en
Feedback
EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Channel EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 29 508 subscribers, ranking 2 430 in the Religion & Spirituality category and 1 147 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 29 508 subscribers.

According to the latest data from 06 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 63 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 9.65%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.30% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 847 views. Within the first day, a publication typically gains 1 859 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

29 508
Subscribers
-124 hours
+127 days
+6330 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
July '26
July '26
+50
in 1 channels
June '26
+219
in 3 channels
Get PRO
May '26
+223
in 5 channels
Get PRO
April '26
+156
in 5 channels
Get PRO
March '26
+93
in 5 channels
Get PRO
February '26
+42
in 2 channels
Get PRO
January '26
+76
in 3 channels
Get PRO
December '25
+74
in 3 channels
Get PRO
November '25
+87
in 1 channels
Get PRO
October '25
+148
in 4 channels
Get PRO
September '25
+167
in 3 channels
Get PRO
August '25
+133
in 5 channels
Get PRO
July '25
+82
in 2 channels
Get PRO
June '25
+81
in 3 channels
Get PRO
May '25
+208
in 3 channels
Get PRO
April '25
+226
in 2 channels
Get PRO
March '25
+147
in 4 channels
Get PRO
February '25
+190
in 4 channels
Get PRO
January '25
+537
in 3 channels
Get PRO
December '24
+564
in 2 channels
Get PRO
November '24
+65
in 4 channels
Get PRO
October '24
+255
in 5 channels
Get PRO
September '24
+54
in 3 channels
Get PRO
August '24
+3
in 3 channels
Get PRO
July '24
+105
in 6 channels
Get PRO
June '24
+34
in 4 channels
Get PRO
May '24
+190
in 3 channels
Get PRO
April '24
+238
in 4 channels
Get PRO
March '24
+765
in 10 channels
Get PRO
February '24
+998
in 14 channels
Get PRO
January '24
+567
in 3 channels
Get PRO
December '23
+547
in 1 channels
Get PRO
November '23
+570
in 10 channels
Get PRO
October '23
+258
in 1 channels
Get PRO
September '23
+513
in 0 channels
Get PRO
August '23
+356
in 0 channels
Get PRO
July '23
+618
in 0 channels
Get PRO
June '23
+378
in 0 channels
Get PRO
May '23
+867
in 0 channels
Get PRO
April '23
+523
in 0 channels
Get PRO
March '23
+1 353
in 0 channels
Get PRO
February '23
+17 523
in 0 channels
Get PRO
January '23
+2 868
in 0 channels
Get PRO
December '22
+650
in 0 channels
Get PRO
November '22
+443
in 0 channels
Get PRO
October '22
+315
in 0 channels
Get PRO
September '22
+213
in 0 channels
Get PRO
August '22
+190
in 0 channels
Get PRO
July '22
+633
in 0 channels
Get PRO
June '22
+255
in 0 channels
Get PRO
May '22
+253
in 0 channels
Get PRO
April '22
+355
in 0 channels
Get PRO
March '22
+706
in 0 channels
Get PRO
February '22
+218
in 0 channels
Get PRO
January '22
+701
in 0 channels
Get PRO
December '21
+106
in 0 channels
Get PRO
November '21
+196
in 0 channels
Get PRO
October '21
+645
in 0 channels
Get PRO
September '21
+208
in 0 channels
Get PRO
August '21
+134
in 0 channels
Get PRO
July '21
+221
in 0 channels
Get PRO
June '21
+472
in 0 channels
Get PRO
May '21
+1 335
in 0 channels
Get PRO
April '21
+431
in 0 channels
Get PRO
March '21
+65
in 0 channels
Get PRO
February '21
+120
in 0 channels
Get PRO
January '21
+146
in 0 channels
Get PRO
December '20
+3 975
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 July+7
06 July+6
05 July+5
04 July+13
03 July+12
02 July+5
01 July+2
Channel Posts
2
https://youtu.be/Msr3UoYYMHA?si=7EYBUF3kSfANvD4Z
1 529
3
https://youtu.be/evu8JLzRL94
1 354
4
No text...
