EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)
تُعد قناة EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 29 581 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 338 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 190 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 29 581 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 27، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 15، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.13%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.64% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 701 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 668 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 5.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
29 581
المشتركون
+1524 ساعات
+337 أيام
+2730 أيام
أرشيف المشاركات
«ሕንጻው ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክ እንጂ ለሰው አይደለም፤ ሥራውም ታላቅ ነው።»
— 1ኛ ዜና መዋዕል 29፥1
ከ15 ዓመታት በላይ የፈጀው የሻሸመኔ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አዲስ ሕንፃ ቤተክርስቲያን ሊመረቅ ነው!
በተለያዩ ፈተናዎችና እልህ አስጨራሽ ተግዳሮቶች ውስጥ አልፎ፣ ከ15 ዓመታት በላይ የፈጀው የሻሸመኔው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተጠናቆ ከመስከረም 10–12 ቀን 2019 ዓ.ም. በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ሊመረቅ ነው።
በሻሸመኔ ከተማ ምስረታ ጋር ብዙም የማይራራቅ የታሪክ ትስስር ያለው ይህ ቤተክርስቲያን፣ በልዩ የሕንጻ ዲዛይኑ፣ በግዝፈቱና በሃይማኖታዊ ተምሳሌቶቹ የተለየ መልክ ይዞ ተገንብቷል።
ባለ ሰባት ጉልላት የሆነው ይህ ሕንጻ ከመንፈሳዊ አገልግሎቱ ባሻገር ለሻሸመኔና ለአካባቢው እንዲሁም ለኢትዮጵያ በቱሪዝምና በባህል ዘርፍ የሚኖረው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው።
የሕንፃው መጠን
• በ 2,512 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ
• ከመሬት ወለል በላይ 49 ሜትር ከፍታ ያለው
• ልዩ የሆነ ባለ ሰባት ጉልላት የሕንፃ አቀማመጥ ያለው
የምረቃ ጥሪ
በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ዝግጅት ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ሊቃነ ጳጳሳት፣ የወንጌል መምህራን፣ ዘማሪያን እንዲሁም ከመላው ኢትዮጵያና ከዓለም የሚመጡ ምዕመናን ይገኛሉ።
በመሆኑም በመላው ዓለም የምትገኙ ምዕመናን፣ በብርቱ ፈተናዎች ውስጥ አልፎ በሞገስ የተጠናቀቀውን የሻሸመኔ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አዲስ ሕንፃ ቤተክርስቲያን ምረቃ በአካል ተገኝታችሁ እንድትባርኩ ቤተክርስቲያኗ በታላቁ መላእክት ስም የፍቅር ጥሪዋን ታቀርባለች።
የድጋፍ ጥሪ
የቤተክርስቲያኑን ቀሪ ሥራዎች ለማጠናቀቅ፣ ለምንጣፍ፣ ለውጭ ወንበሮች ማሰሪያ፣ ለታቦት ማክበሪያ መንበር ማጠናቀቂያና ለተለያዩ ቀሪ ክፍያዎች የሚውል የአቅማችሁን ድጋፍ በሚከተለው የደብሩ የባንክ ሒሳብ ማስገባት ትችላላችሁ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሂሳብ ቁጥር፦ 1000767827257
እንደ አቅማችን እንሳተፍ፤ ለትውልድ የሚያልፍ መንፈሳዊና ባህላዊ አሻራ እንተው።
ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቀን!
የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም። በኢትዮጵያ የተመሠረተበትን የሦስት ሺህ (፴፻) (3,000) ዓመት እያከበረ ነው።
ዘጋቢ መ/ር አቤል አሰፋ
(#EOTCTV መስከረም ፲ ቀን ፳፻፲፱ ዓ.ም ጣና ቂርቆስ)
የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም " የሦስት ሺህ (፴፻) ዓመቱ ሕያው ገዳም ጣና ቂርቆስና የነገረ ልእልናው " በሚል መሪ ቃል የምሥረታ በዓሉን በማክበር ላይ ይገኛል ።
ገዳሙ “የሦስት ሺህ (፴፻) ዓመቱ ሕያው ገዳም ጣና ቂርቆስና የነገ ልእልናው " በሚል መሪ ቃል የምሥረታ በዓሉን ሲያከብር ብፁዕ አቡነ እንድርያስ የሊቃውንት ጉባኤ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ቀሲስ ግርማ ባቱ (ረዳት ፕሮፌሰር) የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ መምህር አባ ገብረሥላሴ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም አበምኔት ፤ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል (ረዳት ፕሮፌሰር) የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የጥናት እና ምርምር መምሪያ ሓላፊ፣ መጋቤ ሐዲስ ኃይለእግዚእ አሰፋ የሰንበት ትምሕርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ ፣ ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ የገዳሙጠየ፬ቱ ጉባኤያት መምህር ፣ የመንበረ ፓትርያርክ የየመምሪያው ምክትል ሓላፊዎች እና የዋና ክፍለል ኃላፊዎች ፣ የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የታላላቅ ገዳማትና አድባራት አስተዳደሪዎችና አበምኔቶች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና በርካታ ምእመናን ተገኝተዋል።
የበዓሉ ዋና ዓላማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከብሉይ ኪዳን እስከ ሐዲስ ኪዳን ያላትን ዘመናት የታሪክ፣ የቅርስና የጥበብ ጉዞ ለትውልድ ማስተዋወቅ መሆኑ ተነግሯል ።
በበዓሉ ሥርዓተ ማኅሌት የተከናወነ ሲሆን ሥርዓተ ቅዳሴው በብፁዕ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ተከናውኗል ።
በዐውደ ምሕረቱ ጉባኤ ሊቃውንት ያሬዳዊ ዜማ ያቀረቡ ሲሆን በሊቃውንት ቅኔ ቀርቧል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም በጣና ሐይቅ ላይ ከሚገኙት የተቀደሱና ታሪካዊ ደሴቶች አንዱ እና ዋነኛው ነው::
ገዳሙ የቃል ኪዳኑ ታቦት (ታቦተ ጽዮን) ለብዙ ዓመታት በላይ መኖሪያ እንደነበረ እንዲሁም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ ዮሴፍ፣ ሰሎሜ እና ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ይዛ ፫ ወራት ከ፲ ቀናት ማረፊያ እንደነበረ ታሪክ ለአብነት ይነገራል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዜማ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ምልክት የሌለውን የመጀመሪያውን የድጓ መጽሐፍ የደረሰውና የጻፈው በዚህ ገዳም ውስጥ እንደሆነ ይታመናል። የእርሱ መጽሐፍና የነሐስ መስቀልም በገዳሙ ቤተመዘክር ውስጥ ይገኛል።
በበዓሉ ጥናታዊ ጽሑፎች ይቀርቡበታል ተብሎ ይጠበቃል ።
የበዓሉን አከባበር ይዘን እንመለሳለን።
የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency
የብራና መጻሕፍት ዝግጅት ላይ ሊቃውንቱ አስተያየት
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የመስቀል ደመራ በዓል መዝሙር ጥናት ጎበኙ
የአንድነት ገዳማት ኅብረት አባቶች የዐዲስ ዓመት መልካም ምኞት
ቅዱስ ፓትርያርኩ ከእስራኤል ኤምባሲ ምክትል አምባሳደር ጋር ተወያዩ
EOTC TV | ዜና ቤተ ክርስቲያን መስከረም 08 2019 ዓ.ም #news
https://youtu.be/qcY-VGF84h4
ዛሬ ምሽት 2፡00 ሰዓት በEOTC TV የዩቲዩብ ቻናል ይጠብቁን
https://www.youtube.com/c/EOTCTV
+6
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ምክትል አምባሳደር (Deputy Ambassador of the State of Israel) ሲቫን ኖይማርክ ዙሪኤልን (Sivan Noymark Zuriel) በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
መ/ር ጌታቸው በቀለ
መስከረም ፯ ቀን ፳፻፲፱ ዓ/ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ምክትል አምባሳደር (Deputy Ambassador of the State of Israel) ሲቫን ኖይማርክ ዙሪኤል (Sivan Noymark Zuriel) በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
ምክትል አምባሳደሯ ሲቫን ኖይማርክ ዙሪኤል እንደተናገሩት “ሁለቱ ሀገራት እስራኤልና ኢትዮጵያ የረጅም ዓመታት የታሪክ፣ የባህልና የሃይማኖት ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፡፡ በተለይም ደግሞ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጋር ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት ጠንካራ በመሆኑ ይበልጥ ማጠናከር የሚቻል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መሥራት እንደሚገባ” ተወይይተናል ብለዋል፡፡ አክለውም “ለቅድስት ቤተክርስቲያን ለአገልግሎት በራችን ክፍት ነው፤ አገልግሎቷንም ለማጠናከር አብረን እንሠራለን” ብለዋል፡፡
የኤምባሲው ቆንስላ ሀዳስ ቫሮና (Hadas Varona Counsul) የቅዱስነታቸው አቀባበል ልዩ ነው በጣም ነው ደስ ያለን ብለዋል አያይዘውም የሁለቱ ሀገሮች ጥብቅ ግንኙነት ቀላል አይደለም፤ በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በእስራኤል ካላት ይዞታ፣ቤተክርስቲያን፣ ካህናት ገዳማት ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ ተወያይተናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ቅዱስነታቸው “እንኳን ደህና መጣችሁ” ብለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለእስራኤል እንደምት
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ምክትል አምባሳደር (Deputy Ambassador of the State of Israel) ሲቫን ኖይማርክ ዙሪኤልን (Sivan Noymark Zuriel) በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
መ/ር ጌታቸው በቀለ
መስከረም ፯ ቀን ፳፻፲፱ ዓ/ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ምክትል አምባሳደር (Deputy Ambassador of the State of Israel) ሲቫን ኖይማርክ ዙሪኤል (Sivan Noymark Zuriel) በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
ምክትል አምባሳደሯ ሲቫን ኖይማርክ ዙሪኤል እንደተናገሩት “ሁለቱ ሀገራት እስራኤልና ኢትዮጵያ የረጅም ዓመታት የታሪክ፣ የባህልና የሃይማኖት ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፡፡ በተለይም ደግሞ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጋር ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት ጠንካራ በመሆኑ ይበልጥ ማጠናከር የሚቻል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መሥራት እንደሚገባ” ተወይይተናል ብለዋል፡፡ አክለውም “ለቅድስት ቤተክርስቲያን ለአገልግሎት በራችን ክፍት ነው፤ አገልግሎቷንም ለማጠናከር አብረን እንሠራለን” ብለዋል፡፡
የኤምባሲው ቆንስላ ሀዳስ ቫሮና (Hadas Varona Counsul) የቅዱስነታቸው አቀባበል ልዩ ነው በጣም ነው ደስ ያለን ብለዋል አያይዘውም የሁለቱ ሀገሮች ጥብቅ ግንኙነት ቀላል አይደለም፤ በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በእስራኤል ካላት ይዞታ፣ቤተክርስቲያን፣ ካህናት ገዳማት ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ ተወያይተናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ቅዱስነታቸው “እንኳን ደህና መጣችሁ” ብለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለእስራኤል እንደምት
