🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️
前往频道在 Telegram
ቻናሉ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያጋራል። አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል። ጠበቃ ካሊድ ከበደ እና ጠበቃ አማረ እሸቱ በማንኛዉም የፌዴራል እና የክልል ፍ/ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ ስልክ- 0935439820 💌- khalidbinkebe@gmail.com 0919311915 -💌 amareeshetu423@gmail.com አደራሻ:- ቆቦ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ደሴ እና አዲስ አበባ
显示更多2 180
订阅者
+324 小时
+237 天
+6230 天
数据加载中...
标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服。
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+58
在1个频道中
五月 '26
+72
在2个频道中
Get PRO
四月 '26
+68
在2个频道中
Get PRO
三月 '26
+62
在3个频道中
Get PRO
二月 '26
+53
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+37
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+67
在3个频道中
Get PRO
十一月 '25
+53
在2个频道中
Get PRO
十月 '25
+60
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+46
在2个频道中
Get PRO
八月 '25
+50
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+41
在1个频道中
Get PRO
六月 '25
+31
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+66
在3个频道中
Get PRO
四月 '25
+66
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+68
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+99
在3个频道中
Get PRO
一月 '25
+131
在3个频道中
Get PRO
十二月 '24
+131
在2个频道中
Get PRO
十一月 '24
+37
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+33
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+38
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+25
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+21
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+10
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+11
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+21
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+59
在3个频道中
Get PRO
二月 '24
+10
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+120
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+25
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+21
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+20
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+8
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+10
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+29
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+49
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+62
