የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
前往频道在 Telegram
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
显示更多📈 Telegram 频道 የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC 的分析概览
频道 የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 242 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 8 177,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 962 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 242 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 1 089,过去 24 小时变化为 5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 15.01%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.54% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 687 次浏览,首日通常累积 1 072 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 12。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።
"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
11 242
订阅者
+524 小时
+1467 天
+1 08930 天
帖子存档
ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የተላለፈ አስቸኳይ የጸሎት ጥሪ!
"መከራ በሚደርስብህ ቀን ጥራኝ፤ እኔም አድንሃለሁ ፤ አንተም ታከብረኛለህ።" (መዝሙር 50:15)
በደቡብ አፍሪካ ለሚኖሩ ውድ ወገኖቻችን በምድሪቱ ላይ ሰላም ይሆን ዘንድ ካውንስሉ በሀገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ወንጌላውያን አማኞችን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ፊት እንዲማልዱ ጥሪውን ያቀርባል።
የምንጸልይ፣ የምንተባበር እና እርስ በእርስ የምንደጋገፍ ክርስቲያኖች እንደመሆናችን፣ ይህንን መልእክት ለሌሎች በማጋራት (Share በማድረግ) ለጸሎት ጥሪው እንዲቀላቀሉ አድርጉ።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
+1
የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ከስደተኞች መውጫ ቀነ-ገደብ በፊት ማስጠንቀቂያ ሰጡ
የስደተኞች መውጫ ቀነ-ገደብ ከመድረሱ በፊት በደቡብ አፍሪካ የፀረ-ስደተኛ ተቃውሞዎች ተከትሎ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተቃዋሚዎች ከዛቻና ከሃይል ተግባር እንዲቆጠቡ ያሳሰቡ ሲሆን፣ ህጋዊ ስደተኞች በህግ የመጠበቅ መብት እንዳላቸው አስታውሰዋል።
በደርባን የሚገኙ ጊዜያዊ የካምፕ ድንኳኖች እየፈረሱ ሲሆን፣ በርካታ ስደተኞች በሰነድ እጥረት፣ በመገለልና በስድብ ምክንያት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እየተገደዱ ነው።
ለማክሰኞ በተፈቀዱት ሰልፎች ላይ ፖሊስ ባህላዊ የጦር መሳሪያዎችን መያዝ የከለከለ ሲሆን ባህላዊ መሣሪያዎችን በሚይዙት የዙሉ ብሔረሰብ አባላትና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት ሊፈጥር እንደሚችል ተሰግቷል።
በዚህ ዓመት ከተቀሰቀሰው ተቃውሞ ወዲህ ከ12,000 በላይ ስደተኞች የተባረሩ ሲሆን፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ዜጎቻቸውን እየመለሱ ነው። በሀገሪቱ ሥር የሰደደው የውጭ ዜጎች ጥላቻ (Xenophobia) በዚህ ዓመት የሁለት ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል።
መረጃው የቢቢሲ ነው
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
+7
ቪዥን ኢንተርናሽናልዩኒቨርሲቲ
በዘንድሮውም አመት በቢኤ ድግሪ፣ በማስተርስና በፒኤች ዲ በጣቃላይ 153 ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ቪዥን ኢንተርናሽናል ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች አሰልጥኖ ያዘጋጃቸውን የ2018 ዓ.ም. ተማሪዎቹን ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በልዩ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። በዚህ ደማቅ የምረቃ በዓል ላይ የተመራቂ ቤተሰቦች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱ የክብር እንግዳ ሆነው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት ቄስ ደረጄ ጀምበሩ በምረቃቱ ላይ በመገኘት
