uk
Feedback
BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

Відкрити в Telegram

AACABOF PUBLIC PAGE

Показати більше
2 960
Підписники
-124 години
+137 днів
+5530 день
Архів дописів
ለ2019 በጀት ዓመት የተደለደለው 502 ቢሊዮን ብር ከፍተኛ አመራሩ በስልትና በቁርጠኝነት እንዲተገብረው የሚጠይቅ ነው ተባለ፡፡  ######################## ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ከክፍለ ከተማ የፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ ከአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ እና ከፍተኛ ገቢ ከሚሰበስቡ 11 የሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር በሐምሌ ወር የገቢ እቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አደረገ። ለ2019 በጀት ዓመት የተያዘው 502 ቢሊዮን ብር በጀት ከተጠናው የገቢ አቅም መሠረት ማስፋፋት ጥናት አንጻር ዝቅ ያለ ቢሆንም፣ በከፍተኛ አመራሩ በኩል በስልትና በቁርጠኝነት ካልተመራ ሊሳካ የማይችል እቅድ መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም ጥብቅና ችግር ፈቺ የሆነ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ መድረኩ ተዘጋጅቷል። መድረኩ በዋናነት በበጀት ዓመቱ የተያዘውን እቅድ በትኩረትና በቁርጠኝነት በመምራት የታቀደውን ያህል ገቢ ማሰብ የሚቻል መሆኑን ለማሳየት እንዲሁም ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበሩ የአፈጻጸም ክፍተቶች በዘመኑ እንዳይደገሙ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል። በመድረኩም ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም ላሉት ጊዜያት የተዘጋጀው የገቢ አቅም መሠረት ማስፋፋት ጥናት ቀርቦ ግልጽነት የተፈጠረ ሲሆን፣ የሴክተር መስሪያ ቤቶች እና የክፍለ ከተሞች የ2018 ዓ.ም የሐምሌ ወር የገቢ አሰባሰብ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የሴክተር መስሪያ ቤቶች እና የክፍለ ከተማ አመራሮች  በቀረቡት ሁለቱም ሰነዶች ላይ ያላቸውን አስተያየትና ጥያቄ አቅርበው ምላሽ ተሰጥቷቸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢንያም ምክሩ መድረኩን በማዘጋጀቱ ለፋይናንስ ቢሮ ምስጋና አቅርበው፣ የተቋማት ኃላፊዎች በቀጣይ ለሚዘጋጁ መድረኮች ተገቢውን ክብር እንዲሰጡ አሳስበዋል። አክለውም የገቢ አሰባሰብ ሂደት በዋና ኃላፊዎች ካልተመራ በስተቀር ሊሳካ እንደማይችል መረዳት ተገቢ መሆኑን ጠቁመው፣ ለአፈፃፀም ግልጽነት ይረዳ ዘንድ የገቢ አቅም መሠረት ከዚህም በላይ ሊሰፋ እንደሚችል ያሳየው ጥናት ለየተቋማቱ ቢደርስ እንደሚያግዝ ገልፀዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን፣ ከመድረኩ «አንችልም» የሚል አስተያየት አለመሰማቱ የ«ይቻላል» መንፈስ መያዙን ያሳያል ብለዋል። በሐምሌ ወር የተሻለ ተነሳሽነት ላሳዩ ተቋማት ምስጋና አቅርበው፣ በቀጣይ በትኩረት ሊተገበሩ ይገባቸዋል ያሏቸውን ዋና ዋና ተግባራት አስቀምጠዋል፡፡   የገቢ እቅዳቸውን ሙሉ በሙሉ ያላስገቡ ተቋማት እስከ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም ድረስ እንዲያጠናቅቁ፣ ኢ-ፎርማል (Informal) የሆኑ የንግድ ተቋማትን ደግሞ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት ለማስገባት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ተገልጿል። በተጨማሪም ከክፍለ ከተሞች የሚሰበሰበው ገቢ አነስተኛ ቢሆንም፣ በከተማዋ ጠቅላላ ገቢ ላይ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ክፍለ ከተሞች ኃላፊነታቸውን በትጋት እንዲወጡ አደራ ብለዋል፡፡ ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !! ዌብሳይት:- aabof.com.et ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu

በአዲስ አበባ በአንድ ጀምበር ከ1 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል በአዲስ አበባ ከተማ ዘንድሮ ለሚከናወነው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን የአዲስ አበባ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አስታውቋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ለኤ ኤም ኤን ዲጂታል እንደገለፁት ፣ በአዲስ አበባ በአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከ1 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። ለምግብነት የሚያገለግሉ፣ ለውበት የሚሆኑ እና የደን ልማት ሽፋንን የሚያሳድጉ ችግኞች መዘጋጀታቸውንና የችግኝ መትከያ ቦታ መረጣ ሥራን ጨምሮ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ መርሐ ግብሩ ለከተማዋ ውበት፣ ለኢትዮጵያ እድገት እንዲሁም የደን ሽፋንን ለማሳደግ የሚደረግ ታሪካዊ እርምጃ በመሆኑ ሁሉም መሳተፍ እንዳለበትም አቶ ግርማ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ለአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብሩ 176 የሚሆኑ ቦታዎች እንደተለዩ እና የሚተከሉ ችግኞችን የጽድቀት መጠን በሚጨምር መልኩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የሚታየው ትጋት የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ በዜጎች መካከል ያለውን አብሮነትና የሥራ ባህል የሚያሻሽል ነው። እንደ ሃገር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር ይከናወናል፡፡ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች በመላ ሀገሪቱ የተተከሉ ሲሆን ይሄም በርካታ ስኬቶችን አስገኝቷል፡፡

2️⃣ቀናት ቀሩት! የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር 2️⃣ DAYS LEFT! One Day National Tree pla
+1
2️⃣ቀናት ቀሩት! የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር 2️⃣ DAYS LEFT! One Day National Tree planting campaign program 📅 August 3, 2026 #PMOEthiopia #GreenLegacy

የ6ኛው ዓመታዊ የወጣቶች የዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን የቱሪዝም መዳረሻዎችና የልማት ስራዎችን ጎበኙ የ6ኛው ዓመታዊ የወጣቶች የዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ እና በሞዴል የዲፕሎማሲ ሲሙሌሽን መርሀ ግብር ለመሳተፍ ወደ የአዲስ አበባ የመጡ ተሳታፊዎች፣ በከተማዋ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በአዲስ አበባ ከተማ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች መደነቃቸውን ገልፀው፣ ይህም ለሌሎች ሀገራት ትልቅ ተሞክሮ እንደሚሆን ተናግረዋል:: ይህ አለማቀፍ ጉባኤ፣ ወጣቶችን ለዲፕሎማሲ፣ ለአመራር፣ ለፖሊሲ ጥናትና ለዓለም አቀፍ ግንኙነት የሚያዘጋጅ የልምድ ልውውጥ መድረክ መሆኑ ተገልጿል::

3️⃣ቀናት ቀሩት! የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር 3️⃣ DAYS LEFT! One Day National Tree pla
3️⃣ቀናት ቀሩት! የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር 3️⃣ DAYS LEFT! One Day National Tree planting campaign program 📅 August 3, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል 1 አርብ ምሽት 2:30 ይጠብቁ።

Video from Fetle

በከተማችን የተዘረጋው አዲሱ የፋይናንስና የበጀት አስተዳደር ስልት ለዘርፈ ብዙ የልማት ስኬቶች መሰረት መሆኑ ተገለጸ። ######################### ሐምሌ23/2018 ዓ.ም  ፋይናንስ ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ አፈጻፀም ሪፖርት፣ የ2019 በጀት ዓመት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ከዘርፉ አመራሮች እና ከቢሮዉ ሰራተኞች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡ የ2019 በጀት ዓመት እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድን ስኬታማ ለማድረግ ከዘርፍና ከክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ጋር የትስስር ሰነድ የውል ስምምነት ተፈርሟል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ  አቶ አብዱልቃድር ሬዲዋን በመክፈቻ ንግግራቸዉ በቅርቡ በተደረገው ግምገማ ከተማዋ በዕቅድ አፈፃፀም 91.8% አማካይ ውጤት በማስመዝገብ ቢሮው የከፍተኛ ሰርተፊኬት ተሸላሚ መሆኑ የሁሉም ዉጤት በመሆኑ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል። ኃላፊው የከተማዋ በጀት ከ98% በላይ የሚሸፈነው ከውስጥ ገቢ መሆኑን ገልፀው ለካፒታል ፕሮጀክቶች ቅድሚያ በመስጠት፤ አላስፈላጊ የቢሮ እና የኮንፈረንስ ወጪዎችን በመቀነስ እንዲሁም የነዳጅ ወጪን በ50% በመቀነስ የበጀት ድርሻውን ለልማት በማዋል  ለልማት (ካፒታል) የሚመደበው በጀት ከ47% ወደ 71% ማደጉንም  ተናግረዋል። የከተማዋ ገጽታና የህዝብ ተጠቃሚነትን በሚመለከት የደካማ ሰፈሮች ቅነሳ፦ መሰረተ ልማት የሌላቸው ሰፈሮች ድርሻ ባለፉት 5 ዓመታት ከ78% ወደ 40% ዝቅ ማለቱን ተናግረው የአረንጓዴ ስፍራ ሽፋን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ8% ወደ 24% (በአንዳንድ አካባቢዎች እስከ 30%) ማደጉን አመላክተዋል። የፕሮጀክቶች ማጠናቀቅ በሚመለከት  በዓመት በአማካይ እስከ 400 የሚደርሱ አነስተኛና በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች እንደሚጠናቀቁ ገልጸው ዘመናዊ የጤና ተቋማት፣ የሆስፒታሎች  የቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የማስተናገድ አቅም ከፍተኛ ዘመናዊነት ታይቶበታል ሲሉ አቶ አብዱልቃር ተናግረዋል። የቢሮዉ የዕቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ደምሴ የ2018 በጀት ዓመት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ የ2019 በጀት ዓመት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ አቅርበዉ ሰፊ ዉይይት ተደርጎበታል፡፡ በመድረኩ የተነሱ የአሰራርና የቴክኖሎጂ (IBEX) መቆራጥ ችግር፣ ተሰብሳቢና ተከፋይን በሚመለከት ከግዥ ጋር በተያያዘ ግልፀኝነት የሚፈልጉ ጥያቄዎች ከካፌ አገልግሎት ጋር በተያያዘ፣ የሚወጡ ጨረታዎችን በሚመለከት የሚሰበሰብ ገቢና ሀብት ማሰባሰብ የመሳሰሉት አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው የፋይናንስ ቢሮ አመራሮች ምላሽ ሰጥተዉበታል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያ ጠንካራ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት፣ የገቢ ማሳደግ ስልቶች እና የወጪ ቁጥጥር አሰራሮች ለከተማዋ ስኬት መሰረት በመሆናቸው የተገኙ አዎንታዊ ልምዶችን በማጠናከር የቀጣይ ዓመታት ዕቅዶችን ለማሳካት አመራሩና ሰራተኛው በቅንጅት መስራት አለባቸው ሲሉ አቶ አብዱልቃድ አሳስበዋል፡፡ ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !! ዌብሳይት:- aabof.com.et ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu

4️⃣ቀናት ቀሩት! የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር 4️⃣ DAYS LEFT! One Day National Tree pla
+1
4️⃣ቀናት ቀሩት! የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር 4️⃣ DAYS LEFT! One Day National Tree planting campaign program 📅 August 3, 2026 #PMOEthiopia #GreenLegacy

