en
Feedback
Hakim

Hakim

Open in Telegram

Ethiopian blend of Medicine, History and Humor.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Hakim

Channel Hakim (@hakimethio) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 60 567 subscribers, ranking 238 in the Medicine category and 523 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 60 567 subscribers.

According to the latest data from 10 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 695 over the last 30 days and by 103 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.66%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.11% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 454 views. Within the first day, a publication typically gains 4 909 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 40.
  • Thematic interests: Content is focused on key topics such as patient, ethiopia, disease, ነው።, medicine.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Ethiopian blend of Medicine, History and Humor.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 11 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Medicine category.

60 567
Subscribers
+10324 hours
+3167 days
+69530 days
Posts Archive
Hakim
60 567
የተራበ አዕምሮ! አንድ ምሽት በLinkedIn መልእክት ደረሰኝ። ጉዳዩ ከባድ የጤና እክል ያጋጠመው ታካሚን የሚመለከት ነበር። ታካሚው ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሙሉ በሙሉ ጤነኛ የነበረ ቢሆንም፣ በድን
+3
የተራበ አዕምሮ! አንድ ምሽት በLinkedIn መልእክት ደረሰኝ። ጉዳዩ ከባድ የጤና እክል ያጋጠመው ታካሚን የሚመለከት ነበር። ታካሚው ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሙሉ በሙሉ ጤነኛ የነበረ ቢሆንም፣ በድንገት መርሳት፣ ግራ መጋባት፣ ማቅለሽለሽ፣ የምግብ ፍላጎት ማጣት፣ ማስታወክ እና ተቅማጥ እንዳጋጠመው ተነገረኝ። ቀድሞ ለቤተሰቦቹ እንደ ደጀን የነበረው ሰው፣ በድንገት ከባድ የጤና ቀውስ ውስጥ ገባ። [የሕክምና ታሪኮች #30] የሕክምና ቡድኑ የማጅራት ገትር በሽታን እንዲሁም የአንጀት ኢንፌክሽን በማሰብ ሰፊ የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን አስጀመሩት። ተከታታይ ምርመራዎች ተካሄዱ፤ የደም ምርመራዎች ፣ የጉበት እና የኩላሊት ተግባር፣ የህብለ ሰረሰር ፈሳሽ ፣ የወባ ምርመራ፣ የአንጐል MRI፣ የደረት ራጅ እና የሆድ ዕቃ አልትራሳውንድ ቢደረግለትም ከቀላል ደም ማነስ እና የኘሮትን ማነስ ውጪ ሁሉም ምርመራዋች ምንም የሚያሳዩት የሕመም ምልክት አልነበረም። ይህ ሁሉ ጥረት ተደርጎም የታካሚው ሁኔታ እየተባባሰ ሄደ። ግራ መጋባቱ ጨመረ፣ ተቅማጡም አልቆመም። የታካሚውን ታሪክ ስሰማ አንድ ነገር ግራ አጋባኝ። ትኩሳት የለም፣ የላቦራቶሪ ምርመራዎች መደበኛ ናቸው፣ ግልጽ የሆነ የኢንፌክሽን ምልክትም የለም። በመሆኑም አንድ ቀላል ጥያቄ ጠየቅኩ፦ "ታካሚው አልኮል ይጠጣል?" መልሱም "አዎ" ነበር። በመቀጠልም "ቆዳው ላይ ሽፍታ የወጣ ካለ ጠየኩ?" "የለም" ብለው መለሱልኝ። የሕክምና መጻሕፍት በሽታዎችን እንደየምልክታቸው በግልጽ ያስቀምጣሉ፤ ነገር ግን ታካሚዎች ሁልጊዜ እንደ መጻሕፍት አይሆኑም። ቢሆንም፣ ውስጣዊ ስሜቴ ያንን "አስማታዊ መድኃኒት" እንድሞክር ነገረኝ። በመጨረሻም፣ ለሕክምናው የሚሆን ተገቢውን መጠን እንዲወስድ ሐሳብ አቀረብኩ። በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ አስገራሚ ለውጥ ታየ። ግራ መጋባቱ እየቀለለ ሄደ፣ ሰዎችን መለየት ጀመረ፣ የምግብ ፍላጎቱ ተመለሰ፣ ተቅማጡም ሙሉ በሙሉ ቆመ። ዋናው መልእክት፣ ፔላግራ (Pellagra); የኒያሲን (ቫይታሚን B3) እጥረት የሚያስከትለው የጤና ችግር ሲሆን በተለምዶ ተቅማጥ፣ የቆዳ መጎዳት፣ የአዕምሮ መታወክ እና ለሕይወት አስጊ የሆኑ ሁኔታዎችን እንደሚያስከትል ይታወቃል። ይሁን እንጂ ፔላግራ በቆዳ ላይ በሚታዩ ምልክቶች ብቻ የሚገለጽ ባለመሆኑ፣ እነዚህ ምልክቶች ባይኖሩም እንኳ እንደ ተቅማጥ ያሉ ሥር የሰደዱ ችግሮች፣ እንዲሁም የአዕምሮ መታወክ ምልክቶች ሲያጋጥሙ የኒያሲን እጥረትን መጠርጠር ይገባል። በተለይም አልኮል አዘውታሪዎች ወይም በአመጋገብ እጥረት የሚሰቃዩ ሰዎች ላይ የቆዳ ለውጥ አለመኖር በሽታውን የመመርመር ዕድልን ማሳጣት የለበትም፤ በመሆኑም ከፍተኛ የሕክምና ጥርጣሬ ካለ፣ ቀደም ብሎ የኒያሲን ሕክምና መጀመር የታካሚውን ጤንነት በፍጥነት ወደ ቀድሞ ሁኔታው ለመመለስ እና ሕይወትን ለማትረፍ ወሳኝ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። Segenet Bizuneh Internist, GI/Hepatology fellow St. Paul's Hospital Millennium Medical College - SPHMMC @HakimEthio