እንኳን ደስ አላችሁ' በማለት፣ ከተማረና ዕውቀት ካለው የሰው ኃይል ጋር አብሮ መስራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ቤተ ክርስቲያንም የወንጌል አማኝ ለሆኑት ወገኖች በሙሉ፦ “ይህ ጊዜ ወንጌልን የምንሰብክበትና የምንሠራበት ወቅት ነው። ለእዚህም እግዚአብሔር አዘጋጅቷችኋል፤ ስለዚህ በትጋት ልታገለግሉ ይገባል”የሚል መልእክት አስተላልፌዋለሁ።
በመጨረሻም ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሜደሊያና የደረጃ ሽልማት ያተበረከተ ሲሆን፣ የምረቃው ሥነ-ሥርዓት በጸሎትና በምስጋና ተጠናቋል
+4
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶክተር ጌትነት ለማ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ባደረጉት ጉብኝት ተቋሙ የደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ እጅግ አስደናቂ መሆኑን ገለጹ።
ጠቅላይ ጸሐፊው በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት፣ ወደ ተቋሙ የመጡት ልምድ ለመውሰድና ሙያ ለመቅሰም ቢሆንም፣ በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ስራዎች ግን የሚበረታቱ ሆነው አግኝተዋቸዋል። በዕለቱ በነበራቸው ቆይታ በግብርና እና በተለያዩ ዘርፎች የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መመልከታቸውንም አብራርተዋል።
ካውንስሉ በቴክኖሎጂ ታግዞ አገልግሎቱን ይበልጥ ለማቅለል ማቀዱን የገለጹት ፓስተር ዶክተር ጌትነት፣ "ከካውንስል አንጻር ብዙ ሥራዎችን እንጠብቃለን" ብለዋል። ወደፊት ማገልገል የሚገባቸውን ሥራዎች ከተቋሙ ባለሙያዎች ጋር በመነጋገርና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም፣ በካውንስሉ አገልግሎት የምወሰዱ ዜጎች በቀላሉ መስተናገድ የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
ለኢቫንጄሊካል ዜና:-ቤተልሔም ደረጀ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
"በሌሎች ሀገራት ያየናቸውን አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ በማየታችን ደስ ብሎናል" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
+9
"በሌሎች ሀገራት ያየናቸውን አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ በማየታችን ደስ ብሎናል" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ
ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ዋና መስሪያ ቤት የተውጣጡ አመራር እና ሰራተኞች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኝተዋል።
የካውንስሉ ዋና ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ ቀደም ሲል በሌሎች ሀገራት ያዩዋቸውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ ውስጥ በማየታቸው ከፍተኛ ደስታ ተሰምቷቸዋል።
ፓስተሩ አክለውም ኢንስቲትዩቱ ለተለያዩ ተቋማትና ዘርፎች እያበረከተ ያለውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ስራዎች መመልከታቸውን ገልጸው፤ በካውንስሉ ስር አገልግሎት የሚያገኙ ተቋማት ፈጣንና የተሳለጠ አሰራር እንዲኖራቸው ከኢንስቲትዩቱ ጋር በጋራ በመስራት ምቹ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
በጉብኝት መርሃ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የዋና የዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊና የቴክኖሎጂ አማካሪ ሻምበል ይልማ (ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች እያከናወናቸው ያሉትን ስራዎች በተመለከተ ለጎብኝዎቹ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
"ወንጌልን ለመስበክ ለሚሰማራ ማንኛውም አካል ልዩ ፈቃድ አያስፈልገውም፤ ይሁን እንጂ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶችና አደጋዎች በሙሉ አስቀድሞ በመገምገምና በዝግጁነት መንፈስ መንቀሳቀስ ይኖርበታል፡፡ በአንጻሩ፣ ህግን በመጣስና ባልተፈቀዱ ቦታዎች ላይ ወንጌልን በመስበክ ለሁከትና ለግጭት ምንጭ መሆን አይገባም፤ ምክንያቱም የወንጌል መሰረታዊ ዓላማና መልዕክት ሰላም ብቻ ነው፡፡ 'አትስበኩ' የሚል የህግ እገዳ ቢጣል እንኳ፣ ወንጌልን የመስበክ ተልዕኳችንን ከቶ አናቋርጥም፡፡ ወንጌልን የማትሰብክ ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን የሚል ስም ሊኖራት አይችልም!!"
ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ
በወንጌል አላፍርም በወንጌል
ያድናል ብዬ እናገራለሁ
ገጠር ከተማ እሰብከዋለሁ
እኔስ በወንጌል እንዴት አፍራለሁ
ዕድሜ ዘሜነን እናገራለሁ
ወንጌል ያሸንፋል
ወንጌል ይታደጋል
ወንጌል ሰው ያደርጋል
ወንጌል ይለውጣል
ወንጌልን ይዞ የምን መፍራት
ተናገር እንጂ ላልሰሙት
ወንጌልን ይዞ የለም ወደ ኋላ
መሄድ እንጂ ከኢየሱስ ጋራ
የምስራቹን እየስበከ በሽተኞችን እየሰበከ
ኢየሱስ ሰጥቶን ሄዱዋል አደራ
ተነስተን ዛሬ ወንጌል እንስራ
በወንጌል አላፍርም...........
ዓለም በልጁ ይጠቀለላል
በእርሱ የሚያምን ከፍርዱ ይድናል
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት 4 ዓመታት ከ200 ሺህ በላይ ዜጎችን በማሳተፍ የለያቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አደረገ
*
ዛሬ ይፋ በተደረገው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስብሰባ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት ቄስ ደረጄ ጀምበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ፓስተር ታሪኩ ብርሀኑ እና የካውንስሉ ጠቅላይ ጸሀፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ ይገኙበታል::
የሀገራዊ ምክክር መድረክ ለቀጣይ ውይይቶች መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎቹን ይፋ ማድረጉ ተገለጸ። በዚሁ መሠረት በቁጥር አራት ላይ የሰፈረውና ዋነኛው የአጀንዳ ክፍል በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር መሆኑ ታውቋል።
በዚህ “የሃይማኖት ጉዳዮች” አጀንዳ ስር አራት ዋና ዋና ነጥቦች ለውይይት የቀረቡ ሲሆን፣ እነሱም፦
በሴኩላሪዝም (የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት) እና በሃይማኖት መካከል ጤናማ ሚዛንን መጠበቅ፣ የሃይማኖት ነፃነት እና ገደቦቹ፣ አነስተኛ ተከታይ ያላቸው የሃይማኖት ተቋማት ጥበቃ፣ እንዲሁም ከባህል እና ከሃይማኖታዊ እሴቶች ጋር የሚጋጩ ድርጊቶች የሚሉት ናቸው።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
"ወንጌልን ለመስበክ ለሚሰማራ ማንኛውም አካል ልዩ ፈቃድ አያስፈልገውም፤ ይሁን እንጂ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶችና አደጋዎች በሙሉ አስቀድሞ በመገምገምና በዝግጁነት መንፈስ መንቀሳቀስ ይኖርበታል፡፡ በአንጻሩ፣ ህግን በመጣስና ባልተፈቀዱ ቦታዎች ላይ ወንጌልን በመስበክ ለሁከትና ለግጭት ምንጭ መሆን አይገባም፤ ምክንያቱም የወንጌል መሰረታዊ ዓላማና መልዕክት ሰላም ብቻ ነው፡፡ 'አትስበኩ' የሚል የህግ እገዳ ቢጣል እንኳ፣ ወንጌልን የመስበክ ተልዕኳችንን ከቶ አናቋርጥም፡፡ ወንጌልን የማትሰብክ ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን የሚል ስም ሊኖራት አይችልም!!"
ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
+3
🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄ ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል
በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) "ፕሮፌት ፊቃዱ" በሚል ስም የሚንቀሳቀስ ግለሰብ የካውንስሉን እና የአባል አብያተ ክርስቲያናትን ስም በመጥቀስ ፍጹም ሀሰተኛ መረጃ እያሰራጨ ይገኛል።
⚠️ ሀሰተኛው ወሬ ምንድን ነው?