1 956
5
ቅዱስ ዮሐንስም በርግብ አምሳል መውረዱን በመመስከር ምሥጢረ ሥላሴን አስተምሯል /ማቴ.፲፯፥፭፤ ዮሐ.፩፥፴፬/፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                   ጌታችንም፡- “ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጣችሁ? … ነቢይን? አዎን ይህ ከነቢይም ይበልጣል። (እነሆ መንገድህን በፊትህ የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ) ተብሎ የተጻፈለት እርሱ ነው፤ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤ ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይህ ነው፤ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ” በማለት የቅዱስ ዮሐንስን ታላቅነት ተናግሯል /ማቴ.፲፩፥፱-፲፩/። ኤልያስ ፀጉራም እንደ ኾነ ኹሉ ዮሐንስም ልብሱ የግመል ፀጉር መኾኑ፤ ሁለቱም መናንያን፣ ጸዋምያን፣ ተሐራምያን (ፈቃደ ሥጋን የተዉ)፣ ዝጉሐውያን (የሥጋን ስሜት የዘጉ)፣ ባሕታውያን መኾናቸው፤ በተጨማሪም ኤልያስ አክአብና ኤልዛቤልን፣ ዮሐንስ ደግሞ ሄሮድስና ሄሮድያዳን መገሠፃቸው፤ ኤልያስ ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት ቀድሞ እንደሚመጣ ሁሉ ዮሐንስም ከክርስቶስ ቀዳሚ ምጽአት (በአካለ በሥጋ መገለጥ) ቀድሞ ማስተማሩ ያመሳስላቸዋልና ጌታችን ዮሐንስን ኤልያስ ብሎታል። “እነርሱም ስለ ዮሐንስ እንደ ነገራቸው አስተዋሉ” ተብሎ እንደ ተጻፈ /ማቴ.፲፩፥፪-፲፱/። መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ “ድንበር አታፍርሱ፤ ዋርሳ አትውረሱ” እያለ ንጉሡ ሄሮድስንና ሄሮድያዳን በመገሠፁ ምክንያት አንገቱን በሰይፍ ተቈርጦ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ የራስ ቅሉ ክንፍ አውጥቶ በዓለም እየተዘዋወረ ፲፭ አምስት ዓመት ወንጌልን አስተምሯል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                      የቅዱስ ዮሐንስ ሕይወቱና ትምህርቱ፣ ያደረጋቸው ተአምራት፣ እንዲሁም እግዚአብሔር የሰጠው ቃል ኪዳንና ሰማዕትነቱ በገድሉ በሰፊው ተጽፏል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሰኔ ፴ ቀን የተወለደበት፤ መስከረም ፩ ቀን ቃል ኪዳን የተቀበለበት፤ መስከረም ፪ ቀን በሰማዕትነት ያረፈበት፤ ጥር ፲፩ ቀን ጌታችንን ያጠመቀበት፤ የካቲት ፴ ቀን ራሱ የተገኘችበት፤ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ራሱ ያረፈችበት (ነፍሱ የወጣችበት)፤ ሰኔ ፪ ቀን ደግሞ ፍልሰተ ዐፅሙ (ዐፅሙ የፈለሰበት) በዓል በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡     የቅዱስ ዮሐንስ ጸሎቱና በረከቱ አይለየን፡፡                 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ዋቤ መጻሕፍት              ✍️  መጽሐፍ ቅዱስ              ✍️ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ              ✍️   መጽሐፈ ስንክሳር               ✍️   የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
1 709
6
በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ የመድኀኒታችን የክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ ስለ ሰጋ ጌታችንን ያገኘሁ መስሎት የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል ጀመረ /ማቴ.፪፥፩-፲፮/፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ ልጇን ከሞት ለማዳን ስትል ሕፃኑ ዮሐንስን ይዛ ወደ በረሓ ተሰደደች። በበረሓም ድንጋይ ቤት ኾኖላቸው፣ እግዚአብሔርም ከብርድ፣ ከፀሐይና ከአራዊቱ አፍ እየጠበቃቸው መኖር ጀመሩ፡፡ ወደ በረሃ ሲገቡ ቅዱስ ዮሐንስ የሁለት ዓመት ከመንፈቅ ሕፃን ነበር፡፡ ሕፃኑም አደገ፤ በመንፈስም ጠነከረ፤ ለእስራኤል እስከታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ /ሉቃ.፩፥፹/፡፡ የሄሮድስ ጭፍሮችም ዮሐንስን ፈልገው ባጡት ጊዜ ዘካርያስን በቤተ መቅደስ ውስጥ በሰይፍ ገደሉት፤ ካህናቱም በንጹሕ ልብስ ገንዘው በአባቱ በበራክዩ መቃብር ቀበሩት፡፡ ደሙም እስከ ፸ ዓመት ድረስ ሲፈላ ኖረ። ጌታችንም የዘካርያስ ደም እንደሚፋረዳቸው ሲያስረዳ “ከአቤል ደም ጀምሮ በመሠዊያውና በቤተ መቅደስ መካከል እስከ ጠፋው እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ ከዚህ ትውልድ ይፈለጋል” በማለት ጸሐፍት ፈሪሳውያንን ገሥጿቸዋል /ሉቃ.፲፩፥፶፩/፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ ወደ በረሓ በገባች በአምስተኛ ዓመቷ፤ ቅዱስ ዮሐንስም ሰባት ዓመት ሲሞላው  ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፈች፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም እግዚአብሔር ከአራዊት አፍ እየጠበቀው፤ ሲርበው ሰማያዊ ኅብስትን እየመገበው፣ ሲጠማው ውኃ እያፈለቀ እያጠጣው፤ አናብስቱና አናምርቱ እንደ ወንድምና እኅት ኾነውለት በበረሃ መኖር ጀመረ፡፡ በበረሃ ሲኖርም የግመል ጠጉር ይለብስ፣ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ፣ አንበጣ  የሚባል (የበረሓ ቅጠል) እና መዓረ ጸደንያ (ጣዝማ ማር) ይመገብ ነበር /ኢሳ.፵፥፫-፭/።                                                                                                                                                                                                                                                                             ዐዋጅ ነጋሪ                                                                                                                                                                                                                                                                  ሠላሳ ዓመት ሲሞላውም በነቢዩ በኢሳይያስ ቃል “የጌታን መንገድ አዘጋጁ፤ ጥርጊያውንም አቅኑ፤ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ፡፡ ዐዘቅቱ ሁሉ ይሙላ፤ ተራራውና ኮረብታውም ኹሉ ዝቅ ይበል፡፡ ጠማማውም የቀና መንገድ ይኹን፤ ሸካራውም መንገድ ትክክል ይኹን፡፡ ሥጋም የለበሰ ኹሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ” ተብሎ እንደ ተነገረ ቅዱስ ዮሐንስ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ!” እያለ እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለው አገር ኹሉ ወጣ /ሉቃ.፫፥፫-፮/።                                                                                                                                                                                                                                                                   የይሁዳ አገር ሰዎች ኹሉ ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር። እርሱም፡- “ እናንተ የእፉኝት ልጆች ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ? እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፤ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቈረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል” ይላቸው ነበር፡፡ “ምን እናድርግ?” ብለው ሲጠይቁት “ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፤ ምግብም ያለው እንዲሁ ያድርግ” ይላቸው ነበር። ቀራጮችን፡- “ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ” ጭፍሮችንም፡- “በማንም ላይ ግፍ አትሥሩ፤ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፤ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ” እያለና ሌላም ብዙ ምክር እየመከረ ወንጌልን ይሰብክላቸው ነበር /ሉቃ.፫፥፯-፲፬/፡፡                                                                                                                                                                                                                                                  በተጨማሪም “… እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ነገር ግን የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ፣ ከእኔ በኋላ የሚመጣውና ከእኔ ይልቅ የሚበረታው እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል፤ መንሹም በእጁ ነው፤ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፤ ሥንዴውንም በጎተራው ይከታል፤ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል” በማለት የክርስቶስን በሥጋ መገለጥ እና አምላክነት ነግሯቸዋል /ማቴ.፫፥፩-፲፪፤ ሐዋ.፲፫፥፳፬-፳፰/። ቅዱስ ዮሐንስ ከፈሪሳውያን ወገን የኾኑ ካህናትና ሌዋውያን “ስለ ራስህ ምን ትላለህ?” ብለው በጠየቁት ጊዜም እርሱ ክርስቶስ እንዳልኾነና “የጌታን መንገድ አቅኑ” ብሎ በምድረ በዳ የሚጮኽ ቃለ ዐዋዲ (ዐዋጅ ነጋሪ) መኾኑን ተናግሯል /ሉቃ. ፫፥፲፭-፲፰፤ ዮሐ.፩፥፲፱-፳፫/።                                                                                                                                                                                                                                                                      ጌታችንን ያጠመቀ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊጠመቅ ወደ እርሱ በሔደ ጊዜ “እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ባሪያ ወደ ጌታው ይሔዳል እንጂ እንዴት ጌታ ወደ ባሪያው ይመጣል?” በማለት የጌታችንን አምላክነት በትሕትና ተናግሯል /ማቴ.፫፥፲፬/፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን “… ሌላውን በአንተ ስም አጠምቃለሁ፤ አንተንስ በማን ስም ላጥምቅህ?” ሲለው “እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሥልጣንህ ዘለዓለማዊ የኾነ የዓለሙ ካህን፤ የዓለምን ኃጢአት የምታስወግደው የእግዚአብሔር በግ፤ ብርሃንን የምትገልጽ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ይቅር በለን?” እያልህ አጥምቀኝ ብሎት እንደታዘዘው አድርጎ አጥምቆታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን ባጠመቀው ጊዜ ከሰማይ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” የሚለውን የእግዚአብሔር አብ ቃል መስማቱንና መንፈስ
