የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
前往频道在 Telegram
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
显示更多📈 Telegram 频道 የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC 的分析概览
频道 የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 811 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 7 591,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 855 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 811 名订阅者。
根据 25 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 263,过去 24 小时变化为 3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.31%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.60% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 044 次浏览,首日通常累积 1 015 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።
"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።”
凭借高频更新(最新数据采集于 26 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
11 811
订阅者
+324 小时
+587 天
+26330 天
帖子存档
ፈጣሪ ሃይማኖት መራጭ አይደለም ወንጌላዊ ሁሴን መሀመድ
https://youtu.be/HRgsm4hhdcM?si=SSKxme0U1qcorc6r
መስጅድ ውስጥ ልሳን ተናገርኩ ወንጌላዊ ሁሴን መሀመድ
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ሙሉ ቪዲዮውን ይመልከቱ
https://youtu.be/HRgsm4hhdcM
🇪🇹 ምስጋና ለሁሉም!
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ46 ቀናት ሲያከናውነው የቆየው የምክክር መድረክ በሰላም በመጠናቀቁ ደስታችንንና ምስጋናችንን እንገልጻለን።
በዚህ ረጅምና አስፈላጊ የምክክር ሂደት በኃላፊነት፣ በትዕግሥትና በመከባበር ለተሳተፉ ተሳታፊዎች፣ ለኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች፣ ውይይቱን በትጋት ሲያስተባብሩ ለነበሩ ባለሙያዎችና ሠራተኞች ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
በተጨማሪም ተሳታፊዎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡና መድረኩ በሰላም እንዲካሄድ፣ ከፈጣሪ ጥበቃ በታች ቀንና ሌሊት የደኅንነትና የሰላም ጥበቃ ሲያደርጉ ለነበሩ ሁሉ ልዩ ምስጋናችን ይድረስ።
ለመላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይህንን የምክክርና የሰላም ጉዞ በጋራ እንድንደግፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ልዩነቶቻችንን በውይይት እያቀራረብን፣ የሚያግባቡንን የጋራ እሴቶች እያጠናከርን፣ ለትውልድ ሰላማዊ፣ የተረጋጋችና የበለጸገች ኢትዮጵያን በጋራ እንገንባ።
ሰላም የሁላችንም ነው፤ ለሰላም መሥራትም የሁላችንም ኃላፊነት ነው! 🇪🇹
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለዜና ሽፋን መልአክት ለመላክ
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
+6
የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሏን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠች
የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ያከናወነችውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት የሚዘክር የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥታለች።
በዓሉ በ1ኛ ሳሙኤል 7፥12 “አቤንኤዘር” እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን፥ በበዓሉ ላይ በርካታ የምስጋና፣ የጸሎት ፕሮግራሞች እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
ይህ ታላቅ ክብረ በዓል ከነሐሴ 3 ቀን ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።
በ1948 ዓ.ም.“መሠረተ ሕይወት” በሚል ስያሜ ጉዞዋን የጀመረችው ይህች ታሪካዊት ቤተክርስቲያን፥ ባለፉት ዓመታት ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ለማድረስ ባደረገችው ጥረት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች ከ60 በላይ አዳዲስ አጥቢያዎችን በመትከል ረገድ ታላቅ ታሪክ መሥራቷ ተጠቅሷል።
