fa
Feedback
EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

کانال EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 29 464 مشترک است و جایگاه 2 469 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 152 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 29 464 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -48 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 9 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.12% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.20% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 572 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 827 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

29 464
مشترکین
+924 ساعت
+337 روز
-4830 روز
آرشیو پست ها
በቀሌም ወለጋ ሀገረ ስብከት ለብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌና ቄሌም ወለጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ደማቅ አቀባበል ተደረገ ። ዘጋቢ መምህር የኔነህ ታፈሰ (#EOTCTV ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ደምቢዶሎ) በቀሌም ወለጋ ሀገረ ስብከት ለተመደቡት ለብፁዕ አቡነ ኤፍሬም በጎልጎታ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን የዞኑ መንግሥት ተወካይ ፣ የቀለም ወለጋ ዞን የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ተደረገ ። በሥነ ሥርዓቱ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ( ዶ/ር ) የኢሉአባቦር እና የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የመቱ ፈለገ ሕይወት መንፈሳዊ ኮለጅ የበላይ ኃላፊ ተገኝተው ምእመናንን አገልግለዋል። ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌ እና ቄለም ወለጋ ሊቀ ጳጳስ የዕለቱን ሥርዓተ ቅዳሴውን በመምራት ቀድሰው ምእመናንን በማቁረብ ያገለገሉ ሲሆን ፤ አቀባበሉ በዐውደ ምሕረቱ ቀጥሎ ጸሎተ ወንጌል የደረሰ ሲሆን የብፁዕነታቸው የምደባ ደብዳቤ በይፋ ተነቧል ። በቤተክርስቲያኑ አገልግሎት ሰፊ የዝማሬ የስብከተ ወንገል ትምህርት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ከአዲስ አበባና የሸገር ከተማ ሀገረ ሰብከት የተገኙ ልዑካን ሰፊ መንፈሳዊ አገልግሎት ከተሰጠ በኃላ በአባ ገዳ ጌታቸው ዲበሳ እና ከቀሌም ወለጋ ሃይማኖት ተቋማት ተወካይ ፖስተር እምሩ አብደታ አንዲሁም የዞኑ መንግሥት ተወካይ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት ቀርቦ ፤ በብፁዓን አባቶቻችን ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መርሐ ግብሩ በሰላም ተጠናቋል ። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ እርዳታም አበረከተ። (#EOTCTV ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም አርሲ-አቦምሳ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግር ተከትሎ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ በሥፍራው በመገኘት ተጎጂዎችን እንዲያጽናና ጊዜያዊ ርዳታም እንዲያደርግ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ማለዳ ወደ አርሲ ዞን አቦምሳ ወረዳ በመጓዝ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናንቷል፤ ጊዜያዊ እርዳታም አበርክቷል። በአቦምሳ ወረዳ የትንሣኤ ብርሃን ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በመገኘት ተጎጂ ኦርቶዶክሳዊያንን ያጽናኑት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በበኦርቶዶክሳዊያን ልጆቿ ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ በጣም ማዘኗን ገልጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ወገኖቻችን መንግስተሰማያትን እንዲያወርስልን፣ለቤተሰቦቻቸው መጽናናት እንዲያድልልን የዘወትር ጸሎታችን ነው።በርቱ፣ጠንክሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን ብለዋል። አያይዘውም ቋሚ ሲኖዶስ በአካል ተገኝቶ እናንተን ለማጽናናትና ጊዜያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመካከላችሁ ተገኝተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታትና የተቃጠለውን ቤተክርስቲያን ለመሥራት የሚያስቼል አቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተክህነት ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በተከሰተው ችግር ጥልቅ ኃዘን የተሰማት መሆኑን ገልጸው ምዕመናን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ፣በፈተና ሁሉ እንዲታገሱ አደራ ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ኃዘንተኞችን እንዲያጽናና ከዳግም ኃዘን እንዲሰውርልን ዘወትር እንጸልያለን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተዘጋጀውን ርዳታ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስረክበዋል።በዚሁ ጊዜ የአቦምሳ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ብፁዓን አባቶችን እንኳን ደህና መጣችሁልን በማለት በሀገሩ ባህል መሰረት የሰንጋ ስጦታ ካበረከቱ በኋላ የደረሰውን ጉዳት በመኮነን ሕዝቡ በስምምነት፣በአንድነትና በመቻል የኖረና ወደፊትም የሚኖር ሕዝበብ መሆኑን ጠቅሰው የተፈጠረውን ችግር ሃይማኖታዊ መልክ ለማስያዝ የሚደረገው ጥረት ተገቢነት የሌለው ነው ብለዋል።ለብፁዓን አባቶች የተበረከተው የሰንጋ ስጦታም ለተፈናቀሉ ወገኖች እንዲደርስ ተደርጎ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

ዜና ዕረፍት “ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤ የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” /መዝ.፻፭፥፲፭/፡፡ በጸሎታችውና በሊቅነታቸው የሚታወቁት እውነተኛው ባህታዊ መናኔ ዓለም በላኤ
ዜና ዕረፍት “ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤ የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” /መዝ.፻፭፥፲፭/፡፡ በጸሎታችውና በሊቅነታቸው የሚታወቁት እውነተኛው ባህታዊ መናኔ ዓለም በላኤ መጻፍሕፍት መጋቤ ብሉያት የኔታ ክፍሌ ዘ በዓታ ለማርያም (አባ ክፍለ ዮሐንስ) ዐረፉ፡፡ የኔታ ክፍሌ በተማሩበት እና በመነኮሱበት በታላቁ በደብረ ሊባኖስ ገዳም በብሉይ ኪዳን ትርጓሜ ምክትል ምህርነት እና በዳግማዊ ሚኒልክ መታሰቢያ የቀሳውስትና መምህራን ማሠልጠኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ለ32 ዓመታት በድምሩ ለ47 ዓመታት በጉባኤ መምህርነት አገልግለዋል፡፡ የበርካታ ሊቃውንት እና ሊቃነ ጳጳሳት መምህር የነበሩት የኔታ ክፍሌ በ98 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል ክቡር አስከሬናቸው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በ9 ሰሰዓት ሊቃውንትና ደቀ መዛሙርቶቻቸው እና ቤተሶቦቻቸው፣ ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ወደ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ገብቶ ሌሊቱን ሥርዓተ ማኅሌት እና ጸሎተ ፍትሐት ሲከናወን አድሮ ጥዋት 12.ዐዐ ሰዓት ወደ ደብረ ሊባኖስ ሽኝት ይደረጋል። +++++++++++++++++++++++++++++++++++++ • EOTC TV 2 | ይህ ሁለተኛው የኢ.ኦ.ተ.ቤ የዩቲዩብ ቻናል ነው... "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" ተቋሙን በገንዘብ ለማገዝ፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000165122406 ዓባይ ባንክ 1462319237132015 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት የዲጂታል ሚዲያ ገጾች ለመረጃ +251985585858 ➽ የዩቲዮብ ገጻችን / eotctv ➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን / eotctvchannel ➽የቴሌግራም ገጻችን https://t.me/eotctvchannel ➽ የቲክ ቶክ ገጻችን https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/ ➽ የዩቲዮብ ገጻ

ቤተክርስቲያን የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ልትሠራ ይገባል

በጉራጌ ሀገረ ስብከት ለቤተክርስቲያን አገልጋዮች ሥልጠና ተሰጠ

ምእመናን የሚሰጡት መብኣ ለተገቢው ዓላማ መዋል እንዳለበት ተገለጸ