🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️
Open in Telegram
ቻናሉ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያጋራል። አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል። ጠበቃ ካሊድ ከበደ እና ጠበቃ አማረ እሸቱ በማንኛዉም የፌዴራል እና የክልል ፍ/ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ ስልክ- 0935439820 💌- khalidbinkebe@gmail.com 0919311915 -💌 amareeshetu423@gmail.com አደራሻ:- ቆቦ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ደሴ እና አዲስ አበባ
Show more2 331
Subscribers
+524 hours
+77 days
+3030 days
Posts Archive
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
+6
የስንብት_ውሳኔ በፍርድ ቤት ይታያል!
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 155/2000 አንቀጽ 37 የሥራ ስንብት ውሳኔን በፍርድ ቤት እንዳይመረመር የጣለው ገደብ፣ ከሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 37(1) ጋር በመቃረኑ ተፈጻሚነት የለውም።
ይህን የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት በመዝገብ ቁጥር 142/17 ወስኗል፤ በዚህም ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 187052 የሰጠው የሥልጣን የለም ውሳኔ ተሽሯል።
ዋናው መርሕ፦ ሠራተኛ የስንብት ውሳኔው ሕጋዊነት በፍርድ ቤት እንዲመረመርለት የመድረስ መብት አለው።
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
10 በህግ ክርክር ወቅት የሚያጋጥሙ የላቲን ቃላትና አማረኛ ትረጉማቸው።
1. Audi alteram partem
🎯እንግሊዝኛ: Hear the other side / Listen to the other side
🎯⚖️አማርኛ: የሌላኛውን ወገን ሀሳብ/መከራከሪያ ስማበኢትዮጵያ ህግ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37 (ፍትሕ የማግኘት መብት) እና በፍትሐ ብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ውስጥ የተካተተ፣ ማንኛውም ወገን ሳይሰማና የመከላከል እድል ሳይሰጠው ሊፈረድበት እንደማይችል የሚደነግግ የመሰማት መብት መርህ ነው።
2. Res ipsa loquitur
🎯እንግሊዝኛ: The thing speaks for itself
🎯አማርኛ: ነገሩ ራሱ ይናገራል
በኢትዮጵያ ህግ ከውል ውጭ ተጠያቂነት (ፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 2027 እና ተከታዮቹ) የጥፋተኝነት ግምት በሚወሰድባቸው አጋጣሚዎች ድርጊቱ እራሱ የቸልተኝነት ወይም የጉዳት መኖርን በግልጽ እንደሚያስረዳ የሚቆጠርበት መርህ ነው። የበሽተኛው ሆድ ውሰወጥመቀስ የረሳ ዶክተር ቸልተኛ ለመሆኑ የመቀሱ በሆድ ውሰጥ መገኜት ብቻ በቂ ነው።
3. Stare decisis
🎯 እንግሊዝኛ: To stand by things decided
🎯 አማርኛ: የቀደመው ውሳኔ ለዚህ ይሰራል።
በኢትዮጵያ ህግ: በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 10(1) መሠረት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ በሚገኙ ፍርድ ቤቶች ላይ አስገዳጅነት አለው።
4. Mens rea
🎯እንግሊዝኛ: Guilty mind
🎯አማርኛ: የወንጀል ሀሳብ / ህገ-ወጥ አላማ
በኢትዮጵያ ህግ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 57 እና 58፤ 59 አንድ ሰው በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በህግ የተከለከለውን ድርጊት ለማድረግ ያሰበ (Intent) ወይም በቸልተኝነት (Negligence) የፈጸመ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
