es
Feedback
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

Ir al canal en Telegram

ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

El canal የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 242 suscriptores, ocupando la posición 8 177 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 962 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 242 suscriptores.

Según los últimos datos del 30 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 1 089, y en las últimas 24 horas de 5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 15.01%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.54% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 1 687 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 072 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 12.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

11 242
Suscriptores
+524 horas
+1467 días
+1 08930 días
Archivo de publicaciones
ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የተላለፈ አስቸኳይ የጸሎት ጥሪ! "መከራ በሚደርስብህ ቀን ጥራኝ፤ እኔም አድንሃለሁ ፤ አንተም ታከብረኛለህ።" (መዝሙር 50:15) በደቡብ አ
ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የተላለፈ አስቸኳይ የጸሎት ጥሪ! "መከራ በሚደርስብህ ቀን ጥራኝ፤ እኔም አድንሃለሁ ፤ አንተም ታከብረኛለህ።" (መዝሙር 50:15) በደቡብ አፍሪካ ለሚኖሩ ውድ ወገኖቻችን በምድሪቱ ላይ ሰላም ይሆን ዘንድ ካውንስሉ በሀገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ወንጌላውያን አማኞችን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ፊት እንዲማልዱ ጥሪውን ያቀርባል። የምንጸልይ፣ የምንተባበር እና እርስ በእርስ የምንደጋገፍ ክርስቲያኖች እንደመሆናችን፣ ይህንን መልእክት ለሌሎች በማጋራት (Share በማድረግ) ለጸሎት ጥሪው እንዲቀላቀሉ አድርጉ። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ከስደተኞች መውጫ ቀነ-ገደብ በፊት ማስጠንቀቂያ ሰጡ የስደተኞች መውጫ ቀነ-ገደብ ከመድረሱ በፊት በደቡብ አፍሪካ የፀረ-ስደተኛ ተቃውሞዎች ተከትሎ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ
+1
የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ከስደተኞች መውጫ ቀነ-ገደብ በፊት ማስጠንቀቂያ ሰጡ የስደተኞች መውጫ ቀነ-ገደብ ከመድረሱ በፊት በደቡብ አፍሪካ የፀረ-ስደተኛ ተቃውሞዎች ተከትሎ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተቃዋሚዎች ከዛቻና ከሃይል ተግባር እንዲቆጠቡ ያሳሰቡ ሲሆን፣ ህጋዊ ስደተኞች በህግ የመጠበቅ መብት እንዳላቸው አስታውሰዋል። በደርባን የሚገኙ ጊዜያዊ የካምፕ ድንኳኖች እየፈረሱ ሲሆን፣ በርካታ ስደተኞች በሰነድ እጥረት፣ በመገለልና በስድብ ምክንያት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እየተገደዱ ነው። ለማክሰኞ በተፈቀዱት ሰልፎች ላይ ፖሊስ ባህላዊ የጦር መሳሪያዎችን መያዝ የከለከለ ሲሆን ባህላዊ መሣሪያዎችን በሚይዙት የዙሉ ብሔረሰብ አባላትና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት ሊፈጥር እንደሚችል ተሰግቷል። በዚህ ዓመት ከተቀሰቀሰው ተቃውሞ ወዲህ ከ12,000 በላይ ስደተኞች የተባረሩ ሲሆን፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ዜጎቻቸውን እየመለሱ ነው። በሀገሪቱ ሥር የሰደደው የውጭ ዜጎች ጥላቻ (Xenophobia) በዚህ ዓመት የሁለት ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። መረጃው የቢቢሲ ነው የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

ቪዥን ኢንተርናሽናልዩኒቨርሲቲ በዘንድሮውም አመት በቢኤ ድግሪ፣ በማስተርስና በፒኤች ዲ በጣቃላይ 153 ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ። ቪዥን ኢንተርናሽናል ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች አሰ
+7
ቪዥን ኢንተርናሽናልዩኒቨርሲቲ በዘንድሮውም አመት በቢኤ ድግሪ፣ በማስተርስና በፒኤች ዲ በጣቃላይ 153  ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ። ቪዥን ኢንተርናሽናል ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች አሰልጥኖ ያዘጋጃቸውን የ2018 ዓ.ም. ተማሪዎቹን ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በልዩ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። በዚህ ደማቅ የምረቃ በዓል ላይ የተመራቂ ቤተሰቦች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዕለቱ የክብር እንግዳ ሆነው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት ቄስ ደረጄ ጀምበሩ በምረቃቱ ላይ በመገኘት እንኳን ደስ አላችሁ' በማለት፣ ከተማረና ዕውቀት ካለው የሰው ኃይል ጋር አብሮ መስራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ቤተ ክርስቲያንም የወንጌል አማኝ ለሆኑት ወገኖች በሙሉ፦ “ይህ ጊዜ ወንጌልን የምንሰብክበትና የምንሠራበት ወቅት ነው። ለእዚህም እግዚአብሔር አዘጋጅቷችኋል፤ ስለዚህ በትጋት ልታገለግሉ ይገባል”የሚል መልእክት አስተላልፌዋለሁ። በመጨረሻም ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሜደሊያና የደረጃ ሽልማት ያተበረከተ ሲሆን፣ የምረቃው ሥነ-ሥርዓት በጸሎትና በምስጋና ተጠናቋል

