱ ውደቅ የሚደረግበት ሥርዓት ነው። 👉/መ/ቁ 206699 ሚያዚያ 28 ቀን 2014 ዓ/ም
1 059
13
👉አንድ ሰዉ የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የተሠጠዉ ዉሳኔ መብቴን ነክቷል የሚል ከሆነ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት መቃወሚያ በማቅረብ የሚተናገድበት ሥርዓት ያለ መሆኑን፤ በሌላ በኩል በፍርድ አፈጻጸም ክርክር ላይ ለፍርድ ማስፈጸሚያ የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት የፍርድ ባለእዳ ሳይሆን የእኔ ነዉ ባይ ሶስተኛ ወገን ንብረቱ ለፍርድ ማስፈጸሚያ ሊዉል አይገባም የሚልበትን ምክንያት በመግለጽ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 418 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች መሰረት የሚስተናገድ ሥርዓት አለ፡፡ 👉 የእነዚህ ድንጋጌዎች ይዘት፣ ዓላማና አተገባበር አድማስ አስመልክቶ የፈዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 29653፣ 53067፣55842፤ 141600 የክርክሩ ተካፋይ ያልነበረ ሶስተኛ ወገን በዋናዉ ክርክር ላይ የተሰጠዉ ፍርድ መብቱን የሚነካ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም ሊቀርብ የሚገባዉ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት መሆን እንዳለበት እና በሌላ በኩል ፍርድ ያላረፈበት ንብረት በፍርድ አፈጻጸም ምክንያት በፍርድ ባለመብት ጥያቄ መሠረት እንዲከበር ወይም እንዲያዝ ሲደረግ ንብረቱ ላይ ሊፈጸም አይገባም የሚል ሶስተኛ ወገን መቃወሚያዉን ማቅረብ ያለበት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 418 መሠረት እንደሆነ፤ የሁለቱም ድንጋጌዎች መሠረታዊ ልዩነቱም የፍ/ብ/ሥ/ስ/ሕ/ቁ 358 ተቃዋሚ ወገን የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን ጥቅሙን የሚነካ ፍርድ የተሰጠ እንደሆነ ፍርዱ እንዲሰረዝ አቤቱታ የሚያቀርብበት ስርዓት የሚመለከት መሆኑን፤ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 418 ደግሞ ለፍርድ ማስፈጸሚያ በሚል በአፈጻጸም ክርክር የተያዘ ንብረት ለማስለቀቅ የመቃወም አቤቱታ የሚቀርብበት መሆኑን፤ በዚሁ ድንጋጌ መሰረት በአፈጻጸም ክርክር ላይ በሚቀርብ መቃወሚያ ዋናዉ ፍርድ ሊሻር እንደማይችል በመግለጽ አስገዳጅ የሆነ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ 👉የሰ.መ.ቁ 213479 ግንቦት 29 ቀን 2014 ዓ.ም
1 109
14
👉በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን ባልተሳተፈበት ክርክር ተደርጎ መብቱን የሚነካ ፍርድ መሰጠቱን ባወቀ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም መብቱን ማስከበር እንደሚችል በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ 358 ላይ ተደንግጓል፡፡ 👉ይሁንና ይህንን መብት በመጠቀም ረገድ ክርክሩ መኖሩን እያወቀ በቸልተኝነት ወይም በሌላ ጉድለት የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የቀረ ወገን ከቅን ልቦና ውጪ ጉዳዩን ለማንሳት የሚያቀርበው መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይገባ ሰበር ችሎቱ ቀዳሚ ውሳኔ የሰጠበት መሆኑ ይታወቃል (ሰበር መ/ቁ/56795፤40229፤93987 እና ሌሎች መሰል መዛግብትን ይመለከታል)፡፡ 👉 ​ስለሆነም ባል በተከራከረበት መዝገብ ሚስቲቱ ክርክሩ መኖሩን አውቃ ነበር ወይስ አልነበረም ወይም ክርክሩ መኖሩን እያወቀች ጣልቃ ገብታ መከራከር ሲገባት ከቅን ልቦና ውጪ ውጤቱን ጠብቃ ያቀረበችው አቤቱታ ነው የሚለውን ለመወሰን በእርግጥም የመቃወም አመልካች ቀደም ሲል ክርክር ሲደረግ የነበረ መሆኑን ክርክሩም የእሷን መብት የሚመለከት መሆኑን አውቃ እንደነበር ማረጋገጥ ያለበት ፍሬነገር ጉዳይ ነው፡፡ 👉በመሆኑም ሚስት በመሆኗ ብቻ ክርክሩን ታውቅ ነበር የሚል ግምት ሊወሰድ አይገባም። 👉 የሰ/መ/ቁ247348፣ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ/ም
1 113
15
ተከሳሽ የመከላከያ መልሱን አቅርቦ ክሱ ሊሰማ በተቀጠረበት ዕለት ባለመቅረቡ በፍ/ሥ/ሕ/ቁ 70(ሀ) መሰረት ክርክሩ በሌለበት እንዲታይ ብይን ከተሰጠ የመከላከያ ክርክር የማቅረብ መብቱን ከማሳጣት አልፎ በቀሪዎቹ የክርክር ሂደቶች ከመሳተፍ አያግደውም። የሰ/መ/ቁ 206006
1 418
16
👉 የአንድ መብትና ግዴታ ምንጭ ሕግ ወይም ውል ሲሆን አንድ ከሳሽ ሌላውን ወገን በተከሳሽነት ፍርድ ቤት መክሰስ የሚያስችለው ምክንያት (cause of action) እንዲኖረው የግድ የሚል መሆኑንና ለመክሰስ የሚያስችል ጥቅም ወይም መብት በማረጋገጥ አቤቱታ ካላቀረበ በቀር በማናቸውም ሰው ላይ ክስ ሊያቀርብ የማይችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 33(2)እና(3) ድንጋጌ ያስገነዝባል፡፡ 👉ሆኖም በአንድወገን ላይ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መብት ወይም ጥቅም መኖሩ ብቻውን ውጤት የሚያመጣ ሳይሆንከሳሹ ተጣሰብኝ ወይም ተደፈረብኝ ወይም አልተፈፀመልኝም የሚለውን ግዴታ በሌላው ወገን በሕግ ወይም በውል የተገኘ መብቱ/ ጥቅሙ / የተጣሰበት መሆኑን፣ ተከሳሹ መብቱ የተደፈረበት ወይም ግዴታ ያልተፈፀመበት መሆኑን፣ መብቱ በመደፈሩ ወይም ሊፈፀምለት ይገባው የነበረው ግዴታ ባለመፈፀሙ ጥቅምየቀረበት ወይም ጉዳት የደረሰበት መሆኑን፣ እንዲሰጥለት የሚጠይቀው ዳኝነት (relief) በሕግ የተፈቀደመሆኑን ካለሳዬ በቀር ያቀረበው ክስ ተቀባይነት ሊኖረው የማይገባ ስለመሆኑም ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ33(2)እና(3) ፤ 231 ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ መዘንዘብ ይቻላል፡፡ 👉 በመሆኑም አንድን ክስ የሚያቀርብተከራካሪ ወገን ይህንን ሊያስረዳ የሚችል ጠቋሚ ማስረጃ (Prima facie evidence) ሊያቀርብ ይገባል፡፡ 👉ከሳሽ የሆነው ወገን ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33(2)እና(3) ድንጋጌ አኳያ የሚጠበቅበት ክስ በመሰረተበት ነገር / ሐብት / ላይ ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ መብት