ከመንፈሳዊ አገልግሎቷ ጎን ለጎን ማኅበረሰቡን የሚጠቅሙ በርካታ ማኅበራዊ ሥራዎችን ስታከናውን የቆየች ሲሆን ከምሥረታዋ ጋር ተያይዞ የተቋቋመው የመጀመሪያው የመሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን መሠረተ ትምህርት ቤት አሁንም ድረስ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በሥነ-ምግባር የታነጸ ዜጋ በማፍራት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
የቤተክርስቲያኗ መሪዎች እንደተናገሩት፤ ነሐሴ 23 በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ወንጌላውያን አማኞች በሙሉ የሚሳተፉበት ታላቅ የምስጋና እና ራዕይ የማጋራት መርሃ ግብር ይካሄዳል ብለዋል።
በተጨማሪም ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. የዝማሬ እና ወንጌል ማወጅ የእግር ጉዞ መርሃ ግብር ይከናወናል። ይህ ጉዞ ከቤተክርስቲያኑ ግቢ ተነስቶ በሞላ ማሩ እና በአብነት በበላ
+6
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እምነት ናት በማለት ተናገሩ።
ነሐሴ8 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛ የካውንስል ስብሰባ አካሄዷል። በስብሰባዉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ መልእክት ያስተላለፋ ሲሆን በመልክታቸዉም የመካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በረጅም የአገልግሎት ዘመኗ በአገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እምነት ናት። ለዛሬው ሁለንተናዊ እድገት የቀደሙ መሪዎች ያበረከቱት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነበር። ያሉት ጠቅላይ ፀሐፊዉ ዛሬም ቢሆን ከትውልድ፣ ከአገርና ከሁሉ በላይ ከእግዚአብሔር የተሰጣትን ታላቅ መለኮታዊ አደራ በታማኝነት መወጣት ይጠበቅባታል። ብለዋል የዛሬዎቹ መሪዎች ትላንትን በማስታወስ፣ ዛሬን በታማኝነት በማገልገል እና ነገን መሠረት በሚጥል ራዕይ በመመልከት ዋናውን ነገር ዋና አድርገው መቀጠል አለባቸውም በማለት አክለዋል።
ለኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነኢየሱስ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ሰጠች #ኢቫ_ዜና
https://youtu.be/4W8SEdsfGm4
ሁሉም ወንጌል አማኝ ሊያየው የሚገባ ድንቅ ፕሮግራም
ክርስትና ውርስ አይሆንም
በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ሚዲያ የቀረበ
በ Evangelical Media Council ዩቲዩብ ቻናል ላይ ያገኙታል
ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://youtu.be/YDH1EH4SnIY?si=8T3fqaIV_6xkF1mB
+8
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር በማኅበራዊ ሚዲያና ብሮድካስት አጠቃቀም ላይ ሥልጠና ሰጠ።
ይህ ሥልጠና የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም ከማኅበራዊ ሚዲያ እና ከብሮድካስት አገልግሎት ሥራዎች ጋር የተያያዘ ሲሆን፤ በካውንስሉ ሥር ለሚገኙ የወንጌል አማኞች ሚዲያዎች በሙሉ የተሰጠ ነው።
የፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አሰፋ መብራቱ እንደገለጹት ሥልጠናው የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃዎች ከሕግ አንጻር የሚያስከትሏቸውን ችግሮች ለማየት እና ለዚህም የመፍትሔ ሐሳብ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች እንዴት መከላከል እንደሚቻል ለመመልከት የተዘጋጀ መሆኑን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሕግ ክፍል ኃላፊ ወይዘሪት መንበረ አንድነት በበኩላቸው የወንጌላዊያን ሚዲያዎች ከሕግ አንጻር ምን ያህል ያውቃሉ? በሕጉስ መሠረት እየሠሩ ነው? የሚለውን ለማስገንዘብ ጭምር ሥልጠናው መዘጋጀቱን አንስተዋል።አክለወም ካውንስሉ በተጨማሪም ከሕግ አንጻር የተለያዩ ሥልጠናዎችን በቀጣይነት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ የሕግ ሥርጸትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት አካዳሚክ ዓቃቤ ሕግ አቶ ሙሴ ባዬ ሥልጠናውን የሰጡ ሲሆን፥ ከተሳታፊዎች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
በስልጠናው ላይ የተሳተፉት ሰልጣኞች በቆይታቸው እጅግ ጠቃሚ እና ጥሩ ጊዜ እንደነበራቸውም ገልጸዋል።ከዚህ ስልጠና የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት በስራቸው ላይ በተግባር እንደሚያውሉትና ውጤታማ እንደሚሆኑ ሙሉ እምነት እንዳላቸው አስታውቀዋል።
ለኢቫንጄሊካል ዜና ቤተልሔም ደረጀ
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ነሐሴን በጾምና በጸሎት የመሻር አገር አቀፍ ጥሪ አስተላለፈ #ኢቫ_ዜና@EGBCC
ነሐሴን በጾምና በጸሎት እንሻገር!