1 130
7
Gecha Eotc Tv: መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!!! መ/ር ጌታቸው በቀለ                                                                                                                                                                                                                                                                          ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱስ ገብርኤልና አባቱ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት፣ ከሕፃንነቱ ጀምሮ ቅኑት እንደ ገበሬ፣ ጽሙድ እንደ በሬ ኾኖ እግዚአብሔርን ያገለገለ፣ ዓለምን የናቀ፣ አምላክን ለማጥመቅ የታደለ ሐዋርያ፣ መምህር፣ ሰማዕት፣ ባሕታዊ የኾነው ቅዱስ ዮሐንስ ሰኔ ፴ ቀን ተወለደ፡፡ ዮሐንስ ማለት “እግዚአብሔር ጸጋ ነው” ማለት ነው፡፡ ትርጓሜ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን “ፍሥሐ ወሐሴት” (ተድላና ደስታ) ይለዋል፤ ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና /ሉቃ.፩፥፲፬/፡፡ በዚህ ዝግጅታችን የመጥምቁ ዮሐንስን ታሪክ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                               ቅዱስ ዮሐንስ ማን ነው?                                                                                                                                                                                                                                                                           ቅዱስ ዮሐንስ የካህኑ ዘካርያስና የቅድስት ኤልሳቤጥ ልጅ ነው፡፡ በሉቃስ ወንጌል እንደተገለጸው ካህኑ ዘካርያስ እና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ የእግዚአብሔር ትእዛዝ እየፈጸሙ ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ፡፡ኤልሳቤጥም መካን ነበረች፤ /ሉቃ.፩፥፭-፯/፡፡ልጅ ይሰጣቸው ዘንድም እግዚአብሔርን ዘወትር ይማጸኑት ነበር፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                        ካህኑ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ዕጣን በማሳረግ ላይ ሳለም የእግዚአብሔር መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ጸሎቱ እንደ ተሰማና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ እንደምትወልድ፤ ስሙንም “ዮሐንስ” እንደሚለው፤ በመወለዱም ብዙዎች እንደሚደሰቱ፤ ልጁም በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ እንደሚኾን፣ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ እንደማይጠጣ፤ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላበት ነገረው /ሉቃ.፩፥፰-፲፯/፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                    ካህኑ ዘካርያስም “እኔ ሽማግሌ ነኝ፤ ሚስቴም አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ?” አለው፡፡ መልአኩም “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፡፡ እነሆም በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ ይህ ነገር እስከሚኾን ቀን ድረስ ዲዳ ትኾናለህ፤ መናገርም አትችልም” አለው /ሉቃ.፩፥፲፰-፳፩/፡፡ ከቤተ መቅደስ በወጣም ጊዜ ሊያናግራቸው ባለመቻሉ ይጠቅሳቸው ነበር፡፡ ሕዝቡም በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፡፡ እርሱም ድዳ ኾኖ ኖረ፡፡ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸምም ወደ ቤቱ ሔደ፤ ከሁለት ቀን በኋላም አረጋዊቷ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፀነሰች፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም በመካንነቷ ከሰዎች የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዷላታልና “እግዚአብሔር በዚህ ወራት ከሰው ስድቤን ያርቅ ዘንድ እንዲህ አደረገልኝ” ስትል ለአምስት ወራት ተሸሸገች /ሉቃ.