5. Actus reus
🎯እንግሊዝኛ: Guilty act
🎯አማርኛ: «የወንጀል ድርጊት»በኢትዮጵያ ህግ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 23 መሰረት አንድ ሰው ወንጀለኛ እንዲባል ከሀሳብ በተጨማሪ በድርጊት የተገለፀ አካላዊ የወንጀል ድርጊት ወይም ማድረግ የሚገባውን አለማድረግ (Omission) ሊኖር ይገባል።
6. Bona fide 🎯
እንግሊዝኛ: In good faith / Genuine 🎯አማርኛ : ቅን ልቦና
በኢትዮጵያ ህግ: በፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 1161 በቀንልቦና ንብረትን ስለመያዝ እና በውል ሕግ ውስጥ ያለምንም ተንኮል ማታለል ወይም ህገ-ወጥ አላማ በእውነተኛና በቅን ልቦና የተደረገ ድርጊትን ወይም ስምምነትን የሚጠበቅ መርህ ነው። በንብረት ውርስ ህጎችም የቅን ልቦና ባለንብረቶች መብት የተጠበቀ ነው።
7. Prima facie
🎯እንግሊዝኛ: At first sight / On the face of it
🎯 አማርኛ: በመጀመሪያ እይታ ወይም ከቀረበው ማስረጃ አንፃር የሌለኛውን ወገን ማስረጃ ሳይሰሙ ነገሩ ስለመደረጉ የቀረበ ማስረጃ።
በኢትዮጵያ ህግ: በሥነ-ሥርዓትና በማስረጃ ሕግ መርህ መሠረት ተቃራኒ ማስረጃ እስካልቀረበ ድረስ በመጀመሪያ እይታ አሳማኝና በቂ ሆኖ የሚቀርብ ማስረጃ ወይም የክስ መሠረት ነው።
8. Habeas corpus
🎯እንግሊዝኛ: You shall have the body
🎯አማርኛ: ሰውየውን ለምን ያዝከው። • በኢትዮጵያ ህግ: በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 19(4) መሠረት ማንኛውም የታሰረ ሰው በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ እና የእስሩ ሕጋዊነት በመመርመር እንዲለቀቅ የመጠየቅ መሠረታዊ መብት ነው። ፍርድ ቤት ሰውን ያለሕጋዊ መሠረት እንዳይታሰር የሚያደርግ የፍርድ ቤት ጥበቃ።
9. Caveat emptor
🎯እንግሊዝኛ: Let the buyer beware 🎯አማርኛ: ገዢ ቢጠነቀቅ ይሻለዎል
በኢትዮጵያ ህግ: 1 መሠረት የሽያጭ ውል ከተፈጸመ በኋላ ገዢ የተረከበውን ዕቃ ሁኔታ እና ጉድለት ወዲያውኑ የመመርመርና የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት።
10. Volenti non fit injuria
🎯እንግሊዝኛ: To a willing person, injury is not done
🎯አማርኛ: «በፈቃደኝነት ጉዳትን የተቀበለ ሰው የካሳ መብት የለውም»በኢትዮጵያ ህግ: በፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 2091 መሠረት ተጎጂው አደጋውን ወይም ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት አውቆና ፈቅዶ የተቀበለው ከሆነ የካሳ ጥያቄ ማቅረብ አይችልም። አጩለኝ ብሎት ቢያጮለው አጮለኝ አይሰራም። የወንጀል ህግ አንቀፅ 70 ፤ ይህን ሀሳብ ሊያካትቱ ይችላሉ የሚባሉ የፍታብሔር አንቀፆች 2038 ፣2067፣ 2068 ፣ 2098
©Mulugeta Belay
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
+2
ለአማራ ክልል ጠበቆች በሙሉ
🔘 🔘 🔘 🔘 🔘
የአማራ ክልል ጠበቆች የጥብቅና ፈቃድ እድሳት ከጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል ።
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
+1
ለአማራ ክልል ጠበቆች በሙሉ
🔘 🔘 🔘 🔘 🔘
የአማራ ክልል ጠበቆች የጥብቅና ፈቃድ እድሳት ከጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል ።
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
+2
⚖️ የሰ.መ.ቁ. 58634 !