"ከጀርመን አብያተ ክርስቲያናት ጋር ስምምነት ተደርጓል" የሚል ማጭበርበሪያ።
"ወንጌል አማኞችን ለትምህርት ወደ ጀርመን እንልካለን" የሚል የሀሰት ተስፋ።
"የጉዞ እና የትምህርት ወጪው በሌሎች አካላት ይሸፈናል" የሚል ማታለያ።
"ከመማር በኋላ በአውሮፓ የአገልግሎት እድል ይመቻቻል" የሚል የቪዛ ማጭበርበር።
📢 ለቅዱሳን እና ለህዝበ ክርስቲያኑ የተላለፈ ጥሪ
ካውንስሉ ይህ መረጃ ሙሉ በሙሉ ሀሰት መሆኑን እያረጋገጠ፣ ምዕመናን ራሳቸውን ከዚህ ማጭበርበር እንዲጠብቁ በጥብቅ ያሳስባል።
🤝 ምን ማድረግ ይኖርብናል?
ከመመዝገብ ይቆጠቡ፦ በግለሰቡ አማካኝነት በሚደረጉ ማናቸውም የቪዛ እና የትምህርት ምዝገባዎች ላይ አይሳተፉ።
መረጃዎችን ያጋልጡ፦ በአካባቢዎ መሰል የሀሰት ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ሰዎችን ሲመለከቱ ለህግ አካላት ጥቆማ ይስጡ።
ለካውንስሉ ያሳውቁ፦ መረጃ ካለዎት በካውንስሉ ዋና ጽሕፈት ቤት በአካል በመቅረብ ለህግ ክፍሉ ጥቆማ ይስጡ።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
Evangelical Media/Council
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
+4
በእምነት ተቋም ላይ ዝርፊያና ውድመት የፈጸሙ 21 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3፣ አያት 49 ቁጥር-2 አካባቢ በሚገኝ "የመንግስተ ሰማይ እንደራሴዎች ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን" ላይ በቡድን በመደራጀት ዝርፊያና ውድመት የፈጸሙ 21 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ፣ የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች የሆኑ 21 ግለሰቦች "ቦታው የእኛ ነው" በሚል ሰበብ በኃይል ወደ ቤተክርስቲያኑ ግቢ በመግባት የቤተክርስቲያኑን ንብረቶች አውድመዋል።
በዚህ ድርጊታቸውም 10,132,000 (አስር ሚሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ሁለት ሺህ) ብር የሚገመት ንብረት መዘረፉንና መውደሙን ፖሊስ ገልጿል።
ወንጀሉ እንደተፈጸመ መረጃው የደረሰው የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፣ ተጠርጣሪዎቹ ከአካባቢው ቢሰወሩም ባደረገው ክትትል በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ አስታውቋል። ፖሊስ አክሎም በወንጀሉ ተሳታፊ የሆኑ ግለሰቦች ላይ ክስ እንደሚመሰርት ገልጿል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ፤ መሰል ድርጊቶች የኃይማኖት ግጭት የሚቀሰቅሱና ተከባብሮ የኖረውን ህዝብ በጥርጣሬ እንዲታይ የሚያደርጉ በመሆናቸው ሁሉም ወገን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።
ለኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
Evangelical Media/Council
#በኋላውም_ቀርባ_የልብሱን_ጫፍ_ዳሰሰች_የደምዋም_ፈሳሽ_በዚያን_ጊዜ_ቆመ።”
— ሉቃስ 8፥44
#ተስፋ_እምነት_እና_ፈውስ_በአንድ_መንገድ_ተገናኙ።
ቅዱሱ መፅሀፍ በዚህ ክፍል ብዙ የደከመችን ለድነቷ ጎንበስ ቀና ያለችን ለፈውሷ ብዙ የታመመችን ለመቆም የዘላችን ለመዳን የታመመችን በውስጧ ግን መውደቋ መዛሏ ህመሟ ተስፋን የማውጣት ጉልበት ያልነበረውም ብዙ ጊዜ ትሞክራለች ያለ ሟቋረጥ ተስፋ ታደርጋለች። ለፈውሷ ትክክለኛ ነው ብላ ያሰበችውን ሁሉ ሞክረዋለች አሁን ድኛለሁ መድሀኒት አግንቻለው ብላ የመዳኗን ተስፋ አግኝታ ወዲያው ጠፍቶባታል።
ይህች ሴት ናት ከተስፋዋ ጋር በእምነት የሰው ብዛትና ግፊት የደሟ መፍሰስ ሳያቆማት የልብሱን ጫፍ በመንካት ፈውሷን ያገኘችው። ተስፋና እምነት አካል የሚለብሱት ጌታን በማግኘታችን ነው።
እንዴት ቢባል የእኛን ትጋት የኛን አለመታከት እንዲሁም ተስፋችንና እምነታችንን አካል የሚያለብሰው ፈውስ ከሚሰጠው ሳይሆን እርሱ እራሱ ፈውስ ከሆነው ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር የተገናኘን ጊዜ ነው። ፍቃዱ ውስጥ መመላስ ነው እርሱን ማግኘት፣እርሱን በመጨረሻ ፍላጎታችን መሻት ነው እርሱን ማግኘት፣ከከበበን ወጥተን አይናችን በእርሱ ላይ ሲሆን ነው እርሱን ማግኘት እና አማራጫችንም ምርጫችንም እርሱ ሲሆን ነው እርሱን ማግኘት። ያን ጊዜ ነው የችግራችን ማብቅያ፣ያን ጊዜ ነው የተስፋችንን አካል በግልጥ የምናየው። ከእምነታችን ጋር የምንጨባበጠው።