Hakim
60 567
A patient may celebrate losing 20 kilograms while unknowingly sacrificing a substantial amount of the very tissue that protects metabolic health, maintains functional capacity, and supports healthy aging. Smaller clothing sizes do not necessarily indicate a healthier body composition. A lower number on the scale does not automatically mean a better metabolic outcome. The physiological explanation is straightforward. These medications reduce appetite and food intake, often dramatically. While this reduction in calorie consumption drives fat loss, it can also reduce protein intake. When dietary protein becomes insufficient, the body may obtain amino acids from existing muscle tissue to meet its biological needs. At the same time, many individuals become less physically active or fail to engage in resistance training, removing the mechanical stimulus required to preserve muscle mass. From an evolutionary perspective, muscle is metabolically expensive tissue. During periods of perceived energy scarcity, the body often adapts by reducing both fat stores and lean tissue unless there is a compelling reason to maintain muscle. Adequate protein intake and resistance exercise provide that reason. This is why successful obesity treatment should not focus exclusively on weight loss. The goal should be fat loss while preserving lean mass. These are not the same thing. Patients receiving GLP-1 receptor agonists or dual agonists should be encouraged to prioritize dietary protein, engage in regular resistance training, and monitor body composition whenever possible. Measurements such as DXA scans, bioimpedance analysis, waist circumference, strength assessments, and functional performance tests provide a far more meaningful picture of health than body weight alone. The future of obesity medicine should move beyond the simplistic concept of weight reduction. Excess body fat contributes to metabolic disease, but skeletal muscle is one of the body’s greatest protective organs. The ideal outcome is not maximum weight loss. The ideal outcome is maximum fat loss with minimum muscle loss. As clinicians, we must remember that our patients do not simply need to become lighter. They need to become metabolically healthier, physically stronger, and more resilient. The scale measures weight. Body composition measures health. And when it comes to long-term metabolic health, strength, function, and longevity, muscle may be the most important tissue we possess. References 1. Wilding JPH, Batterham RL, Calanna S, et al. Once-Weekly Semaglutide in Adults with Overweight or Obesity. New England Journal of Medicine. 2021;384:989-1002. 2. Rubino DM, Greenway FL, Khalid U, et al. Effect of Weekly Subcutaneous Semaglutide vs Placebo on Body Composition in Adults with Overweight or Obesity. STEP 1 DXA Substudy. 3. Jastreboff AM, Aronne LJ, Ahmad NN, et al. Tirzepatide Once Weekly for the Treatment of Obesity. New England Journal of Medicine. 2022;387:205-216. 4. SURMOUNT-1 Body Composition Substudy Investigators. Effects of Tirzepatide on Fat Mass and Lean Mass Distribution in Adults with Obesity. 5. Systematic Review of Muscle-Related Outcomes Associated with Incretin-Based Therapies. Annals of Internal Medicine. 2026. 6. Cruz-Jentoft AJ, Bahat G, Bauer J, et al. Sarcopenia: Revised European Consensus on Definition and Diagnosis. Age and Ageing. 2019;48(1):16-31. 7. Wolfe RR. The Underappreciated Role of Muscle in Health and Disease. American Journal of Clinical Nutrition. 2006;84(3):475-482. 8. Srikanthan P, Karlamangla AS. Muscle Mass Index as a Predictor of Longevity in Older Adults. American Journal of Medicine. 2014;127(6):547-553 Dr. Berry Dubiso, MD Dr Berry Right Medical Consultancy Contact & Location 📞 0911581692 DrBerry Health Consultancy Gerji (Totot), Addis Ababa Right Medical Consultancy Bole, DH Geda Tower, Addis Ababa Service registration link: https://form.drberrydubiso.com Facebook: https://www.facebook.com/share/15ku8YYkV8X/?mibextid=wwXIfr Telegram: https://t.me/drberrydubiso

Hakim
60 567
Muscle Matters More Than the Scale: The Hidden Cost of Modern Weight-Loss Drugs The number on the scale tells us how much weight has been lost. It does not tell us what has been lost. This distinction is becoming increasingly important as millions of people worldwide achieve substantial weight reduction with GLP-1 receptor agonists and dual GIP/GLP-1 agonists such as semaglutide and tirzepatide. These medications have revolutionized obesity treatment and have helped many patients improve blood sugar control, reduce cardiovascular risk factors, and lose significant amounts of body weight. Yet an important question often remains unanswered: how much of that weight loss is actually body fat, and how much is valuable lean tissue? Many patients assume that every kilogram lost represents excess body fat. Human physiology is far more complex. Weight loss can come from fat mass, glycogen, water, connective tissue, organ mass, and skeletal muscle. From a metabolic standpoint, these tissues are not equal. Losing excess body fat is generally beneficial. Losing skeletal muscle is not. Recent scientific evidence has highlighted this concern. A 2026 meta-analysis that evaluated 20 randomized controlled trials involving nearly 16,000 participants found that approximately 35.2% of total weight lost with semaglutide consisted of lean mass. In practical terms, this means that for every 10 kilograms of body weight lost, more than 3 kilograms may come from lean tissue rather than fat. The findings are consistent with the STEP 1 body-composition substudy, which used dual-energy X-ray absorptiometry (DXA) to examine changes in body composition during semaglutide treatment. Participants experienced substantial fat loss, but they also demonstrated meaningful reductions in lean body mass. Tirzepatide appears to perform somewhat better. In the SURMOUNT-1 trial, approximately 25% of total weight lost consisted of lean mass, while roughly 75% represented fat mass. This suggests that the dual GIP/GLP-1 mechanism may offer some advantage in preserving lean tissue compared with GLP-1 receptor agonism alone. However, even under these circumstances, one-quarter of total weight loss still came from lean tissue. The concern extends beyond individual medications. A 2026 systematic review published in the Annals of Internal Medicine evaluated 36 randomized controlled trials involving incretin-based therapies and found that approximately two-thirds of studies exceeded predefined muscle-loss benchmarks. Across these studies, the median proportion of weight loss attributable to muscle-related tissue loss approached 35%. These findings should not be dismissed as a cosmetic issue. Skeletal muscle is one of the most important organs in the human body. It is the primary site for glucose disposal after meals and plays a critical role in insulin sensitivity and blood sugar regulation. Muscle serves as a reservoir of amino acids during illness and injury. It supports mobility, balance, strength, physical function, and independence. It also contributes significantly to resting energy expenditure and overall metabolic health. Perhaps most importantly, muscle mass and strength are among the strongest predictors of healthy aging and longevity. Numerous studies have demonstrated that lower muscle mass is associated with increased risks of frailty, falls, fractures, hospitalization, disability, loss of independence, and premature mortality. The medical term for the progressive loss of skeletal muscle mass and strength is sarcopenia. Although traditionally associated with aging, sarcopenia is increasingly recognized in individuals who undergo rapid weight loss. This includes people following aggressive calorie restriction, those recovering from illness, patients undergoing bariatric surgery, and individuals receiving modern weight-loss medications. The danger is not simply becoming lighter. The danger is becoming weaker.

Hakim
60 567
photo content

Hakim
60 567
Vacancy Announcement : Tazma Medical & Surgical Specialized Center Location: Ethiopia, Addis Ababa, Gotera Condominium Compou
Vacancy Announcement : Tazma Medical & Surgical Specialized Center Location: Ethiopia, Addis Ababa, Gotera Condominium Compound Positions 1. Position: Matron Education: BSc in Nursing with relevant skills and experience (3 years of experience and above) Required Number: 1 2. Position: Clinical Coordinator Education: BSc in Nursing or Public Health with relevant skills and experience (1 year of experience and above) Required Number: 2 3. Position: Clinical Nurse Education: BSc in Nursing, 0 years of experience and above Required Number: 5 4. Position: General Practitioner Education: Degree in Medicine (MD), 0 years of experience and above Required Number: 2 5. Position: Laboratory Technologist Education: BSc in Medical Laboratory Technology, 0 years of experience and above Required Number: 2 Application Deadline: June 18, 2026 N.B.: All applicants must possess a valid professional license. Please indicate the position you are applying for in the subject line of your email. E-mail Address: tazmamedical@gmail.com In-Person Application: Tazma Medical & Surgical Specialized Center, Gotera Condominium Compound, Addis Ababa, Ethiopia @HakimEthio

