uz
Feedback
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC analitikasi

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 11 811 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 7 591-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 855-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 11 811 obunachiga ega bo‘ldi.

25 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 263 ga, so‘nggi 24 soatda esa 3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 17.31% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.60% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 044 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 015 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 26 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

11 811
Obunachilar
+324 soatlar
+587 kunlar
+26330 kunlar
Postlar arxiv
ፈጣሪ ሃይማኖት መራጭ አይደለም ወንጌላዊ ሁሴን መሀመድ https://youtu.be/HRgsm4hhdcM?si=SSKxme0U1qcorc6r

መስጅድ ውስጥ ልሳን ተናገርኩ ወንጌላዊ ሁሴን መሀመድ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ሙሉ ቪዲዮውን ይመልከቱ https://youtu.be/HRgsm4hhdcM

🇪🇹 ምስጋና ለሁሉም! የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ46 ቀናት ሲያከናውነው የቆየው የምክክር መድረክ በሰላም በመጠናቀቁ ደስታችንንና ምስጋናችንን እንገልጻለን። በዚህ ረጅምና አስፈላጊ የምክ
🇪🇹 ምስጋና ለሁሉም! የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ46 ቀናት ሲያከናውነው የቆየው የምክክር መድረክ በሰላም በመጠናቀቁ ደስታችንንና ምስጋናችንን እንገልጻለን። በዚህ ረጅምና አስፈላጊ የምክክር ሂደት በኃላፊነት፣ በትዕግሥትና በመከባበር ለተሳተፉ ተሳታፊዎች፣ ለኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች፣ ውይይቱን በትጋት ሲያስተባብሩ ለነበሩ ባለሙያዎችና ሠራተኞች ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን። በተጨማሪም ተሳታፊዎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡና መድረኩ በሰላም እንዲካሄድ፣ ከፈጣሪ ጥበቃ በታች ቀንና ሌሊት የደኅንነትና የሰላም ጥበቃ ሲያደርጉ ለነበሩ ሁሉ ልዩ ምስጋናችን ይድረስ። ለመላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይህንን የምክክርና የሰላም ጉዞ በጋራ እንድንደግፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ልዩነቶቻችንን በውይይት እያቀራረብን፣ የሚያግባቡንን የጋራ እሴቶች እያጠናከርን፣ ለትውልድ ሰላማዊ፣ የተረጋጋችና የበለጸገች ኢትዮጵያን በጋራ እንገንባ። ሰላም የሁላችንም ነው፤ ለሰላም መሥራትም የሁላችንም ኃላፊነት ነው! 🇪🇹 የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለዜና ሽፋን መልአክት ለመላክ t.me/evangelicalmedia 📞251 991827226 ላይ ያገኙናል

የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሏን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠች የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ያከናወነችውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት የሚዘክር የ70ኛ ዓመ
+6
የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሏን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠች የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ያከናወነችውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት የሚዘክር የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥታለች። በዓሉ በ1ኛ ሳሙኤል 7፥12 “አቤንኤዘር” እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን፥ በበዓሉ ላይ በርካታ የምስጋና፣ የጸሎት ፕሮግራሞች እንደሚካሄዱ ተገልጿል። ይህ ታላቅ ክብረ በዓል ከነሐሴ 3 ቀን ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በ1948 ዓ.ም.“መሠረተ ሕይወት” በሚል ስያሜ ጉዞዋን የጀመረችው ይህች ታሪካዊት ቤተክርስቲያን፥ ባለፉት ዓመታት ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ለማድረስ ባደረገችው ጥረት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች ከ60 በላይ አዳዲስ አጥቢያዎችን በመትከል ረገድ ታላቅ ታሪክ መሥራቷ ተጠቅሷል። ከመንፈሳዊ አገልግሎቷ ጎን ለጎን ማኅበረሰቡን የሚጠቅሙ በርካታ ማኅበራዊ ሥራዎችን ስታከናውን የቆየች ሲሆን ከምሥረታዋ ጋር ተያይዞ የተቋቋመው የመጀመሪያው የመሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን መሠረተ ትምህርት ቤት አሁንም ድረስ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በሥነ-ምግባር የታነጸ ዜጋ በማፍራት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የቤተክርስቲያኗ መሪዎች እንደተናገሩት፤ ነሐሴ 23 በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ወንጌላውያን አማኞች በሙሉ የሚሳተፉበት ታላቅ የምስጋና እና ራዕይ የማጋራት መርሃ ግብር ይካሄዳል ብለዋል። በተጨማሪም ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. የዝማሬ እና ወንጌል ማወጅ የእግር ጉዞ መርሃ ግብር ይከናወናል። ይህ ጉዞ ከቤተክርስቲያኑ ግቢ ተነስቶ በሞላ ማሩ እና በአብነት በበላ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እም
+6
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እምነት ናት በማለት ተናገሩ። ነሐሴ8 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛ የካውንስል ስብሰባ አካሄዷል። በስብሰባዉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ መልእክት ያስተላለፋ ሲሆን በመልክታቸዉም የመካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በረጅም የአገልግሎት ዘመኗ በአገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እምነት ናት። ለዛሬው ሁለንተናዊ እድገት የቀደሙ መሪዎች ያበረከቱት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነበር። ያሉት ጠቅላይ ፀሐፊዉ ዛሬም ቢሆን ከትውልድ፣ ከአገርና ከሁሉ በላይ ከእግዚአብሔር የተሰጣትን ታላቅ መለኮታዊ አደራ በታማኝነት መወጣት ይጠበቅባታል። ብለዋል የዛሬዎቹ መሪዎች ትላንትን በማስታወስ፣ ዛሬን በታማኝነት በማገልገል እና ነገን መሠረት በሚጥል ራዕይ በመመልከት ዋናውን ነገር ዋና አድርገው መቀጠል አለባቸውም በማለት አክለዋል። ለኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነኢየሱስ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ሰጠች #ኢቫ_ዜና https://youtu.be/4W8SEdsfGm4