የአንድ ዓመት ጉዞ ሲጠናቀቅ፣ አዲስ ዓመትም ሲጀምር፤ በምስጋና ያለፈውን እናስብ፣ በጸሎት የሚመጣውን እንቀበል።
ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም — አገር አቀፍ የጾምና የጸሎት ወር!
ስለ ሀገራችን፣ ስለ ሕዝባችን፣ ስለ ትውልዳችንና ስለ ቤተ ክርስቲያን በአንድ ልብ እንጹም፤ እንጸልይ።
📖 “ በቸርነትህ ዓመቱን ታቀዳጃለህ .......” — መዝሙር 65፥11
+9
ኦርቶቶሜኦ የእውነትን ቃል በትክክል መክፈል የተሰኘውና በመጋቢ ቤዛዓለም በላይ የተዘጋጀው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ።
በመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት ፓስተር ጌታሁን ነሲቡ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን መጽሐፉ ለምእመናንና ለቤተክርስቲያን ያለውን ጠቀሜታ በመግለጽ የተሰማቸውን ታላቅ ደስታ አጋርተዋል።
በምረቃው ላይ የመጽሐፉን ይዘት አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡት የቋንቋ ጥናት ባለሙያው አቶ አሺኔ አስቴን በበኩላቸው መጽሐፉ የወቅቱን ፍላጎት ያገናዘበና እጅግ ጠቃሚ የሆነ ሥራ መሆኑን መስክረዋል።
በማቀጠልም ወንጌላው ዙርያ ሱማ የመጽሐፉን ዳሰሳ አቅርበዋል።
የመጽሐፍ ጸሐፊ መጋቢ ቤዛ ዓለም እንደተናገሩት ኦርቶቶሜኦ" የግሪክ ቃል ሲሆን "ኦርቶ" ማለት "በትክክል" ማለት ሲሆን"ቶሚሆ" ማለት ደግሞ "መቁረጥ" ከሚለው የግሪክ ቃል የተወሰደ መሆኑ ገልጿል።በዚህ ዘመን ያሉ አገልጋዮች መጽሐፍ ቅዱስን በራሳችን አውድና ለእኛ እንደሚመቸን እያፈታን ስለሆነ ለዚያ መፍትሔ ታስቦ የተጻፈ መሆኑን አክለው ተናግራዋል።
ለኢቫንጄሊካል ዜና ቤተልሔም ደረጀ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
Telegram | Facebook | Youtube | Tiktok | Website
+5
“ተስፋችን በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ ነው'' ቬኔዙዌላውያን
በቬኔዙዌላ ከ300 በላይ በሚሆኑ ከተሞች በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተሰብስበው ኢየሱስ ክርስቶስ በሀገራቸው ላይ ጌታ መሆኑን በይፋ ያወጁበት ታላቅ የጸሎትና የምስጋና መርሃ ግብር አካሄዱ።
"ቬኔዙዌላ የጸጋ ምድር" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ ዝግጅት አማኞች አደባባዮችንና ጎዳናዎችን በአምልኮ፣ በምስጋናና በጸሎት በመሙላት ለሀገራቸው ሰላም፣ አንድነት፣ ተስፋና ዘላቂ ለውጥ ተመኝተዋል።
ሀገሪቱ በፈታኝና እርግጠኝነት በጎደላቸው የችግር ጊዜያት ማለፏ የሚታወስ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የመጨረሻ ተስፋቸው በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አውጀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
Telegram | Facebook | Youtube | Tiktok | Website
+7
የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ሥነ መለኮት መምሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት ማስተባበሪያ ያዘጋጀው የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት መምህራንና የሥራ ተሳታፊዎች ስልጠና ተካሄደ፡፡
ሥልጠና ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሐዋሳ ሐይቅ ዳር ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገልጿል።
"ከሙያ አልባ መምህር ወደ መምህር አልባ ክፍል ወይስ የመምህርነት ሙያና የትምህርት ጥራት በኢትዮጵያ"በሚል ዋና ርዕስ በሚካሄደው ሥልጠና፣ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፣ በሥነ መለኮት ተቋማት የመምህራንና የአመራሮች ሚናን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሏል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከሐዋርያትና ከነቢያት አገልግሎት ጋር ተያይዞ ሊኖር የሚገባውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አቋም በስፋት ውይይት እንደሚካሄድበት ታውቋል።