Hakim
60 567
An Encounter from Today’s Ward Rounds: The Lasix Trap During our morning rounds in the Stabilization Center today, we evaluat
An Encounter from Today’s Ward Rounds: The Lasix Trap During our morning rounds in the Stabilization Center today, we evaluated a newly admitted child presenting with severe, tense bilateral pitting edema. Looking at the profound swelling, one well-meaning nurse turned to me and said: "Doctor, the swelling is severe and the child looks uncomfortable. Should we give a dose of Lasix (furosemide) right now to help flush out this fluid and relieve the tension?" It is a completely understandable instinct. In standard pediatric or adult medicine, when we see massive fluid retention, diuretics are our go-to solution. But in Severe Acute Malnutrition (SAM), this exact, well-intentioned decision can be fatal. Here is why I told the team we must step away from the Lasix, and why the official guidelines explicitly state that diuretics are strictly contraindicated for nutritional edema: ❌ INCORRECT AND ✅️ CORRECT PRACTICE 1. Giving Diuretics for Edema: Never give these! Edema will resolve naturally with correct initial treatment using therapeutic feeds. 2. Giving IV Fluids Freely: Giving IV fluids when the child is not in shock can be fatal. Give IV fluids *only* if there are clear signs of shock (cold hand plus slow capillary refill or a weak/fast pulse). 3. Starting High-Protein Diets Immediately: Do not do this. Give F-75 until the child stabilizes; only transition to F-100/RUTF during the rehabilitation phase. 4. Using Standard ORS: Standard ORS can overload the child. Always use ReSoMal for severely malnourished children presenting with diarrhea. 5. Withholding Antibiotics: Do not wait for clinical signs of infection (like fever). Presume infection and give routine broad-spectrum antibiotics to all admitted SAM children. 6. Starting Iron Immediately: Treating anemia with iron from admission is dangerous. Wait to start iron until the child has successfully transitioned to F-100 for at least 2 days. 7. Skipping Night Protocols: Children must not be left unfed or uncovered at night. Ensure the child is fed every 2 hours at night and stays warmly covered with a blanket to prevent hypothermia. The Takeaway: Adherence to standard, evidence-based protocols saves lives. Let's audit our ward practices and keep our fragile pediatric patients safe! Reference: Management of Acute Malnutrition Participant Module, #Pediatrics #SAM #ClinicalExcellence #Nutrition #BulePrimaryHospital #EvidenceBasedMedicine Dr. Surafel Mulugeta: General practitioner @HakimEthio

Hakim
60 567
The Illusion of the “Benign” Cosmetic Thyroidectomy: An Ethics and Teamwork Wake-Up Call 📌 [BMJ Journal of Medical Ethics] ✍
+2
The Illusion of the “Benign” Cosmetic Thyroidectomy: An Ethics and Teamwork Wake-Up Call 📌 [BMJ Journal of Medical Ethics] ✍️ Behaylu Tesfamaryam Hagos (Assistant Professor of Internal Medicine, Debre Berhan University) 🧨The Core Issue: This commentary reviews a sobering real-world case of an asymptomatic patient who underwent a bilateral thyroidectomy purely due to societal pressure regarding the cosmetic appearance of her neck. Post-surgery, she was left with permanent hypoparathyroidism, requiring life-long, costly, and frequently unavailable active vitamin D analogs with calcium supplement, alongside repeated emergency visits for acute hypocalcemic crises. I strongly believe that when an operation is performed for an entirely benign conditions, especially for cosmetic reasons, our clinical tolerance for preventable, life-altering complications should be exactly zero. 🗣️The Three Main Takeaways: 1. The Local "Reality vs. Statistics" Gap: While Western literature quotes the risk of permanent hypoparathyroidism at a mere 0–3%, our local data paint a vastly different picture. Studies from resource-constrained settings (such as St. Paul's Hospital Millennium Medical College) show local thyroidectomy complication rates as high as 29.4%, with 6.1% developing chronic hypoparathyroidism. This discrepancy is driven by a critical shortage of subspecialized endocrine surgeons, meaning generalists frequently perform these delicate procedures. 2. The Deficit in Preoperative Counseling: Reflecting on my own communication habits, I note that we clinicians heavily rely on paternalistic communication norms, often dismissing potential risks as "statistically rare" events to streamline patient decision-making. Minimizing these risks to avoid overwhelming a layperson is a systemic betrayal of patient autonomy. 3. Postoperative Isolation & Siloed Care: This case highlights a dangerous structural flaw: managing complex surgical complications in isolated silos. When the patient developed severe postoperative hypocalcemia, the surgical team attempted to manage the metabolic crisis on their own using mega-doses of oral calcium, overlooking the basic physiological fact that parathyroid hormone deficiency requires active vitamin D analogs for absorption. No formal multidisciplinary consultation was made to the concerned department. 📣Call to Action: Managing surgical complications effectively requires cross-departmental collaboration, moving beyond the boundaries of the operating theater. I am calling for: 1. Moving away from a single consent template for a variety of procedures, and shifting toward accurate, localized risk disclosures for specific operations. 2. Activating multidisciplinary team communications whenever a complex clinical case demands it, ensuring the patient receives the highest standard of institutional care available. 🖇️ Read the full commentary here: https://blogs.bmj.com/medical-ethics/2026/06/10/the-illusion-of-the-benign-cosmetic-thyroidectomy-an-ethics-and-teamwork-wake-up-call/?utm_campaign=shareaholic&utm_medium=linkedin&utm_source=socialnetwork Behaylu Tesfamaryam Hagos, MD, Internist @HakimEthio

Hakim
60 567
Beyond global North–led response: South–South collaboration at the frontline of Marburg virus outbreak control Tsion Firew, Finot Debebe, Woldesenbet Waganew, Tesfaye Getachew, Lemlwm Beza, Menelas Nkeshimana Link: PLOS Glob Public Health 6(6): e0006515. doi:10.1371/journal.pgph.0006515 To send your papers use @HakimAds @HakimEthio

Hakim
60 567
Viral suppression status and associated factors among key populations on ART in Western Oromia, Ethiopia: a retrospective analysis Kenate Bekele, Endalu Tesfaye Guteta, Abdi Diriba, Gadisa Chewaka, Demeke Jabessa, Daniel Amsalu Link: https://pubmed.ncbi.nlm.nih.gov/42108473/ To send your papers use @HakimAds @HakimEthio

Hakim
60 567
ቡና መጠጣት በኩላሊት ላይ ምን ውጤት ያስከትላል? መጠነኛ የሆነ ቡና መጠጣት የኩላሊት ተግባርን ለመጠበቅ እንደሚረዳ እና የኩላሊት ጠጠር እንዳይፈጠር እንደሚቀንስ ተጠቁሟል። ነገር ግን ጥቅሙ ለሁሉም
+2
ቡና መጠጣት በኩላሊት ላይ ምን ውጤት ያስከትላል? መጠነኛ የሆነ ቡና መጠጣት የኩላሊት ተግባርን ለመጠበቅ እንደሚረዳ እና የኩላሊት ጠጠር እንዳይፈጠር እንደሚቀንስ ተጠቁሟል። ነገር ግን ጥቅሙ ለሁሉም ሰው ተመሳሳይ አይደለም። የዶ/ር ዶናልድ ዲ. ሄንስሩድ (የማዮ ክሊኒክ የህክምና አርታኢ) እንደሚሉት “ቡና በየጊዜው በሚጠጡ ሰዎች ላይ የስኳር በሽታ (ዓይነት 2)፣ የፓርኪንሰን በሽታ፣ የጉበት በሽታ፣ አንዳንድ ካንሰሮች (ለምሳሌ የጉበት ካንሰር)፣ ድብርትና ራስን የማጥፋት ስሜት፣ የኩላሊትና የሐሞት ጠጠር እንዲሁም አጠቃላይ ሞት የመጋለጥ እድል ይቀንሳል።” እ.ኤ.አ. በ2018 በኔፍሮሎጂ ዳያሊሲስ ትራንስፕላንቴሽን ጆርናል ላይ የታተመ ጥናት በአሜሪካ ውስጥ ሥር የሰደደ የኩላሊት በሽታ ካላቸው ከ4,860 አዋቂዎች በላይ መረጃ ተንትኗል። ተሳታፊዎቹ በዕለታዊ የካፌይን መጠን በአራት ቡድን ተከፍለዋል፦ - በቀን ከ28.2 ሚሊግራም ያነሰ ካፌይን (ከአንድ ኩባያ ቡና ከሶስተኛ ያነሰ) - ከ28.2 እስከ 103 ሚሊግራም - ከ103 እስከ 213.5 ሚሊግራም - ከ213.5 ሚሊግራም በላይ (ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ኩባያ) በአምስት ዓመት ክትትል ወቅት ወደ 1,280 የሚጠጉ ተሳታፊዎች ሞተዋል። ሌሎች አስተዋጽዖ ሊያደርጉ የሚችሉ ነገሮችን ከተቆጣጠሩ በኋላ፣ ውጤቱ እንዳሳየው ሦስቱም ከፍተኛ የካፌይን ፍጆታ ያላቸው ቡድኖች ከዝቅተኛው ቡድን ጋር ሲነጻጸሩ የመሞት እድላቸው ከ22% እስከ 26% ዝቅ ብሏል። የኩላሊት ጠጠርን መቀነስ በአሜሪካ ብሔራዊ የኩላሊት ፋውንዴሽን መሠረት ካፌይን የሽንት መጠንን ይጨምራል፣ ይህም በሽንት ቱቦ ውስጥ ጠጠር የሚፈጥሩ ማዕድናት እንዳይከማቹና ክሪስታል እንዳይሆኑ ሊረዳ ይችላል። አንዳንድ ጥናቶች ቡና በየጊዜው በሚጠጡ ሰዎች ላይ የኩላሊት ጠጠር የመጋለጥ እድሉ እንደሚቀንስ አስተውለዋል። ነገር ግን ይህ ብዙ ቡና መጠጣት የተሻለ ነው ማለት አይደለም። ባለሙያዎች ጤናማ አዋቂዎች የካፌይን ፍጆታቸውን በቀን ከ400 ሚሊግራም በላይ እንዳያደርጉ ይመክራሉ፣ ይህም ከሦስት እስከ አራት መደበኛ ኩባያ ቡና ጋር እኩል ነው። ከመጠን በላይ ካፌይን መውሰድ እንቅልፍ ማጣት፣ እረፍት ማጣት፣ ጭንቀት፣ እንዲሁም የልብ ምት መደናገርን ሊያስከትል ይችላል። ካፌይን በተለይ ለእሱ ተጋላጭ በሆኑ ሰዎች ላይ ለአጭር ጊዜ የደም ግፊትን በመጠኑ ከፍ ሊያደርግ ይችላል። ከዚህ በተጨማሪ ቡናው በብዛት ከስኳር፣ ከወተት፣ ከከባድ ክሬም ወይም ጣዕም ከተጨመረበት ሽሮፕ ጋር በየጊዜው ከተጠመቀ ጥቅሙ ሊቀንስ ይችላል፤ ምክንያቱም እነዚህ ንጥረ ነገሮች የስኳር እና የካሎሪ መጠንን ይጨምራሉ። የኩላሊት በሽታ፣ የደም ግፊት ወይም ሌላ ሥር የሰደደ የጤና ችግር ያለባቸው ሰዎች ተገቢውን የካፌይን መጠን በተመለከተ ሐኪማቸውን ማማከር አለባቸው። References 1. Vieira, M. B., et al. "Caffeine consumption and mortality in chronic kidney disease: a nationally representative analysis." Nephrology Dialysis Transplantation, Volume 33, Issue 6, June 2018, Pages 974–980. 2. Dr. Donald D. Hensrud and the general recommendation to limit caffeine to 400 mg per day https://www.mayoclinic.org/healthy-lifestyle/nutrition-and-healthy-eating/in-depth/caffeine/art-20049372 3. National Kidney Foundation - Diet and Kidney Stones Note on source: This NKF resource mentions limiting instant coffee if you have oxalate stones . However, more recent research indicates that caffeine's diuretic effect helps prevent stones in healthy people . ፋርማሲስት አብነት ድንቅነህ @HakimEthio

Hakim
60 567
The PPH CART During my stay as medical intern in Gyne/Obs I have witnessed a number of patients that came with PPH and there
The PPH CART During my stay as medical intern in Gyne/Obs I have witnessed a number of patients that came with PPH and there was a lot of obstacles when it came to managing these mothers 1. The first obstacle was the time of arrival By the time the mother arrives she has lost nearly 50% of her blood volume and I am not saying primary hospitals are the blame. But there are ways to avoid this and if the inevitable happens referral should not be delayed!! 2. Trying to find blood First of all why doesn’t the GYNE/OBS have their own blood bank? Why is it that the most pressing matter in that situation is blood and the closest a person can go get blood is at least 20-30minutes! My idea is when blood banks are out gathering blood donations their first moto is save a dying mother yet there are times these mothers don’t get the blood they need. 3. The medication and the equipment If we look at other departments they have crash carts why don’t we? Think about it among the most emergency cases is PPH yet we have to look (or prescribe) life saving medication and equipment. Imagine having to borrow IV cannulas from another patient! Or anything for that matter hence the need for the PPH crash carts. 4. Proper training Most of our society prefers primary hospitals to tertiary hospitals, that’s something that should be its own subject. I think we should provide primary hospitals with the proper training and a more strict selection process for the gyne/obs emergency department personnel. It’s not criticism of any sorts but we all know some people are quick to think on their feet and some take time to process and I also believe they need a good understanding of priorities in that situation. STORY I have encountered a PPH patient on my first day attaching GYNE emergency as an intern and the situation was horrendous we were trying everything we can to save this mother which might I add has been bleeding for nearly 5 hours before she arrived at the hospital. She had received 2 units of blood on the way and as she was being transferred from the gurney to the bed one of the IV lines disconnected and imagine all hands on deck situation. The personnel that was transporting the patient from the primary hospital said “give me the NASG (Non Pneumatic Anti-shock garment) I need to go" hence the lack of priority oriented training. Here I am not saying she was supposed to stay for the entire time this mother was at the hospital but me personally I would not worry about NASG while a mother is actively bleeding and might die. If we don’t do everything properly, and let me say I am not a saint, but I believe my training was "the patient first." I would help until the mother is stable enough to transport to the OR team. There are so many things I would like to say but I am afraid no one will read such a lengthy thread. Dr. Estahil Mohamed MD @HakimEthio