ሁሉም ወንጌል አማኝ ሊያየው የሚገባ ድንቅ ፕሮግራም ክርስትና ውርስ አይሆንም በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ሚዲያ የቀረበ በ Evangelical Media Council ዩቲዩብ ቻናል ላይ ያገኙታል ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://youtu.be/YDH1EH4SnIY?si=8T3fqaIV_6xkF1mB

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር በማኅበራዊ ሚዲያና ብሮድካስት አጠቃቀም ላይ ሥልጠና ሰጠ። ይህ ሥልጠና የጥላቻ ን
+8
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር በማኅበራዊ ሚዲያና ብሮድካስት አጠቃቀም ላይ ሥልጠና ሰጠ። ይህ ሥልጠና የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም ከማኅበራዊ ሚዲያ እና ከብሮድካስት አገልግሎት ሥራዎች ጋር የተያያዘ ሲሆን፤ በካውንስሉ ሥር ለሚገኙ የወንጌል አማኞች ሚዲያዎች በሙሉ የተሰጠ ነው። የፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አሰፋ መብራቱ እንደገለጹት ሥልጠናው የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃዎች ከሕግ አንጻር የሚያስከትሏቸውን ችግሮች ለማየት እና ለዚህም የመፍትሔ ሐሳብ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች እንዴት መከላከል እንደሚቻል ለመመልከት የተዘጋጀ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሕግ ክፍል ኃላፊ ወይዘሪት መንበረ አንድነት በበኩላቸው የወንጌላዊያን ሚዲያዎች ከሕግ አንጻር ምን ያህል ያውቃሉ? በሕጉስ መሠረት እየሠሩ ነው? የሚለውን ለማስገንዘብ ጭምር ሥልጠናው መዘጋጀቱን አንስተዋል።አክለወም ካውንስሉ በተጨማሪም ከሕግ አንጻር የተለያዩ ሥልጠናዎችን በቀጣይነት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ የሕግ ሥርጸትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት አካዳሚክ ዓቃቤ ሕግ አቶ ሙሴ ባዬ ሥልጠናውን የሰጡ ሲሆን፥ ከተሳታፊዎች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉት ሰልጣኞች በቆይታቸው እጅግ ጠቃሚ እና ጥሩ ጊዜ እንደነበራቸውም ገልጸዋል።ከዚህ ስልጠና የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት በስራቸው ላይ በተግባር እንደሚያውሉትና ውጤታማ እንደሚሆኑ ሙሉ እምነት እንዳላቸው አስታውቀዋል። ለኢቫንጄሊካል ዜና ቤተልሔም ደረጀ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ነሐሴን በጾምና በጸሎት የመሻር አገር አቀፍ ጥሪ አስተላለፈ #ኢቫ_ዜና@EGBCC

ነሐሴን በጾምና በጸሎት እንሻገር! የአንድ ዓመት ጉዞ ሲጠናቀቅ፣ አዲስ ዓመትም ሲጀምር፤ በምስጋና ያለፈውን እናስብ፣ በጸሎት የሚመጣውን እንቀበል። ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም — አገር አቀፍ የጾምና የ
ነሐሴን በጾምና በጸሎት እንሻገር! የአንድ ዓመት ጉዞ ሲጠናቀቅ፣ አዲስ ዓመትም ሲጀምር፤ በምስጋና ያለፈውን እናስብ፣ በጸሎት የሚመጣውን እንቀበል። ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም — አገር አቀፍ የጾምና የጸሎት ወር! ስለ ሀገራችን፣ ስለ ሕዝባችን፣ ስለ ትውልዳችንና ስለ ቤተ ክርስቲያን በአንድ ልብ እንጹም፤ እንጸልይ። 📖 “ በቸርነትህ  ዓመቱን ታቀዳጃለህ  .......” — መዝሙር 65፥11