፩፥፳፪-፳፭/፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                     አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ የዐዋጅ ነጋሪ ቃል ተብሎ እንደተነገረው  የእግዚአብሔርን  መንገድ  በምድረ  በዳ  ጥረጉ፥  ለአምላካችንም ጐዳና  በበረሓ  አስተካክሉ  በማለት ፊት አውራሪ ሆኖ የሚላከውን ቅዱስ ዮሐንስን የፀነሰችው  ቅድስት ኤልሳቤጥ በፀነሰች በስድስተኛው ወር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልትጠይቃት ወደ እርሷ በሔደች ጊዜም ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ውስጥ ኾኖ ለቅድስት ድንግል ማርያም እና በማኅፀኗ ላደረው አካላዊ ቃል (ለኢየሱስ ክርስቶስ) ሰግዷል /ሉቃ.፩፥፳፮-፵፩/፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም ድምጿን ከፍ አድርጋ “አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፤ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይኾንልኛል? እነሆ የሰላምታሽን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሏልና፡፡ ከጌታ የተነገረላት ቃል እንደሚፈጸምላት ያመነች ብፅዕት ናት፤” በማለት እመቤታችንን አመስግናታለች /ሉቃ.፩፥፵፪-፵፭/፡፡ የመውለጃዋ ቀን ሲደርስም ሰኔ ፴ ቀን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ። የመልአኩን የብሥራት ቃል ባለመቀበሉ አንደበቱ ተይዞ የነበረው ካህኑ ዘካርያም ስሙ “ዮሐንስ” ይባል ብሎ ሲጽፍ አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱም ተፈታ፡፡  በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ “… አንተ ሕፃን ሆይ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና፡፡ የኃጢአታቸው ስርየት የኾነውን የመዳን ዕውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፡፡ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፡፡ ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል፤ እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል” በማለት የቅዱስ ዮሐንስ ነቢይነትና አጥማቂነት፣ እንደዚሁም የክርስቶስን የማዳን ትምህርት እንደሚያበሥር አስቀድሞ ትንቢት ተናገረ /ሉቃ.፩፥፶፯-፸፱/፡፡
1 302
8
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን “ታሪክን ለትውልድ የማሻገር ተራው የእኔ ነው” በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 26-28 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው ዓ
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን “ታሪክን ለትውልድ የማሻገር ተራው የእኔ ነው” በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 26-28 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው ዓለም ዐቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ተጠናቀቀ፡፡
1 893
9
ለዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓለም አቀፍ የሀብት ማሰባሰቢያ ንቅናቄ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና የመንፈሳዊ ሥራ አመራር ኮሌጅን ለመደገፍ ዓለም ዓቀፍ የሀብት ማሰባሰ
ለዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓለም አቀፍ የሀብት ማሰባሰቢያ ንቅናቄ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና የመንፈሳዊ ሥራ አመራር ኮሌጅን ለመደገፍ ዓለም ዓቀፍ የሀብት ማሰባሰቢያ ንቅናቄ የማስጀመሪያ እና የምክክር ጉባኤ ተካሄደ፡፡
1 860
10
ዘመኑን የዋጀና ከአብነት ጋር የተናበበ ትምህርት በመማራችን ለውጤት በቅተናል “የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት ዘመኑን የዋጀና ከአብነት ጋር የተናበበ ትምህርት በመማራቸው ለውጤት መ
ዘመኑን የዋጀና ከአብነት ጋር የተናበበ ትምህርት በመማራችን ለውጤት በቅተናል “የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት ዘመኑን የዋጀና ከአብነት ጋር የተናበበ ትምህርት በመማራቸው ለውጤት መብቃታቸውን ገለጹ፡፡
1 936
11
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ምርቃት የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለተኛ ዲግሪ፣በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማና በካህናት የሥልጠና መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ዕጩ ደቀ መ
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ምርቃት የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለተኛ ዲግሪ፣በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማና በካህናት የሥልጠና መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ዕጩ ደቀ መዛሙርት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት አስመረቀ።
1 807
12
+3
No text...
2 273
13
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሕንጻ ቤተ መቅደስ ለማጠናቀቅ በተከናወነው ዓለም አቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ። የደብሩ ሕንጻ ቤተክርስቲያኑን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቧል ። (#EOTCTV ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም) ከ13 ዓመታት በፊት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ወደ ግንባታ የገባው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በውስጡ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እና ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን የያዘ ነው። በደብሩ የሚገኘው የቅድስት አርሴማ ሕንጻ ቤተመቅደስ በአቶ ሰማቸው ከበደን እና ቤተሰቦቻቸው ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ቤተክርስቲያኑ ለአገልግሎት መብቃቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጠፋኖስ ይርጋ አስተታውሰዋል። አስተዳዳሪው እዚያው ግቢ ውስጥ ከቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ቀድሞ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ከቅድስት አርሴማ በኋላም እንኳ ማለቅ ያልቻለው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያንን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ሕንጻውን ለማጠናቀቅ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቦ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ አእላፍ ጸጋዬ ቸሩ በግላቸው 9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው ፣ በደብሩ አስተዳዳሪ አስተባባሪነት ወልደጊዮርጊስ ተብሎ በጥምቀት ስሙ የተገለጸ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጅ 10 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ለመርጡለ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የክርስትና ቤት ለመሥራት ቃል መግባቱን ገልጸዋል። የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጢፋኖስ በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ አቶ ሰማቸው ከበደን እና ባለቤታቸውን ወ/ሮ ሀናን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትና በመላው ዓለም የሚገኙ ምእመናን ላደረጉት ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። በተለይም አቶ ስማቸው ከበደ በሆቴላቸው መርሐ ግብሩ በነጻ እንዲከናወን ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ አገልግሎት መስጠታቸው እና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው ለሌሎች ባለሀብቶችም አርአያነታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። ደብሩ ገቢ የተደረገውን እና በቃል ኪዳን ሰነድ ቃል የተገባውን ገንዘብ በመሰብሰብ በአጭር ጊዜ ቀሪውን የማጠናቀቂያ ሥራ ፈጽሞ ሕንጻ ቤተመቅደሱን ወደ አገልግሎት ለማስገባት የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴው በሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል ። የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በ1986 ዓ.ም የተመሠረተ ደብር ነው። ➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕ https://youtu.be/Wqgq1KebrOo 🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹 ➽ የዩቲዮብ ገጻችን http://www.youtube.com/c/eotctv ➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/eotctvchannel ➽የቴሌግራም ገጻችን https://t.me/eotctvchannel ➽ የቲክ ቶክ ገጻችን https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/ ➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2 https://youtu.be/Wqgq1KebrOo ➽የትዊተር ገጻችን https://twitter.com/EotcT/ ➽የኢንስታግራም ገጻችን https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=
1 984
14
+4
No text...
