en
Feedback
EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Channel EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 29 482 subscribers, ranking 2 404 in the Religion & Spirituality category and 1 150 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 29 482 subscribers.

According to the latest data from 28 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -13 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 7.78%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.48% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 293 views. Within the first day, a publication typically gains 1 615 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 4.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

29 482
Subscribers
No data24 hours
-97 days
-1330 days
Posts Archive
ቁልቢ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም መጠናቀቁኔ በማስመልከት የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ወቅታዊ መግለጫ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ወርቅነህ የዘንድሮው ሐምሌ 19 በቁልቢ የተከበረው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በድሬዳዋ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በሰላም፣ በፍቅርና በታላቅ ስኬት መከበርና መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። ለዚህም በዓል ከተለያዩ የዓለም ሀገራትና ከኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢዎች የመጡ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶች በየብስ ትራንስፖርት፣ በባቡር፣ እንዲሁም በአየር መንገድ ወደ ድሬዳዋ ከተማ መግባታቸውን ገልጸዋል። አስተዳደሩ ይህንን ግዙፍ ሕዝባዊ ፍሰት ለማስተናገድ ካለው ከፍተኛ ዝግጁነት የተነሳ፣ ከተማዋ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የእንግዳ ተቀባይነት እሴት አስተናግዳ የፍቅርና የአብሮነት ማዕከልነቷን ዳግም አስመስክራለች ብለዋል። በዓሉ በዓመት ሁለት ጊዜ በታኅሣሥ እና በሐምሌ ወራት የሚከበር ታላቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴት መሆኑን ያብራሩት አቶ ብሩክ፣ ይህ ታላቅ ሁነት በየዓመቱ የሕዝቦችን ትስስርና አንድነት ይበልጥ የሚያጠናክር መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። የቢሮ ኃላፊው አቶ ብሩክ ወርቅነህ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፣ ድሬዳዋ ዘንድሮም እንደ ወትሮው ሁሉ የመጡትን በርካታ እንግዶች የከተማዋን የቆየና ድንቅ የእንግዳ ተቀባይነት ስም በሚመጥን መልኩ በሰላም፣ በፍቅርና በአብሮነት ስሜት ተቀብላ አስተናግዳለች። ከተማዋ በቀንም ሆነ በምሽት ሙሉ በሙሉ አስተማማኝ ሰላም የነበራት ከመሆኑም በላይ፣ ንቁና ደማቅ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ እንቅስቃሴ የታየባት መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ ይህም እንግዶች ያለምንም የጸጥታ ስጋትና በሙሉ ነፃነት እንዲንቀሳቀሱ አስችሏል ሲሉ ተናግረዋል። አስተዳደሩ የበዓሉን ታላቅነትና ስልታዊ ጠቀሜታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ከድሬዳዋ መግቢያ፣ ከገነት መናፈሻ እንዲሁም ከድሬዳዋ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ እንግዶችን በከፍተኛ የአመራር አካላት አማካኝነት በክብርና በደመቀ ሁኔታ መቀበሉን አቶ ብሩክ ገልጸው፣ ምዕመናንና ጎብኚዎች በቆይታቸው በሄዱበት የልማትና የአገልግሎት ተቋማት ሁሉ የድሬዳዋን እውነተኛ የሕዝቦች መተሳሰብ መንፈስ በተግባር እንዲያዩና ደረጃውን የጠበቀ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉንም አብራርተዋል። በተለየ መልኩ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የተመራውን የከፍተኛ የቤተክርስቲያኗ አባቶች ልዑካን ቡድን ከአውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ ደማቅና የመንግስትን ታላቅ አክብሮት የገለጸ የክብር አቀባበል ማድረጋቸውን አቶ ብሩክ በመግለጫቸው አስታውቀዋል። ይህንን የከፍተኛ አባቶች ቡድን በታላቅ ፍቅርና ድንቅ መስተንግዶ ያስተናገደው የድሬዳዋ አስተዳደር፣ በዓሉ ተጠናቆ እስኪመለሱ ድረስ ተገቢውን የክብር አሸኛኘት ማድረጉን ኃላፊው ገልጸዋል። በአጠቃላይ ድሬዳዋ ለዚህ ታላቅ በዓል መሳካት፣ ለሕዝብ ደህንነትና ጸጥታ ጥበቃ፣ ለአምልኮ ሥነ-ሥርዓቶች መቃናት እንዲሁም ለሕዝቦች ትስስርና አንድነት ያበረከተችው ዘርፈ ብዙ አስተዋፅዖ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አቶ ብሩክ ገልፀዋል። አስተዳደሩ ያሳየው የተቀናጀ፣ ሙያዊ እና ስኬታማ ሥራ ከተማዋን እጅግ የሚያስመሰግንና በቀጣይም መሰል ግዙፍ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን የመቀበልና የማስተናገድ ከፍተኛ አቅምና ዝግጁነት እንዳላት በግልጽ ያሳየ መሆኑን አቶ ብሩክ ወርቅነህ በጽኑ አምነውበታል። በመጨረሻም አቶ ብሩክ የዘንድሮው በዓል በሰላም፣ በፍቅር እና በታላቅ አብሮነት በስኬት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቀንና ሌሊት ለደከሙ ለመላው የፀጥታ አካላት፣ ለትራንስፖርትና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲሁም በአጠቃላይ ለድሬዳዋ ነዋሪዎች ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፆ በታላቅ አክብሮት ምስጋናቸውን አቅረበዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ !

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል (ሐምሌ ፳፪) ቀን በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ !!!
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል (ሐምሌ ፳፪) ቀን በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ !!!

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሃያኛው ምዕት ዓመት ሰማዕት ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሲሉ ሰማዕት የሆኑበት ዕለት ነው፡፡ ዘ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሃያኛው ምዕት ዓመት ሰማዕት   ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሲሉ ሰማዕት የሆኑበት ዕለት ነው፡፡ ዘንድሮ በ፳፻፲፰ ዓ.ም የሰማዕቱን  ዘጠናኛ ዓመት እናዘክራለን፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሷ ልጆች አምስት ኢትዮጵያውያን መነኮሳት እስክንድርያ (ግብጽ) ድረስ ልካ በ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. ከተሾሙት አምስት  ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት አንዱ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው፡፡

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ስምከ ሕያው ዘኢይመውት “ሰው የተመኘውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው” የሚሉት ታላቁን የቤተክርስቲያን አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ.ም ዐረ
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ስምከ ሕያው ዘኢይመውት “ሰው የተመኘውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው” የሚሉት ታላቁን የቤተክርስቲያን አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ.ም ዐረፉ፡፡ ዘንድሮ ፳፻፲፰ ዓ.ም ፴፮ኛ ዓመታቸውን እናዘክራለን፡፡ጥቂት ስለ ብፁዕነታቸው

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ

ቅዱስ ፓትርያርኩ ገዳማት ከአደጋ ሊጠበቁ እንደሚገባ አሳሰቡ

ቅዱስ ፓትርያርኩ የእንግሊዝ አምባሳደርና በአፍሪካ ኅብረት የቋሚ መልእክተኛን አነጋገሩ

ከተለያዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች ጋር በመተባበር ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችም እየተሰጡ ሲሆን በብፁዕ አባታችን መልካም ፈቃድና በመንበረ ፓትርያርክ በኩል በተደረገው ውሳኔ መሠረት፣ ከሰላሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የገንዘብ ድጋፍ ተመድቦ ከከተማው መግቢያ አንሥቶ እስከ ገዳሙ ድረስ የመንገድ መብራት መስመር በመዘርጋት የገዳሙ ዙሪያና የአካባቢው ማኅበረሰብ የመንገድ መብራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ። የዕድሳት ሥራው ተጠናቆ ሐምሌ አሥራ ሥድስት ቀን በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ አገልግሎት መጀመሩ የተገለጸ ሲሆን ገዳሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከማኅበረሰቡ ዕድገት ጋር ተያያዥነት ያላቸው መሠራት ያለባቸው በርካታ ቀሪ ሥራዎች ስላሉበት የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆችና ባለሟሎች ቀጣይ ትብብራቸውና ድጋፋቸው እንዳይለይ አስተዳዳሪው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የልማት ትሩፋቶች #የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆች ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ ከዘጠነኛ ክፍል እስከ አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንዲሁም ለከፍተኛ ትምህርት ዝግጅት የሚሆን ተጨማሪ የትምህርት ሕንጻ ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል ። #ለሃያ ሰባት የገጠርና የከተማ ማኅበረሰብ ክፍሎች የሚጠቅም የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ተዘርግቶ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል ። #ከሰላሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የገንዘብ ድጋፍ ተመድቦ ከከተማው መግቢያ አንሥቶ እስከ ገዳሙ ድረስ የመንገድ መብራት መስመር በመዘርጋት የገዳሙ ዙሪያና የአካባቢው ማኅበረሰብ የመንገድ መብራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ። ዘጋቢ፦ መምህር ፍቃዱ ኪሮስ (#EOTCTV ሐምሌ ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኘው ታዋቂውና ጥንታዊው የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓመታዊ የንግሥ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቤተ ክርስቲያን የሥራ ኃላፊዎችና እጅግ ቁጥራቸው የበዛ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበሯል ። ይህ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም በየዓመቱ የሐምሌ አሥራ ዘጠኝ ቀንን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት እንደሚያከብር የሚታወቅ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት ግን በዓሉን ልዩ የሚያደርገው ለብዙ ጊዜያት ሲጠበቅ የነበረውና በከፍተኛ የገንዘብና የሰው ኃይል ጉልበት የተከናወነው የቤተ ክርስቲያኑ ዕድሳት ሥራ ተጠናቆ ለምርቃት መብቃቱ ነው ። በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችና ከውጭ አገራት ጭምር የመጡ የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆችና ምዕመናን በቅጽረ ገዳሙ ተገኝተው የበዓለ ንግሡ ተሳታፊ ሆነዋል ። በዚህ ደማቅና ታሪካዊ የንግሥ በዓል መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣ የምሥራቅ ሐረርጌ፣ የምሥራቅ ወለጋ እና የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ የሥራ ኃላፊዎች፣ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ቀሲስ ንጋቱ ደሳለኝ፣ የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ሰላማ፣ የገዳሙ ሊቃውንት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና በርካታ ምዕመናን በበዓለ ንግሡ ላይ ተገኝተዋል ። በበዓሉ መክፈቻ ላይ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የቤተ ክርስቲያኑ ዕድሳት ሥራ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ ለዛሬው የንግሥ በዓል ለመብቃት ሌሊትና ቀን ለሃያ አራት ሰዓታት ያህል በትጋት፣ ጥረትና ሥራ ሲሠራ መቆየቱን በሰፊው አብራርተዋል ። ይህ የተከናወነው ታላቅ ሥራ በጥቂት ወራት ብቻ የተገደበ ሳይሆን ለአንድ ሙሉ ዓመት ያህል የተሠራ ያህል ከባድና በትጋት የተሞላበት መሆኑን በመግለጽ ለሥራው ስኬት ድጋፍ ላደረጉት ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ሰላማ ባቀረቡት ሰፊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ «ጊዜ ዝንቱ ለእግዚአብሔር» የሚለውን የነቢዩ ዳዊት ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ የገዳሙን ታሪካዊ አመጣጥና ያጋጠሙትን ፈተናዎች ዘርዝረዋል ። ይህ ታላቅ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው ገዳም በጥንታዊነቱ በሺህ ዘጠኝ መቶ አምሳ ሰባት ዓመተ ምሕረት በግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴና በወቅቱ በነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አባታዊ አመራር የተገነባ ቢሆንም በጊዜ ብዛትና በተገቢው ወቅት ዕድሳት ባለማግኘቱ ምክንያት በሕንጻውና በዙሪያው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰበት መምጣቱን አስረድተዋል ። ቀደም ሲል የነበሩት የገዳሙ አስተዳደሮች የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ዕድሳት እንዲደረግለት ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ የቆዩ ቢሆንም መፍትሔው በመዘግየቱ ምክንያት ችግሩ እየከበደ በመምጣቱ ጉዳዩ እንደገና ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትና ለቅዱስ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ ተደርጓል በለዋል ። በሪፖርታው መሠረትም የቅዱስ ሲኖዶስ ርዕሰ መንበር በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ መመሪያ ሰጪነት ቅዱስ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት በመገንዘብ በአስቸኳይ የዕድሳት ሥራው እንዲጀመር አስፈላጊውን በጀት ፈቅዷል ፤ በመቀጠልም በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅ የቅርብ ክትትልና መመሪያ ከፍተኛ ዕውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ሥራውን እንዲያከናውኑ በግልጽ ጨረታ ፋሲል ጊዮርጊስ አማካሪ ድርጅት ከተቀጠረ በኋላ በቀረበው የመጨረሻ ጥናት መሠረት አዶር ኢንጂነሪንግ የተባለው ድርጅት ጨረታውን አሸንፎ በሁለት ሺህ አሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት የዕድሳት ሥራውን እንዲጀምር ተደርጓል ። ሥራው ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ምርቃቱ ዕለት ድረስ የብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅና የብፁዕ ዋና ጸሐፊ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ሳይለየው ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ተከናውኖ ዛሬ ለምርቃት መብቃቱን አብስረዋል ። የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ሰላማ በሪፖርታቸው ማጠቃለያ ላይ ለበጎ ሥራው መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን አካላት በሙሉ አመስግነዋል ። በዚህም መሠረት በጸሎታቸው፣ በምክራቸውና በአባታዊ አመራራቸው ከጎናቸው ላልተለዩት ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ለዚህ ዓለም አቀፋዊ ፕሮጀክት ልዩ ትኩረትና የቅርብ ክትትል ላደረጉት ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ከሥራው መጀመሪያ አንሥቶ ሂደቱን በመጎብኘትና በማበረታታት ትልቅ ድጋፍ ላደረጉት ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ እንዲሁም በየጊዜእየተገኙ በመምከርና በማበረታታት ትጋታቸውን ላሳዩት ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል ። በተጨማሪም ፣ ሥራው እንዲሳካ ቀንና ሌሊት ለደከሙ ሠራተኞች፣ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚገኙ ረዳቶች፣ አባቶች፣ ልዩ ልዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች በሙሉ በቅዱስ ገብርኤል ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። በገዳሙ በኩል የተከናወኑትን ዘርፈ-ብዙ ልማታዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች በተመለከተ አስተዳዳሪው በሰፊው አብራርተዋል ። በመጀመሪያ ደረጃ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል የሚደርስ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ተገንብቶ የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆች ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ ከዘጠነኛ ክፍል እስከ አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንዲሁም ለከፍተኛ ትምህርት ዝግጅት የሚሆን ተጨማሪ የትምህርት ሕንጻ ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል ። በሌላ በኩል ደግሞ ለሃያ ሰባት የገጠርና የከተማ ማኅበረሰብ ክፍሎች የሚጠቅም የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ተዘርግቶ አገልግሎት እንዲሰጥ የተደረገ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ የሕዝብ መገልገያዎች ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ።