Falcon Grade 12 Social 2018E.C
Open in Telegram
Falcon Academy grade 11 channel is dedicated to students and their parents to send worksheets and exchange information.
Show more1 277
Subscribers
+124 hours
-57 days
+1930 days
Posts Archive
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን ወስደው በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋምና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲያስገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ተማሪዎች ምርጫቸውን ትምህርት ቤት መሄድ ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው በኦንላይን ማስገባት ይችላሉ።
የምርጫ ማስገቢያ ድረ-ገጹ፦ student.ethernet.edu.et ነው።
- በሕክምና ምክንያት ልዩ ሁኔታ ያላቸው፣
- የአካል ጉዳተኛ የሆኑ፣
- ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች
- ከ6 ወር በታች ሕፃን የሚያጠቡ እናቶች ተገቢውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
#MoE
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን ወስደው በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋምና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲያስገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ተማሪዎች ምርጫቸውን ትምህርት ቤት መሄድ ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው በኦንላይን ማስገባት ይችላሉ።
የምርጫ ማስገቢያ ድረ-ገጹ፦ student.ethernet.edu.et ነው።
- በሕክምና ምክንያት ልዩ ሁኔታ ያላቸው፣
- የአካል ጉዳተኛ የሆኑ፣
- ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች
- ከ6 ወር በታች ሕፃን የሚያጠቡ እናቶች ተገቢውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
#MoE
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ውድ የፋልከን አካዳሚ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን፣ ሰራተኞች እና ምሩቃን፣
በታላቅ ደስታና ኩራት የምናበስራችሁ ዜና አለን።
ፋልከን አካዳሚ ለኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኦሎምፒያድ (IOAI 2026) ይፋዊ የሀገር ወኪል (Accredited Country Representative) በመሆን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ወደ አስታና፣ ካዛክስታን ልኳል።
ይህ ለፋልከን አካዳሚ ታሪካዊ ክንውን ሲሆን፣ የትምህርት ቤታችን ራዕይ የሆነውን ዓለም አቀፍ ብቃት፣ ፈጠራ እና የላቀ ውጤት በተግባር ያሳየ ኩራት ነው።
በዚህ አጋጣሚ በቡድኑ ውስጥ የተካተቱትን ተማሪዎቻችንን እና የቡድን መሪውን ከልብ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ መወከላችሁ ለሁላችንም ታላቅ ኩራት ነው።
እንዲሁም ለወላጆች፣ ለመምህራን፣ ለአሰልጣኞች፣ ለሁሉም የፋልከን አካዳሚ ማህበረሰብ እና ይህ ስኬት እንዲመዘገብ ለረዱ ሁሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
ይህ ስኬት የፋልከን አካዳሚ ተማሪዎች በትጋት፣ በእውቀት፣ በሥነ-ምግባር እና በፈጠራ ከሠሩ በዓለም መድረክ ላይ መወዳደር እንደሚችሉ የሚያረጋግጥ ትልቅ መልዕክት ነው።
ስለዚህ ሁሉንም የፋልከን አካዳሚ ተማሪዎች ይህን ስኬት እንደ መነሻ በመውሰድ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በሂሳብ፣ በፕሮግራሚንግ እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መስኮች ራሳችሁን በትጋት እንድታዘጋጁ እናበረታታችኋለን። በቀጣይ ዓመታት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን የምትወክሉት ከእናንተ መካከል ይሆናሉ።
መላው የፋልከን አካዳሚ ማህበረሰብ ለቡድናችን መልካም ዕድል እንዲመኝ እና በጸሎትና በሞራል ድጋፍ እንዲያበረታታቸው እንጠይቃለን።
መልካም ዕድል ለቡድን ኢትዮጵያ!
መልካም ዕድል ለፋልኮን አካዳሚ!
የፋልከን አካዳሚ – ለዓለም የሚወዳደር ትውልድ እያፈራ ነው!
የ12ኛ ክፍል የምርቃት ፕሮግራምን በተመለከተ አስቀድመን መረጃ የሰጠን መሆኑ ይታወቃል:: ስለሆነም በፕሮግራሙ ላይ የመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች በቀሩት ጥቂት ቦታዎች የምናስተናግደው እስከ ዓርብ(17/11/18) ድረስ ብቻ መሆኑን እየገለፅን ከተገለፀው ቀን ውጭ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።
ትም/ቤቱ
4ኛ እና 5ኛ ዙር ማ/ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ በ04/11/18 3:30 ላይ ከ1-6ኛ ግቢ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ትም/ቤቱ
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
ጉዳዩ:- የምርቃትፕሮግራምን ይመለከታል
የዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል የምርቃት ፕሮግራም ሐምሌ 26/2018ዓ.ም በ Friendship hotel ለማድረግ ታቅዷል። በመሆኑም በዚህ ፕሮገራም ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች 3,300(ሶስት ሽህ ሶስት መቶ) ለወለጅ ደግሞ 3,000(ሶስት ሽህ ብር) በአቢሲኒያ ባንክ አካውንት ቁጥር 26 16 20 99 5(ተማሪ ምስጋና እና አቶ ኪዳኔ ብርሃኔ) እስከ 10/11/18 በተገለፀው አካውንት በማስገባት ደረሰኙን እንድትይዙ እናሳስባለን።
ትም/ቤቱ
ለ4ኛ እና 5ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች
የፈተና ገለፃ የሚሰጠው ዓርብ በ03/11/18 ይሆናል።ስለሆነም በዕለቱ ሁሉም የማ/ሳይንስ ተፈታኞች 3:00 ላይ ትም/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ:- ስትመጡ መደበኛውን የትም/ቤቱን የደንብ ልብስ መልበስ የሚጠበቅባችሁ ይሆናል።
ትም/ቤቱ
አስቸኳይ
የተፈታኝነት መለያ ካርድ(Admission card) ያልወሰዳችሁ የማ/ሳይንስ ተማሪዎች
1.Smon Atsebeha
2.Loza Mekuria
3.Melat Asrat
4.Natnael Addis
5. Ruth Asmerom
6. Ezana Daniel
7.Arsema Kidus
8. Dagmawi Samson
የሚጠበቅባችሁን ፈፅማችሁ ነገ ማክሰኞ እንድትወስዱ በጥብቅ እያሳሰብን በዚህ ምክንያት ለሚፈጠረው መጉላላት ሐላፊነት አንወስድም።
ትም/ቤቱ