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+24
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+169
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+61
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+108
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+18
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+64
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+7
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+5
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+11
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+10
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+24
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+45
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+13
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+36
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+146
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+16
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+15
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+9
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+10
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+13
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+10
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+27
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+26
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+42
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+19
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+534
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 18 六月 | +3 | |||
| 17 六月 | +2 | |||
| 16 六月 | +3 | |||
| 15 六月 | +5 | |||
| 14 六月 | +5 | |||
| 13 六月 | +9 | |||
| 12 六月 | 0 | |||
| 11 六月 | +4 | |||
| 10 六月 | +2 | |||
| 09 六月 | +2 | |||
| 08 六月 | +2 | |||
| 07 六月 | +3 | |||
| 06 六月 | +2 | |||
| 05 六月 | +4 | |||
| 04 六月 | +1 | |||
| 03 六月 | +3 | |||
| 02 六月 | +1 | |||
| 01 六月 | +7 |
频道帖子
👉ቼክ ተላላፊ የገንዘብ ሠነድ በመሆኑና በዋስትናነት አይሰጥም በሚል በሕግ የተደነገገ ክልከላ ባለመኖሩ በመርህ ደረጃ ቼክ ለዋስትና ሊሰጥ ይችላል፡፡
👉ሆኖም በሰበር መዝገብ ቁጥር 166392 ላይ በቀን 26/08/2012 ዓ/ም በተሰጠ ዉሳኔ ላይ በመርህ ደረጃ አግባብነት ያለዉ የፍ/ብ/ህጉና የንግድ ህጉ ለቼክ የሰጡት ዋና ዓላማ ለመያዣነት እንዲያገለግል ነዉ ባይባልም እንደማንኛዉም ሊተላለፉ እንደሚችሉ ሰነዶች በመያዣነት ወይም በዋስትና ሊሰጥ እንደሚችልና ይህ በሚሆንበት ጊዜ ግን በንግድ ህጉና በፍ/ብ/ህጉ ላይ በተቀመጡት ግልፅ ድንጋጌዎች መመራት ይኖርበታል (የን/ህ/ቁ 950 ና ፍ/ብ/ህ/ቁ. 2866)።