ወይም ጥቅም እንዳለው እና ይሄው ጥቅሙ ወይም መብቱ በተከሳሹ የተነካበት ወይም የተጣሰበት መሆኑን እንጂ ገና ተከሳሹ ሳይጠራ በክሱ የተጠቀሰውንፍሬነገር በማስረጃ እንዲያረጋግጥ አይደለም፡፡ 👉ይህም ከሳሽ የሆነው ተከራካሪ ወገን ከጅምሩ እንዲያረጋግጥ የሚጠበቅበት አለኝ የሚለውን መብት በክስ አቤቱታው ላይ እንዲያሳይ እና ይህንንም የሚያረጋግጥለት ጠቋሚ ማስረጃ ማቅረብ እንደሆነ፤ ክስ የማቅረብ መብት ወይም ጥቅም ማስረዳት መቻል እና እንደክሱ አቀራረብ ወይም እንደተጠየቀዉ ዳኝነት ዉሳኔ ለመስጠት የሚያስችል የማስረጃ ምዘና ደረጃ ልዩነት ያላቸው መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ 👉ተከራካሪ የሆኑ ወገኖች የሚያቀርቧቸውን ክርክሮች ለመወሰን በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች ደግሞ ተከሳሽ ወገን ክሱን ለማስተባበል የሚያቀርበውን መከራከሪያ እና ማስረጃ መሠረት በማድረግ ፍሬነገርን አጣርተው እና ማስረጃ መዝነው ዉሳኔ መስጠት የሚጠበቅባቸው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2 እና 231፤ 182 እና 273 ድንጋጌዎች ይዘት ያስገነዝቡናል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም በዚህ ረገድ በተለይም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 እና 231 አተገባበርን አስመልክቶ በሰ.መ.ቁ 82234፤ 135639፤ 144052 እና በሌሎችም መዝገቦች ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ 👉የሰ.መ.ቁ 233250 ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ.ም
1 529
17
Final Draft Regulation of ANRS Land law.pdf
937
18
አዲሱ የአብክመ የማረሚያ ቤት አዋጅ.pdf
977
19
+7
የአብክመ የህግ መፅሄት ቅፅ 1.pdf
1 529
20
👉 በንግድ ህግ ቁጥር 683(1) ላይ "ጉዳት ያደረሱ ሦስተኛ ወገኖች" የሚለው አገላለጽ በቀጥታ ሲታይ መድህን ገቢውን (ባለቤቱን) የማይመለከት ቢመስልም፤ የህጉ ዋና ዓላማ ኢንሹራንሶች ውላቸውን አ+2
👉 በንግድ ህግ ቁጥር 683(1) ላይ "ጉዳት ያደረሱ ሦስተኛ ወገኖች" የሚለው አገላለጽ በቀጥታ ሲታይ መድህን ገቢውን (ባለቤቱን) የማይመለከት ቢመስልም፤ የህጉ ዋና ዓላማ ኢንሹራንሶች ውላቸውን አክብረው ካሳ ከከፈሉ በኋላ ጥፋተኛ ከሆነው አካል ላይ ገንዘቡን እንዲያስመልሱ መፍቀድ ነው። ​👉ጉዳት ያደረሰው ተሽከርካሪ በሌላ ራሱን በቻለ የኢንሹራንስ ድርጅት (ብርሃን ኢንሹራንስ) ስር የሦስተኛ ወገን መድህን ሽፋን ያለው በመሆኑ፣ ሁለቱም መኪናዎች የአንድ ሰው ንብረት ቢሆኑም እንኳ ጉዳት አድራሹን ተሽከርካሪ በተመለከተ አመልካች ለተጠሪ እንደ "ሦስተኛ ወገን" ሊቆጠር ይገባዋል። ​👉 በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2081 እና 2083 መሠረት አንድ የሞተር ተሽከርካሪ ባለቤት መኪናው ላደረሰው ጉዳት ተጠያቂ መሆኑ ስለሚደነገግ፣ አመልካች ከተጠሪ ካሳ ወስዶ "ተጠሪ በመዳረግ ሊጠይቀኝ አይችልም" በማለት ያቀረበው ክርክር የሕጉን ትክክለኛ ትርጉምና ፍትሕን የተከተለ አይደለም። 👉የሰ/መ/ቁ. 235515 ቀን፡28/8/16
995