Hakim
60 567
ማህፀን መንሸራተት (Pelvic Organ Prolapse) ምንድን ነው? ሰላም ውድ ተከታታዮች: ዛሬ ብዙ ሴቶች የሚያጋጥማቸው ነገር ግን ብዙ ጊዜ የማይነገርበትን የማህፀን መንሸራተት ወይም የዳሌ ውስ
+3
ማህፀን መንሸራተት (Pelvic Organ Prolapse) ምንድን ነው? ሰላም ውድ ተከታታዮች: ዛሬ ብዙ ሴቶች የሚያጋጥማቸው ነገር ግን ብዙ ጊዜ የማይነገርበትን የማህፀን መንሸራተት ወይም የዳሌ ውስጥ አካላት ወደውጭ መውጣት (Pelvic Organ Prolapse) ስለሚባለው እንነጋገራለን። ማህፀን መንሸራተት ምንድን ነው? ማህፀን፣ ፊኛ፣ አንጀት እና ሌሎች የዳሌ ውስጥ አካላት በጡንቻዎችና በጅማቶች ይደገፋሉ። እነዚህ ድጋፍ ሰጪ አካላት ሲደክሙ ወይም ሲጎዱ ማህፀን፣ ፊኛ ወይም አንጀት ወደ ታች ሊወርዱ ይችላሉ። ይህንን ሁኔታ የዳሌ ውስጥ አካላት መንሸራተት ወይም Pelvic Organ Prolapse እንላለን። መንስኤዎቹ ምንድናቸው? - ብዙ ልጅ የወለዱ እናቶች - ከባድ ወይም ረዥም ጊዜ የፈጀ ምጥ - በወሊድ ጊዜ የተፈጠረ የዳሌ ጡንቻ ጉዳት - እድሜ መጨመር - ከማረጥ (Menopause) በኋላ የሚከሰት የሆርሞን መቀነስ - ከፍተኛ ውፍረት - ረዥም ጊዜ የሚቆይ ሳል - የረዥም ጊዜ ድርቀት እና በሰገራ ጊዜ አብዝቶ መግፋት - ከባድ ዕቃ በተደጋጋሚ ማንሳት ምልክቶቹ ምንድናቸው? 🔹 በብልት ውስጥ ያልተለመደ ነገር እንዳለ የሚሰማ ስሜት 🔹 በብልት ውስጥ ኳስ ወይም ክብ ነገር እንዳለ መሰማት 🔹 የዳሌ ክብደት ወይም ጫና መሰማት 🔹 የጀርባ ህመም 🔹 ሽንት በተደጋጋሚ መምጣት 🔹 ሳል ሲያስል፣ ሲስቅ ወይም ሲሮጥ ሽንት ማምለጥ 🔹 ሽንት ሙሉ በሙሉ እንዳይወጣ መከልከል ወይም ለመሽናት በእጅ የወጣውን ነገር መመለስ ማስፈለግ 🔹 የሰገራ ችግር 🔹 በግብረ ሥጋ ጊዜ ህመም ወይም ምቾት ማጣት ችግሩ ካልታከመ ምን ሊያስከትል ይችላል? - የተደጋጋሚ የሽንት ኢንፌክሽን - ሽንት ለማውጣት መቸገር - በወጣው ክፍል ቁስለት ወይም መድማት - የግብረ ሥጋ ግንኙነት ላይ ችግር ይህም ለባለ ትዳሮች ትዳራቸው አደጋ ላይ መውደቅ - የአእምሮ ጭንቀት፣ የራስ መተማመን መቀነስ - በከባድ ሁኔታ የኩላሊት ሥራ ላይ ተጽዕኖ ሊፈጥር ይችላል እንዴት መከላከል ይቻላል? ✔️ የዳሌ ጡንቻ ልምምድ (Kegel Exercise) ማድረግ ✔️ ጤናማ ክብደት መጠበቅ ✔️ የሆድ ድርቀትን መከላከል ✔️ ረዥም ጊዜ የሚቆይ ሳል ካለ መታከም ✔️ ከባድ ዕቃዎችን በተደጋጋሚ አለማንሳት ✔️ በወሊድ ጊዜ ተገቢ የሕክምና ክትትል ማግኘት "ማህፀን መንሸራተት የእርጅና መደበኛ ክፍል አይደለም፤ ሕክምና ያለው ችግር ነው። በብልትዎ ውስጥ ያልተለመደ ነገር እንዳለ ከተሰማዎት፣ የሽንት ወይም የሰገራ ችግር ካለብዎት ወይም ማህፀን እንደሚወርድ ከተሰማዎት በፍጥነት ሕክምና ባለሙያ ያማክሩ።" ይህን መረጃ ለሌሎች ሴቶችም ያጋሩ እናመሰግናለን References 1. Walters MD, Karram MM. Urogynecology and Reconstructive Pelvic Surgery. 5th ed. Philadelphia: Elsevier; 2022. 2. American College of Obstetricians and Gynecologists (ACOG). Pelvic Organ Prolapse: ACOG Practice Bulletin Summary, Number 214. Obstet Gynecol. 2019;134(5):1124-1127. doi:10.1097/AOG.0000000000003520. 3. Hoffman BL, Schorge JO, Halvorson LM, Hamid CA, Corton MM, Schaffer JI. Williams Gynecology. 4th ed. New York: McGraw-Hill Education; 2024. Chapter 24, Pelvic Organ Prolapse. ዶ/ር ፍኖት በቅ/ጴጥሮስ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት እና የሴቶች ሽንት ፊኛና ዳሌ ወለል ቀዶ ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት @HakimEthio

Hakim
60 567
የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ለልጆች ጠቃሚ ነው ወይስ ጎጂ? ብዙ ወላጆች ላይ ከሚፈጠሩ ጥያቄዎች መካከል አንዱ የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ለልጆች ጠቃሚ ነው ወይስ ጎጂ የሚለው ነው። ታዲያ ለ
+3
የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ለልጆች ጠቃሚ ነው ወይስ ጎጂ? ብዙ ወላጆች ላይ ከሚፈጠሩ ጥያቄዎች መካከል አንዱ የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ለልጆች ጠቃሚ ነው ወይስ ጎጂ የሚለው ነው። ታዲያ ለዚሁ ጥያቄ መልስ ምን እንደሆነ አብረን እናያለን። በተለያዩ ሆስፒታሎች የህፃናት መራመጃ ጋሪ በሚጠቀሙ እና በማይጠቀሙ ህፃናት ላይ የተደረገው ጥናት ይህንን ውጤት አስቀምጧል የህፃናት መራመጃ ጋሪ ጥቅሞቹ 1. ህፃናት መቆምና መራመድ እንዴት እንደሆነ ያውቃሉ 2. ያለማንም እርዳታ እንደልባቸው በመዟዟር ይጫወታሉ 3. ከጎናቸው ወላጆች በነፃነት ሌላ ስራን ማከናወን ይችላሉ 4. ጋሪው የተለያዩ ማጫወቻዎች ስላሉት ልጆችን ያዝናናል የህፃናት መራመጃ ጋሪ ጉዳቶቹ 1. አብዛኛውን ጊዜ ከሚጠበቅባቸው ፍጥነት በላይ ስለሚሄዱ ለተለያዩ አደጋዎች ይጋለጣሉ። ለምሳሌ -  ከተጋጩ ጭንቅላታቸው ላይ እቃ ሊወድቅባቸው እና ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል - የምግብ ማብሰያ እሳት ጋር ሊደርሱና የቃጠሎ አደጋ ወይም ትኩስ የሆነ ነገር ሊደፋባቸው ይችላል -  በቀላሉ ባእድ የሆኑ ነገሮችን ስለሚያገኙ እና በመብላት ለትንታ ወይም ለመታነቅ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ - ከደረጃ ላይ በመገልበጥ ወይም በራሳቸው ሲጫወቱ በመገልበጥ የጭንቅላት እና የአንገት እስከሞት ሊያደርስ የሚችል ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል። 2. በራሳቸው ጊዜ እና ጥረት ለመገላበጥ ለመቀመጥ ለመዳህ ለመቆም እንዲሁም ለመራመድ የሚጠቅሟቸውን ጡንቻዎች እንዲዳከሙ በማድረግ የእንቅስቃሴ እድገታቸውን ያዘገየዋል 3. ጋሪ ውስጥ ሆነው ሲራመዱ እግራቸውን ማየት ስለማይችሉ የአይን እይታ እና እርምጃ ጥምረትን ያዛባል 4. የወገብ እና ጉልበት መገጣጠሚያዎችን የሰውነት ክብደት የመሸከም ብቃትን ይቀንሳል 5. ራሳቸውን ችለው ሚዛናቸውን ጠብቀው እንዳይቆሙ እና እንዳይራመዱ ያሰንፋቸዋል 6. የጀርባ አከርካሪ አጥነታቸው ላይ ሚዛኑን ያልጠበቀ ጫና ስለሚፈጥር ካደጉ በኋላ ለወገብ ለህመም  ሊያጋልጣቸው ይችላል ስለዚህ በአጠቃላይ በተደረገው ጥናት መሰረት ውጤቱ የሚያሳየው የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ጥቅሞቹ እንዳሉ ሆነው ጉዳቶቹ ግን ያመዝናሉ ማለት ነው። Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCxaCrDCN4DS53DvRYi4dWcQ ዶ/ር ዮናታን ከተማ: በቅዱስ ፓውሎስ ሆስፒታል የህፃናት ቀዶ ህክምና ሬዚደንት ሀኪም @HakimEthio