ፈራሽ የቤት ሽያጭ ውል ምክንያት የተከፈለ ገንዘብ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ፣ የገንዘብ ክፍያውን በሰው ምስክር ማስረዳት ይቻላል።
የፍ/ብ/ሕ.ቁ. 2472 የሚያስቀምጠው የማስረጃ ገደብ ለብድር ውል ነው፤ ግንኙነቱ ፈራሽ የቤት ሽያጭ ውል ከሆነ በዚህ ድንጋጌ ላይ ተመስርቶ የሰው ምስክር ማስረጃን መከልከል አይቻልም።
👉 ዋናው መርህ፦ የገንዘቡ ክፍያ የተፈጸመው በብድር ሳይሆን በፈራሽ የቤት ሽያጭ ውል ምክንያት ከሆነ፣ ክፍያውን በሰው ምስክር ማስረዳት ይቻላል።
2 331
👉የፍትሐ ብሔር ሕጋችን ከቁጥር 1681 እስከ 1695 ድረስ ባሉ ድንጋጌዎች ላይ የአገራችን የዉል ሕግ
የዉል ሀሳብ በማቅረብ (Offer) እና የቀረበዉን ሀሳብ በመቀበል (Acceptance) ዉል ሊቋቋም የሚችልበትን እንዲሁም የዉል ማቅረብን (Offer) ወይም መቀበልን (Acceptance) እና ማስቀረት የሚቻልበትን አግባብ(Withdrawal of Offer) ደንግጓል፡፡
👉በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1687 እና 1688/1 ስር እንደተደነገገዉ አንድ ሰዉ ተጠቃሚዉን ሳይለይ (የዉሉ ተዋዋይ ሊሆን የሚችል ሰዉ ለይቶ ሳይገልጽ) አንድን ነገር ለመስጠት፣
አንድን ነገር ለማድረግ ወይም ላለማድረግ ፈቃደኛ መሆኑን የሚያሳይ ሀሳቡን መግለጹ፣ይህንኑ ሀሳቡን
የሚያሳዉቅ ማስታወቂያ በአደባባይ መለጠፉ፣ሀሳቡን በብዙሀን መገናኛ ማስነገሩ…(Communication of the intention or declaration of the intention without addressing particular person) ወዘተ ከሚያሳይ በስተቀር ተለይቶ ለሚታወቅ ተዋዋይ ወገን የዉል ማቅረብ (Offer) ተግባር ፈጽሟል የሚያስብል አይደለም፡፡
👉ይህ ተግባር ዉል የማቅረብ ተግባር (Offer) ተደርጎ የሚወሰድ ቢሆንና ለብዙሀን የተገለጸዉን ሃሳብ ወይም በአደባባይ የተለጠፈዉን ማስታወቂያ አይተዉ የመጡ ሰዎች በሙሉ ዉል የመቀበል ተግባር ፈጽመዋል (Acceptance) የሚባል ቢሆን ሀሳቡን በማስታወቂያ የገለጸዉ ሰዉ ፍትሐዊ ባልሆነ ሁኔታ ከብዙ ሰዎች ጋር ብዙ ዉል ፈጽሟል ወደሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ የሚያደርስ ይሆናል፡፡
👉በዚህ መሰረት አንድ ሰዉ አንድን
ነገር ለማድረግ ወይም ላለማድረግ እንደፈለገ የሚያሳይ ሀሳብ ለብዙሀን በማስታወቅ መግለጫ እንደመስጠት
(declaration of the intention without addressing particular person) የሚቆጠር እንጂ ዉል የማቅረብ ተግበር (Offer) እንደመፈጸም የሚቆጠር አይደለም፡፡👉በመሆኑም በኢትዮጵያ የዉል ሕግ መሠረት ዉል ተቋቋመ ሊባል የሚችለዉ የዉሉ ጉዳይ በሚገባ አኳኋን ተለይቶ ሲገለጽ እና ተዋዋዮች የዉል ሀሳባቸዉን በማቅረብና በመቀበል ሕጋዊ ግንኙነት ሲፈጥሩ ነዉ፡፡
👉ከዚህ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁጥር 188371 ላይ እና በሌሎች መዛግብት ላይ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
👉የከተማ ቦታ በሊዝ የማስተላለፍ ሥልጣን በአዋጅ ቁጥር 721/2004 የተሰጠዉ ለመንግሥት አስተዳደር
አካል በመሆኑ በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 16/1 እና በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1724 ስር በተደነገገዉ መሰረት መሬቱ
