ar
Feedback
EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

تُعد قناة EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 29 478 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 418 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 156 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 29 478 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -15، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 7.75‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.48‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 285 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 617 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 4.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

29 478
المشتركون
+424 ساعات
-277 أيام
-1530 أيام
أرشيف المشاركات
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ

ቅዱስ ፓትርያርኩ ገዳማት ከአደጋ ሊጠበቁ እንደሚገባ አሳሰቡ

ቅዱስ ፓትርያርኩ የእንግሊዝ አምባሳደርና በአፍሪካ ኅብረት የቋሚ መልእክተኛን አነጋገሩ

ከተለያዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች ጋር በመተባበር ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችም እየተሰጡ ሲሆን በብፁዕ አባታችን መልካም ፈቃድና በመንበረ ፓትርያርክ በኩል በተደረገው ውሳኔ መሠረት፣ ከሰላሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የገንዘብ ድጋፍ ተመድቦ ከከተማው መግቢያ አንሥቶ እስከ ገዳሙ ድረስ የመንገድ መብራት መስመር በመዘርጋት የገዳሙ ዙሪያና የአካባቢው ማኅበረሰብ የመንገድ መብራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ። የዕድሳት ሥራው ተጠናቆ ሐምሌ አሥራ ሥድስት ቀን በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ አገልግሎት መጀመሩ የተገለጸ ሲሆን ገዳሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከማኅበረሰቡ ዕድገት ጋር ተያያዥነት ያላቸው መሠራት ያለባቸው በርካታ ቀሪ ሥራዎች ስላሉበት የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆችና ባለሟሎች ቀጣይ ትብብራቸውና ድጋፋቸው እንዳይለይ አስተዳዳሪው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የልማት ትሩፋቶች #የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆች ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ ከዘጠነኛ ክፍል እስከ አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንዲሁም ለከፍተኛ ትምህርት ዝግጅት የሚሆን ተጨማሪ የትምህርት ሕንጻ ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል ። #ለሃያ ሰባት የገጠርና የከተማ ማኅበረሰብ ክፍሎች የሚጠቅም የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ተዘርግቶ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል ። #ከሰላሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የገንዘብ ድጋፍ ተመድቦ ከከተማው መግቢያ አንሥቶ እስከ ገዳሙ ድረስ የመንገድ መብራት መስመር በመዘርጋት የገዳሙ ዙሪያና የአካባቢው ማኅበረሰብ የመንገድ መብራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ። ዘጋቢ፦ መምህር ፍቃዱ ኪሮስ (#EOTCTV ሐምሌ ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኘው ታዋቂውና ጥንታዊው የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓመታዊ የንግሥ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቤተ ክርስቲያን የሥራ ኃላፊዎችና እጅግ ቁጥራቸው የበዛ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበሯል ። ይህ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም በየዓመቱ የሐምሌ አሥራ ዘጠኝ ቀንን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት እንደሚያከብር የሚታወቅ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት ግን በዓሉን ልዩ የሚያደርገው ለብዙ ጊዜያት ሲጠበቅ የነበረውና በከፍተኛ የገንዘብና የሰው ኃይል ጉልበት የተከናወነው የቤተ ክርስቲያኑ ዕድሳት ሥራ ተጠናቆ ለምርቃት መብቃቱ ነው ። በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችና ከውጭ አገራት ጭምር የመጡ የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆችና ምዕመናን በቅጽረ ገዳሙ ተገኝተው የበዓለ ንግሡ ተሳታፊ ሆነዋል ። በዚህ ደማቅና ታሪካዊ የንግሥ በዓል መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣ የምሥራቅ ሐረርጌ፣ የምሥራቅ ወለጋ እና የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ የሥራ ኃላፊዎች፣ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ቀሲስ ንጋቱ ደሳለኝ፣ የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ሰላማ፣ የገዳሙ ሊቃውንት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና በርካታ ምዕመናን በበዓለ ንግሡ ላይ ተገኝተዋል ። በበዓሉ መክፈቻ ላይ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የቤተ ክርስቲያኑ ዕድሳት ሥራ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ ለዛሬው የንግሥ በዓል ለመብቃት ሌሊትና ቀን ለሃያ አራት ሰዓታት ያህል በትጋት፣ ጥረትና ሥራ ሲሠራ መቆየቱን በሰፊው አብራርተዋል ። ይህ የተከናወነው ታላቅ ሥራ በጥቂት ወራት ብቻ የተገደበ ሳይሆን ለአንድ ሙሉ ዓመት ያህል የተሠራ ያህል ከባድና በትጋት የተሞላበት መሆኑን በመግለጽ ለሥራው ስኬት ድጋፍ ላደረጉት ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ሰላማ ባቀረቡት ሰፊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ «ጊዜ ዝንቱ ለእግዚአብሔር» የሚለውን የነቢዩ ዳዊት ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ የገዳሙን ታሪካዊ አመጣጥና ያጋጠሙትን ፈተናዎች ዘርዝረዋል ። ይህ ታላቅ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው ገዳም በጥንታዊነቱ በሺህ ዘጠኝ መቶ አምሳ ሰባት ዓመተ ምሕረት በግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴና በወቅቱ በነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አባታዊ አመራር የተገነባ ቢሆንም በጊዜ ብዛትና በተገቢው ወቅት ዕድሳት ባለማግኘቱ ምክንያት በሕንጻውና በዙሪያው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰበት መምጣቱን አስረድተዋል ። ቀደም ሲል የነበሩት የገዳሙ አስተዳደሮች የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ዕድሳት እንዲደረግለት ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ የቆዩ ቢሆንም መፍትሔው በመዘግየቱ ምክንያት ችግሩ እየከበደ በመምጣቱ ጉዳዩ እንደገና ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትና ለቅዱስ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ ተደርጓል በለዋል ። በሪፖርታው መሠረትም የቅዱስ ሲኖዶስ ርዕሰ መንበር በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ መመሪያ ሰጪነት ቅዱስ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት በመገንዘብ በአስቸኳይ የዕድሳት ሥራው እንዲጀመር አስፈላጊውን በጀት ፈቅዷል ፤ በመቀጠልም በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅ የቅርብ ክትትልና መመሪያ ከፍተኛ ዕውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ሥራውን እንዲያከናውኑ በግልጽ ጨረታ ፋሲል ጊዮርጊስ አማካሪ ድርጅት ከተቀጠረ በኋላ በቀረበው የመጨረሻ ጥናት መሠረት አዶር ኢንጂነሪንግ የተባለው ድርጅት ጨረታውን አሸንፎ በሁለት ሺህ አሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት የዕድሳት ሥራውን እንዲጀምር ተደርጓል ። ሥራው ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ምርቃቱ ዕለት ድረስ የብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅና የብፁዕ ዋና ጸሐፊ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ሳይለየው ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ተከናውኖ ዛሬ ለምርቃት መብቃቱን አብስረዋል ። የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ሰላማ በሪፖርታቸው ማጠቃለያ ላይ ለበጎ ሥራው መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን አካላት በሙሉ አመስግነዋል ። በዚህም መሠረት በጸሎታቸው፣ በምክራቸውና በአባታዊ አመራራቸው ከጎናቸው ላልተለዩት ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ለዚህ ዓለም አቀፋዊ ፕሮጀክት ልዩ ትኩረትና የቅርብ ክትትል ላደረጉት ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ከሥራው መጀመሪያ አንሥቶ ሂደቱን በመጎብኘትና በማበረታታት ትልቅ ድጋፍ ላደረጉት ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ እንዲሁም በየጊዜእየተገኙ በመምከርና በማበረታታት ትጋታቸውን ላሳዩት ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል ። በተጨማሪም ፣ ሥራው እንዲሳካ ቀንና ሌሊት ለደከሙ ሠራተኞች፣ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚገኙ ረዳቶች፣ አባቶች፣ ልዩ ልዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች በሙሉ በቅዱስ ገብርኤል ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። በገዳሙ በኩል የተከናወኑትን ዘርፈ-ብዙ ልማታዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች በተመለከተ አስተዳዳሪው በሰፊው አብራርተዋል ። በመጀመሪያ ደረጃ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል የሚደርስ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ተገንብቶ የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆች ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ ከዘጠነኛ ክፍል እስከ አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንዲሁም ለከፍተኛ ትምህርት ዝግጅት የሚሆን ተጨማሪ የትምህርት ሕንጻ ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል ። በሌላ በኩል ደግሞ ለሃያ ሰባት የገጠርና የከተማ ማኅበረሰብ ክፍሎች የሚጠቅም የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ተዘርግቶ አገልግሎት እንዲሰጥ የተደረገ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ የሕዝብ መገልገያዎች ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ።