Hakim
60 567
🔍 Forensic Case Spotlight: The Heart That Confused the Cardiologists🔍 The Scenario: A 52-year-old man with no prior cardiac
🔍 Forensic Case Spotlight: The Heart That Confused the Cardiologists🔍 The Scenario: A 52-year-old man with no prior cardiac history presented to the emergency department with progressive shortness of breath and fatigue. An echocardiogram showed a "thickened left ventricle with restrictive physiology." Cardiologists debated: hypertrophic cardiomyopathy? Amyloidosis? Sarcoidosis? Endomyocardial fibrosis? Advanced imaging was inconclusive. Before a biopsy could be scheduled, the patient died suddenly. The Autopsy Findings: External Examination: Unremarkable. The Heart: The heart appeared normal externally. But when a standard transverse section through the ventricles made, the left ventricular myocardium was riddled with multiple, small, white, linear streaks radiating from the endocardium outward. The right ventricular wall showed similar but less extensive changes. The endocardium was thickened, pearly white, and leathery. The Valves: The mitral and tricuspid valves were mildly thickened but not destroyed. The Diagnosis: Endomyocardial Fibrosis (EMF): The white, fibrous streaks and leathery endocardium are pathognomonic for endomyocardial fibrosis, a restrictive cardiomyopathy of unknown cause, common in tropical regions but rarely diagnosed antemortem. Why This Case Wowed the Cardiologists: 1) Answer in plain sight – Cardiologists debated echo/MRI. It's diagnosed in seconds with scalpel and naked eye. Endomyocardial fibrosis has a distinctive gross pattern. 2) Missed clues – Classic signs absent. Autopsy showed "burnt-out" stage: inflammation gone, dense fibrosis only. 3) Public health lesson – EMF is a leading cause of restrictive cardiomyopathy in Africa/Asia, rarely diagnosed before death. Astonishing part – Heart was rigid, white-lined, imprisoned by fibrosis, not hypertrophy. Takeaway: Died from a disease diagnosable years earlier. White streaks were a message. Sometimes the simplest tool, a sharp scalpel and open mind, solves the mystery. Further reading materials 1) Grimaldi, A., Mocumbi, A. O., Freers, J., & Sidi, D. (2016). Endomyocardial fibrosis: recent advances and future directions. Orphanet Journal of Rare Diseases, 11(1), 1-9. 2) Pathoma. (n.d.). Restrictive cardiomyopathy: endomyocardial fibrosis. Pathoma. [Based on real case scenarios but have been redrafted, findings and specifics are changed for medico-legal reasons.] Dr. Tesfaye G. Sadam, MD, MPH, Forensic medicine and toxicology specialist @HakimEthio

Hakim
60 567
ያለመውለድ ችግር (መካንነት) 10 ዋና ዋና ምክንያቶች ጥንዶች ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ በቀጣዩ የህይወት ምዕራፍቸው የሚጠብቁት ነገር ልጅ መውለድ ነው። አንድ ሴት ምንም የመውለድ ችግር ሳይኖርባት እና
+2
ያለመውለድ ችግር (መካንነት) 10 ዋና ዋና ምክንያቶች ጥንዶች ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ በቀጣዩ የህይወት ምዕራፍቸው የሚጠብቁት ነገር ልጅ መውለድ ነው። አንድ ሴት ምንም የመውለድ ችግር ሳይኖርባት እና የወሊድ መከላከያ ሳትጠቀም በአንድ ወር ውስጥ የማርገዝ እድሏ 20% ሲሆን 6 ወር ውስጥ 60% እንዲሁም በ1 ዓመት 85% ነው። ለሁለት አመት ቢሞክሩ ደግሞ 95% የማርገዝ እድል አላቸው። 15% የሚሆኑ ጥንዶት በአንድ አመት ውስጥ ምንም አይነት የወሊድ መከላከያ ሳይጠቀሙ ቋሚ የግብረስጋ ግንኙነት እያደረጉ የማርገዝ ችግር ያጋጥማቸዋል። ይህም መካንነት ወይም ያለመውለድ ችግር አጋጥሟቸዋል ተብሎ ህክምና ይጀመርላቸዋል። የሴቷ እድሜ ከ35 አመት በላይ ከሆነ ለ6ወር ሙከራ አድርጋ እርግዝና ካልተፈጠረ የመካንነት ህክምና መጀመር አለባት። መውለድ ያለመቻል እጅግ በርካታ ምክንያቶች ሲኖሩት አንዳንዶቹ ወደ 20% የሚሆኑት ይህ ነው የሚባል ምክንያት የላቸውም። ያለመውለድ ችግር (መካንነት) ዋናዋናዎቹ ምክንያቶች እነሆ 1. ከወንድ በኩል የሚኖር መካንነት (male factor infertility) እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ መሰረት 20% የሚሆነው ያለመውለድ ችግር (መካንነት) ከወንድ በኩል የሚኖር ነው።ይህም በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርምሞን ማነስ, በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ሰፐርም የማምረት ችግር (primary testicular defect in spermatogenesis), የወንድ የዘር ትቦ መዘጋት, እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት (idiopathic male infertility) ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ከ70-80% የሚሆነው በወንዶች በኩል የሚያጋጥም መካንነት በዘር ፍሬ (testes) በተለያዩ ምክንያቶች ዘር ያለማምረት ችግር የሚመጣ ነው። ይህም በዘር (genetics) ፣ በኢንፌክሽን ፣ በአደጋ፣ ጨረር መጋለጥ፣ ለሙቀት መጋለጥ እንዲሁም የሆርሞን ማነስ ምክንያት ሊሆን ይችላል። 2. በሴቶች ላይ እንቁላል የመለቀቅ ችግር (ovulatory dysfunction) 25% የሚሆነው ያለመውለድ ችግር (መካንነት) ምክንያት የእንቁላል ያለመለቀቅ ችግር ነው። አንዲት ሴት ስትወለድ ከ1-2 ሚሊየን የሚጠጉ እንቁላሎች በኦቫሪ ውስጥ ይኖራሉ። አነዚህ እንቁላሎች እድሜዋ አየጨመረ ሲሄድ እየቀነሱ ይመጣሉ። እርግዝና እንዲፈጠር እንቁላል ከኦቫሪ ወደ ማህፀን ግድግዳ መለቀቅ አለበት ይህ የመለቀቅ ሂደት በተለያየ ሆርሞኖች ቁጥጥር ስር የወደቁ ናቸው። የእነዚህ ሆርሞኖች መዛባት እንቁላል እንዳይለቀቅ ሊያደርጉ ይችላሉ። PCOS ፣ ከአንጎል የሚመነጭ ሆርሞን ማነስ፣የፕሮላክቲን መብዛት ፣ የታይሮይድ ሆርሞን ማነስ/መብዛት እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ። 3. የማህፀን ቱቦ መዘጋት በግራና በቀኝ በኩል የሚገኙ እንቁላል አስተላላፊ ትቦዎች በተለያየ ምክንያት ሊዘጉ ይችላሉ። በሰርጀሪ፣ በኢንፌክሽን፣ ከማህፀን ውጭ በሚያጋጥም እርግዝና እንዲሁም በሆድ እቃ ውስጥ በሚያጋጥም ጠባሳና መጣበቅ ሊዘጋ ይችላል። 4. በማህፀን ግድግዳ ላይ የሚያድግ እጢ በማህፀን ግድግዳ ላይ የሚፈጠር እጢ እንቁላልና ስፐርም ሴል እንዳይገናኙ እንዲሁም እርግዝና ከተፈጠረ በኋላም ምቹ ሁኔታ እንዳይኖር ሊያደርጉ ይችላሉ። 5. የማህፀን አፈጣጠር ችግር በተፈጥሮ ለሁለት የተከፈለ ማህፀን (septated uterus) ተደጋጋሚ ውርጃ እንዲኖር እንዲሁም ምንም ማህፀን ያለመፈጠር ችግር የመካንነት ችግር ሊያመጡ ይችላሉ። 6. ኢንዶሜትሪዮሲስ (endometriosis) ጠባሳና መጣበቅን በመፍጠር የማህፀን ትቦ እንዲዘጋ እንዲሁም በኦቫሪ ውስጥ እጢ (endometrioma) በመፈጠር የእንቁላል ማምረት ሂደትን በማወክ መካንነትን ሊያመጣ ይችላል። 7. የዘረ መል (chromosome) ችግር Turner syndrome, down syndrome, Kallman syndrome, የተባሉ የዘረመል ችግሮች ያለመውለድ ችግር ያመጣሉ። 8. ምክንያቱ የማይታወቅ (unexplained infertility) ብዙ ምርመራዎች ተደርገውም ምንም ምክንያት ላይገኝ ይችላል።ይህም 20% የሚሆኑት ያለመውለድ ችግር ያለባቸው ጥንዶች ላይ ያጋጥማል። 9. የግብረ ስጋ ግንኙነት አደራረግ ችግር እርግዝና እንዲፈጠር እርግዝና የሚፈጠርበትን የወር አበባ ኡደት ጊዜ ጠብቆ የማድረግ ችግር፣ ማለስለሻ ጄሎችን መጠቀም ያለማርገዝ እድልን ይጨምራሉ። እንቁላል የሚለቀቅበትን ወቅት ጠብቆ (Fertile period) ተደጋጋሚ ግንኙነት ማድረግ የማርገዝ እድልን ይጨምራል። 10. እድሜና የአኗኗር ሁኔታ የሴቶች እድሜ ሲጨምር የእንቁላል መጠን እየቀነሰ ይሄዳል። በተጨማሪም ሲጋራ ማጨስ ፣ ለተለያዪ ኬሚካሎች መጋለጥ፣ ለጨረር መጋለጥ፣ የክብደት መጨመር፣ ጭንቀት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል መውሰድ ለመካንነት ያጋልጣል። ዶ/ር በላይ አለሙ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት @HakimEthio