በሊዝ በሚተላለፍለትና መሬቱን በሊዝ በሚያስተላልፈዉ አስተዳደር አካል መካከል የሊዝ ዉሉ በጽሁፍ
ሊደረግ ይገባል፡፡
👉 በመሆኑም
2 331
👉የፍትሐ ብሔር ሕጋችን ከቁጥር 1681 እስከ 1695 ድረስ ባሉ ድንጋጌዎች ላይ የአገራችን የዉል ሕግ
የዉል ሀሳብ በማቅረብ (Offer) እና የቀረበዉን ሀሳብ በመቀበል (Acceptance) ዉል ሊቋቋም የሚችልበትን እንዲሁም የዉል ማቅረብን (Offer) ወይም መቀበልን (Acceptance) እና ማስቀረት የሚቻልበትን አግባብ(Withdrawal of Offer) ደንግጓል፡፡
👉በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1687 እና 1688/1 ስር እንደተደነገገዉ አንድ ሰዉ ተጠቃሚዉን ሳይለይ (የዉሉ ተዋዋይ ሊሆን የሚችል ሰዉ ለይቶ ሳይገልጽ) አንድን ነገር ለመስጠት፣
አንድን ነገር ለማድረግ ወይም ላለማድረግ ፈቃደኛ መሆኑን የሚያሳይ ሀሳቡን መግለጹ፣ይህንኑ ሀሳቡን
የሚያሳዉቅ ማስታወቂያ በአደባባይ መለጠፉ፣ሀሳቡን በብዙሀን መገናኛ ማስነገሩ…(Communication of the intention or declaration of the intention without addressing particular person) ወዘተ ከሚያሳይ በስተቀር ተለይቶ ለሚታወቅ ተዋዋይ ወገን የዉል ማቅረብ (Offer) ተግባር ፈጽሟል የሚያስብል አይደለም፡፡
👉ይህ ተግባር ዉል የማቅረብ ተግባር (Offer) ተደርጎ የሚወሰድ ቢሆንና ለብዙሀን የተገለጸዉን ሃሳብ ወይም በአደባባይ የተለጠፈዉን ማስታወቂያ አይተዉ የመጡ ሰዎች በሙሉ ዉል የመቀበል ተግባር ፈጽመዋል (Acceptance) የሚባል ቢሆን ሀሳቡን በማስታወቂያ የገለጸዉ ሰዉ ፍትሐዊ ባልሆነ ሁኔታ ከብዙ ሰዎች ጋር ብዙ ዉል ፈጽሟል ወደሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ የሚያደርስ ይሆናል፡፡
👉በዚህ መሰረት አንድ ሰዉ አንድን
ነገር ለማድረግ ወይም ላለማድረግ እንደፈለገ የሚያሳይ ሀሳብ ለብዙሀን በማስታወቅ መግለጫ እንደመስጠት
(declaration of the intention without addressing particular person) የሚቆጠር እንጂ ዉል የማቅረብ ተግበር (Offer) እንደመፈጸም የሚቆጠር አይደለም፡፡👉በመሆኑም በኢትዮጵያ የዉል ሕግ መሠረት ዉል ተቋቋመ ሊባል የሚችለዉ የዉሉ ጉዳይ በሚገባ አኳኋን ተለይቶ ሲገለጽ እና ተዋዋዮች የዉል ሀሳባቸዉን በማቅረብና በመቀበል ሕጋዊ ግንኙነት ሲፈጥሩ ነዉ፡፡
👉ከዚህ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁጥር 188371 ላይ እና በሌሎች መዛግብት ላይ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
👉የከተማ ቦታ በሊዝ የማስተላለፍ ሥልጣን በአዋጅ ቁጥር 721/2004 የተሰጠዉ ለመንግሥት አስተዳደር
አካል በመሆኑ በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 16/1 እና በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1724 ስር በተደነገገዉ መሰረት መሬቱ
በሊዝ በሚተላለፍለትና መሬቱን በሊዝ በሚያስተላልፈዉ አስተዳደር አካል መካከል የሊዝ ዉሉ በጽሁፍ
ሊደረግ ይገባል፡፡