👉በተለይ የመያዣ ዉል ስምምነት በሚደረግ ጊዜ ዉሉ መከተል ስላለበት ፎርም በተመለከተም በግልፅ የተደነገገ ስለመሆኑ ከን/ህጉ ቁ. 952 እና የፍ/ብ/ህጉ ቁ. 2828 መመልከት ይቻላል።
👉 የመያዣ ወይም የዋስትና ዉል
ህጉ በፅሑፍ በሰነድ ካልተደረጉ በህግ ፊት ዋጋ የላቸዉም (ፈራሽ ናቸዉ) በማለት ከደነገጋቸዉ ጥቂት የዉል ዓይነተች ዉስጥ አንዱ ስለመሆኑ ግልፅ ነዉ (የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1725(ሀ)፤ 1922(1-3)፣ 2828(1-2))። ሌላዉ ደግሞ የመያዣዉ ስምምነት ለምን ግዴታ እንደተደረገ፣ የግዴታዉ መጠን (ከፍተኛ የገንዘብ ወሰን) በጥንቃቄ ግልፅ መደረግ እንዳለበትናስምምነቱ የተደረገበት ቀን በግልፅ ልቀመጥ እንደሚገባ ህጉ የግድ ይላል (የፍ/ብ/ህ/አንቀጽ 2828 (1-2)፣ 2864-2866ና የን/ህ/ቁ. 952)። እነዚህ የህጉ አስገዳጅ ድንጋጌዎች
ካልተሟሉ የመያዣ ስምምነት ዉል አለ ማለት አይቻልም።
👉 ስለሆነም ቼኩ የተሰጠዉ ለዋስትና ዓላማ እንደሆነ ተገልጾ በጽሁፍ የዋስትና ዉል ስምምነት ካልተደረገ በስተቀር ቼክ ለዋስትና አላማ ተሰጥቷል በሚል የሚቀርብ ክርክር ተቀባይነት እንደሌለዉ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡
👉ተጠሪ ቼኩን የሠጡት የዕቁብ ዕጣ ሲወጣላቸው ለዋስትና ዓላማ ከሆነ ይሕ ስለመሆኑ በጸሁፍ የተደረገ የመያዣ ውል (pledge) በማቅረብ ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል፡፡
👉የሰ/መ/ቁ. 201980
ቀን ፡- ህዳር 27 ቀን 2014 ዓ/ም
| 2 | 👉 በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 94 መሠረት ጋብቻ መኖሩን ማስረዳት የሚቻለው በጋብቻ የምስክር ወረቀት መሆኑ የተደነገገ ሲሆን የምስክር ወረቀቱ በሌለ ጊዜ የትዳር ሁኔታ መኖርን በማስረዳት ጋብቻ እንዳለ ማረጋገጥ እንደሚቻል ከሕጉ አንቀጽ 96 እና 97 ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡
👉ነገር ግን በተያዘው ጉዳይ አመልካችና ተጠሪ ፎቶ ግራፍ ተነስተዋል የተጠሪ እህትም እራት ጋብዘዋል መባሉ በህጉ በሚታወቁት ጋብቻዎች ሥርዓት ጋብቻ ተፈጽሟል የሚያሰኝ አይደለም፡፡
👉በዚህ መልኩም የትዳር ሁኔታ
መኖሩን አሳይተዋል ሊባልም አይችልም፡፡
👉ከመነሻውም የአሁን ተጠሪ አስቀድመው ካቀረቡት አቤቱታና በዚህ ፍርድ ቤት ከሰጡት መልስ መገንዘብ የሚቻለው እራሳቸው ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበራቸው ግንኙነት ጋብቻ የፈፀሙ ባልና ሚስት ሳይሆን እንደባልና ሚስት ግንኙነት መሆኑን እንደሚቆጥሩት እና የተጠሪ ቤተሰቦችም ባልና ሚስት ናቸው በማለት ያልተቀበላቸው እንደነበር የሚያሳይ ነው።
👉 ይህ አይነቱ ሁኔታ ደግሞ በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 96 መሠረት በመካከላቸው የትዳር ሁኔታ መኖሩን የሚያስገነዝብ አይደለም፡፡ በቤተሰብ ህጉ በአንቀጽ 97/1/ መሠረትም ግምት መውሰድ የሚቻልበት አይደለም።
👉 የሰ/መ/ቁ. 246124 ጥቅምት 6 ቀን 2015 | 471 |
| 3 | 👉በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጋችን ከቁጥር 467 እስከ 479 ስር በተደነገገዉ መሰረት ገንዘብ የሌለዉና ለማግኘት የማይችል ማንኛዉም ደኃ ሰዉ ለሚያቀርበዉ ክስ የሚያስፈልገዉን የዳኝነት ገንዘብ በሙሉም ሆነ በከፊል ለመክፈል የማይችል መሆኑን ገልጾ አቤቱታዉን ካቀረበና ይህንኑ በተዘረጋዉ ስርዓት መሰረት በማስረጃ ካስረዳ በሙሉ ወይም በከፊል ዳኝነት ሳይከፍል የክስ መዝገቡ እንዲከፈትለትና በነጻ እንዲከራከር ሊፈቀድለት እንደሚገባ
ተደንግጓል፡፡
👉ሕጉ እነዚህ ድንጋዎች የደነገገበት ዋነኛ ዓላማ ለዳኝነት የሚከፈል ገንዘብ በሙሉም ሆነ በከፊል መክፍል ባለመቻላቸዉ ብቻ ሰዎች በፍርድ ሊወሰን የሚገባን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ወይም ለሌላ በሕግ የዳኝነት ሥልጣን ለተሰጠዉ አካል አቅርበዉ ፍርድ ወይም ዉሳኔ
በማግኘት መብትና ጥቅሞቻቸዉን ሳያስከብሩ እንዳይቀሩ የመፍትሔ ሥርዓት በመዘርጋት ለሰዎች