ኦርቶቶሜኦ የእውነትን ቃል በትክክል መክፈል የተሰኘውና በመጋቢ ቤዛዓለም በላይ የተዘጋጀው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ። በመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የኢትዮጵያ ምስጋና
+9
ኦርቶቶሜኦ የእውነትን ቃል በትክክል መክፈል የተሰኘውና በመጋቢ ቤዛዓለም በላይ የተዘጋጀው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ። በመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት ፓስተር ጌታሁን ነሲቡ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን መጽሐፉ ለምእመናንና ለቤተክርስቲያን ያለውን ጠቀሜታ በመግለጽ የተሰማቸውን ታላቅ ደስታ አጋርተዋል። በምረቃው ላይ የመጽሐፉን ይዘት አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡት የቋንቋ ጥናት ባለሙያው አቶ አሺኔ አስቴን በበኩላቸው መጽሐፉ የወቅቱን ፍላጎት ያገናዘበና እጅግ ጠቃሚ የሆነ ሼል መሆኑን መስክረዋል። በማቀጠልም ወንጌላው ዙርያ ሱማ የመጽሐፉን ዳሰሳ አቅርበዋል። የመጽሐፍ ጸሐፊ መጋቢ ቤዛ ዓለም እንደተናገሩት ኦርቶቶሜኦ" የግሪክ ቃል ሲሆን "ኦርቶ" ማለት "በትክክል" ማለት ሲሆን"ቶሚሆ" ማለት ደግሞ "መቁረጥ" ከሚለው የግሪክ ቃል የተወሰደ መሆኑ ገልጿል።በዚህ ዘመን ያሉ አገልጋዮች መጽሐፍ ቅዱስን በራሳችን አውድና ለእኛ እንደሚመቸን እያፈታን ስለሆነ ለዚያ መፍትሔ ታስቦ የተጻፈ መሆኑን አክለው ተናግራዋል። ለኢቫንጄሊካል ዜና ቤተልሔም ደረጀ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia 📞251 991827226 ላይ ያገኙናል Telegram | Facebook | Youtube  | Tiktok | Website

“ተስፋችን በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ ነው'' ቬኔዙዌላውያን በቬኔዙዌላ ከ300 በላይ በሚሆኑ ከተሞች በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተሰብስበው ኢየሱስ ክርስቶስ በሀ
+5
“ተስፋችን በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ ነው'' ቬኔዙዌላውያን በቬኔዙዌላ ከ300 በላይ በሚሆኑ ከተሞች በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተሰብስበው ኢየሱስ ክርስቶስ በሀገራቸው ላይ ጌታ መሆኑን በይፋ ያወጁበት ታላቅ የጸሎትና የምስጋና መርሃ ግብር አካሄዱ። "ቬኔዙዌላ የጸጋ ምድር" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ ዝግጅት አማኞች አደባባዮችንና ጎዳናዎችን በአምልኮ፣ በምስጋናና በጸሎት በመሙላት ለሀገራቸው ሰላም፣ አንድነት፣ ተስፋና ዘላቂ ለውጥ ተመኝተዋል። ሀገሪቱ በፈታኝና እርግጠኝነት በጎደላቸው የችግር ጊዜያት ማለፏ የሚታወስ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የመጨረሻ ተስፋቸው በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አውጀዋል። በያፌት ገ/ህይወት የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia 📞251 991827226 ላይ ያገኙናል Telegram | Facebook | Youtube  | Tiktok | Website

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ሥነ መለኮት መምሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት ማስተባበሪያ ያዘጋጀው የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት መምህራንና የሥራ ተሳታፊዎች ስልጠና ተካሄደ፡
+7
የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ሥነ መለኮት መምሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት ማስተባበሪያ ያዘጋጀው የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት መምህራንና የሥራ ተሳታፊዎች ስልጠና ተካሄደ፡፡ ሥልጠና ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሐዋሳ ሐይቅ ዳር ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገልጿል። "ከሙያ አልባ መምህር ወደ መምህር አልባ ክፍል ወይስ የመምህርነት ሙያና የትምህርት ጥራት በኢትዮጵያ"በሚል ዋና ርዕስ በሚካሄደው ሥልጠና፣ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፣ በሥነ መለኮት ተቋማት የመምህራንና የአመራሮች ሚናን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከሐዋርያትና ከነቢያት አገልግሎት ጋር ተያይዞ ሊኖር የሚገባውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አቋም በስፋት ውይይት እንደሚካሄድበት ታውቋል። መረጃውን በቤተክርስቲኒቱ አገኘነው፡፡ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ • YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732 • TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media • Telegram: https://t.me/EGBCC • Website: ecgbc.org የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia 📞251 991827226 ላይ ያገኙናል

