cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Yismake Worku

ስለ እኔ . . .

Show more
Advertising posts
22 131
Subscribers
-2824 hours
-1027 days
-27930 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

“አትደንግጡ፤ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል፥ በዚህ የለም፤ እነሆ እርሱን ያኖሩበት ስፍራ" ማርቆስ 16:6 እንኳን አደረሳችሁ!
Show all...
120👍 16
ፋሲካ MEGA GIVEAWAY 📍Dagi Laptop presents ! 🎉ፋሲካን ከእኛ ጋር ተደሰቱ፤ እናንተም እድላችሁን ሞክሩ ለጓደኞቻችሁም ላኩላቸው። 🎁ከ 15 አንድ አታጡም። 🚨የውድድሩን መስፈርት ሙሉ ለሙሉ እና በትክክል ያላሟሉ ተሳታፊዎችን እጣ ውስጥ አናካትትም። 👍መልካም እድል፤ 🎊መልካም በአል። የቲክቶክ ሊንኩ 👇👇👇👇 https://vm.tiktok.com/ZMMsxdDuQ
Show all...
👍 9🔥 3
የምስራች.. ስለ ቢዝነስ ማወቅና የቢዝነስ ሰው መሆን ለምትፈልጉ በሙሉ!! Stockmarket.et በቅርቡ በአዲስ የካፒታል ገበያ ኮርስ የሚመጣ ሲሆን ይህ ኮርስ ለሁሉም ሰው ቀላል በሆነ መንገድ የተዘጋጀ በአማርኛ የሚሰጥ ኮርስ ነው። የኮርሱም አላማ ለካፒታል ገበያ መሰረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖረን ማድረግና ለመጪው የካፒታል ገበያ ጅማሮ ዝግጅት መንገድ እንዲሆን ማድረግ ነው። ይህን ኮርስ በዌብሳይታቸው እንዲሁም በ Youtube ገፃቸው https://www.youtube.com/@stockmarket_et ማግኘት ይችላል። ቻናሉን ሰብስክራይብ አድርጋችሁ እንድትጠቀሙ ጋበዝኳችሁ! የቴሌግራም ገፃቸው ደግሞ ይሄ ነው 👉🏼 @stockmarket_eth
Show all...
👍 46👎 3 2
ነፍስ ይማር!
Show all...
😢 319👍 31 12👏 6
በአረብ ሀገራት የምትገኙ ወዳጆች እስኪ ይቺን ✅ በመንካት አሳውቁኝ። ላንድ ጥናት ፈልጌው ነው!
Show all...
👍 71 12🔥 3
በተሰጠህ መክሊት - በተሰጠህ መፍቻ ደጋግመህ ካልከፈትክ - ለድልህ መባቻ የዘንዶው ጭንቅላት - ካልተቀጠቀጠ ሲወፍር ይኖራል - አንተን እየዋጠ ዣንቶዣራ (ይስማዕከ ወርቁ) ለሚመለከተው በሙሉ . . .
Show all...
341👍 131👏 19🔥 7🍾 2
ልዑል ዶ/ር አስፋወሰን አስራተ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣ ረ/ፕሮፌሰር ዘላለም ጥላሁን፣ አርቲስት ሽመልስ አበራ፣ ጋዜጠኛ ብሩክ ይባስ፣ ...ክብርን ከእግዚአብሔር ውሰዱ። ከዚህ በኋላ ብሞትም አይቆጨኝም። እንደዛሬ ተከብሬ አላውቅም። እንደዛሬም የልቤን ተናግሬ አላውቅም። ለግፉዓን ምርቃት በእሳት ዳር በመሶብ የሙዚቃ ባንድ አጋፋሪነት የተሰበሰባችሁ ፣ ደራሲ ተርጓሚና ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ አርቲስት ሐብታሙ ማሞ (ጨርቦሌ)፣ ጋዜጠኛ አለማዬሁ ባዘዘው፣ ገጣሚ ምልዕልቲ ኪሮስ፣ ገጣሚ ፍሬዘር አድማሱ፣ ገጣሚ እንዳለ አለም፣ ገጣሚ ሳሙኤል ሰይፉ፣ እንዲሁም ያሬድ የእናንተ ግጥሞች እንደ እሳት ወላፈን ይፋጃሉ። ልቤን አሞቁኝ፣ በድንገተኛ ፈንጠዝያ አስፈነጣዛችሁኝ። እውነት ለመናገር እዚህ ጀርመን ሀገር ሆኜ ጋሽ ነቢይ መኮንን አገኘዋለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም። ታታሪዋ ሳሮን አገናኘችኝ። እንደዚህ አልጠበቅኩም ነበር። ሰርፕራይዝ አደረጋችሁኝ። ምን ማለት እችላለሁ? ቪዲዮውን ሳየው ደንግጫለሁ። አልቅሻለሁ። እኔን እንዳከበራችሁኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ። እሳቱን ጋሽ ነቢይ ግጥም እያነበበልን፣ ከእናንተ ጋር አብሬ እንድሞቅ እግዚአብሔር ያድለኝ። አርቲስት አልማዝ ልመንህና እህቴ ሳሮን የእናንተ ለብቻው ነው። የዜማ ባንድ አባላት ሁላችሁም ክብርና ሞገስን ከአምላክ ውሰዱ። የግፉዓን መጻህፍትን ለመመረቅ የመጣችሁ በሙሉ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ሁላችሁም እኔን እንዳከበራችሁኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ። አባቴን አልበላም ብዬ ነው እንጂ ግፉዓንን በኬክ መልኩ ወጠወጥነው። የታባቱ! ግፍ በኢትዮጵያችን ተወግዶ ሁላችንም ለመሰባሰብ ያብቃን። አሜን በሉ የልጅ ምርቃት ይደርሳል።
Show all...
ልደቴን በማስመልከት በውስጥ መስመር ብዙዎቻችሁ አበባ ልካችሁልኛል:: እጅግ በጣም አመሰግናለሁ:: ደስታዬ ግን ሙሉ አይደለም:: ምክንያቱም ወገኖቼ በሙሉ በማንነታቸው ምክንያት እስር ቤት ውስጥ ናቸው:: ባለፈው ትግራዮች ሲታሰሩ በሬን አንኳኩተው መታወቂያ ጠየቁኝ። እኔም ሰጠኋቸው። ውጣ አሉኝ። ለአምስት ቀናት አሰሩኝ። አንድ የሚያውቀኝ ፖሊስ መጣና "አንተ ትግሬ ነህ እንዴ?" አለኝ። "ለምን ፍርድ ቤት አታቆሙኝም። ያኔ የእኔን ማንነት ታውቁት ነበረ። ለማንኛውም ከተገፉት ወገን ነኝ" አልኩት። "ኧረ ይሄ ሰውዬ አማራ ነው" አለ እየጮኸ። "እንዴውም ደራሲ ነው... የዴርቶጋዳ ደራሲ... የክቡር ድንጋይ ደራሲ..." እንዲያ ሲል ሁሉም ታሳሪ ወደ እኔ አፈጠጠ። ይህን ብሎ ወደ ቢሮ ገባ። ትንሽ ቆይቶ አለቃቸው መጣ። "ሚን ማረጋገጫ አለህ ደራሲ ለመሆንህ?" አለኝ። በሸቅሁ። ዝም አልኩት። ስልኬን አስቀድመው ቀምተውኝ ነበር። እኔ ግን ሁሉንም በ Data የሚሰሩ ነገሮችን በፍጥነት አጥፍቼ ነበር የሰጠኋቸው። ፌስ ቡክ የለ ኢሜል የለ። ተጭናችሁ ማጥፋት ነው። አለቀ። እንዴውም ሰልፉ ብዙ ስለነበር ከፊቴና ከኋላዬ ያሉትን ሰዎች በሹክሹክታ ነግሪአቸው ስልካቸውን እያቀበሉኝ በData የሚሰሩ ነገሮችን አጥፍቼላቸዋለሁ። ከዛም አለቃቸው ይቅርታ ጠይቆ ሊፈታኝ መጣ። ከመፈታቴ አስቀድሞ ሁሉም እስረኞች ወደ እኔ ቁልጭ ቁልጭ ማለት ቀጠሉ። "እየመጣሁ እጠይቃችኋለሁ። የእኔ ተራ እስከ ሚደርስ ድረስ። በኋላ ግን እነርሱ ነው የሚያፍሩት። በእነርሱ ላይ ግን ቂም እንዳትይዙ" ብዬ ወጣሁ። እቅዳቸው ገብቶኝ ከሀገር ባልወጣ ኖሮ እስካሁን ይገሉኝ፣ ወይም ደግሞ ያስሩኝ ነበር። ቀድሞ በስሜ አሁን በማንነቴ። ለታሰሩትም ሆነ በጦርነት ላሉት የአማራ ህዝብ ለኢትዮጵያ እየታገላችሁ ነውና የእናንተ መታሰርና መፋለም ለኢትዮጵያ ቤዛ ነው። በትንሣኤው እንገናኝ። ድል ለፋኖ!
Show all...
👍 373 61🥰 21😢 9🔥 7👎 4
11👍 6
"ዛሬ ልደቴ ነው🎂 ፣ ነገም ልደቴ ነው፣ ትናንትም ልደቴ ነበር!" የወንድ ምጥ ይስማዕከ ወርቁ መልካም ልደት ለእኔ🎂 እንኳን ለ2016 ዓ.ም አደረሳችሁ። ዘመኑ እንዳለፈው ዘመን አይሁን።
Show all...
👍 128 41🍾 12👎 1