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ:: ዘጋቢ፦ መምህር ፍቃዱ ኪሮስ (#EOTCTV ሐምሌ ፲ ፰ ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ/ም ድሬዳዋ ) ዓመታዊውን የቅዱስ ገብርኤልን በዓል በቁልቢ ደብረ ኃይል ገዳም ለማንገሥ ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤተ ክርስቲያን በግንባታ ላይ ያሉ ባለ 8 የገበያ ማዕከላትን የሥራ ሂደት ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ ሐዋርያዊ ጉዞውን በመምራት ላይ የሚገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲሁም ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በዕለቱ ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ማብራሪያ የሰጡት የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ ኃይለ ማርያም ገብረ ሚካኤል፣ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ናቸው። የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤተ ክርስቲያን ራስን በራስ ለመደገፍና የገቢ አቅምን ለማሳደግ የጀመረው ይህ የገበያ ማዕከላት ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጀምሮ በአሁኑ ወቅት በአማካይ 70 በመቶ (70%) ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ይህ የልማት ፕሮጀክት ቤተ ክርስቲያኗ በኢኮኖሚ ራሷን ችላ ማኅበራዊና መንፈሳዊ አገልግሎቷን በተጠናከረ መልኩ እንድታስቀጥል ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ቤተ ክርስቲያንን በራስ አገዝ የልማት ሥራዎች የመደገፍና የማጠናከር ተግባር እጅግ የሚበራታታ መሆኑን ገልጸው፣ ይህ ዓይነቱ አርአያነት ያለው ተግባር በሌሎችም አድባራትና ገዳማት ዘንድ ሊለመድና ሊተገበር ይገባል። በተጨማሪም በፁዓን አበው ሊቃነ ጰጳሳት በግንባታ ላይ ያለውን የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ፅ/ቤት ዕድሳት እና ሁለገብ የስብሰባ አዳራሽ የጎበኑ ሲሆን በጉብኝቱ ወቅት ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የሀገረ ስብከቱ ዕድሳት 90 በመቶ (90%) ደርሷል በማለት ገልፀዋል።

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ:: ዘጋቢ፦ መምህር ፍቃዱ ኪሮስ (#EOTCTV ሐምሌ ፲ ፰ ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ/ም ድሬዳዋ ) ዓመ
+8
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ:: ዘጋቢ፦ መምህር ፍቃዱ ኪሮስ (#EOTCTV ሐምሌ ፲ ፰ ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ/ም ድሬዳዋ ) ዓመታዊውን የቅዱስ ገብርኤልን በዓል በቁልቢ ደብረ ኃይል ገዳም ለማንገሥ ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤተ ክርስቲያን በግንባታ ላይ ያሉ ባለ 8 የገበያ ማዕከላትን የሥራ ሂደት ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ ሐዋርያዊ ጉዞውን በመምራት ላይ የሚገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲሁም ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በዕለቱ ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ማብራሪያ የሰጡት የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ ኃይለ ማርያም ገብረ ሚካኤል፣ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ናቸው። የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤተ ክርስቲያን ራስን በራስ ለመደገፍና የገቢ አቅምን ለማሳደግ የጀመረው ይህ የገበያ ማዕከላት ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጀምሮ በአሁኑ ወቅት በአማካይ 70 በመቶ (70%) ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ይህ የልማት ፕሮጀክት ቤተ ክርስቲያኗ በኢኮኖሚ ራሷን ችላ ማኅበራዊና መንፈሳዊ አገልግሎቷን በተጠናከረ መልኩ እንድታስቀጥል ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ቤተ ክርስ

የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት መግለጫ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገደም በተከሰተው የድሮን
የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት መግለጫ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገደም በተከሰተው የድሮን ጥቃት የደረሰው የመነኰሳይያት ሕልፈተ ሕይወት፣ ከፍተኛ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመትን አስመልክቶ የኃዘን መግለጫ አውጥቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አገልጋዮችና ምእመናን በሚገጥማቸው መጠነ ሰፊ ችግር በሞት እየተለዩና በሕይወት ያሉትም በከፍተኛ ስጋት እየኖሩ መሆኑን በመግለጫው ጠቅሷል። በሀገረ ስብከቱ ገዳማትና አድባራት ተመሳሳይ አስከፊ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ከዛሬ ነገ ይሻሻላል በሚል ያልተገባ መስዋእትነት እንዳይከፈል አርቆ በማሰብ የሚችለውን ሁሉ ሲያደርግ ቢቆይም ምእመናንን ከሞት ንብረታቸውንም ከውድመት ሊታደጋቸው አለመቻሉን ገልጿል። በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገደም ከምናኔ ሕይወት በስተቀር ሌላ አመለካከት በሌላቸው መናንያን ላይ የደረሰውን አስከፊ ድርጊት በጽኑዕ አውግዟል። ይህ ዓይነቱ ዘግናኝ ድርጊት በቤተክርስቲያንና በአማኞቿ ላይ እንዳይደገም የሚመለከተው አካል በትኩረት እንድያስብበትም ጠይቋል።

የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ አስመረቀ