ፍትህ የማግኘት መብት ጥበቃ ለማድረግ ነዉ፡፡
👉በመሆኑም በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕግ ቁጥር 467/1 ስር“…ገንዘብ የሌለዉና ለማግኘት የማይችል… “ ተብሎ የተገለጸዉ ሕጉ ለማሳካት የፈለገዉን የሰዎች ፍትህ የማግኘት መብት በሚያስጠብቅ መልኩ በጠባቡ መተርጎም አለበት፡፡
👉ምክንያቱም ይህ የሕጉ
አገላለጽ በሰፊዉ የሚተረጎም ከሆነ ሰዎች በእጃቸዉ ላይ የሌለን ገንዘብ በፍርድ ቤት አስወስነዉና አስፈጽመዉ ወይም በሌላ አካኋን በእጃቸዉ አስገብተዉ ለሚያቀርቡት ክስ የሚያስፈልገዉን ዳኝነት
አግኝተዉ የዳኝነት ገንዘብ እስከሚከፍሉ ድረስ ክስ የማቅረብ መብታቸዉ በይርጋና በመሰል
ምክንያቶች ሊታገድ ስለሚችል እንዲሁም የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸዉም ሊጣበብ ስለሚችል በአሁኑ ጊዜ ገንዘብ የሌለዉ መሆኑ እስከተረጋገጠ ድረስ ለወደፊት ገንዘብ የሚያገኝበት እድል በመኖሩ ብቻ የዳኝነት ገንዘብ ሳይከፍል በነጻ መዝገብ እንዲከፈትለት ያቀረበዉ አቤቱታ ተቀባይነት ሊያጣ አይገባም፡፡ 👉በተጨማሪም የዳኝነት ገንዘብ ሳይከፈል በነጻ መዝገብ ከተከፈተ በኋላ መዝገቡን ያስከፈተዉ ሰዉ ገንዘብ በሚያገኝበት በማንኛዉም ጊዜ የዳኝነት ገንዘብ እንዲከፍል
የሚደረግብትን ሥርዓት የሥነ ሥርዓት ሕጉ ስለዘረጋ በተጠቀሰዉ መሰረት የሕጉ አገላለጽ በጠባቡቢተረጎም የሚደርስ የማይተካ ጉዳት የለም።
👉የሠ/መ/ቁጥር 188406
መስከረም 27 ቀን 2013ዓ/ም | 642 |
| 4 | 👉የሕፃናትን ቀለብ አስመልክቶ ቀለብ እንዲከፍል የተወሰነበት ሰው በየጊዜው እንዲከፍል የተወሰነበትን የቀለብ ገንዘብ ጊዜው ደርሶ ካልከፈለና ለወደፊቱም የማይከፍል ሲመስል የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረቱ ተከብሮ ለቀለብ ክፍያ እንዲውል ማድረጉ የሕፃናትን መብት ከማስከበር አኳያ ተገቢ ከመሆኑም በላይ ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 45819 የመክፈያ ጊዜው ገና ለሆነው የቀለብ ገንዘብ አከፋፈል ጭምር የቀለብ ከፋዩን ንብረት አስከብሮ መያዝ እንደሚቻል ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ 👉ሆኖም የሚታገደው ወይም
የሚከበረው ገንዘብ ከዕዳው ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይገባዋል፡፡ ተመጣጣኝ ካልሆነ የተከበረውን ንብረት ወይም ገንዘብ በከፊል ከዕገዳ ነፃ በማድረግ ማመጣጠን ተገቢ ይሆናል፡፡
👉የሰ/መ ቁ፡-237498 ቀን፡-05/02/2016ዓ/ም | 772 |
| 5 | 👉ከክርከሩ እንደሚያሳዉ የጠየቁት ክፍያ የትርፍ ሰዓት፣የበዓላትና የሳምንት የእረፍት ቀናት የሰሩበት በተጨማሪነትም የአልጋ አበል ታስቦ እንዲከፈላቸዉ ነዉ፡፡
👉አመልካች አጥብቆ የሚከራከረዉ እነዚህ ከፍያዎች ለመክፈል የሚያስችል የሥራ ትእዛዝ አልሰጠሁም፤የዉል ግዴታም የለም በማለት ነዉ፡:
👉በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ እንደተመለከተዉ የትርፍ
ሰዓት፤የሳምንት የእረፍት ቀናት እና የበዓል ቀናት ስራ ለመስራት ሰራተኛዉ የሚገደደዉ በህግ
በተመለከቱ ዉስን ምክንያቶች ስለመሆኑና በአሰሪዉ ትእዛዝ መሰጠቱ መረጋገጥ እንዳለበት
ህጉ ያስገነዝባል፡፡
👉አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 66-72ያሉት ድንጋጌዎች
ይመለከታል፡፡ከዚህ መገንዘብ እንደሚቻለዉ ሰራተኛዉም እነዚህን ክፍያዎች ሊጠይቅ የሚችለዉ እና አሰሪዉም ከፍያዉን ለመክፈል የሚገደደዉ ስራዉ በአሰሪዉ እዉቅና እና በተሰጠዉ የስራ ትእዛዝ መሰረት መስራቱን ሰራተኛዉ ማስረዳት ከቻለ ነዉ፡፡
👉የትርፍ ሰኣት፣የበዓል ቀናትና የሳምንት እረፍት ጊዜ ጋር የተያያዙ ክፍያዎች በባህርያቸዉ ሰራተኛዉ
እንደመብት የሚጠይቀዉ ሳይሆን ለስራዉ መልካም አካሄድ አስፈላጊ መሆኑ በአሰሪዉ ታምኖበት ትእዛዝ ሲሰጥ እና ሰራተኛዉም ተስማምቶ በተሰጠዉ ትእዛዝ መሰረት መስራቱ
ሲረጋገጥ የሚፈጸም መሆኑ ነዉ፡:
👉የሰ/መ/ቁ፡-206765