በአምበሪቾ AIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ በአምበሪቾ ዓለም አቀፍ የጸሎትና የወንጌል አገልግሎት (AIPM) የሚገነባው የAIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ (AIPM–GMU) የ
+8
በአምበሪቾ AIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ በአምበሪቾ ዓለም አቀፍ የጸሎትና የወንጌል አገልግሎት (AIPM) የሚገነባው የAIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ (AIPM–GMU) የመሠረት ድንጋይ የማኖር ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል። በሥነ ሥርዓቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አረጋ እሸቱ፣ እንዲሁም የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክብርት ወይዘሮ ውባየሁ በቀለ ተገኝተው የመሠረት ድንጋዩን አኑረዋል። በመድረኩ የAIPM መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ደስታ ላንገና ጨምሮ የተገኙ እንግዶች ንግግር አድርገዋል። ተናጋሪዎቹ ተቋሙ እስካሁን በወንጌል፣ በጸሎት እና በማኅበረሰብ አገልግሎት ያከናወናቸውን ሥራዎች በማድነቅ፣ በማኅበረሰቡ ላይ ያሳደሩትን በጎ ተፅዕኖ አመስግነዋል። እንዲሁም ይህ ዩኒቨርሲቲ የAIPM ብቻ ሳይሆን የመላው የከምባታ ሕዝብ ፕሮጀክት መሆኑን በመግለጽ፣ ሁሉም በትብብር እንዲደግፉት ጥሪ አቅርበዋል፤ መንግሥትም ለፕሮጀክቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል። የAIPM መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ደስታ ላንገና በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ከሚሽን አገልግሎት ባሻገር በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽን፣ በሥነ ምግባር እና በሙያ ክህሎት የተበቁ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎችን ማፍራት ዋና ዓላማው መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በተቋሙ ውስጥ የእውቀት እና የሁለንተናዊ እድገት ትምህርት በትኩረት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። AIPM-Ambaricho International Prayer and Missions Movement

"ቤተክርስቲያን የሰውን ሁለንተና ማለትም መንፈሳዊና አካላዊ ፍላጎቱን ማገልገል ይኖርበታል" "Waldaan guutummaa namma(fooniifi hafuura namaa) tajaajiluu qabdii"
"ቤተክርስቲያን የሰውን ሁለንተና ማለትም መንፈሳዊና አካላዊ ፍላጎቱን ማገልገል ይኖርበታል" "Waldaan guutummaa namma(fooniifi hafuura namaa) tajaajiluu qabdii" "The Church must serve the whole person - spiritual and physical needs." ቄስ ጉዲና ቱምሳ

አስቸኳይ እና ወሳኝ ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል! ⚠️ በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) የሚሰራጭ አደገኛ የማጭበርበር መረጃ በመሆኑ ቅዱሳን ራሳችሁን ጠብ
አስቸኳይ እና ወሳኝ ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል! ⚠️ በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) የሚሰራጭ አደገኛ የማጭበርበር መረጃ በመሆኑ ቅዱሳን ራሳችሁን ጠብቁ! በቲክቶክ ስም ፕሮፌት ፊቃዱ፣ ዶክተር አቤል እና የወንጌላውያን የትምህርትና ልማት ማህበር በሚሉ ስሞች የሚንቀሳቀሱ አካላት ናቸው።የካውንስሉንና የአባል ቤተ እምነት ስም በመጥቀስ ከጀርመን አብያተ ክርስቲያናት ጋር ስምምነት አድርገናል ምዕመናንን ለትምህርት ወደ ጀርመን እንልካለን የሚል ነው።የትምህርት ወጪው ሙሉ በሙሉ እንደሚሸፈንና ከአውሮፓ ጉዞ በኋላ የአገልግሎት ዕድል እንደሚመቻች በማስመሰል ሰዎችን እያመዘገቡ ይገኛሉ። ይህ መረጃ ሙሉ በሙሉ የሐሰት ነው። ካውንስሉ የፈረመው ምንም አይነት ስምምነት የለም! ብዙ ምዕመናን በዚህ ድርጊት እየተታለሉና እየተበዘበዙ በመሆኑ ሁላችሁም ከዚህ የሐሰት መረጃ ራሳችሁን እንድትጠብቁ እናሳስባለን። ይህንን መረጃ ሟር በማድረግ ወንድም እህቶቻችንን ከማጭበርበር እንታደግ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia 📞251 991827226 ላይ ያገኙናል Telegram | Facebook | Youtube  | Tiktok | Website

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ የቤተ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የወንጌል አማኞች ድምፅ የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ! ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም t.me/evangelicalmedia 📞251 991827226 ላይ ያገኙናል Telegram | Facebook | Youtube  | Tiktok | Website

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC - Telegram kanali @egbcc statistikasi va tahlili