👉 በመሆኑም የዉል ሕግድንጋጌዎች መሰረትም ሆነ የከተማ ቦታ በሊዝ ስለሚተላለፍበት አግባብ በአዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 16 እና አዋጁን ለማስፈጸም በወጣ ደንብና መመሪያ መሰረት አመልካች የአከራካሪዉ የከተማ ቦታ የሊዝ ባለይዞታ ሆነዋል ማለት የሚቻለዉ በቅድሚያ የሚከፈለዉን ገንዘብ መጠን ገቢ ሲያደርጉ፤ የግንባታ መጀመሪያ፣ የግንባታ ማጠናቀቂያ፣የክፍያ አፈጻጸም ሁኔታ፣ የችሮታ ጊዜ፣የዉል ሰጪና የዉል ተቀባይ መብትና ግዴታዎች እንዲሁም ሌሎች አግባብነት ያላቸዉ ዝርዝር ሁኔታዎች የተገለጸበት የሊዝ ዉል አግባብ ካለዉ አካል ጋር ካልተፈራረሙ እና የሊዝ ይዞታ የምስክር ወረቀት ካላገኙ የከተማ ቦታ ላይ ያቋቋሙት የባለይዞታነት መብት
የለም፡፡
👉የሠ/መ/ቁጥር 236645
ታህሳስ 29 ቀን 2016 ዓ/ም
2 331
👉ህግ በዜጎች መካከል ያለዉን ግንኙነት ለመቆጣጠር ሲባል በሕግ አዉጪዉ አካል የሚወጣ መሣሪያ ነዉ፡፡
👉በዚህ አግባብ የሚወጣዉም ሕጉ በሥራ ላይ ባለበት ወቅት በዜጎች መካከል ያለዉን ወይም ወደ ፊት የሚፈጠረዉን ግንኙነት ለመቆጣጠር ወይም ለመዳኘት በመሆኑ ሕጉ ከመዉጣቱ በፊት ወይም ከተሻረ በኋላ በተፈጠረ/በሚፈጠር ግንኙነት ላይ ሕግን ተፈፃሚ ማድረግ አይቻልም፡፡
👉ይህም ሕግ ወደ ኋላ ተመልሶ አይሰራም ከሚለዉ አጠቃላይ መርህ (the principle of non-retroactivity of laws) ጋር የተያያዘ ነው፡፡
👉ሕግ ወደ ኋላ ተመልሶ አይሰራም የሚለዉም መርህ መሠረተ ሃሳቡም ሕጉ በስራ ላይ ከዋለ በኋላ ለተፈጠረ መብትና ግዴታ ወይም ፍሬ ነገር ላይ ተፈጻሚ መሆን ስላለበት እና ዜጎች በሚያዉቁት ሕግ መተዳደር አለባቸዉ የሚለዉን ታሳቢ ያደረገ ነዉ፡፡
👉እንዲሁም አንድ ሕግ የሚጸናበትን ጊዜ አስመልክቶ በሕግ አዉጪዉ ከተደነገገዉ ቀን በፊት ለተፈጠሩት ክስተቶች ወይም መብትና ግዴታዎች ተፈፃሚነት አይኖረዉም የሚል ሃሳብ ያለዉ ነዉ፡፡
👉 የዚህ መርህ ተግባራዊነት የሕግ የበላይነት ከሚረጋገጥባቸዉ መገለጫዎች
መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ስለሆነም አንድ መሠረታዊ ሕግ (substantive law) ወደ ኋላ ተመልሶ እንዲሰራ ሕግ አዉጪዉ በሕጉ ላይ በልዩ ሁኔታ ካላመላከተ በስተቀር ፍርድ ቤት ወይም ሌላ የዳኝነት ስልጣን የተሰጠዉ አካል ለያዘዉ ጉዳይ ተፈፃሚነት ያለዉን መሠረታዊ ሕግ ሲወስን መሠረት ሊያደርግ የሚገባዉ ወይም እንዲያደርግ የሚጠበቅበት ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ጉዳይ በተፈጠረበት ጊዜ ተፈጻሚ ሲሆን
የነበረዉን ሕግ ሊሆን ይገባል፡፡
👉 በዚህ መሰረት አንድ ሕጋዊ ዉጤት ያለዉ ተግባር (Juridical act) ወይም መብትና ግዴታ በተፈጠረበት ጊዜ የነበረዉ ሕግ በሌላ ሕግ የተተካ ሆኖ ሲገኝ እና ክርክሩ ለፍርድ ቤት ወይም ለዳኝነት ሰጪ አካል የቀረበዉ አዲሱ ሕግ በሥራ ላይ ከዋለ በኋላ ሆኖ ከተገኘ ፍርድ ቤቱ ክርክሩን መምራት እና ዉሳኔ መስጠት ያለበት በመብትና ግዴታው በተፈጠረበት ጊዜ ተፈጻሚ ሲሆን በነበረው ሕግ መሠረት ይሆናል፡፡
👉 ክርክሩ አዲሱ ሕግ ሥራ ላይ ከዋለ በኋላ ለፍርድ ቤት መቅረቡ ጉዳዩ በአዲሱ ሕግ መሠረት እንዲመራ ምክንያት ሊሆንአይገባም፡፡ 👉ይህን ማድረግ ሕግ ወደ ኋላ ተመልሶ አይሰራም የሚለዉን
የሕግ መርህ የሚጥስ ከመሆኑም በላይ የሕግ የባላይነት እንዳይረጋገጥ ወይም እንዲሸረሸር ምክንያት ይሆናል።
👉የሰ/መ/ቁ፡-200555
ቀን፡-29/02/2014ዓ
2 331
+2
በኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ላይ በስሕተት የተመዘገበ መረጃ ካለ ተቋሙ አጣርቶ በራሱ የማስተካከል ሥልጣን አለው::
ስለሆነም ፍርድ ቤቶች “በፋይዳ መታወቂያ ላይ የተፈጠረ ስሕተት ይታረምልኝ” የሚሉ አቤቱታዎችን በቀጥታ ተቀብለው የማየት ሥልጣን የላቸውም::
ፍ/ቤቶች የዚህ ዓይነት አቤቱታዎችን መቀበል የሚችሉት ተቋሙን አስተዳደራዊ መፍትሔ ጠይቀው ካልተሰጣቸው ወይም የተሰጣቸው መፍትሔ ላይ ቅሬታ ካላቸው ብቻ ነው:: "
-የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) ለፍ/ቤቶች የጻፈው ደብዳቤ
"ጠበቆች ደንበኞቻችሁን በዚህ አግባብ እንደምታማክሩ ይሁን::)👴🏽
2 331
Repost from Click Ethiopian Laws⚖
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዐት እና የማስረጃ ሕግ 1410-2018 by Click Ethiopian Laws
2 331
Repost from Minda Girma Law Office ምንዳ ግርማ ህግ ቢሮ 0910126619
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ፣ መዝገብ ቁጥር 1248/18፣ 1249/18 እና 1250/18 (ተጣምረው የቀረቡ)፣ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም
===========
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በ6ኛው የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 2ኛ መደበኛ ጉባኤው፣ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በመዝገብ ቁጥር 1248/18፣ 1249/18 እና 1250/18 (ተጣምረው የቀረቡ) ባያቸው መዝገቦች ላይ ክርክሩ በይግባኝ ባይ ኢትዮ ቴሌኮም እና በመልስ ሰጪዎች የድርጅቱ 208 ሠራተኞች መካከል የተደረገ ሲሆን፣ ጉዳዩ የጀመረው መልስ ሰጪዎች በትግራይ ክልል ከሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 13 ቀን 2015 ዓ.ም በነበረው የጦርነት ወቅት ሥራ ሠርተናል በማለት የ17 ወራት ውዝፍ ደሞዝ እና ጥቅማጥቅም እንዲከፈላቸው በወረዳ ፍርድ ቤት ክስ በማቅረባቸው ነው።
የትግራይ ክልል የቀዳማይ ወያኔ ወረዳ ፍርድ ቤት በጦርነቱ ወቅት የነበረውን ሁኔታ በሕግ እውቅና (Judicial Notice) የሰጠው ቢሆንም፣ ሠራተኞቹ በክልሉ መንግሥት ትዕዛዝ ሥራ ላይ ነበሩ በሚል ኢትዮ ቴሌኮም ደሞዝ የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ወስኗል። በዚህ ውሳኔ ቅር የተሰኘው ኢትዮ ቴሌኮም ይግባኝ እና የሰበር አቤቱታውን ለመቀሌ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ለትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እና ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በየደረጃው ቢያቀርብም፣ ሁሉም ችሎቶች የስር ፍርድ ቤት ውሳኔን በማጽናት ወስነዋል። አሁንም ውሳኔውን ያልተቀበለው ኢትዮ ቴሌኮም ለሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ውሳኔዎቹ እንዲሻሩለት የሕገ መንግሥት ትርጉም አቤቱታ ያቀረበ ቢሆንም፣ ጉባኤው ጉዳዩ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልገውም በማለት ውድቅ አድርጎታል።