ቀን፡-30/03/2014ዓ/ም | 686 |
| 6 | 👉በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 231(1) መሠረት በክስ አቤቱታው የተገለጸው የማያስከስስ መሆን መሆን አለመሆኑን ፍርድ ቤቱ የመመርመር ኃላፊነት አለበት፡፡
👉የክስ ምክንያት ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ ግዴታ መኖሩን፣
የተጠየቀው ዳኝነት በፍርድ ቤት የሚዳኝ መሆን አለመሆኑን እና በክሱ ዝርዝር ውስጥ የተመለከቱት ጉዳዮች ቢረጋገጡ የተጠየቀውን ዳኝነት ለከሳሽ ለመወሰን ህግ የሚፈቅድ መሆን አለመሆኑን መመርመርን የሚጠይቅ ነው፡፡
👍ይህም የክስ ምክንያት የሌለው ጉዳይ የሚለው በዋነኛነት ዳኝነቱን ለመጠየቅ ከህግ የመነጨ ግንኙነት
እያለው ግን በፍርድ ቤት ሊዳኙ የማይችሉ ጉዳችን (non-justiciable matters) ፍርድ ቤት አከራክሮ ሊፈጸም የሚችል ውሳኔ ሊሰጥባቸው የማይችሉ በመሆናቸውና ከሳሽ ወገን ክሱን ሲያቀርብ የጠቀሰው ወይም
የገለጸው የክሱ መሰረት የሆነው ምክንያት በህግ የክስ መሰረት ሊሆን የማይችል ከሆነ የማያስከስስ ነው
ተብሎ ክሱ ውደቅ የሚደረግበት ሥርዓት ነው።
👉/መ/ቁ 206699 ሚያዚያ 28 ቀን 2014 ዓ/ም | 743 |
| 7 | 👉አንድ ሰዉ የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የተሠጠዉ ዉሳኔ መብቴን ነክቷል የሚል ከሆነ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት መቃወሚያ በማቅረብ የሚተናገድበት ሥርዓት ያለ መሆኑን፤ በሌላ በኩል በፍርድ አፈጻጸም ክርክር ላይ ለፍርድ ማስፈጸሚያ የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት የፍርድ ባለእዳ ሳይሆን
የእኔ ነዉ ባይ ሶስተኛ ወገን ንብረቱ ለፍርድ ማስፈጸሚያ ሊዉል አይገባም የሚልበትን ምክንያት በመግለጽ
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 418 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች መሰረት የሚስተናገድ ሥርዓት አለ፡፡
👉 የእነዚህ ድንጋጌዎች ይዘት፣ ዓላማና አተገባበር አድማስ አስመልክቶ የፈዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 29653፣ 53067፣55842፤ 141600 የክርክሩ ተካፋይ ያልነበረ ሶስተኛ ወገን በዋናዉ ክርክር ላይ የተሰጠዉ ፍርድ መብቱን የሚነካ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም ሊቀርብ የሚገባዉ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት መሆን እንዳለበት እና በሌላ በኩል ፍርድ ያላረፈበት ንብረት በፍርድ
አፈጻጸም ምክንያት በፍርድ ባለመብት ጥያቄ መሠረት እንዲከበር ወይም እንዲያዝ ሲደረግ ንብረቱ ላይ
ሊፈጸም አይገባም የሚል ሶስተኛ ወገን መቃወሚያዉን ማቅረብ ያለበት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 418 መሠረት
እንደሆነ፤ የሁለቱም ድንጋጌዎች መሠረታዊ ልዩነቱም የፍ/ብ/ሥ/ስ/ሕ/ቁ 358 ተቃዋሚ ወገን የክርክሩ
ተካፋይ ሳይሆን ጥቅሙን የሚነካ ፍርድ የተሰጠ እንደሆነ ፍርዱ እንዲሰረዝ አቤቱታ የሚያቀርብበት ስርዓት የሚመለከት መሆኑን፤ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 418 ደግሞ ለፍርድ ማስፈጸሚያ በሚል በአፈጻጸም ክርክር የተያዘ ንብረት ለማስለቀቅ የመቃወም አቤቱታ የሚቀርብበት መሆኑን፤ በዚሁ ድንጋጌ መሰረት በአፈጻጸም ክርክር ላይ በሚቀርብ መቃወሚያ ዋናዉ ፍርድ ሊሻር እንደማይችል በመግለጽ አስገዳጅ የሆነ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡
👉የሰ.መ.ቁ 213479
ግንቦት 29 ቀን 2014 ዓ.ም | 720 |