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶክተር ጌትነት ለማ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ባደረጉት ጉብኝት ተቋሙ የደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ
+4
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶክተር ጌትነት ለማ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ባደረጉት ጉብኝት ተቋሙ የደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ እጅግ አስደናቂ መሆኑን ገለጹ። ጠቅላይ ጸሐፊው በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት፣ ወደ ተቋሙ የመጡት ልምድ ለመውሰድና ሙያ ለመቅሰም ቢሆንም፣ በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ስራዎች ግን የሚበረታቱ ሆነው አግኝተዋቸዋል። በዕለቱ በነበራቸው ቆይታ በግብርና እና በተለያዩ ዘርፎች የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መመልከታቸውንም አብራርተዋል። ካውንስሉ በቴክኖሎጂ ታግዞ አገልግሎቱን ይበልጥ ለማቅለል ማቀዱን የገለጹት ፓስተር ዶክተር ጌትነት፣ "ከካውንስል አንጻር ብዙ ሥራዎችን እንጠብቃለን" ብለዋል። ወደፊት ማገልገል የሚገባቸውን ሥራዎች ከተቋሙ ባለሙያዎች ጋር በመነጋገርና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም፣ በካውንስሉ አገልግሎት የምወሰዱ ዜጎች በቀላሉ መስተናገድ የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። ለኢቫንጄሊካል ዜና:-ቤተልሔም ደረጀ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

"በሌሎች ሀገራት ያየናቸውን አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ በማየታችን ደስ ብሎናል" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

"በሌሎች ሀገራት ያየናቸውን አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ በማየታችን ደስ ብሎናል" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ዋ
+9
"በሌሎች ሀገራት ያየናቸውን አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ በማየታችን ደስ ብሎናል" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ዋና መስሪያ ቤት የተውጣጡ አመራር እና ሰራተኞች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኝተዋል። የካውንስሉ ዋና ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ ቀደም ሲል በሌሎች ሀገራት ያዩዋቸውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ልጆች ተሰርተው በኢንስቲትዩቱ ውስጥ በማየታቸው ከፍተኛ ደስታ ተሰምቷቸዋል። ፓስተሩ አክለውም ኢንስቲትዩቱ ለተለያዩ ተቋማትና ዘርፎች እያበረከተ ያለውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ስራዎች መመልከታቸውን ገልጸው፤ በካውንስሉ ስር አገልግሎት የሚያገኙ ተቋማት ፈጣንና የተሳለጠ አሰራር እንዲኖራቸው ከኢንስቲትዩቱ ጋር በጋራ በመስራት ምቹ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በጉብኝት መርሃ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የዋና የዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊና የቴክኖሎጂ አማካሪ ሻምበል ይልማ (ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች እያከናወናቸው ያሉትን ስራዎች በተመለከተ ለጎብኝዎቹ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

"ወንጌልን ለመስበክ ለሚሰማራ ማንኛውም አካል ልዩ ፈቃድ አያስፈልገውም፤ ይሁን እንጂ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶችና አደጋዎች በሙሉ አስቀድሞ በመገምገምና በዝግጁነት መንፈስ መንቀሳቀስ ይኖርበታል፡፡ በአንጻሩ፣ ህግን በመጣስና ባልተፈቀዱ ቦታዎች ላይ ወንጌልን በመስበክ ለሁከትና ለግጭት ምንጭ መሆን አይገባም፤ ምክንያቱም የወንጌል መሰረታዊ ዓላማና መልዕክት ሰላም ብቻ ነው፡፡ 'አትስበኩ' የሚል የህግ እገዳ ቢጣል እንኳ፣ ወንጌልን የመስበክ ተልዕኳችንን ከቶ አናቋርጥም፡፡ ወንጌልን የማትሰብክ ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን የሚል ስም ሊኖራት አይችልም!!" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ በወንጌል አላፍርም በወንጌል ያድናል ብዬ እናገራለሁ ገጠር ከተማ እሰብከዋለሁ እኔስ በወንጌል እንዴት አፍራለሁ ዕድሜ ዘሜነን እናገራለሁ ወንጌል ያሸንፋል ወንጌል ይታደጋል ወንጌል ሰው ያደርጋል ወንጌል ይለውጣል ወንጌልን ይዞ የምን መፍራት ተናገር እንጂ ላልሰሙት ወንጌልን ይዞ የለም ወደ ኋላ መሄድ እንጂ ከኢየሱስ ጋራ የምስራቹን እየስበከ በሽተኞችን እየሰበከ ኢየሱስ ሰጥቶን ሄዱዋል አደራ ተነስተን ዛሬ ወንጌል እንስራ በወንጌል አላፍርም........... ዓለም በልጁ ይጠቀለላል በእርሱ የሚያምን ከፍርዱ ይድናል

ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት 4 ዓመታት ከ200 ሺህ በላይ ዜጎችን በማሳተፍ የለያቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አደረገ * ዛሬ ይፋ በተደረገው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስብሰባ የኢትዮጵያ የወንጌል አማ
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት 4 ዓመታት ከ200 ሺህ በላይ ዜጎችን በማሳተፍ የለያቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አደረገ * ዛሬ ይፋ በተደረገው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስብሰባ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት ቄስ ደረጄ ጀምበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ፓስተር ታሪኩ ብርሀኑ እና የካውንስሉ ጠቅላይ ጸሀፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ ይገኙበታል:: የሀገራዊ ምክክር መድረክ ለቀጣይ ውይይቶች መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎቹን ይፋ ማድረጉ ተገለጸ። በዚሁ መሠረት በቁጥር አራት ላይ የሰፈረውና ዋነኛው የአጀንዳ ክፍል በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር መሆኑ ታውቋል። በዚህ “የሃይማኖት ጉዳዮች” አጀንዳ ስር አራት ዋና ዋና ነጥቦች ለውይይት የቀረቡ ሲሆን፣ እነሱም፦ በሴኩላሪዝም (የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት) እና በሃይማኖት መካከል ጤናማ ሚዛንን መጠበቅ፣ የሃይማኖት ነፃነት እና ገደቦቹ፣ አነስተኛ ተከታይ ያላቸው የሃይማኖት ተቋማት ጥበቃ፣ እንዲሁም ከባህል እና ከሃይማኖታዊ እሴቶች ጋር የሚጋጩ ድርጊቶች የሚሉት ናቸው። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

"ወንጌልን ለመስበክ ለሚሰማራ ማንኛውም አካል ልዩ ፈቃድ አያስፈልገውም፤ ይሁን እንጂ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶችና አደጋዎች በሙሉ አስቀድሞ በመገምገምና በዝግጁነት መንፈስ መንቀሳቀስ ይኖርበታል፡፡ በአንጻሩ፣ ህግን በመጣስና ባልተፈቀዱ ቦታዎች ላይ ወንጌልን በመስበክ ለሁከትና ለግጭት ምንጭ መሆን አይገባም፤ ምክንያቱም የወንጌል መሰረታዊ ዓላማና መልዕክት ሰላም ብቻ ነው፡፡ 'አትስበኩ' የሚል የህግ እገዳ ቢጣል እንኳ፣ ወንጌልን የመስበክ ተልዕኳችንን ከቶ አናቋርጥም፡፡ ወንጌልን የማትሰብክ ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን የሚል ስም ሊኖራት አይችልም!!" ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄ ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) "ፕሮፌት ፊቃዱ" በሚል ስም የሚንቀሳቀስ ግለሰብ የካውንስሉን እና የ
+3
🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄ ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) "ፕሮፌት ፊቃዱ" በሚል ስም የሚንቀሳቀስ ግለሰብ የካውንስሉን እና የአባል አብያተ ክርስቲያናትን ስም በመጥቀስ ፍጹም ሀሰተኛ መረጃ እያሰራጨ ይገኛል። ⚠️ ሀሰተኛው ወሬ ምንድን ነው? "ከጀርመን አብያተ ክርስቲያናት ጋር ስምምነት ተደርጓል" የሚል ማጭበርበሪያ። "ወንጌል አማኞችን ለትምህርት ወደ ጀርመን እንልካለን" የሚል የሀሰት ተስፋ። "የጉዞ እና የትምህርት ወጪው በሌሎች አካላት ይሸፈናል" የሚል ማታለያ። "ከመማር በኋላ በአውሮፓ የአገልግሎት እድል ይመቻቻል" የሚል የቪዛ ማጭበርበር። 📢 ለቅዱሳን እና ለህዝበ ክርስቲያኑ የተላለፈ ጥሪ ካውንስሉ ይህ መረጃ ሙሉ በሙሉ ሀሰት መሆኑን እያረጋገጠ፣ ምዕመናን ራሳቸውን ከዚህ ማጭበርበር እንዲጠብቁ በጥብቅ ያሳስባል። 🤝 ምን ማድረግ ይኖርብናል? ከመመዝገብ ይቆጠቡ፦ በግለሰቡ አማካኝነት በሚደረጉ ማናቸውም የቪዛ እና የትምህርት ምዝገባዎች ላይ አይሳተፉ። መረጃዎችን ያጋልጡ፦ በአካባቢዎ መሰል የሀሰት ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ሰዎችን ሲመለከቱ ለህግ አካላት ጥቆማ ይስጡ። ለካውንስሉ ያሳውቁ፦ መረጃ ካለዎት በካውንስሉ ዋና ጽሕፈት ቤት በአካል በመቅረብ ለህግ ክፍሉ ጥቆማ ይስጡ። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ Evangelical Media/Council የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