በመጨረሻም ኢትዮ ቴሌኮም ይግባኙን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቅርቧል። አመልካች በቅሬታው፣ ተቋሙ በጦርነቱ ወቅት ሥራ ባልሠራበት እና ግንኙነቱ በተቋረጠበት ሁኔታ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጁ አንቀጽ 54(1) መሠረት "ላልተሠራ ሥራ ደሞዝ አይከፈልም" የሚለው መርህ ሊጣስ እንደማይገባው ገልጿል። በተጨማሪም ፍርድ ቤቶች ሕገ መንግሥታዊ እውቅና በሌለው አካል የተሰጠ የሥራ ትዕዛዝን መሠረት አድርገው ውሳኔ መስጠታቸው የኢትዮ ቴሌኮምን ፍትሕ የማግኘት መብት (አንቀጽ 37(1)) እና የዳኞችን ገለልተኝነትና በሕግ ብቻ የመዳኘት ግዴታ (አንቀጽ 79(2)) የጣሰ በመሆኑ የሕገ መንግሥት ትርጉም ያስፈልገዋል ብሏል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤትም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በትግራይ ክልል ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ መቋረጡን እና የፌዴራል ተቋማት አለመኖራቸውን ያረጋገጠ በሕግ የተቀበሉት ሀገራዊ ስምምነት በሆነበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቶች ይህንን ሳይቀበሉ በጦርነቱ ወቅት መደበኛ የሥራ ሁኔታ እንደነበረ አድርገው የሰጡት ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ መሠረት አለው ወይስ የለውም የሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን መርምሮታል።
ከዚያም ምክር ቤቱ በሰጠው ውሳኔ፣ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 9(4) መሠረት የሀገሪቱ ሕግ አካል እንደሆነና ስምምነቱ በትግራይ ክልል የነበረው የፌዴራል መዋቅር መፍረሱን እንዲሁም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን መልሶ ማቋቋም (Restoration of Constitutional Order) እንደሚያስፈልግ በይፋ ያረጋገጠ ሰነድ ነው። በመሆኑም ፍርድ ቤቶች የፕሪቶሪያውን ስምምነት እና በውስጡ የተገለጹትን እውነታዎች በሕግ እውቅና ሰጥተው ሊቀበሉት (Judicial Notice ሊወስዱ) ሲገባ፣ ከሕገ መንግሥቱ ውጪ በነበረ አካል የተሰጠን የሥራ ትዕዛዝ በፌዴራል ተቋም (ይግባኝ ባይ) ላይ አስገዳጅ ማድረግ ተገቢነት ያለው አይደለም። የስር ፍርድ ቤቶች ሠራተኞቹ በጦርነቱ ወቅት ገቢ ሰብስበዋል ያሉት ገንዘብ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ወደ ባንክ ገቢ የተደረገ እንጂ በጦርነቱ ወቅት ሥራ መሠራቱን የሚያስረዳ አይደለም፤ ላልተሠራ ሥራ ደሞዝ እንዲከፈል ማዘዝ የይግባኝ ባይን ፍትሕ የማግኘት መብት እና የዳኝነት ገለልተኝነትን የጣሰ ነው በማለት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ውሳኔን እና የስር ፍርድ ቤቶችን ውሳኔ በሙሉ ድምጽ ሽሮታል።
2 331
Repost from Minda Girma Law Office ምንዳ ግርማ ህግ ቢሮ 0910126619
+2
በቤተሰብ ህግ መሰረት ባልና ሚስት ከጋብቻ በኋላ በውርስ ወይም በስጦታ በየግላቸው ያገኟቸው ንብረቶች የግል ንብረቶቻቸው ሆነው እንደሚቀሩ በተደነገገበት ሁኔታ በጋብቻ ወቅት ባልና ሚስት በፍ/ቤት ወይም ስልጣን ባለው አካል ባልፀደቀ ውል ከውርስ የሚገኝ ንብረት የጋራ ነው በሚል ቢዋዋሉም ውሉ በፍርድ ቤት ካልተረጋገጠ በቀር ውጤት ስለሌለው በጋብቻ ወቅት በውርስ የተገኘ ንብረት የአንደኛው ተጋቢ የግል ንብረት ሆኖ የሚቀጥል ስለመሆኑ፣
የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅፅ 26 በሰበር መዝገብ ቁጥር 198277 ላይ በተመሣሣይ ጉዳይ አስገዳጅነት ያለውን ውሣኔ ሰጥቷል።
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
+9
#የሙስና ወንጀል ዋስትና ጉዳይ
~~~~~~~~
በተሻሻለው የፀረ ሙስና ጉዳዬች ስነ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 882/07 አንቀፅ 3(1) መሰረት "ከአራት አመት በላይ እና ከአስር አመት በታች የሚያስቀጡ ተደራራቢ የሙስና ወንጀሎች ሲኖሩም እየተደመሩ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ከሆነ ዋስትናን ያስከለክላል" የሚለው ድንጋጌ "ከአራት አመት በላይ" የሚለው ሀረግ መነሻቸው ከአራት በላይ እስከ 10 ዓመት የሆኑትን ብቻ የሚመለከት ነው ወይስ መነሻቸው ከአራት አመት በታች ቢሆንም ጣሪያቸው ከአራት አመት በላይና ከ10 ዓመት በታች ያሉትን የሚመለከት ነው? ለሚለው ክርክር እልባት የሚሰጥ ውሳኔ ነው።
~~~ የቀላል እስራትንና የፅኑ እስራትን ቅጣት በአማራጭ ላስቀመጡ ድንጋጌዎች ዋስትና የሚከለከለው መነሻቸው ከአራት አመት በላይ ያሉትን ተደራራቢ የሙስና ወንጀሎች በመደመር ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጡ ከሆነ እንጂ መነሻቸው ከአራት አመት በታች ያሉትንም ጭምር በመደመር የሚመጣውን ድምር በማየት አይደለም። (ለተደራራቢ የሙስና ወንጀሎቹ ዋስትና ጥያቄን ለመወሰን ሊታይ የሚገባው መነሻ ቅጣታቸው ከአራት አመት በላይ የሆኑትን በመደመር ነው እንጂ መነሻው ከአራት አመት በታች ሆኖ ጣራው ከአራት በላይ ፅኑ እስራት የተቀመጡ ተደራራቢ ወንጀሎች ተደምረው ከ10 ዓመት ቢበልጥም ዋስትናን ለማስከልከል በቂ አይሆኑም)
#የሰ/መዝ/ቁ 182050
2 331
Repost from Bedru & Getachew law office!
+3
#አንድ_ተከሳሽ አስቀድሞ በፈጸመዉ ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ በአመክሮ ከተፈታ አምስት ዓመት የሆነዉ ቢሆንም በፍ/ቤት የመሰየም ጥያቄ አቅርቦ ባልተሰየመበትና ቅጣቱም ከፍርድ መዝገብ ተሰርዞ እንዳልተሰጠ ባልተቆጠረበት ሁኔታ የጥፋተኝነቱ ሪከርድን በቅጣት ማክበጃነት መያዝ ተገቢ ስለመሆኑ በማለት #የፌደራል_ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 161791 በሆነው በቅጽ 24 ላይ የወ/ሕ/አንቀጽ 82(1/ሀ)፣84(1/ለ)፣ 232፣233 ድንጋጌን መሰረት በማድረግ የሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ውሳኔ፡
2 331
👉ማንኛውም ተቋማት፤ ትምህርት ቤቶች ሕፃናት አስተማሪዎችም ሆነ ቤተሰቦቻቸው ወይም ሞጋዚዎቻቸው ፈቃድ ሳይሰጡበት የሕፃናቱን ፎቶግራፍ በበይነ-መረብ ወይም ኢንተርኔት ላይ በመልቀቅ ማስታወቂያ በመሥራት ገንዘብ ሰብሰብ ማስታወቂያ መሥራት በየትኛውም ክፍለ-አህጉራት ያለ ሰው ሊመለከተው የሚችል በመሆኑ ባለቤቶቹ ፈቃድ በአደባባይ ሊለጠፍ ሆነ ሊባዛ ወይም ሊሸጥ የማይችል በመሆኑ የተለጠፈ ማስታወቂያ እንዲነሳ እና በፎቶግራፉ የተገኘው ጥቅም ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ካሣ ሊከፈል የሚገባ ነው።
👉በፍ/ሕ/ቁ. 27፤ 29(1)(2)
👉 መ/ቁ 168527
👉ጥቅምት 26/ 2012 ዓ.ም