| 8 | 👉በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን ባልተሳተፈበት ክርክር ተደርጎ መብቱን የሚነካ ፍርድ መሰጠቱን ባወቀ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም መብቱን ማስከበር እንደሚችል በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ 358 ላይ ተደንግጓል፡፡ 👉ይሁንና ይህንን መብት በመጠቀም ረገድ ክርክሩ መኖሩን እያወቀ በቸልተኝነት ወይም በሌላ ጉድለት የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የቀረ ወገን ከቅን ልቦና ውጪ ጉዳዩን ለማንሳት የሚያቀርበው መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይገባ ሰበር ችሎቱ ቀዳሚ ውሳኔ የሰጠበት መሆኑ ይታወቃል (ሰበር መ/ቁ/56795፤40229፤93987 እና ሌሎች መሰል መዛግብትን ይመለከታል)፡፡
👉 ስለሆነም ባል በተከራከረበት መዝገብ ሚስቲቱ ክርክሩ መኖሩን አውቃ ነበር ወይስ አልነበረም ወይም ክርክሩ መኖሩን እያወቀች ጣልቃ ገብታ መከራከር ሲገባት ከቅን ልቦና ውጪ ውጤቱን ጠብቃ ያቀረበችው አቤቱታ ነው የሚለውን ለመወሰን በእርግጥም የመቃወም አመልካች ቀደም ሲል ክርክር ሲደረግ የነበረ መሆኑን ክርክሩም የእሷን መብት የሚመለከት መሆኑን አውቃ እንደነበር ማረጋገጥ ያለበት ፍሬነገር ጉዳይ ነው፡፡
👉በመሆኑም ሚስት በመሆኗ ብቻ ክርክሩን ታውቅ ነበር የሚል ግምት ሊወሰድ አይገባም።
👉 የሰ/መ/ቁ247348፣ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ/ም | 935 |
| 9 | ተከሳሽ የመከላከያ መልሱን አቅርቦ ክሱ ሊሰማ በተቀጠረበት ዕለት ባለመቅረቡ በፍ/ሥ/ሕ/ቁ 70(ሀ) መሰረት ክርክሩ በሌለበት እንዲታይ ብይን ከተሰጠ የመከላከያ ክርክር የማቅረብ መብቱን ከማሳጣት አልፎ በቀሪዎቹ የክርክር ሂደቶች ከመሳተፍ አያግደውም።
የሰ/መ/ቁ 206006 | 1 280 |
| 10 | 👉 የአንድ መብትና ግዴታ ምንጭ ሕግ ወይም ውል ሲሆን አንድ ከሳሽ ሌላውን ወገን በተከሳሽነት
ፍርድ ቤት መክሰስ የሚያስችለው ምክንያት (cause of action) እንዲኖረው የግድ የሚል መሆኑንና
ለመክሰስ የሚያስችል ጥቅም ወይም መብት በማረጋገጥ አቤቱታ ካላቀረበ በቀር በማናቸውም ሰው ላይ ክስ
ሊያቀርብ የማይችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 33(2)እና(3) ድንጋጌ ያስገነዝባል፡፡
👉ሆኖም በአንድወገን ላይ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መብት ወይም ጥቅም መኖሩ ብቻውን ውጤት የሚያመጣ ሳይሆንከሳሹ ተጣሰብኝ ወይም ተደፈረብኝ ወይም አልተፈፀመልኝም የሚለውን ግዴታ በሌላው ወገን በሕግ ወይም
በውል የተገኘ መብቱ/ ጥቅሙ / የተጣሰበት መሆኑን፣ ተከሳሹ መብቱ የተደፈረበት ወይም ግዴታ
ያልተፈፀመበት መሆኑን፣ መብቱ በመደፈሩ ወይም ሊፈፀምለት ይገባው የነበረው ግዴታ ባለመፈፀሙ ጥቅምየቀረበት ወይም ጉዳት የደረሰበት መሆኑን፣ እንዲሰጥለት የሚጠይቀው ዳኝነት (relief) በሕግ የተፈቀደመሆኑን ካለሳዬ በቀር ያቀረበው ክስ ተቀባይነት ሊኖረው የማይገባ ስለመሆኑም ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ33(2)እና(3) ፤ 231 ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ መዘንዘብ ይቻላል፡፡
👉 በመሆኑም አንድን ክስ የሚያቀርብተከራካሪ ወገን ይህንን ሊያስረዳ የሚችል ጠቋሚ ማስረጃ (Prima facie evidence) ሊያቀርብ ይገባል፡፡
👉ከሳሽ የሆነው ወገን ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33(2)እና(3) ድንጋጌ አኳያ የሚጠበቅበት ክስ በመሰረተበት ነገር / ሐብት / ላይ ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ መብት ወይም ጥቅም እንዳለው እና ይሄው ጥቅሙ ወይም መብቱ በተከሳሹ የተነካበት ወይም የተጣሰበት መሆኑን እንጂ ገና ተከሳሹ ሳይጠራ በክሱ የተጠቀሰውንፍሬነገር በማስረጃ እንዲያረጋግጥ አይደለም፡፡
👉ይህም ከሳሽ የሆነው ተከራካሪ ወገን ከጅምሩ እንዲያረጋግጥ
የሚጠበቅበት አለኝ የሚለውን መብት በክስ አቤቱታው ላይ እንዲያሳይ እና ይህንንም የሚያረጋግጥለት