2 003
15
በደብረ ሮሓ ቅዱስ ላሊበላ የቅድስት መስቀል ክብራ መካነ ቅርስ መልሶ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። (#EOTCTV ሰኔ 28 ቀን 2018 ዔም ላሊበላ) በታሪካዊቷ የደብረ ሮሓ ቅዱስ ላሊበላ ከተማ የሚገኘውን የቅድስት መስቀል ክብራ ገዳምን መልሶ ለማልማት በሚደረገው ታላቅ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ እውን እንዲሆን በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል ። በዕለቱም ለዚሁ የተቀደሰ መካነ ቅርስ መልሶ ግንባታ የሚሆን የመሠረት ድንጋይ ለመጣል፣ ብፁዕነታቸው የጫካውን መንገድ በጽናትና በትዕግስት በእግራቸው አቋርጠዋል፤ አስቸጋሪውን አቀበትና ቁልቁለት በመውረድም ረዥም መንገድ ተጉዘው በቦታው ተገኝተዋል። ብፁዕነታቸው በመስክ ምልከታቸው ወቅት ታሪካዊውን ልማት በበላይነት ለመምራትና ለማንቀሳቀስ የተመረጡትን የኮሚቴ አባላት ያበረታቱ ሲሆን፣ ለሥራው መሳካት የሚረዱ ዘላቂና ግልጽ የሆኑ አባታዊ የሥራ አቅጣጫዎችንም ሰጥተዋል። አባታችን አያይዘውም ይህ ግንባታ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን አባታዊ መመሪያና ክትትል እያደረጉ፣ ሁልጊዜም ከኮሚቴው ጎን በጸሎትና በዕቅድ አብረው እንደሚቀጥሉ በመግልጽ ለሥራ አስፈጻሚዎቹ ትልቅ ብርታትና ተስፋ ለግሰዋል። በሥነ-ሥርዓቱ መጀመሪያ ላይ የገዳሙ ዋና አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ሕርያቆስ ፀጋየ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ ብፁዕ አባታችን አቡነ ኤርምያስ በወቅቱ በርካታ ሌሎች ተጨማሪ መንፈሳዊ ተግባራት የነበሩባቸው ቢሆንም፣ ሁሉንም ነገር ትተው በዋናነት የመጡት ግን የዚችን የቅድስት እናታችንን መሠረት ድንጋይ ለማስቀመጥ እንደሆነ በመግለጽ፣ ለቦታውና ለሥራው የሰጡትን ላቅ ያለ ክብርና አባታዊ ትኩረት አምላከ ቅዱሳን ያክብርልን ሲሉ ምስጋና አቅርበዋል ። ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ እንደገለጹት ፣ ይህ እንዲሠራ የታቀደው የእናቶች ገዳም በከተማ ውስጥ ለሚገኙና ለሚሰደዱ መናንያን እናቶች ትልቅ የመንፈስ እፎይታ ማዕከል ይሆናል። የዚህም ምክንያት እስካሁን እናቶች በስፋት የሚገለገሉበት የቤተ አማኑኤል የእናቶች ገዳም ለብዙ ሕዝብ መተላለፊያና መሻገሪያ መንገድ በመሆኑ፣ እናቶች በሥርዓት፣ በጸጥታና በአግባቡ ጸሎታቸውንና ተጋድሏቸውን እንዳያካሂዱ ትልቅ እንቅፋት ሆኖባቸው ስለቆየ እንደሆነ በመግለጽ፤ ይህ አዲስ የእናቶች ገዳም በዚህ ጥንታዊ መካነ ቅርስ ላይ መሠረቱ መጣሉ ታሪካዊቷን እናታችንን ቅድስት መስቀል ክብራን ከመዘከርና ታሪኳን ከማደስ ባለፈ፣ ለመናንያኑ እናቶች ፍጹም ሰላም የሰፈነበት ከፍተኛ መንፈሳዊ እረፍት የሚሰጥ መሆኑን ብፁዕነታቸው በሰፊው አስገንዝበዋል። በመጨረሻም፣ የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓቱ የገዳሙ ዋና አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ሕርያቆስ ፀጋየ እና የካህናት ተወካዮች በተገኙበት፣ በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ተከናውኖ መርሐ ግብሩ በጸሎት ተፈጽሟል። ዘገባው የቅዱስ ላሊበላ ገዳም ጸ/ቤት ነው። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/
1 676
16
+7
No text...
