የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
前往频道在 Telegram
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
显示更多📈 Telegram 频道 የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC 的分析概览
频道 የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 934 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 7 407,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 823 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 934 名订阅者。
根据 16 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 188,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.28%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.47% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 540 次浏览,首日通常累积 892 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።
"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
11 934
订阅者
+2324 小时
+537 天
+18830 天
帖子存档
+7
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች ለአዲስ አመት ከ600,000 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለማህበረሰቡ የምግብ ድጋፍ አደረጉ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 አጥቢያ እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ በአካባቢያቸው ለሚገኙ 432 የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ አድርገዋል።
የሆለታ 44 አጥቢያ ለ226 አቅመ ደካሞችና ድሆች 295,500.00 ብር ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው 10 ኪ.ግ ዱቄትና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ ስታደርግ እንዲሁም የሆለታ ጭሪ አጥቢያ ለ206 ችግረኞች 307,193.00 ብር ወጪ በማድረግ ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጋለች።
በተጨማሪም የሆለታ 44 አጥቢያ በኤጀሬ ማረሚያ ቤት ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ሦስት ኩንታል አልባሳት እና የበዓል መዋያ የሚሆን የ18,000 ብር ድጋፍ ስትሰጥ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተካሄደው የወንጌል ሥርጭት 10 የሕግ ታራሚዎች ጌታ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል።
መረጃው የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲየን ነው
የአሜን ቲቪ ሥራ አስኪያጅና አገልጋይ ሰብሌ በቀለ
ሰው ሁሉ ስለ ነገ ሲያስብና ሲጨነቅ ይፈራል እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።(ትንቢተ ኤርምያስ 29:11)
ይህን የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል በመጥቀስ እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁበማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል
Wisdom Intergration ከ Gaps International Ministry ጋር በመተባበር የአይምሮ ውስንነት ካላቸው ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ጋር የአዲስ አመት ልዩ የበዓል ዝግጅት በሳር ቤት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ያከናወነ ሲሆን በዕለቱም ከልጆቹ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር የህብረት ፣ የጨዋታ እና ማዕድ በጋራ የመካፈል ጊዜ የነበረ ሲሆን ለአዲስ አመት በዓል የሚሆን የልጆች መጫወቻዎች ፣ ዘይትና ዱቄት፣ ህይወታቸውን እንዲመሩበት ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
የዕለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የWisdom የቦርድ አባል እህት ማርታ ፈለቀ ሁሉም ሰው ከዊዝደም ኢንቲግሬሽን ጋር በመተባበር በሙያ፣ በገንዘብ እና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብረው እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።
የዊዝደም ኢንቲግሬሽን መስራች የሆኑት ወንድም ዳንኤል እና ባለቤታቸው የኔነሽ ለልጆቹ ፣ ለወላጆች እና በዕለቱ ለተገኙ ታዳሚዎች ሁሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እና ለዊዝደም ኢንቲግሬሽን አገልግሎት መመስረት ምክንያት ስለሆናቸው ስለ ልጃቸው ካሌብ ዳንኤል እና ባጋጠመው የዓይምሮ ውስንነት ምክንያት ይህ አገልግሎት ለመመስረት ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
የዕለቱ ተጋባዥ ዘማሪት የነበረችው ዘማሪት ሩት እጅግ በሚያጽናኑ ዝማሬዎች ጉባኤውን አገልግላለች።
የጋፕስ ዓለም አቀፍ አገልግሎት መስራች እና መሪ በሆኑት መጋቢ ዳንኤል ዋለልኝ ከዮሐንስ 4 ጠቅሰው በአይሑድ ማህበረሰብ ስለተገለሉት ሳምራውያን እና በሳምራውያኑ ስለተገለለችው ሳምራዊቷ ሴት ፣ እሷን ስለቀረባት እና ስለተቀበላት እየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል አካፍለዋል።
+8
የወጣቶች የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴ በሆሳዕና
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች፣ በከተማዋ ጎዳናዎችና አደባባዮች የወንጌል ስርጭት አካሂደዋል።
ወጣቶቹ ይህን የወንጌል ስርጭት ያካሄዱት ከክረምት የወጣቶች ሳምንት የስልጠናና የትምህርት መርሐ ግብር በኋላ ሲሆን፣ በስርጭቱም ከሆሳዕና ከተማና አካባቢዋ የተውጣጡ ወጣቶች፣ ልጆች፣ መሪዎች፣ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ተሳትፈዋል።
በእንቅስቃሴውም የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ለተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍሎች ተሰብኳል፤ በርካታ ሰዎችም የወንጌሉን መልዕክት እንዲሰሙ ዕድል ተፈጥሯል። የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ አዴሣም በወንጌል ስርጭቱ ተሳትፈው፣ በከተማዋ አደባባይ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል።
ቄስ ወንድማገኝ በተጨማሪም ወጣቶቹ በወንጌል ስርጭት እያደረጉ ላሉት አገልግሎት አበረታተዋል፤ ወንጌልን በድፍረትና በትጋት መመስከራቸውን እንዲቀጥሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ነሐሴ ወር የወንጌል ስርጭትና የምስክርነት ወር በመሆኑ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች በወንጌል ምስክርነት አገልግሎት በስፋት እየተሳተፉ ነው።
የሆሳዕና ወጣቶች ያካሄዱት ይህ የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴም፣ የወጣቶችን ተሳትፎ በማጠናከር የክርስቶስን ወንጌል ለሕዝብ ለማድረስ የተደረገ አገልግሎት ሆኗል።
EECMY Youth Ministry