5️⃣ቀናት ቀሩት! በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካዊው ሀ
+1
5️⃣ቀናት ቀሩት! በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካዊው ሀገራዊ ዘመቻ በጋራ በመሰብሰብ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን ይተክላሉ። 📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም እርሶም የዚህ ታሪካዊ ንቅናቄ አካል ይሁኑ! #ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር #PMOEthiopia #GreenLegacy

የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ ለመስራት 5 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! ውድ የሀገሬ ልጆች፤ በእነዚህ ቀናት አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ፣ በቁርጠኝነት እንድትነሱ እና በአንድነታችን የምናስመዘግበውን ድል እውን እንድናደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ። ‎በጋራ ተስፋን እንትከል! Irreen Itoophiyaanotaa walta'insaan guyyaa tokkotti biqiltuuwwan miliyoona 800 dhaabuudhaan seenaa kanbiraa hojjechuuf guyyoota 5 qofaatu hafe! Ijoollee biyyakoo jaalatamoo, guyyoota kanneenitti qophii barbaachisaa akka gootan, kutannoodhaan akka kaataniifi injifannoo tokkummaa keenyaan galmeessifnu akka dhugoomsitanin waamichakoo dhiyeessa. Waliin abdii haadhaabnu! Only 5 days remain to make history through the united arm of all Ethiopians by planting 800 million seedlings in a single day! In these remaining days, I call upon my beloved fellow citizens to make the necessary preparations, rise with determination, and ensure the victory we will achieve in our unity. Together, let us plant hope! #GreenLegacy ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ዛሬ ማምሻዉን ከመላ አመራራችን ጋር በክረምት ወቅት የምንስራቸው የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች፥ የቤት ግንባታ፣የጎርፍ አደጋን መከላከል ፥ የፅዳት ስራዎች፥ የአረጓዴ አሻራ፥ ማዕድ ማጋራት፥ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ፥ ደም ልገሳ፥ ተረጅነትና ድህነት ቅነሳ ወዘተ ስራዎች አፈፃፀምን ገምግመናል። በሁሉም መስክ ውጤታማ ተግባራት እየተፈፀሙ መሆኑን አረጋግጠናል።ሆኖም በክፍለ ከተሞች እና በተቋማት መካከል የአፈፃፀም ልዩነቶች ይታያሉ። በቀጣይም ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በቅንጅት መመራት የሚገባቸው፡- 👉የጀመርናቸዉን የቤቶች ግንባታን ማፉጠን፣ 👉ዲቾችን ማፅዳት እንዲሁም አዳዲስ ዲቾችን መገንባት 👉ከፍተኛ ሀብት ፈሶባቸው የለሙ ቦታዎች መንከባከብ ፅዳታቸውን መጠበቅ 👉አጠቃላይ የከተማ ፅዳት ባህል እንዲሆን መስራት 👉 በግንባታ ምክንያት በተረፈ ምርቶች መንገዶችን የሚያበላሹ፥ ዲቾችን የሚዘጉ አካላት በአፋጣኝ ችግሩን እንዲያርሙ ተጠያቂም እንዲሆኑ ማድረግ 👉 በአረንጋዴ አሻራ የጀመርነው ውጤታማ ስራ ለጥራቱም ትኩረት መስጠት እንዲሁም የችግኝ ተከላ ስራ በአጠረ ጊዜ እና ከእቅድ በላይ ማሳካት 👉 የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሁሉም ዜጋ ባህል እንዲያደርገዉ የማስቻል ስራ መስራት 👉 ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በልዩ ትኩረት መስራት 👉 የጎልማሶች ትምህርት ማጠናከር 👉 ከተረጅነት ለመሸጋገር የተጀመሩ የሰብዓዊ ስራዎች ለመተግበር መጋዘኖች በጥራት የተገነቡ ቢሆንም ቀጣይ ስራ የሚሆነው በቂ የሰብዓዊ ድጋፍ ቁሶች እንዲኖራቸው ማድረግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ሁሉም አመራር በጥብቅ የሚፈፅማቸው ናቸው። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