በእምነት ተቋም ላይ ዝርፊያና ውድመት የፈጸሙ 21 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3፣ አያት 49 ቁጥር-2 አካባቢ በሚገኝ "የመንግስተ ሰማይ እንደራሴዎች ዓለም አቀፍ ቤተ
+4
በእምነት ተቋም ላይ ዝርፊያና ውድመት የፈጸሙ 21 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3፣ አያት 49 ቁጥር-2 አካባቢ በሚገኝ "የመንግስተ ሰማይ እንደራሴዎች ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን" ላይ በቡድን በመደራጀት ዝርፊያና ውድመት የፈጸሙ 21 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ፣ የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች የሆኑ 21 ግለሰቦች "ቦታው የእኛ ነው" በሚል ሰበብ በኃይል ወደ ቤተክርስቲያኑ ግቢ በመግባት የቤተክርስቲያኑን ንብረቶች አውድመዋል። በዚህ ድርጊታቸውም 10,132,000 (አስር ሚሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ሁለት ሺህ) ብር የሚገመት ንብረት መዘረፉንና መውደሙን ፖሊስ ገልጿል። ወንጀሉ እንደተፈጸመ መረጃው የደረሰው የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፣ ተጠርጣሪዎቹ ከአካባቢው ቢሰወሩም ባደረገው ክትትል በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ አስታውቋል። ፖሊስ አክሎም በወንጀሉ ተሳታፊ የሆኑ ግለሰቦች ላይ ክስ እንደሚመሰርት ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ፤ መሰል ድርጊቶች የኃይማኖት ግጭት የሚቀሰቅሱና ተከባብሮ የኖረውን ህዝብ በጥርጣሬ እንዲታይ የሚያደርጉ በመሆናቸው ሁሉም ወገን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል። ለኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ Evangelical Media/Council

#በኋላውም_ቀርባ_የልብሱን_ጫፍ_ዳሰሰች_የደምዋም_ፈሳሽ_በዚያን_ጊዜ_ቆመ።” — ሉቃስ 8፥44 #ተስፋ_እምነት_እና_ፈውስ_በአንድ_መንገድ_ተገናኙ። ቅዱሱ መፅሀፍ በዚህ ክፍል ብዙ የደከመችን ለድነቷ ጎ
#በኋላውም_ቀርባ_የልብሱን_ጫፍ_ዳሰሰች_የደምዋም_ፈሳሽ_በዚያን_ጊዜ_ቆመ።” — ሉቃስ 8፥44 #ተስፋ_እምነት_እና_ፈውስ_በአንድ_መንገድ_ተገናኙ። ቅዱሱ መፅሀፍ በዚህ ክፍል ብዙ የደከመችን ለድነቷ ጎንበስ ቀና ያለችን ለፈውሷ ብዙ የታመመችን ለመቆም የዘላችን ለመዳን የታመመችን በውስጧ ግን መውደቋ መዛሏ ህመሟ ተስፋን የማውጣት ጉልበት ያልነበረውም ብዙ ጊዜ ትሞክራለች ያለ ሟቋረጥ ተስፋ ታደርጋለች። ለፈውሷ ትክክለኛ ነው ብላ ያሰበችውን ሁሉ ሞክረዋለች አሁን ድኛለሁ መድሀኒት አግንቻለው ብላ የመዳኗን ተስፋ አግኝታ ወዲያው ጠፍቶባታል። ይህች ሴት ናት ከተስፋዋ ጋር በእምነት የሰው ብዛትና ግፊት የደሟ መፍሰስ ሳያቆማት የልብሱን ጫፍ በመንካት ፈውሷን ያገኘችው። ተስፋና እምነት አካል የሚለብሱት ጌታን በማግኘታችን ነው። እንዴት ቢባል የእኛን ትጋት የኛን አለመታከት እንዲሁም ተስፋችንና እምነታችንን አካል የሚያለብሰው ፈውስ ከሚሰጠው ሳይሆን እርሱ እራሱ ፈውስ ከሆነው ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር የተገናኘን ጊዜ ነው። ፍቃዱ ውስጥ መመላስ ነው እርሱን ማግኘት፣እርሱን በመጨረሻ ፍላጎታችን መሻት ነው እርሱን ማግኘት፣ከከበበን ወጥተን አይናችን በእርሱ ላይ ሲሆን ነው እርሱን ማግኘት እና አማራጫችንም ምርጫችንም እርሱ ሲሆን ነው እርሱን ማግኘት። ያን ጊዜ ነው የችግራችን ማብቅያ፣ያን ጊዜ ነው የተስፋችንን አካል በግልጥ የምናየው። ከእምነታችን ጋር የምንጨባበጠው። #written_by_@Teshaletaye የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ Evangelical Media/Council

