en
Feedback
EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Channel EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 29 504 subscribers, ranking 2 370 in the Religion & Spirituality category and 1 165 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 29 504 subscribers.

According to the latest data from 26 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 20 over the last 30 days and by -17 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.40%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.97% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 068 views. Within the first day, a publication typically gains 1 760 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 27 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

29 504
Subscribers
-1724 hours
-537 days
+2030 days
Posts Archive
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የአመራሮች ምርጫ ​የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የአዲስ አመራሮች ምርጫ ያካሄደ ሲሆን፣ አገልግሎታቸውን ላጠናቀቁ ነባር አመራሮችም የሽኝትና የዕውቅና መርሐ ግብር አከናወነ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የአመራሮች ምርጫ ​የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የአዲስ አመራሮች ምርጫ ያካሄደ ሲሆን፣ አገልግሎታቸውን ላጠናቀቁ ነባር አመራሮችም የሽኝትና የዕውቅና መርሐ ግብር አከናወነ።

የአየር ጤና ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል  የልማት ሥራዎች ​​የአየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል አስተዳደር፣ የልማትና የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎች፣ ለምእመናን የጤናና የትምህርት ማዕከልነት የሚያገለግሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎችን በመሥራት ላይ እንደሚገኙ ገለጹ።

የሲኤምሲ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ግቢ የማስዋብ ሥራ ​የሲኤምሲ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ግቢ የማስዋብ ሥራ በመጪው መስከረም ወር እንደሚጀመር የካቴድራሉ አስተዳዳሪ መላእከ መንክራት ኃይሌ አብርሃ ገለጹ ።

ሁለት መቶ ደቀ መዛሙርት በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተመረቁ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ መንፈሳዊ ማኅበር ድጋፍ  የሰለጠኑ ሁለት መቶ የዋልዳ ሥላሴ መንፈሳዊ ማኅበር ደቀ መዛሙርት ተመረቁ፡፡

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ደማቅ የአቀባበል ተደረገ ​የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆን የተመደቡት መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ እና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆን ለተመደቡት ለመልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ በደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ። ዘጋቢ መ/ር መዝገቡ ጌታቸው (#EOTCTV ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆን ለተመደቡት ለመልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቀባበል ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ ኮንታ ከንባታና አላባ ጠንባሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት መምሪያ ኃላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ልዩ ልዩ ክፍል ኃላፊዎችና ሠራተኞች የክፍላተ ከተማ ኃላፊዎችና ልዩ ልዩ ሠራተኞች የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችና አገልጋዮች በተገኙበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል ። መርሐ ግብሩ በጸሎተ ወንጌል ተጀመረ ሲሆን ለሥራ አስኪያጁ የሥራ ዘመን መመሪያ ይሆን ዘንድ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 20 ከቁጥር 26 ጀምሮ ተነቦ ለመርሐ ግብሩ ተስማሚ የሆነ ወረብ በቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ሊቃውንት መዘምራን ቀርቧል ። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ የሢመት ደብዴቤ ከተነበበ በኋላ የሀገረ ስብከቱ ክፍል ኃላፊዎች እና የክፍላተ ከተማ ቤተክህነት ሊቃነ ካህናት በጉባኤው ፊት ቀርበው ትውውቅ ተደርጓል ። በሊቃውንትም ቅኔ ተበርክቷል ። የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ስብከተ ወንጌልን ሰበካ ጉባኤን ሰንበት ትምህርት ቤትን በማደራጀትና በማስፋፋት ፣ ቤተክርስቲያንን ጠብቆ በማስጠበቅ ሁለንተናዊ ልማትን እንዲያጠናክሩ ፣ ሕገ ቤተክርስቲያንን ጠብቀው የመልካም አስተዳደር ችግርና ሙስናን እንዲቀርፉ ኃላፊነት ተሰጥቶአቸዋል። ክቡር ሊቀ ሊቃውንት ቆሞስ አባ ተ/ሃይማኖት ወልዱ ሰለ ሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ያላቸውን የሥራ ክህሎት በመግለጽ ቤተ ክርስቲያንን አብረን እናሻግራት ማሻገር ባንችል ባለቤት ሆኖ የመሠረታት ክርስቶስ ያሻግራታል እኛ ሰጥመን እንዳንቀር ሲሉ ማስጠንቀቂያ አዘል ምክራቸውን ለግሰዋል። የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ተወካይ ክቡር መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በደብራችን ዘርፈ ብዙ ሰዋዊ እና የመሠረተ ልማት ተግባሮችን አከናውነዋል በማለት በዝርዝር አቅርበዋል። መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በታማኝነት እንደሚወጡ በሢመቱ ላይ የተነበበውን ዝርዝር መመሪያ በማንሳት አሁን ላይ ሀገረ ስብከቱን የተጋረጡበትን ተግዳሮቶች በጋራ እንቀርፋለን ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሮሜ 3፣ 11 በመጥቀስ ወንጌል የሰውን ልጅ በሀጢአቱ እንደምትከስ በመጥቀስ ከውድቀታችን በንስሐ ልንመለስ ይገባል ብለዋል። ብፁዕነታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥንታዊነትና ታሪካዊ መሆኗን በመጥቀስ " ተሿሚው ወንድምና ልጃችን ወደፊት በሚያከናውኗቸው ተግባራት ከብሔርና ከቡድን አሠራር ነጻ የሆነ መዋቅር ቤተክርስቲያንን ብቻ ማዕከል ያደረገ አድሏዊ ያልሆነና እውነተኛ የመንፈስ ቅዱስ ሀሳብን በአሠራር በመዘርጋት የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔና ልዕልና በማክበር የበላይ አካል መመሪያና ለሀገረ ስብከቱ የተሰጠውን ደንብ ጠብቀው በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር የፋይናንስና ንብረት አስተዳደሩን ግልጽ፣ ዘመናዊና ቁጥጥር የሚደረግበት በማድረግ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ፈጽመው እንደሚያጠፉ ትልቅ ተስፋና አደራ ጭምር ጥለንባቸዋል።" ብለዋል። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

ጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት የአንድነት ኑሮ ማኅበር ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 41ኛ ዙር ሰባኪያነ ወንጌልን፣ ዲያቆናትንና ሕጻናትን አስመረቀ። ዘጋቢ ፈለጉሽ አሻግሬ (#EOTCTV ነሐሴ18 ቀን 2018 ዓ.ም) ጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት የአንድነት ኑሮ ማኅበር ላለፉት አራት ወራት ሲያሰለጥናቸው የነበሩትን 86 ደቀመዛሙርት እና በክረምቱ 35 ልዩ ልዩ የቤተክርስቲያንን ትምህርት ያስማራቸውን ሕጻናትን ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በማኅበሩ አዳራሽ በድምቀት አስመርቋል። በዕለቱ የተገኙ የክብር እንግዶች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ፣ ኮንታ፣ አላባ፣ ጠንባሮ እና የከምባታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ፣ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተጨማሪም ጥሪ የተደረገላቸው ቀሳውስት እና ምእመናንን ተገኝተዋል። መምህር ሙሉጌታ ምትኩ በፕሮግራሙ ላይ በቀረቡት ሪፖርት ከተመራቂዎቹ መካከል ፤ ብፁዕ አቡነ ገሪማ በሀገራችን ገጠራማ አካባቢዎች 30 ደቀመዛሙርትን፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ደግሞ 28 ደቀመዛሙርትን መልምለው ለማኅበሩ ያስረከቧቸው ሰባኪያነ ወንጌል እንደሚገኙ ገልጸዋል ። ብፁዓን አባቶች በተገኙበት በዚህ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ማኅበሩ ሰባኪያነ ወንጌልን ሲያስመርቅ የዘንድሮው የ41ኛ ዙር ሲሆን፥ ባለፉት 28 ዓመታት በርካታ ወንጌላውያንን በማፍራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተገልጿል። ለእነዚህ ተመራቂዎች ሥልጠናና አጠቃላይ መርሐ-ግብር ማስፈጸሚያ የሚሆን 4.5 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል። ይህ የወጣው የገንዘብ መጠን የተሸፈነው ማህበሩ መለከት መጽሔትን ጨምሮ፣ ጽዮን የኦቾሎኒ ቅቤ እና ሌሎችን የገቢ ማስገኛ ስራዎች እየሠራ እና በማኅበሩ አባላት ቁጠባ በሚገኝ ገንዘብ እና በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በሚኖሩ በጎ አድራጊ ምዕመናን እንዲሁም ከተለያዩ አጋር ማኅበራት በተገኘ የገቢ ምንጭ መሆኑን መምህር ሙሉጌታ በቀረቡት ሪፖርት ገልጸዋል ። በደቀመዛሙርቱ፣ ዲያቆናቱ እና ሰባክያሰ ሥልጠና ከተመረቁት 86 ደቀመዛሙርት መካከል የቤተክርስቲያንን ሥርዓትና ዜማን ያጠኑ ዲያቆናት እንዲሁም የወንጌል ትምህርትን የተከታተሉ ሰባክያን ይገኙበታል። የሠልጣኞቹ ስብጥር ከተለያዩ 21 አህጉረ ስብከት እና ከጎረቤት አገር ኬንያም የተወጣጡ መሆናቸው ልዩ ያደርገዋል። ይህ ሥልጠና ወንጌልን ለሰው ልጅ ሁሉ ተደራሽ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ፥ ተመራቂዎቹ በሀገር በቀልና የውጭ ቋንቋዎችን የሚናገሩ ደቀመዛሙርት ወደ የመጡበት አካባቢ ሲመለሱ በማኅበረሰቡ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ወንጌልን ማስተማር የሚያስችላቸውን ጥልቅ ሥልጠና እንደወሰዱ ተገልጿል ። በተጨማሪም በክረምቱ ወራት ዕድሜያቸው ከ8 እስከ 10 ዓመት የሚሆናቸው 35 ሕጻናት፣ ላለፉት 45 ቀናት መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት፣ ሥነ-ምግባር እና የበገና ድርደራ ሥልጠና ሲከታተሉ ቆይተው በስኬት አጠናቀው በዕለቱ አብረው ተመርቀዋል። ሕጻናቱ የቀሰሙትን የበገና ድርደራና የዜማ ጥበብ ልብን በሚረሰርስ የበገና መዝሙር የቀረቡ ሲሆ ደቀመዛሙርቱም የተማሩትን ቃለ እግዚአብሔር በየቋንቋቸው ለታደሚው ወንጌልን አስተምረዋል ። በዚሁ በድምቀት በተከናወነው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ፣ ኮንታ፣ አላባ፣ ጠንባሮ እና የከምባታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ፣ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለተመራቂዎቹ ቤተክርስቲያን የጣለባችሁን አደራ እና የተሰጣችሁን ወንጌልን የማስተማር ሥራ በራሳችሁ በኩል ከእግዚአብሔር የገባችሁት ቃል ኪዳን እንድትጠበቁ ሲሉ አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ሰጥተዋል። ተመራቂዎቹም ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው ለቅድስት ቤተክርስቲያን ተተኪና ታማኝ አገልጋዮች ለመሆን ቃል ገብተዋል። ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ እና ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት የአንድነት ኑሮ ማኅበር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ቋንቋዎች ወንጌልን እንዲስፋፋ እያደረገ ያለው አስተዋጽኦ አመስግነዋል። በመጨረሻም በብፁዓን አባቶች ቃለ ምዳን እና ቡራኬ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/