cookie

МО вОкПрОстПвуєЌП файлО cookie Ўля пПкращеММя вашПгП ЎПсвіЎу перегляЎу. НатОсМувшО «ПрОйМятО все», вО пПгПЎжуєтеся Ма вОкПрОстаММя файлів cookie.

avatar

🇪🇹ዘወልድ ምክሹ-ሕግ🇪🇹‌

ቻናሉ ሕጎቜንና ዹፍ/ቀት ዉሳኔዎቜን ያጋራል። አጫጭር ዹሕግ ማብራሪያዎቜንና ዹምክር አገልግሎቶቜን ይሰጣል። ጠበቃ ካሊድ ኹበደ እና ጠበቃ አማሹ እሞቱ በማንኛዉም ዚፌዎራል እና ዹክልል ፍ/ቀት ጠባቃና ዹሕግ አማካሪ ስልክ- 0935439820 ኢሜይል- [email protected]

Більше
РеклаЌМі ЎПпОсО
1 332
ПіЎпОсМОкО
-224 гПЎОМО
-17 ЎМів
-230 ЎМів

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ПрОріст піЎпОсМОків

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

4_5976718550281230192.pdf6.92 KB
አዳዲስ አዋጆቜ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዹጾደቁ ዋና ዋና አዋጆቜ፡- 👉 ዚኢትዮጵያ ዚሜዳይ፣ ኒሻን እና ሜልማት አዋጅ 1325/2016 👉 ዹገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 👉 ዚልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጅ ቁጥር 1322/2016 👉ዚመኖሪያ ቀት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016
ППказатО все...
ዚኢትዮጵያ_ዚሜዳይ_ኒሻን_እና_ሜልማት_አዋጅ_ቁጥር_1325_2016.pdf1.39 MB
ዹፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358 ላይ ጥሩ ዚሚባል ዹህግ ትርጉም! ***** ሰ/መ/ቁ. 144359፡- ኹፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህግ ቁጥር 358 እና 41 አስቀድሞ መብቱን ዚሚነካ ክርክር መኖሩን ያወቀ አካል ክርክሩ አብቅቶ ውሳኔውን ኚመስማቱ በፊት ወደ ክርክሩ ሊገባ እንደሚገባ ዚሚያሳዩ ሲሆኑ ፍርድ ሲሰጥ ጠብቀው በመምጣት ዹተሰጠው ፍርድ ይነሳልኝ በማለት አቀቱታ ማቅሚብ ዹፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህግ ቁጥር 358 ላይ ዹተመለኹተውን ዹህግ ድንጋጌ አላማ ዚሚያሳካ አይደለም። ይሁን እንጂ ይህ ድንጋጌ ለውርስ ሀብት ክርክርን በተመለኹተ ተፈፃሚነት ያለው ነው ለማለት ዚሚቻል አይደለም። እንኳን ዚውርስ ሀብቱ ሳይኚፋፈል ቀርቶ ኹተኹፋፈለ በኋላም በሌለበት ዚውርስ ሀብቱ ዚተኚፋፈለበት አካል በሚያቀርበው አቀቱታ ክፍፍሉ ሊፈርስ እና እንደገና ክፍፍል ሊደሹግ እንደሚገባ በፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 1080 ላይ ተደንግጎ ይገኛል። ስለሆነም ምንም እንኳን አመልካ቟ቜ ያቀሚቡት ዚፍርድ መቃወሚያ አስቀድሞ ዹነበሹውን ክርክር በሚያውቁበት ሁኔታ ቢሆንም ዚፍርድ መቃወሚያ ዚቀሚበበት ክርክር ዚውርስ ሀብትን መሰሚት ያደሚገ ኹሆነ ዚውርስ ሀብቱ ክፍፍል ኹተደሹገ በኋላም ቢሆን ዚሚቻል ክርክር በመሆኑ ዚአመልካ቟ቜ ዚፍርድ መቃወሚያ አቀቱታ አመልካ቟ቜ አስቀድመው ክርክሩን ያውቁት ነበር በሚል ውድቅ ሊሆን አይገባም። ዚካቲት 14 ቀን 2010 ዓ.ም 👇👇👇👇👇👇
ППказатО все...
ሰ/መ/ቁ. 184371 /ያልታተመ/ *** ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ሰበር ሰሚ ቜሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 106560 መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ/ም በዋለው ቜሎት እና በሰበር መዝገብ ቁጥር 116583 ታህሳስ 4 ቀን 2008 ዓ/ም በዋለው ቜሎት ኚመሬት ይዞታ ክርክር ልዩ ባህር እና ጉዳዩን በተለይ ዹሚገዛው ኹአዋጅ ቁጥር 25/1988 በኋላ ዚወጣው ልዩ ሕግ አዋጅ ቁጥር 456/1997 መሠሚት ዚተኚራካሪ ወገኖቜ መደበኛ ነዋሪነት ዚተለያዚ ቢሆንም/ባይሆንም ዚተኚራካሪዎቹ ማንነት ኚግምት ውስጥ ሳይገባ ዹገጠር መሬት ይዞታን በተመለኹተ ዚሚነሱ ክርክሮቜን በመጀመሪያ ደሹጃ ዚማዚት ዚሥሚ ነገር ሥልጣን ዹገጠር መሬት ይዞታው ዚሚገኝበት ክልል ዹገጠር መሬት አዋጅ በሚደነግገው መሰሚት መሆኑን አገዳጅ ዹሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል። በመሆኑም ተኚራካሪዎቹ ነዋሪነታ቞ው በተለያዚ ክልል መሆኑ ጉዳዩን ዚፌዎራል ጉዳይ አያደርገውም ።
ППказатО все...
በገጠር ዚመሬት ሜያጭ እና ግዢ ዚሚያኚናውኑ ሰዎቜን እስኚ አምስት አመት በእስር ዚሚያስቀጣ አዋጅ በፓርላማ ጾደቀ ዹገጠር መሬትን ዹሾጠ ወይም በገዛ ማንኛውም ሰው ላይ እስኚ አምስት ዓመት ዚሚደርስ ዹፅኑ እስራት ቅጣት ዚሚጥል አዋጅ በተወካዮቜ ምክር ቀት ጞደቀ። አዲሱ አዋጅ ዚግል፣ ዹወል ወይም ዚመንግስት ይዞታን በህገ ወጥ መንገድ ወርሮ ለተገኘ ሰውም ተመሳሳይ ዚእስራት ቅጣት ደንግጓል። ዚተወካዮቜ ምክር ቀት ዛሬ ማክሰኞ ግንቊት 6ፀ 2016 በነበሹው መደበኛ ስብሰባው በሙሉ ድምጜ ያጞደቀው ይህ አዋጅፀ ኹ18 ዓመት በፊት ዚወጣውን ዹገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅን ያሻሻለ ነው። አዲሱ አዋጅ አርሶ አደሮቜ፣ አርብቶ አደሮቜ እና ኹፊል አርብቶ አደሮቜ በመሬት ላይ ያላ቞ውን መብቶቜ ያሻሻለ ሲሆንፀ ዚሎቶቜ እና ድጋፍ ዚሚሹ ሰዎቜን ዚመሬት ተጠቃሚነት መብት ያሚጋገጡ ድንጋጌዎቜንም አካትቷል። አዋጁ በሹቂቅ ደሹጃ ለፓርላማ ኹቀሹበ በኋላ ኹተደሹጉ ማሻሻያዎቜ መካኚልፀ “ዹወንጀል ተጠያቂነት” በሚመለኹተው ዹተጹመሹው አንቀጜ ይገኝበታል። “ኚመሬት ጋር ተያይዘው ዹሚፈጾሙ ወንጀሎቜ ላይ አስተማሪ እና ተመጣጣኝ ቅጣት ማስቀመጥ አስፈላጊ በመሆኑ” ምክንያት እንደተካተተ ዚተነገሚለት ይህ ድንጋጌፀ ኚመሬት ወሚራ እስኚ መሬት ሜያጭ ድሚስ ያሉ ዹህግ ጥሰቶቜ ዚሚያስኚትሏ቞ውን ቅጣቶቜ ዘርዝሯል። ማንኛውም ሰው መሬት ዹሾጠ ወይም ዹገዛ እንደሆነፀ ኹ100 ሺህ እስኚ 200 ሺህ ብር ወይም ኹ1 ዓመት እስኚ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ወይም በሁለቱም ሊቀጣ እንደሚቜል በአዲሱ ድንጋጌ ላይ ሰፍሯል። በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት መሰሚት “መሬት ዚማይሞጥ፣ ዚማይለወጥ ዚኢትዮጵያ ብሔሮቜ፣ ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ዚጋራ ንብሚት ነው”። ሕገ መንግስቱ ዹገጠርም ሆነ ዹኹተማ መሬት ዚባለቀትነት መብትን ዹሰጠው “ለመንግስት እና ለህዝብ” ነው። ዛሬ በጾደቀው አዋጅ ዚግል፣ ዹወል ወይም ዚመንግስት ይዞታን በህገ ወጥ መንገድ ዹወሹሹ ማንኛውም ሰውፀ ኹ1 ዓመት እስኚ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት አሊያም ኹ30 ሺህ እስኚ 100 ሺህ ብር ቅጣት ሊጣልበት እንደሚቜል ተደንግጓል። በእነዚህ ይዞታዎቜ ላይ ጉዳት አድርሶ ዹተገኘ ማንኛውም ሰውፀ ኹ3 ዓመት እስኚ 7 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ወይም ኹ50 ሺህ እስኚ 150 ሺህ ብር እንደሚቀጣም በአዋጁ ላይ ተቀምጧል። ባልተፈቀደ ቊታ ላይ ማንኛውንም ግንባታ ዚሰራ ወይም እንዲሰራ ዹፈቀደ ሰው ደግሞ በአዲሱ አዋጅ መሰሚት ኹ1 ዓመት እስኚ 3 ዓመት በሚደርስ እስራት አሊያም ኹ25 ሺህ እስኚ 50 ሺህ ብር ይቀጣል። እነዚህ ቅጣቶቜፀ ኚመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ውጪ ይዞታውን ጥቅም ላይ አውሎ ዹተገኘ ሰው ላይ በተመሳሳይ መልኩ ተግባራዊ ዹሚደሹጉ ይሆናል። ሀሰተኛ ዚመሬት ይዞታ ማስሚጃ ያቀሚበ ባለይዞታ እንዲሁም ማስሚጃ ዹሰወሹ ወይም ዚተሳሳተ ማስሚጃ ዹሰጠ ባለሙያ ላይ ዚሚጣለው እስራት ኹላይ እንዳሉት ዹህግ ጥሰቶቜ ተመሳሳይ ቢሆንም ዚገንዘብ ቅጣቱ መነሻ ግን ወደ 20 ሺህ ብር ዝቅ ብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ППказатО все...
በዋስ ቢወጡ ሌላ ወንጀል ዚሚፈጜሙበት ሁኔታ ሰፊ ነው በሚል ዋስትናን ሰለመኹልኹል *** ዹሰ.መ.ቁ 245661/ያልታተመ/ #Daniel Fikadu Law Office - አመልካ቟ቜ ዚተጠሚጠሩበት ዹወንጀል ድርጊት በተመሳሳይ ማታለል ወንጀሎቜ ሌሎቜ መዛግብቶቜ ያሉባ቞ው በወንጀሉም ዹመጠርጠር ሙያ አድርገው ዚያዙት መሆኑ ሲታይ በዋስ ቢወጡ ሌላ ወንጀል ዚሚፈጜሙበት ሁኔታ ሰፊ ነው በሚል ነው፡፡ ዹዚህ ግምት መሠሚቱ አመልካ቟ቜ በዋስትና ቢወጡ ሌላ ወንጀል ዚሚፈጜሙበት እድል ሰፊ ነው ዹሚል እሳቀ ዚያዘ ስለመሆኑ ግንዛቀ ዚሚወሰድበት ነው፡፡ ሕጉ ፍ/ቀቱ ይህን ምክንያት ለግምቱ መነሻ እንዳያደርግ እስካልኚለኚለ እና ሕጉ ለፍ/ቀቱ ስልጣን ዹሰጠው ለመሆኑ ዚሚታመን እስኚ ሆነ ድሚስ ዚስር ፍ/ቀት ዚአመልካቜን ዚዋስትና መብት በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 67(ሀ)(ለ)(ሐ) መሠሚት ዹኹለኹለው በሕጋዊ ምክንያት ነው ለማለት ይቻላል፡፡ ስለሆነም ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ዚአመልካ቟ቜን ዚዋስትና መብት በመንፈግ በሰጡት ትዕዛዝ ላይ ዹተፈጾመ መሠሚታዊ ዹሕግ ስሕተት አልተገኘበትም፡፡
ППказатО все...
245661 - Stamped.pdf8.20 KB
ኚመላኩ ጥላሁን ዹተወሰደ ****** ሰ/መ/ቁ.220926፡-ዹወንጀል ድርጊቱ ኚምሜቱ 5፡00 ሰዓት ኹተፈፀመ ዹወንጀል ድርጊቱ በሌሊት እንደተፈፀመ በማድሚግ በወ/ህ/አ.84 (1)(ሐ) መሰሚት ቅጣቱን ማክበድ እንዲሁም ዹወንጀል ድርጊቱን ዚፈፀሙት ወንጀል ለመፈፀም ኹተቋቋመ ቡድን ጋር መሆኑ ካልተሚጋገጠ ተኚሳሟቜ ኚአንድ በላይ ቢሆኑም ቅጣቱን በወ/ህ/አ.84(1)(መ) ማክበድ ተገቢ አይደለም። ሚያዝያ 25 ቀን 2014 ዓ/ም
ППказатО все...
185837_ዹሰበር_አጣሪ_ቜሎት_አሰያዚምና_ኚዳኞቜ_አሰያዚም_አንጻር_ዹጠቅላይ_ፍርድ_ቀት_ፕሬዝዳንት_ሥልጣን.pdf3.25 KB
ሰ/መ/ቁ 114927     መስኚሚም 27 ቀን 2009 ዓ/ም ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2143(2) አተሹጓጎም በተጠሪ ደንበኛ ንብሚት ላይ ጉዳት አደሹሰ ዚተባለው ዚአመልካ቟ቜ ተሞኚርካሪ አሜኚርካሪ ዹወንጀል ሕግ አንቀፅ 506(1(ሐ)) ተጠቅሶ ዹወንጀል ክስ ቀርቊበት ድርጊቱ ስለመፈጜሙ ዹቀሹበ ማስሚጃ ዹለም ተብሎ ምንም መኹላኹል ሳያስፈልገው በነጻ ተሰናብቷል። በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2143(2) ስር ጉዳቱ በወንጀል ዚሚያስቀጣ ሆኖ በሚል ዹተቀመጠው ዚድንጋጌው አቀራሚፅና ይዘቱ ሲታይ ለጉዳቱ ዹተኹሰሰ ሰው በወንጀል ቜሎቱ ነፃ መውጣቱ ይርጋውን ወደ ሁለት አመት ዝቅ ዚሚያደርገው መሆኑን ዚሚያስገነዝብ ሳይሆን ጉዳቱ በራሱ ዹወንጀል ድርጊት መሆኑ ብቻ ዹይርጋውን ጊዜ በወንጀል ሕጉ በተመለኹተው ዹይርጋ አቆጣጠር ለማስላት ዚሚገባ መሆኑን ዚሚያስገነዝብ ነው፡፡ ዚድንጋጌው ዚእንግሊዝኛው ቅጂ ሲታይም "where a damage arises form the commission of a criminal offence in respect of which the Penal code prescribes a longer period of limitations, the latter period shall apply to the action for the damage." በሚል ዹተቀመጠ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ ዹዚህ ድነጋጌ ይዘትና መንፈስ ዚሚያሳዚው ጉዳቱን ያስኚተለው ድርጊት በወንጀል ሕጉ ዹወንጀል ድርጊት ተብሎ ዚሚወሰድ ስለመሆኑ እንጂ ድርጊት ፈጾሚው ዚግድ በወንጀል ጥፋተኛ ሁኖ መገኘትን ለይርጋ አቆጣጠር መለኪያ ሊሆን ዚሚቜል አለመሆኑን ነው፡፡  በዚህ ሚገድ ይህ ሰበር ሰሚ ቜሎት በሰ/መ/ቁጥር 61326 በቀሹበው ጉዳይ ላይ በአዋጅ ቁጥር 454/97 አንቀፅ 2(1) ድንጋጌ አግባብ በዚትኛውም እርኚን ዹሚገኝ ፍርድ ቀትን ዚሚያስገድድ ዹህግ ትርጉም ሰጥቶአል፡፡ በዚህ ትርጉም ጉዳቱ በወንጀል ድርጊት ዹተኹሰተ መሆኑ ብቻ ሳይሆን በወንጀል ጥፋተኛ ሁኖ መገኘትን ወይም በወንጀሉ ጉዳይ ዚማስሚጃውን ምዘና ሁሉ ዚሚመለኚት ነው ኚተባለ በውጀቱ ለጉዳት ካሳ ተጠያቂ ዹሚሆኑ ሰዎቜ(ለምሳሌ ጥፋት ሳይኖር ኃላፊነት ያለባ቞ው ሰዎቜ)ሁሉ ተጎጂዎቜን እንዳይክሱ ዚሚያደርግ ዹሚሆን መሆኑ ዚሚታመን ስለመሆኑም ተገልጟአል፡፡ ስለሆነም ዚድንጋጌው አስገዳጅ ትርጉም ጉዳቱ በወንጀል ዚሚያስቀጣ መሆኑ ዹሚለው ዚድንጋጌው ሐሹግ ተኚሳሜ በወንጀል ጥፋተኛ ሁኖ መገኘትን ዚሚያሳይ ሳይሆን ጉዳቱ በወንጀል ሊያስጠይቅ በሚቜል ድርጊት መኚሰቱ ኹተሹጋገጠ ብቻ ዹይርጋ ጊዜ ርዝመት ሊሆን ዚሚገባው በወንጀል ሕጉ ስር ዹተመለኹተው ዹይርጋ ጊዜ መሆኑን ዚሚያሳይ ነው፡፡   በአመልካ቟ቜ ተሜኚርካሪ አሜኚርካሪ በተጠሪ ደንበኛ ተሜኚርካሪ ላይ ለደሹሰው ጉዳት ዹወንጀሉ ድርጊት ሊያስጠይቅ ዚሚቜለው ዹሕግ አግባብ ሲታይ ይርጋው አስር አመት ስለመሆኑ ኚኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ አንቀፅ  506(1(ሐ) እና 224(1(ሐ)) ድንጋጌዎቜ ጣምራ ንባብ ለመገንዘብ ይቻላል፡፡ ኹዚህ አኳያ ድርጊቱ ተፈጾመ ዚተባለው መስኚሚም 14 ቀን 2005ዓ/ም ሁኖ ክሱ ዹቀሹበው ሁለት አመት ኹአለፈ መሆኑ በፍሬ ነገር ደሹጃ ግራ ቀኙን ያላኚራኚሚ ጉዳይ በመሆኑ ድርጊቱ በወንጀል ዚሚያስጠይቅ ድርጊት ነው ኚተባለ ይርጋው በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2143 (2) እና ኹላይ በተጠቀሱት ዹወንጀል ሕግ ድንጋጌዎቜ መሰሚት ዚአስር አመት ዹይርጋ ጊዜ አላለፈም፡፡  
ППказатО все...
ዚቀት ኪራይ .pdf ዚመኖሪያ ቀት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016
ППказатО все...
ዚቀት ኪራይ .pdf3.83 MB
Оберіть іМшОй тарОф

На вашПЌу тарОфі ЎПступМа аМалітОка тількО Ўля 5 каМалів. ЩПб ПтрОЌатО більше — Пберіть іМшОй тарОф.