ጠቋሚ ማስረጃ ማቅረብ እንደሆነ፤ ክስ የማቅረብ መብት ወይም ጥቅም ማስረዳት መቻል እና እንደክሱ
አቀራረብ ወይም እንደተጠየቀዉ ዳኝነት ዉሳኔ ለመስጠት የሚያስችል የማስረጃ ምዘና ደረጃ ልዩነት ያላቸው
መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
👉ተከራካሪ የሆኑ ወገኖች የሚያቀርቧቸውን ክርክሮች ለመወሰን በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች ደግሞ ተከሳሽ ወገን ክሱን ለማስተባበል የሚያቀርበውን መከራከሪያ እና ማስረጃ
መሠረት በማድረግ ፍሬነገርን አጣርተው እና ማስረጃ መዝነው ዉሳኔ መስጠት የሚጠበቅባቸው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2 እና 231፤ 182 እና 273 ድንጋጌዎች ይዘት ያስገነዝቡናል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም በዚህ ረገድ በተለይም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 እና 231 አተገባበርን አስመልክቶ
በሰ.መ.ቁ 82234፤ 135639፤ 144052 እና በሌሎችም መዝገቦች ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡
👉የሰ.መ.ቁ 233250
ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ.ም | 1 385 |
| 11 | Final Draft Regulation of ANRS Land law.pdf | 911 |
| 12 | አዲሱ የአብክመ የማረሚያ ቤት አዋጅ.pdf | 947 |
| 13 | +7 የአብክመ የህግ መፅሄት ቅፅ 1.pdf | 1 479 |
| 14 | 👉 በንግድ ህግ ቁጥር 683(1) ላይ "ጉዳት ያደረሱ ሦስተኛ ወገኖች" የሚለው አገላለጽ በቀጥታ ሲታይ መድህን ገቢውን (ባለቤቱን) የማይመለከት ቢመስልም፤ የህጉ ዋና ዓላማ ኢንሹራንሶች ውላቸውን አክብረው ካሳ ከከፈሉ በኋላ ጥፋተኛ ከሆነው አካል ላይ ገንዘቡን እንዲያስመልሱ መፍቀድ ነው።
👉ጉዳት ያደረሰው ተሽከርካሪ በሌላ ራሱን በቻለ የኢንሹራንስ ድርጅት (ብርሃን ኢንሹራንስ) ስር የሦስተኛ ወገን መድህን ሽፋን ያለው በመሆኑ፣ ሁለቱም መኪናዎች የአንድ ሰው ንብረት ቢሆኑም እንኳ ጉዳት አድራሹን ተሽከርካሪ በተመለከተ አመልካች ለተጠሪ እንደ "ሦስተኛ ወገን" ሊቆጠር ይገባዋል።
👉 በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2081 እና 2083 መሠረት አንድ የሞተር ተሽከርካሪ ባለቤት መኪናው ላደረሰው ጉዳት ተጠያቂ መሆኑ ስለሚደነገግ፣ አመልካች ከተጠሪ ካሳ ወስዶ "ተጠሪ በመዳረግ ሊጠይቀኝ አይችልም" በማለት ያቀረበው ክርክር የሕጉን ትክክለኛ ትርጉምና ፍትሕን የተከተለ አይደለም።
👉የሰ/መ/ቁ. 235515
ቀን፡28/8/16 | 995 |
| 15 | መኪና በውክልና ለምትሻሻጡ ወገኖች:-
==============
የተሽከርካሪ ሽያጭ ውል ህጋዊነት እና ማስረጃ አቀራረብ በሰበር መ/ቁ 283524 በቀን 27/05/2018 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ
መኪና ሲገዙ ወይም ሲሸጥ በውልና ማስረጃ በኩል ሳያረጋግጡ በመንደር ውል መደረጉ ያለው እጣ ፈንታ በተለይም ግለሰቡ (ተጠሪ) ከአንድ ሻጭ (አመልካች) ጋር የመኪና ሽያጭ ውል ተፈራርመው፣ ከፊል ክፍያ ፈጽመውና መኪናውን ተረክበው ለዓመት ያህል ሲጠቀሙ ይቆያሉ ። ነገር ግን ሻጭ መኪናውን በሌላ ቁልፍ ከፍተው በመውሰድ "አልሸጥኩም፣ እንዲያስተዳድሩልኝ ውክልና ነው የሰጠኋቸው" በማለት በመካድ ተከራክረዋል ። በሰበር ሰሚ ችሎትም መኪና እንደ ተራ ንብረት ሳይሆን እንደ "ልዩ ተንቀሳቃሽ ንብረት" የሚቆጠር በመሆኑ፣ ዝውውሩ በህግ ፊት እንዲጸና በሚመለከተው የመንግስት አካል ዘንድ መመዝገብና መረጋገጥ አለበት ። በተጨማሪም የመኪና ሽያጭ መኖሩን ለማረጋገጥ በሚመለከተው አካል የተረጋገጠ የሽያጭ ሰነድ ማቅረብ እንጂ በሰው ምስክር ብቻ ማረጋገጥ የማይቻል ስለመሆኑ። | 624 |
| 16 | በኤሌክትሪክ አደጋ ምክንያት ለሚደርስ ጉዳት ተገልጋዮች ከአገልግሎት ሰጪው እውቅና እና ፈቃድ ውጭ በራሳቸው በሚዘረጉት የኤሌክትሪክ መስመር ለሚደርሰው ጉዳት አገልግሎት ሰጪው ተቋም ተጠያቂ አይሆንም።