Hakim
60 567
"ልጄ ቀኝ እና ግራ እግሩ እኩል አደሉም ወይም ሲራመድ ይስበዋል ምን ሊሆን ይችላል?" ይህ ከአንድ ወላጅ የተጠየቅኩት ጥያቄ ነው:: መራመድ በጀመሩ ህፃናት የእግር ቁመት እኩል አለመሆን ወይም አንዱ
+3
"ልጄ ቀኝ እና ግራ እግሩ እኩል አደሉም ወይም ሲራመድ ይስበዋል ምን ሊሆን ይችላል?" ይህ ከአንድ ወላጅ የተጠየቅኩት ጥያቄ ነው::  መራመድ በጀመሩ ህፃናት የእግር ቁመት እኩል አለመሆን ወይም አንዱ መሰለል ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩትም አንደኛው ከነርቭ መወጠር ጋ የተገናኘ ነው::     በእግር ላይ ያለው ምልክት ቆይቶ ከወራት ወይም ዓመታት በሁአላ ቢሆንም የሚታየው ችግሩ ግን የሚከሰተው ቀድሞ ነው:: በአብዛኛው በተፈጥሮ ነው የሚከሰተው:: ቀድሞ ማወቅም ይቻላል::    በተፈጥሮ የሚከሰት የህብለሰረሰር መወጠር (Tethered cord) ወደ እግር የሚሄድ የነርቭ መልክት መዛባት ስለሚያመጣ አንደኛው እግር ከሌላኛው እኩል አያድግም:: ልጁም እግሩን በነፃነት ማዘዝ እየከበደው ይመጣል:: ይሄንንም ለማካካስ ሲል በተርከዝ መርገጥ ትቶ በ ግር ጣቶች ብቻ ለመርገጥ ይሞክራል:: እግሩም እየተወጠረ መሄድ ስለሚከብደዉ እየሳበው ይሄዳል::    ከዚህ ባለፈ የነርቭ መልክት መተላለፍ መዛባት ወደ ሽንት ፊኛ ሲደርስ ሽንት መቆጣጠር አለመቻል ይሄም በልጆች ቀኑን ሙሉ ዳይፐር አንደረጠበ መቆየት ይኖራል:: ሽንት በፊኛ እየተጠራቀመ ሲመጣ ወደ ኩላሊት እየተመለሰ ኩላሊት ዉስጥ መጠራቀም እና ተደጋጋሚ የኩላሊት እንፈክሽን ያመጣል አለፍ ሲልም ኩላሊት ስራ ሊያቆም ይችላል::   ወደ ታችኛው የአንጀት ክፍል የሚሄድ የነርቭ መልክት መዛባት ደግሞ ድርቀት ያመጣባቸዋል:: ይህ መወጠር ከአርከካሪ ጎን ያሉ ጡንቻዎችን በማዛባት የአከርካሪ መጣመም ሁሉ ያመጣል::    እንዴት ማወቅ ይቻላል? ችግሩ ከዉስጥ ቢሆንም ከቆዳ ላይ የሚያሳየው ምልክት አለ:: ለምሳሌ ከጀርባ ላይ ያለ አንድ ቦታ ችምችም ያለ ፀጉር: መሃል ወገብ ላይ ያበጠ ወይም የተከማች ስብ: መሃል ወገብ ላይ ያለ Dimple (መሰርጎድ) : የአከርካሪ መጣመም እና የመሳሰሉት:: ሕክምና አለው? አዎ መታከም ይችላል:: ነገር ግን ሕክምናው ህመሙ እንደታወቀበት ጊዜ ይወሰናል:: ተጨማሪ የMRI ምርመራ ያስፈልጋል:: በዋነኘት የተወጠርዉን ህብለሰረሰር በማላቀቅ ያንን ተከትሎ የሚመጣዉን መዘዝ መቀነስ ነው:: አንዴ የደርሰዉን ጉዳት መመለስ ግን እጅግ አዳጋች ነው:: ለእያናዳንዱ ታካሚ የራሱ የህክምና እና የክትትል plan ያስፈልጋል:: ሁሉም አንድ አይነት ስላልሆነ:: References 1. Guggisberg, D., et al. (2004). Skin markers of occult spinal dysraphism in children: a review of 54 cases. Child's Nervous System 2. International Survey on the Management of Skin Stigmata and Suspected Tethered Cord. Child's Nervous System, Vol. 26 3. Kulkarni, A. V., et al. (2017). Evaluation and management of tethered cord syndrome in occult spinal dysraphism. Child's Nervous System. ቸር ያሰማን! ዶ/ር ሱራፌል መኮንን: ረዳት ፕሮፌሰር የህፃናት አንጎል ህብለሰረሰር ነርቭ ቀዶ ጥገና ሰብ ስፔሺያሊስት @HakimEthio

Hakim
60 567
በዘመናዊው Mindray Resona i9 አልትራሳውንድ ማሽን የጉበት ስብ ክምችት እና የጉበት ጠባሳ ደረጃ ለማወቅ የኢላስቶግራፊ ምርመራ እናደርጋለን፡፡ ተክለሃይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል ከልብ በመነጨ
በዘመናዊው Mindray Resona i9  አልትራሳውንድ ማሽን  የጉበት ስብ ክምችት እና የጉበት ጠባሳ ደረጃ ለማወቅ የኢላስቶግራፊ ምርመራ እናደርጋለን፡፡ ተክለሃይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል ከልብ በመነጨ እንክብካቤ ወደ ላቀ ምዕራፍ! With advanced Mindray Resona i9 ultrasound machine, we perform liver fat accumulation and liver fibrosis stages examination. Teklehaimanot General Hospital Healing with Heart to Tertiary Excellence!