1 562
17
+9
No text...
1 489
18
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የአራቱ ጉባኤያት የምስክር ጉባኤ ቤት 19 ደቀመዛሙርትን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ። ዘጋቢ ያረካል አድማሱ 📷 ፈለገ ገነት ሚዲያ (#EOTCTV ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባሕርዳር) በምርቃት መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያንስ እና የግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስክር ጉባኤ ቤቱ መምህር ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የምስክር ጉባኤ ቤቶች መምህራን ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ተመራቂዎችና የተመራቂ ደቀመዛሙርት ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ጥሪ የተረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመርሐ ግብሩ ላይ ለተመራቂ ደቀመዛሙርት እና ለቤተክርስቲያን የእንኳን ደስ ያለን መልእክታቸው አስተላልፈው "የዛሬ ተመራቂ ደቀመዛሙርት የነገ መምህራን የቅድስት ቤተክርስቲያን ሉዓላዊነትነት ተከብሮ እንዲዘልቅ ፣ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ የቅዱስ ሲኖዶስ የተዘረጋው የቤተክርስቲያን ሰንሰለት ይበልጥ ጠንካራ እንዲሆን ለሐዋርያዊ አገልግሎት በምትጓዙበት ሁሉ በርትታችሁ ልትሠሩ ይገባል" ብለዋል። የብፁዕነታቸው አክለውም "በማያስፈልገው መልኩ የጥንቱን እውቀታችሁን አታዘምኑት" የአባቶቻችን ትርጓሜም ወደ ቀጣይ ትውልድ ተጠብቆ እንዲተላለፍ ተግታችሁ ሥሩ ፣ ከእውቀት ባሻገር ለመንፈሳዊነትም ልዩ ትኩረት እንድትሰጡ ደግሞም የምታስተምሩትን በተግባር መኖር ከተመራቂ ደቀመዛሙርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል። ብፁዕ አቡነ ኤልያስ በበኩላቸው ተመራቂ ደቀመዛሙርት ለፍሬ እንዲበቁ ምኞታቸውን በመግለፅ ሊቃውንት በዚህ መልኩ መመረቃቸው ጥንት ያልነበረ አሁን ግን የተለመደ ታላቅ ተግባር ነውና "ትልቅ ዕድል" ነው ብለዋል። ከዚህ ባሻገር ብፁዕነታቸው የብፁዕ አቡነ አብርሃምን መልእክት በሚያጠናክር መልኩ "ሊቃውንቱ ለቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነት ፣ ከቀድሞው በበለጠ በጋራ ሊቆሙ ፣ አንድ ድምፅ ሁነውም ሊመክሩ ፣ ምክረ ሐሳባቸውንም ለቅዱስ ሲኖዶስ በትጋት ሊያቀርቡ" እንደሚገባ ጠቁመዋል። የተመራቂ ደቀመዛሙርት መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ደግሞ ተማሪዎቻቸው ለዚህ ደረጃ በመብቃታቸው መደስታቸውን ገልጸው በቀጣይም በምስክር ጉባኤ ቤቱ በነበራቸው ቆይታ የቀሰሙትን ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዕውቀት ተግባር ላይ በማዋል ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር የሚጠቅም አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል። ከዚህ በመለስ የምስክር ጉባኤ ቤቱ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን በዛሬው የደቀመዛሙርት የምርቃት በዓል ላይ ለመምህራን ማረፊያ እንዲሁም ወደ ምስክር ጉባኤ ቤቱ ለሚመጡ እንግዶች መቀበያ የሚሆን ሕንጻ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ይህ አዲስ ሕንጻ የጉባኤ ቤቱን የትምህርት ሥርዓት ለማጠናከር፣ ለተማሪዎችም የተሻለ የአስተዳደርና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/
1 493
19
"የቅዱስ ዑራኤል ታሪካዊ ጥሪ በከፋ ሀገረ ስብከት!"
"የቅዱስ ዑራኤል ታሪካዊ ጥሪ በከፋ ሀገረ ስብከት!"
2 149
20
No text...
1 944