መረጃውን በቤተክርስቲኒቱ አገኘነው፡፡
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
+8
በአምበሪቾ AIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ
በአምበሪቾ ዓለም አቀፍ የጸሎትና የወንጌል አገልግሎት (AIPM) የሚገነባው የAIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ (AIPM–GMU) የመሠረት ድንጋይ የማኖር ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
በሥነ ሥርዓቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አረጋ እሸቱ፣ እንዲሁም የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክብርት ወይዘሮ ውባየሁ በቀለ ተገኝተው የመሠረት ድንጋዩን አኑረዋል።
በመድረኩ የAIPM መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ደስታ ላንገና ጨምሮ የተገኙ እንግዶች ንግግር አድርገዋል። ተናጋሪዎቹ ተቋሙ እስካሁን በወንጌል፣ በጸሎት እና በማኅበረሰብ አገልግሎት ያከናወናቸውን ሥራዎች በማድነቅ፣ በማኅበረሰቡ ላይ ያሳደሩትን በጎ ተፅዕኖ አመስግነዋል።
እንዲሁም ይህ ዩኒቨርሲቲ የAIPM ብቻ ሳይሆን የመላው የከምባታ ሕዝብ ፕሮጀክት መሆኑን በመግለጽ፣ ሁሉም በትብብር እንዲደግፉት ጥሪ አቅርበዋል፤ መንግሥትም ለፕሮጀክቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
የAIPM መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ደስታ ላንገና በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ከሚሽን አገልግሎት ባሻገር በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽን፣ በሥነ ምግባር እና በሙያ ክህሎት የተበቁ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎችን ማፍራት ዋና ዓላማው መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በተቋሙ ውስጥ የእውቀት እና የሁለንተናዊ እድገት ትምህርት በትኩረት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
AIPM-Ambaricho International Prayer and Missions Movement
"ቤተክርስቲያን የሰውን ሁለንተና ማለትም መንፈሳዊና አካላዊ
ፍላጎቱን ማገልገል ይኖርበታል"
"Waldaan guutummaa namma(fooniifi hafuura namaa) tajaajiluu qabdii"
"The Church must serve the whole person - spiritual and physical needs."
ቄስ ጉዲና ቱምሳ
አስቸኳይ እና ወሳኝ ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል! ⚠️
በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) የሚሰራጭ አደገኛ የማጭበርበር መረጃ በመሆኑ ቅዱሳን ራሳችሁን ጠብቁ!
በቲክቶክ ስም ፕሮፌት ፊቃዱ፣ ዶክተር አቤል እና የወንጌላውያን የትምህርትና ልማት ማህበር በሚሉ ስሞች የሚንቀሳቀሱ አካላት ናቸው።የካውንስሉንና የአባል ቤተ እምነት ስም በመጥቀስ ከጀርመን አብያተ ክርስቲያናት ጋር ስምምነት አድርገናል ምዕመናንን ለትምህርት ወደ ጀርመን እንልካለን የሚል ነው።የትምህርት ወጪው ሙሉ በሙሉ እንደሚሸፈንና ከአውሮፓ ጉዞ በኋላ የአገልግሎት ዕድል እንደሚመቻች በማስመሰል ሰዎችን እያመዘገቡ ይገኛሉ።
ይህ መረጃ ሙሉ በሙሉ የሐሰት ነው። ካውንስሉ የፈረመው ምንም አይነት ስምምነት የለም! ብዙ ምዕመናን በዚህ ድርጊት እየተታለሉና እየተበዘበዙ በመሆኑ ሁላችሁም ከዚህ የሐሰት መረጃ ራሳችሁን እንድትጠብቁ እናሳስባለን።
ይህንን መረጃ ሼር በማድረግ ወንድም እህቶቻችንን ከማጭበርበር እንታደግ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
Telegram | Facebook | Youtube | Tiktok | Website
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
Telegram | Facebook | Youtube | Tiktok | Website
