uk
Feedback
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

Відкрити в Telegram

ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

Канал የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 11 934 підписників, посідаючи 7 407 місце в категорії Релігія і духовність та 2 823 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 11 934 підписників.

За останніми даними від 16 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 188, а за останні 24 години на 23, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 21.28%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 7.47% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 2 540 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 892 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

11 934
Підписники
+2324 години
+537 днів
+18830 днів
Архів дописів
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች ለአዲስ አመት ከ600,000 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለማህበረሰቡ የምግብ ድጋፍ አደረጉ። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያ
+7
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች ለአዲስ አመት ከ600,000 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለማህበረሰቡ የምግብ ድጋፍ አደረጉ። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 አጥቢያ እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ በአካባቢያቸው ለሚገኙ 432 የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ አድርገዋል። የሆለታ 44 አጥቢያ ለ226 አቅመ ደካሞችና ድሆች 295,500.00 ብር ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው 10 ኪ.ግ ዱቄትና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ ስታደርግ እንዲሁም የሆለታ ጭሪ አጥቢያ ለ206 ችግረኞች 307,193.00 ብር ወጪ በማድረግ ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጋለች። በተጨማሪም የሆለታ 44 አጥቢያ በኤጀሬ ማረሚያ ቤት ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ሦስት ኩንታል አልባሳት እና የበዓል መዋያ የሚሆን የ18,000 ብር ድጋፍ ስትሰጥ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተካሄደው የወንጌል ሥርጭት 10 የሕግ ታራሚዎች ጌታ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል። መረጃው የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲየን ነው

የአሜን ቲቪ ሥራ አስኪያጅና አገልጋይ ሰብሌ በቀለ ሰው ሁሉ ስለ ነገ ሲያስብና ሲጨነቅ ይፈራል እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ
የአሜን ቲቪ ሥራ አስኪያጅና አገልጋይ ሰብሌ በቀለ ሰው ሁሉ ስለ ነገ ሲያስብና ሲጨነቅ ይፈራል እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።(ትንቢተ ኤርምያስ 29:11) ይህን የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል በመጥቀስ እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁበማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል

Wisdom Intergration ከ Gaps International Ministry ጋር በመተባበር የአይምሮ ውስንነት ካላቸው ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ጋር የአዲስ አመት ልዩ የበዓል ዝግጅት በሳር ቤት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ያከናወነ ሲሆን በዕለቱም ከልጆቹ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር የህብረት ፣ የጨዋታ እና ማዕድ በጋራ የመካፈል ጊዜ የነበረ ሲሆን ለአዲስ አመት በዓል የሚሆን የልጆች መጫወቻዎች ፣ ዘይትና ዱቄት፣ ህይወታቸውን እንዲመሩበት ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። የዕለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የWisdom የቦርድ አባል እህት ማርታ ፈለቀ ሁሉም ሰው ከዊዝደም ኢንቲግሬሽን ጋር በመተባበር በሙያ፣ በገንዘብ እና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብረው እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ። የዊዝደም ኢንቲግሬሽን መስራች የሆኑት ወንድም ዳንኤል እና ባለቤታቸው የኔነሽ ለልጆቹ ፣ ለወላጆች እና በዕለቱ ለተገኙ ታዳሚዎች ሁሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እና ለዊዝደም ኢንቲግሬሽን አገልግሎት መመስረት ምክንያት ስለሆናቸው ስለ ልጃቸው ካሌብ ዳንኤል እና ባጋጠመው የዓይምሮ ውስንነት ምክንያት ይህ አገልግሎት ለመመስረት ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል። የዕለቱ ተጋባዥ ዘማሪት የነበረችው ዘማሪት ሩት እጅግ በሚያጽናኑ ዝማሬዎች ጉባኤውን አገልግላለች። የጋፕስ ዓለም አቀፍ አገልግሎት መስራች እና መሪ በሆኑት መጋቢ ዳንኤል ዋለልኝ ከዮሐንስ 4 ጠቅሰው በአይሑድ ማህበረሰብ ስለተገለሉት ሳምራውያን እና በሳምራውያኑ ስለተገለለችው ሳምራዊቷ ሴት ፣ እሷን ስለቀረባት እና ስለተቀበላት እየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል አካፍለዋል።

የወጣቶች የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴ በሆሳዕና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች፣ በከተማዋ ጎዳናዎችና አደባባዮች የወንጌል ስርጭት
+8
የወጣቶች የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴ በሆሳዕና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች፣ በከተማዋ ጎዳናዎችና አደባባዮች የወንጌል ስርጭት አካሂደዋል። ወጣቶቹ ይህን የወንጌል ስርጭት ያካሄዱት ከክረምት የወጣቶች ሳምንት የስልጠናና የትምህርት መርሐ ግብር በኋላ ሲሆን፣ በስርጭቱም ከሆሳዕና ከተማና አካባቢዋ የተውጣጡ ወጣቶች፣ ልጆች፣ መሪዎች፣ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ተሳትፈዋል። በእንቅስቃሴውም የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ለተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍሎች ተሰብኳል፤ በርካታ ሰዎችም የወንጌሉን መልዕክት እንዲሰሙ ዕድል ተፈጥሯል። የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ አዴሣም በወንጌል ስርጭቱ ተሳትፈው፣ በከተማዋ አደባባይ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል። ቄስ ወንድማገኝ በተጨማሪም ወጣቶቹ በወንጌል ስርጭት እያደረጉ ላሉት አገልግሎት አበረታተዋል፤ ወንጌልን በድፍረትና በትጋት መመስከራቸውን እንዲቀጥሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ነሐሴ ወር የወንጌል ስርጭትና የምስክርነት ወር በመሆኑ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች በወንጌል ምስክርነት አገልግሎት በስፋት እየተሳተፉ ነው። የሆሳዕና ወጣቶች ያካሄዱት ይህ የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴም፣ የወጣቶችን ተሳትፎ በማጠናከር የክርስቶስን ወንጌል ለሕዝብ ለማድረስ የተደረገ አገልግሎት ሆኗል። EECMY Youth Ministry