Hakim
60 567
አንዲት ነፍሰጡር እናት የቅድመ-ወሊድ ቫይታሚኖችን (Prenatal Vitamins) እንዴት መውሰድ አለባት? 1. የቅድመ-ወሊድ ቫይታሚን መቼ መጀመር አለበት? 👍ከእርግዝና በፊት፦ የተሻለው ጊዜ እር
+3
አንዲት ነፍሰጡር እናት የቅድመ-ወሊድ ቫይታሚኖችን (Prenatal Vitamins) እንዴት መውሰድ አለባት? 1. የቅድመ-ወሊድ ቫይታሚን መቼ መጀመር አለበት? 👍ከእርግዝና በፊት፦ የተሻለው ጊዜ እርግዝና ከመከሰቱ ከ2 እስከ 3 ወራት በፊት መጀመር ነው። ይህም በፅንሱ ላይ የሚከሰቱ የነርቭ እና የአከርካሪ አጥንት ችግሮችን (Neural tube defects) ለመከላከል ይረዳል። 👍 እርግዝና እንደታወቀ፦ አስቀድመው ካልጀመሩ፣ እርግዝና መኖሩን ካወቁበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ መውሰድ መጀመር አለብዎት። 👍 በእርግዝና ወቅት ሁሉ፦ ቫይታሚኖቹን በእርግዝና ዘመን ሁሉ እስከ መውለጃ ቀን ድረስ መቀጠል ያስፈልጋል። 2. ምን ዓይነት ቅድመ-ወሊድ ቫይታሚን(prenatal) መውሰድ አለባት? ( የምትወስጂውን prenatal ጀርባውን ተመልከቺ) 💊Folic Acid ፦ በቀን 400 mcg 💊 Iron ፦ 27 mg :- ለደም ማነስ መከላከያ እና ለፅንሱ እድገት 💊 Calcium 1000-1300mg , Vitamin D 600IU(15mcg) ፦ ለፅንሱ አጥንት እና ጥርስ ጥንካሬ። 💊 Iodine ፦ 150mcg - ለፅንሱ የአንጎል እድገት 💊 Omega 3 DHA - 200-300mcg - ለፅንሱ የአንጎል እድገት 3. Prenatal እንዴት መውሰድ ይገባል? 👉 በየቀኑ፦ እስከ ወሊድ ድረስ 👉 ከምግብ ጋር፦ ሆድ ላይ መጠነኛ መረበሽ እንዳያመጣ 👉 ከበቂ ውሃ ጋር 4. ቀላል የጎንዮሽ ጉዳቶች ሲያጋጥሙ ምን ማድረግ አለብን? 🫴 የማቅለሽለሽ ስሜት ቫይታሚኑን ማታ ከመተኛት በፊት መውሰድ ወይም ከቀላል ምግብ ጋር መውሰድ ማቅለሽለሽን ይቀንሳል 🫴 የሆድ ድርቀት ብዙ ውሃ መጠጣት፣ ፋይበር ያላቸውን ምግቦች (አትክልትና ፍራፍሬ) ማዘውተር እና መጠነኛ እንቅስቃሴ ማድረግ። 🫴 የቫይታሚኑን አይነት መቀየር 🫴 የሚወሰድበትን ሰዓት መቀየር ዶ/ር ዳዊት መስፍን: የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት www.tiktok.com/@drdaveobgyn @HakimEthio

Hakim
60 567
የጨቅላ ህፃናት ቢጫ መሆን + የካካ መንጣት ‼️ የጨቅላ ህፃናት አይን እና ገላ ቢጫ መሆን በተለያየ ከቀላል እስከ ከባድ የጤና እክል ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል። ነገር ግን በዋነኝነት አሳሳቢ የሚሆ
+3
የጨቅላ ህፃናት ቢጫ መሆን + የካካ መንጣት ‼️ የጨቅላ ህፃናት አይን እና ገላ ቢጫ መሆን በተለያየ ከቀላል እስከ ከባድ የጤና እክል ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል። ነገር ግን በዋነኝነት አሳሳቢ የሚሆነው 👉 በተወለዱ 24ሰአት ውስጥ ከተከሰተ 👉 ቢጫነቱ ከ 2 ሳምንት በላይ ከቆየ 👉 ቢጫነቱ ከጭንቅላት ጀምሮ ወደታች ከእንብርት አልፎ ከሄደ 👉 የካካ ነጭ መሆን ወይም የሽንት መጥቆር ካለ 👉 ተያይዞ ማስመለስ ፣ የክብደት አለመጨመር ፣ የእንቅልፍ መዛባት እና የመሳሰሉት የህመም ምልክቶች ካሉ ነው። ስለዚህ እነዚህን ምልክቶች ካስተዋሉ በጊዜ የልጅዎን ሀኪም ማማከር እና የደም ምርመራ እንዲሁም እንዳስፈላጊነቱ የሆድ አልትራሳውንድ ምርመራ በማስመርመር መንስኤው ምን እንደሆነ መለየት እና ተገቢውን ህክምና ህፃኑ እንዲያገኝ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህን ርዕስ ያነሳውበት ምክንያት አንዳንድ ጊዜ ከአፈጣጠር ጋር በተያያዘ ከጉበት ወደ ትንሹ አንጀት ክፍል የሀሞት ፈሳሽን የሚያስተልፈው ቱቦ መዘጋት ወይም አለመኖር ሊከሰት ይችላል። በዋነኝነት የሚታየው ምልክት የአይን እና ገላ ቢጫ መሆን እና ከዚሁ ጋር በተያያዘ በምስሉ ዳይፐሩ ላይ እንደሚታየው የካካ ቀለሙ ነጣ ማለት ነው። ይህ የጤና እክል ደግሞ በመጀመሪያ 3 ወር እድሜያቸው በጊዜ ታውቆ በቀዶ ህክምና ተፈጥሮአዊ ችግሩ ካልታከመ ጉበትን በጊዜ ሂደት በመጉዳት ከጥቅም ውጪ ያደርጋል። ይህ ሁኔታ ከተከሰተ ደግሞ በጉበት ንቅለ ተከላ ቀዶ ህክምና ካልታከመ የህፃኑን ህይወት በአሳዛኝ ሁኔታ ይቀጥፋል። ስለዚህ ወላጆት በተለምዶ አባባል የጨቅላ ህፃናት ቢጫ መሆን በፀሀይ መሞቅ ብቻ በጊዜ ሂደት በራሱ ይጠፋል ብላችሁ እንዳትዘናጉ እና ጥንቃቄ እንዳታደርጉ እንዲሁም ተያይዞ የጠቀስኳቸውን ምልክቶች ካስተዋላቹ በጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ልጃችሁን ማስመርመር ያስፈልጋቹሀል። ማጣቀሻ 1. Coran Pediatric Surgery 7th Edition 2. American pediatric surgical Association Guideline ዶ/ር ዮናታን ከተማ: በቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናት ቀዶ ህክምና ሬዚደንት ሀኪም ሰላምና ጤና በያላችሁበት ይሁን! ለበለጠ ማብራሪያ 👇👇👇 መጎብኘት ይችላሉ። YouTube - https://youtube.com/@kedmialetenawo?si=4k6s0RROG_lVCA3u @HakimEthio