EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) 的分析概览
频道 EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 29 464 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 2 469,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 152 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 29 464 名订阅者。
根据 14 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -48,过去 24 小时变化为 9,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 12.12%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.20% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 572 次浏览,首日通常累积 1 827 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 15 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
29 464
订阅者
+924 小时
+337 天
-4830 天
帖子存档
በቀሌም ወለጋ ሀገረ ስብከት ለብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌና ቄሌም ወለጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ደማቅ አቀባበል ተደረገ ።
ዘጋቢ መምህር የኔነህ ታፈሰ
(#EOTCTV ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ደምቢዶሎ)
በቀሌም ወለጋ ሀገረ ስብከት ለተመደቡት ለብፁዕ አቡነ ኤፍሬም በጎልጎታ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን የዞኑ መንግሥት ተወካይ ፣ የቀለም ወለጋ ዞን የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ተደረገ ።
በሥነ ሥርዓቱ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ( ዶ/ር ) የኢሉአባቦር እና የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የመቱ ፈለገ ሕይወት መንፈሳዊ ኮለጅ የበላይ ኃላፊ ተገኝተው ምእመናንን አገልግለዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌ እና ቄለም ወለጋ ሊቀ ጳጳስ የዕለቱን ሥርዓተ ቅዳሴውን በመምራት ቀድሰው ምእመናንን በማቁረብ ያገለገሉ ሲሆን ፤ አቀባበሉ በዐውደ ምሕረቱ ቀጥሎ ጸሎተ ወንጌል የደረሰ ሲሆን የብፁዕነታቸው የምደባ ደብዳቤ በይፋ ተነቧል ።
በቤተክርስቲያኑ አገልግሎት ሰፊ የዝማሬ የስብከተ ወንገል ትምህርት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ከአዲስ አበባና የሸገር ከተማ ሀገረ ሰብከት የተገኙ ልዑካን ሰፊ መንፈሳዊ አገልግሎት ከተሰጠ በኃላ በአባ ገዳ ጌታቸው ዲበሳ እና ከቀሌም ወለጋ ሃይማኖት ተቋማት ተወካይ ፖስተር እምሩ አብደታ አንዲሁም የዞኑ መንግሥት ተወካይ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት ቀርቦ ፤ በብፁዓን አባቶቻችን ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መርሐ ግብሩ በሰላም ተጠናቋል ።
የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/
የየኔታ ክፍሌ ወልደ ጊዮርጊስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
ለሀገራችን አንድነት በሰላምና በፍቅር ማገልገል
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በአርሲ አቦምሳ ወረዳ
በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ እርዳታም አበረከተ።
(#EOTCTV ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም አርሲ-አቦምሳ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግር ተከትሎ
በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ በሥፍራው በመገኘት ተጎጂዎችን እንዲያጽናና ጊዜያዊ ርዳታም እንዲያደርግ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ማለዳ ወደ አርሲ ዞን አቦምሳ ወረዳ በመጓዝ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናንቷል፤ ጊዜያዊ እርዳታም አበርክቷል።
በአቦምሳ ወረዳ የትንሣኤ ብርሃን ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በመገኘት ተጎጂ ኦርቶዶክሳዊያንን ያጽናኑት
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በበኦርቶዶክሳዊያን ልጆቿ ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ በጣም ማዘኗን ገልጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ወገኖቻችን መንግስተሰማያትን እንዲያወርስልን፣ለቤተሰቦቻቸው መጽናናት እንዲያድልልን የዘወትር ጸሎታችን ነው።በርቱ፣ጠንክሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን ብለዋል።
አያይዘውም ቋሚ ሲኖዶስ በአካል ተገኝቶ እናንተን ለማጽናናትና ጊዜያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመካከላችሁ ተገኝተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታትና የተቃጠለውን ቤተክርስቲያን ለመሥራት የሚያስቼል አቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተክህነት ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በተከሰተው ችግር ጥልቅ ኃዘን የተሰማት መሆኑን ገልጸው ምዕመናን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ፣በፈተና ሁሉ እንዲታገሱ አደራ ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ኃዘንተኞችን እንዲያጽናና ከዳግም ኃዘን እንዲሰውርልን ዘወትር እንጸልያለን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተዘጋጀውን ርዳታ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስረክበዋል።በዚሁ ጊዜ የአቦምሳ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ብፁዓን አባቶችን እንኳን ደህና መጣችሁልን በማለት በሀገሩ ባህል መሰረት የሰንጋ ስጦታ ካበረከቱ በኋላ የደረሰውን ጉዳት በመኮነን ሕዝቡ በስምምነት፣በአንድነትና በመቻል የኖረና ወደፊትም የሚኖር ሕዝበብ መሆኑን ጠቅሰው የተፈጠረውን ችግር ሃይማኖታዊ መልክ ለማስያዝ የሚደረገው ጥረት ተገቢነት የሌለው ነው ብለዋል።ለብፁዓን አባቶች የተበረከተው የሰንጋ ስጦታም ለተፈናቀሉ ወገኖች እንዲደርስ ተደርጎ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
ዜና ዕረፍት
“ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤
የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” /መዝ.፻፭፥፲፭/፡፡
በጸሎታችውና በሊቅነታቸው የሚታወቁት እውነተኛው ባህታዊ መናኔ ዓለም በላኤ መጻፍሕፍት መጋቤ ብሉያት የኔታ ክፍሌ ዘ በዓታ ለማርያም (አባ ክፍለ ዮሐንስ) ዐረፉ፡፡
የኔታ ክፍሌ በተማሩበት እና በመነኮሱበት በታላቁ በደብረ ሊባኖስ ገዳም በብሉይ ኪዳን ትርጓሜ ምክትል ምህርነት እና በዳግማዊ ሚኒልክ መታሰቢያ የቀሳውስትና መምህራን ማሠልጠኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ለ32 ዓመታት በድምሩ ለ47 ዓመታት በጉባኤ መምህርነት አገልግለዋል፡፡
የበርካታ ሊቃውንት እና ሊቃነ ጳጳሳት መምህር የነበሩት የኔታ ክፍሌ በ98 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል ክቡር አስከሬናቸው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በ9 ሰሰዓት ሊቃውንትና ደቀ መዛሙርቶቻቸው እና ቤተሶቦቻቸው፣ ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ወደ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ገብቶ ሌሊቱን ሥርዓተ ማኅሌት እና ጸሎተ ፍትሐት ሲከናወን አድሮ ጥዋት 12.ዐዐ ሰዓት ወደ ደብረ ሊባኖስ ሽኝት ይደረጋል።
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
• EOTC TV 2 | ይህ ሁለተኛው የኢ.ኦ.ተ.ቤ የዩቲዩብ ቻናል ነው...
"የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"
ተቋሙን በገንዘብ ለማገዝ፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000165122406
ዓባይ ባንክ 1462319237132015
የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
/ eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
/ eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻ
ቤተክርስቲያን የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ልትሠራ ይገባል
በጉራጌ ሀገረ ስብከት ለቤተክርስቲያን አገልጋዮች ሥልጠና ተሰጠ
ምእመናን የሚሰጡት መብኣ ለተገቢው ዓላማ መዋል እንዳለበት ተገለጸ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