#written_by_@Teshaletaye
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
Evangelical Media/Council
"የቆርቆሮ አጥር በማፍረስ የሚቆም ወንጌል የለም" — ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ
አዲስ አበባ — የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ፣ ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በአካል በመገኘት ጉዳት የደረሰባትን ቤተ ክርስቲያን ጎብኝተዋል። ጠቅላይ ጸሐፊው በጉብኝታቸው ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት "የቆርቆሮ አጥር በማፍረስ የሚቆም ወንጌል የለም" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ በስፍራው ከመገኘታቸውም በላይ፣ ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ መዋቅሮች ጋር በጉዳዩ ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር እና የጸጥታ መዋቅሮች ይህንን ጥፋት የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ስር አውለው ምርመራ እያካሄዱ መሆናቸው ተገልጿል። ላጠፉት ጥፋትም አስተማሪ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ማጣራት እየተደረገ በመሆኑ፣ ጠቅላይ ጸሐፊው ለአስተዳደሩና ለጸጥታ አካላቱ ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በተጨማሪም፦ለአጥፊዎች የተላለፈ መልዕክት: የክፍለ ከተማውን ሰላማዊ ማህበረሰብ ገጽታ ለማበላሸት የሚለፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።
ችግሩ በተፈጠረበት ወቅት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እና መንፈሳዊ ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ጉዳዩን ለሕግ ላቀረቡት የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ምስጋናቸውን ለግሰዋል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የሕግ የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ።
የሚመለከተው የመንግሥት አካል ሕጋዊ እርምጃ ወስዶ ለሕዝብ ማሳወቅ ይኖርበታል።
ይህንን አመጽ ያስተባበሩና በቀጥታ የተሳለፉ አካላት በወንጀል ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንዲሁም ለወደመው ንብረት ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
የሕግ የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ።
የሚመለከተው የመንግሥት አካል ሕጋዊ እርምጃ ወስዶ ለሕዝብ ማሳወቅ ይኖርበታል።
ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 አያት ቁጥር 2 ኮንድሚንየም
የሰላም ቤት ባለቤቶች ማህበር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ለወንጌል አማኝ እምነት ተከታዮች ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች በሕግ የራሷ ካርታና ሕጋዊ ፕላን እንዲሁም እንደማንኛውም ሕጋዊ ተቋም የሕግ ሰውነት ያላትን ቤተ እምነት በማፈራረስ በአከባቢያችን ወንጌል አማኞች ሊኖሩ አይገባም በሚል ሰበብ በአንድ ቤተ እምነት ላይ የፈጸሙትን ጥቃት ካውንክሉ በቀላሉ የማይመለከተው መሆኑን ለሚመለከተው አካል እያሳወቅን ይህንን አመጽ ያስተባበሩና በቀጥታ የተሳለፉ አካላት በወንጀል ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንዲሁም ለወደመው ንብረት ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