እንደ ኤሌክትሪክ አደጋ ባሉ የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ በፖሊስ የሚደረግ የባለሙያ (Forensic) ምርመራ ከፍተኛ የማስረጃነት ዋጋ (High Probative Value) አለው። ይህንን የባለሙያ ምርመራ ውጤት ያለ በቂ ምክንያት ወደ ጎን በማለት ውሳኔ መስጠት መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው።
አገልግሎት ሰጪው ኃላፊነት የሚኖርበት እሱ ራሱ በዘረጋውና ባለቤት በሆነበት መስመር ላይ ለሚደርስ ጉዳት ብቻ ነው። በተገልጋዮች ጥፋት ለሚደርስ አደጋ ተቋሙ ካሣ የመክፈል ግዴታ የለበትም።
የኤሌክትሪክ ኃይል ባለቤት መሆን ብቻውን ኃላፊነትን አያስከትልም፤ ኃላፊነት ሊኖር የሚችለው ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገ እና ጥፋት ከተፈጸመ ብቻ ነው።
ሰ/መ/ቁ.175142 (ግንቦት 24 ቀን 2012 ዓ.ም) | 650 |
| 17 | Final_1_28_full_published_cassation_Daniel_Fikadu_Law_Office_Reduced.pdf | 0 |
| 18 | በዋስ የመፈታት መብት vs ከፍርድ በፊት እንደጥፋተኛ ያለ መቆጠር መብት መሰረት በማድረግ በሰመቁ 292349 በቀን 24/6/2018 ዓ/ም የተሰጠ አስገዳጅ ትርጉም
፨የተወገዘ ድርጊት ነው።
፨አያስተምርም ።
፨የሚስቀጣው ቅጣት ከባድ ነው በማለት በህግ ዋስትና የማያስከለክል ወንጀል ዋስትና መከልከል የሕግ ጥሰት መሆኑን ውሳኔ ተሰጥቶበታል ። | 0 |
| 19 | +9 Total 92 HoF Decisions.pdf | 0 |
| 20 | የፍርድ ቤት ቀጠሮዎን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!
ባህርዳር፣ሚያዚያ 21/2018(የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት)
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍትሕን በታማኝነት ለማረጋገጥ የጀመረውን ጉዞ በቴክኖሎጅ ይበልጥ ለአገልግሎት ፈላጊው ተደራሽ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ጠቅላይ ፍርድ ቤታችን ለባለጉዳዮቻችን ተደራሽ እየሆነባቸው ካሉ የቴክኖሎጅ አማራጮች አንዱ ደግሞ የሞባልይ መተግበሪያችን ነው።
አዲሱ የሞባይል መተግበሪያ የተገልጋዮችን እንግልት ለመቀነስ እና ግልጽነትን ለማስፈን ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
የሞባይል መተግበሪያው 👇
ቀጠሮ ፍለጋ፦ በመዝገብ ቁጥር፣ በአመልካች ወይም በተጠሪ ስም መፈለግ ያስችላል።
ቀጠሮዎችን ማየት፦ የዕለቱን የችሎት ውሎዎች በቀላሉ ለማየት ያስችላል።
ቀላል አጠቃቀም፦ ለማንኛውም ሰው ግልጽ በሆነ አማርኛ የተዘጋጀ ነው።
የመዝገብ ቁጥርዎን በማስገባት ብቻ የቀጠሮ መረጃ ማግኘት የሚችሉበት አማራጭ ነው።
ወደ ፍርድ ቤት በአካል መሄድ ሳያስፈልግዎት መረጃዎችን ባሉበት የሚያገኙበት ነው።
የሞባይል መተግበሪያው አሁን ላይ የባህር ዳር እና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት እና የጠቅላይ ፍርድ ቤት መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፣ በቀጣይ የሁሉም ከፍተኛና ወረዳ ፍርድ ቤቶች መረጃ የሚካተትበት ይሆናል።
አሁኑኑ መተግበሪያውን በመጫን ጊዜዎን እና ጉልበትዎን ይቆጥቡ!
መተግበሪያውን ለማውረድ 👇
1. በድረ-ገጽ (Web): https://amhsc.gov.et/ ላይ በመግባት ማንኛውንም መረጃ ይፈልጉ።
የዕለቱን መዝገቦች ለማየት https://amhsc.gov.et/?page_id=1929
ዌብሳይቱ ላይ በመዝገብ ቁጥር በአመልካች ስም እና በተጠሪ ስም ለመፈለግ https://amhsc.gov.et/?page_id=1815
2. በሞባይል መተግበሪያ (App): መተግበሪያውን ለማውረድ
እዚህ ይጫኑ፦ https://amhsc.gov.et/?page_id=1957 | 0 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