"የቆርቆሮ አጥር በማፍረስ የሚቆም ወንጌል የለም" — ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ አዲስ አበባ — የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ
"የቆርቆሮ አጥር በማፍረስ የሚቆም ወንጌል የለም" — ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ አዲስ አበባ — የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ፣ ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በአካል በመገኘት ጉዳት የደረሰባትን ቤተ ክርስቲያን ጎብኝተዋል። ጠቅላይ ጸሐፊው በጉብኝታቸው ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት "የቆርቆሮ አጥር በማፍረስ የሚቆም ወንጌል የለም" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፓስተር (ዶ/ር) ጌትነት ለማ በስፍራው ከመገኘታቸውም በላይ፣ ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ መዋቅሮች ጋር በጉዳዩ ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ወቅት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር እና የጸጥታ መዋቅሮች ይህንን ጥፋት የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ስር አውለው ምርመራ እያካሄዱ መሆናቸው ተገልጿል። ላጠፉት ጥፋትም አስተማሪ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ማጣራት እየተደረገ በመሆኑ፣ ጠቅላይ ጸሐፊው ለአስተዳደሩና ለጸጥታ አካላቱ ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተጨማሪም፦ለአጥፊዎች የተላለፈ መልዕክት: የክፍለ ከተማውን ሰላማዊ ማህበረሰብ ገጽታ ለማበላሸት የሚለፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። ችግሩ በተፈጠረበት ወቅት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እና መንፈሳዊ ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ጉዳዩን ለሕግ ላቀረቡት የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ምስጋናቸውን ለግሰዋል። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ

የሕግ የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ። የሚመለከተው የመንግሥት አካል ሕጋዊ እርምጃ ወስዶ ለሕዝብ ማሳወቅ ይኖርበታል። ይህንን አመጽ ያስተባበሩና በቀጥታ የተሳለፉ አካላት በወንጀል ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንዲሁም ለወደመው ንብረት ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል

የሕግ የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ። የሚመለከተው የመንግሥት አካል ሕጋዊ እርምጃ ወስዶ ለሕዝብ ማሳወቅ ይኖርበታል። ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 አያት ቁጥር 2
የሕግ የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ። የሚመለከተው የመንግሥት አካል ሕጋዊ እርምጃ ወስዶ ለሕዝብ ማሳወቅ ይኖርበታል። ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 አያት ቁጥር 2 ኮንድሚንየም የሰላም ቤት ባለቤቶች ማህበር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ለወንጌል አማኝ እምነት ተከታዮች ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች በሕግ የራሷ ካርታና ሕጋዊ ፕላን እንዲሁም እንደማንኛውም ሕጋዊ ተቋም የሕግ ሰውነት ያላትን ቤተ እምነት በማፈራረስ በአከባቢያችን ወንጌል አማኞች ሊኖሩ አይገባም በሚል ሰበብ በአንድ ቤተ እምነት ላይ የፈጸሙትን ጥቃት ካውንክሉ በቀላሉ የማይመለከተው መሆኑን ለሚመለከተው አካል እያሳወቅን ይህንን አመጽ ያስተባበሩና በቀጥታ የተሳለፉ አካላት በወንጀል ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንዲሁም ለወደመው ንብረት ተጠያቂ እንዲደረጉልን እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል