BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page
Kanalga Telegram’da o‘tish
2 882
Obunachilar
-124 soatlar
-37 kunlar
-530 kunlar
Postlar arxiv
ለስፖርት መሠረተ-ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት የትውልድ የዘመናት ጥያቄን የመለሰችው አዲስ አበባ!
ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ለህፃናት፣ ለአዋቂዎችና ለወጣቶች ምቹ ያልነበሩ ተሽከርካሪ እና እግረኛ እኩል የሚጋፋባቸው ለአደጋ የተጋለጡ በተለይም በየመንደሩ የሚኖሩ ታዳጊዎች ኳስ ለመጫወት የተመቸ ቦታ ባለማግኝታቸው እራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠው የተሽከርካሪን መንገድ ዘግተው ሲጫወቱ ማየት የተለመደ ነበር። ዛሬ ይህ ታሪክ ሆኖ አልፏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚሰራቸው ስራዎች ሁሉ ለታዳጊዎች ፣ ለወጣቶች እና ለህፃናት ምቹ ከተማን በመገንባት የከተማዋ ጎዳናዎች ለሁሉም ተስማሚ እንዲሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች አከናውኗል፡፡ በተለይም ለስፖርቱ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ በማዘመንና ተደራሽነቱን በማስፋፋት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ 1,547 ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በመገንባት ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡
እነዚህ መሠረተ ልማቶች፣ ነዋሪው በቅርበት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን እንዲያከናውን በማስቻል የከተማዋን የስፖርት ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ቀይረውታል።
በተጨማሪም የአካል ብቃት እንቅስቃሴን የህይወት ዘይቤና ባህል በማድረግ ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበት እና በሚሰራበት አካባቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማዘውተር ጤናማና አምራች ዜጋ እንዲሆን እንዲሁም የጋራ ትውስታ (Shared Memories) እንዲኖረው አስችለውታል ።
የመንግስት ግዥ አሰራርን ለማዘመንና ግልጽነትን ለማስፈን አዲስ አዋጅና መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለጸ፡፡
#############################
ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥ ዳይሬክቶሬት በከተማዋ የሚታየውን ሰፊ የልማት ፍላጎት በብቃት ለማስተናገድና አሰራሩን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ ቢሮው አዲስ አዋጅና መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መግባቱን አስታወቀ።
የቀድሞው የመንግስት ግዥ አዋጅ ከ16 ዓመታት በላይ ያገለገለ በመሆኑ አሁን ላይ በከተማዋ ካለው ፈጣን የኮሪደር ልማት፣ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና የዋጋ ንረት ጋር አብሮ መጓዝ ባለመቻሉ አዲሱን አዋጅ በካቢኔ አጽድቆ ስራ ላይ ማዋል የግድ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ዳንኤል ብዙአየሁ ገልፀዋል፡፡
ይህ አዲስ አሰራር በተለይም ከዚህ ቀደም በቢሮው ደረጃ ይሰጥ የነበረውን የልዩ ግዥ ፈቃድ ጥያቄ አግባብነትን በመመርመር በቀጥታ ለባለድርሻ ተቋማት ውሳኔ የመስጠት ስልጣን በማጋራቱ፣ የልማት ፕሮጀክቶች ያለምንም የአሰራር መጓተትና መወሳሰብ በፍጥነት እንዲከናወኑ ትልቅ በር ከፍቷል ብለዋል።
ዳይሬክቶሬቱ በሰው ኃይልና በንብረት ረገድ ያሉበትን ውስንነቶች ተቋቁሞ የመንግስትንና የሕዝብን ሀብት ከብክነት ለመታደግ ከፍተኛ የክትትል፣ የድጋፍና የኦዲት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፤ በተለይ በየዓመቱ ግንቦት እና ሰኔ ወራት ላይ የሚስተዋሉ ያልተገቡ የግዥ ጥያቄዎችና ብልሹ አሰራሮችን አስቀድሞ ለመከላከል ከሚያዝያ 28 ጀምሮ ጥብቅ የግዥ እገዳ ተጥሎ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል። ይሁን እንጂ የሕዝብን የዕለት ተዕለት ሕይወትና ደህንነት በቀጥታ የሚነኩ እንደ ሆስፒታሎች የመድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶች ግዥዎች፣ እንዲሁም የትምህርት ቤቶች የብሔራዊ ፈተና ዝግጅቶች ከዚህ እገዳ ውጭ ተደርገው በግልጽ ጨረታ እንዲስተናገዱ በመደረጉ ማህበረሰቡ ሊያገኝ የሚገባው አገልግሎት እንዳይስተጓጎል መደረጉን ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል በአሰራር ሂደት ውስጥ ጥፋትና የህግ ጥሰት በሚፈፅሙ ተጫራቾችና ተቋማት ላይ ተቋሙ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችና ባለሙያዎች የሚጠቆሙ የሙስና እና የህግ አሰራርን ያልተከተሉ የድብቅ ግዥዎችን በመመርመር በርካታ ብልሹ ግዥዎችን ማስቆም የተቻለ ሲሆን፣ በጥፋት ላይ የተሰማሩ ተጫራቾችም እንደ ጥፋታቸው ክብደት ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ከማንኛውም የመንግስት ጨረታ እንዲታገዱ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ቢሮው አዲሱን አዋጅና መመሪያ ተደራሽ ለማድረግ ለአመራሮችና ለባለሙያዎች ሰፊ ስልጠናዎችን የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይም ከነጋዴውና ከቀሪው ማህበረሰብ ጋር በጋራ በመስራት የከተማዋን በጀት ለታለመለት የሕዝብ ልማት ብቻ እንዲውል ቁርጠኛ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
ቢሮው የከተማዋ የፋይናንስ አፈጻጸምና የውስጥ ኦዲት ጥራትን በማጠናከር የነዋሪዎቿን ፍላጎት ለማርካት እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡
#######################################################################
ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ፣ ከተማዋ ያላትን ጠንካራ የፋይናንስ አቅምና የውስጥ ኦዲት አሰራርን ለማጠናከር እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኃላፊው እንደገለጹት፣ ባለፈው ዓመት ዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ኤጀንሲዎች በስድስት የአፍሪካ ከተሞች ላይ ባደረጉት የፋይናንስ አፈጻጸም ግምገማ አዲስ አበባ ቀዳሚ ሆና ተገኝታለች።
የኦዲት ግኝቶችን ማጥራት መደበኛና ፎርማል ኦዲት በማስደረግ ረገድ አዲስ አበባና ናይሮቢ ቀዳሚ ቢሆኑም፣ በአዲስ አበባ የኦዲት ሪፖርቶች ላይ የሚታዩ ጥቃቅን ግኝቶችን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ ይገባል። የውጭ አበዳሪዎችና አጋሮች እምነት የሚገነባው ጥራት ባለውና ነጻ በሆነ የኦዲት ሪፖርት ላይ በመሆኑ ሂሳብን በየዓመቱ በአግባቡ መዝጋትና ተከፋይና ተሰብሳቢ ሂሳቦችን በዲስፕሊን ማጽዳት እንደሚገባ ኃላፊዉ አሳስበዋል፡፡
የግዥና የበጀት ዝውውር ስነ-ስርዓት ካልታቀዱና ካልተዘጋጁ የግዥ ሂደቶች በመውጣት፣ ግዥን በእቅድ መምራትና የበጀት ዝውውር በአዋጅና በIFMIS መካከል የሚፈጥረውን ክፍተት ማረም እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በማህበረሰቡ ዘንድ ያለው የልማት ፍላጎትና የአቅርቦት ልዩነት ከ350 ቢሊዮን ብር በላይ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው፣ በአሁኑ ወቅት በየወረዳውና ክፍለ ከተማው ትላልቅ የካፒታል ፕሮጀክቶች፣ የሥራ ዕድል ፈጠራና የኑሮ ማረጋጋት ሥራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ እያንዳንዱን ብር ከብክነት ማዳን ወሳኝ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑት የውስጥ ኦዲት ባለሙያዎች ነባር በመሆናቸው ያላቸውን ልምድ በመጠቀም ችግሮችን በንቃት (Proactively) እንዲፈቱ እና አዳዲስ አሰራሮችን በመጠቀም ከተማዋ የጀመረችውን የልማት ጉዞ በፋይናንስ ስነ-ስርዓት እንዲደግፉ አመላክተዋል፡፡
የቢሮዉ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበበ እንደገለፁት የጋራ ስኬትን ለማምጣትና የሀብት ብክነትን ለመቀነስ በተከናወኑ የትስስር ሥራዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸው ተናግረው በተደረገው ተከታታይ ክትትልና ድጋፍ በከተማ፣ በክፍለ ከተማና በዋና ኦዲተር ግኝቶች ላይ የክትትል ሥርዓት በመዘርጋት 75 መሥሪያ ቤቶች የእርምት እርምጃ እንዲወስዱ የተደረገ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ብር 187,700,263.35 ላይ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉ ታውቋል ።
በትስስር ሥራዎቹ የኦዲት ሽፋንን 3242 ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም ከዕቅድ (2500) በላይ 171% አፈፃፀም ማሳየቱና የኦዲት ሪፖርት ጥራትንም 85% ማድረስ መቻሉ በጥንካሬ ጠቅሰዋል ።
በኦዲት ግኝቶች ላይ የሚወሰደው የእርምት እርምጃ ከባለፉት ዓመታት አንፃር መሻሻል ማሳየቱና ባለው የሰው ኃይል ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ መሞከሩ በበጎ ጎኑ አንስተው በቀጣይም የውስጥ ኦዲት ነጻና ገለልተኛ ሆኖ እንዲሠራ ያሉበትን የሰው ኃይልና የጥቅማጥቅም ችግሮች መፍታት እንደሚያስፈልግ ዳይሬክተሯ ጠቁመዋል፡፡
ለበጀት ዓመቱ ዕቅድ ሲታቀድ ለስጋት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት የበላይ ኃላፊዎችንና የከተማ አስተዳደሩን የትኩረት አቅጣጫ መሠረት ያደረገ የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ አቅጣጫ መቀመጡን ወ/ሮ መዓዛ ለቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ገልፀዋል። ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
ጎስቋላ ከባቢዋን የቀየረችው አዲስ አበባ!
መዲናችን አዲስ አበባ፣ ዕድሜ ጠገብ ባለታሪክ ከተማ ብትሆንም፣ ስምና ዕድሜዋን የሚመጥን ዕድሳት ሳይደረግላት በመቆየቱ፣ መንደሮቿና መንገዶቿ የፈራረሱ ለዓይን የማይጥሙ፣ አፍንጫ የሚሰነፍጡ ሆነው ቆይተዋል።
ይሁን እንጂ፥ ባለፈው ኣጭር ጊዜ በተሰራው ስኬታማ ስራ ከተማዋ ገፅታዋን እየለወጠች፣ የምትጀምራቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እያጠናቀቀች፣ ነዋሪዎቿን እያቀፈች፣ መስህቦቿን እያበዛች፣ የአፍሪካ የብልፅግና ፊት የመሆን ፅኑ መንገዷን ይዛ ትገኛለች፡፡
አዲስ አበባ፥ ውብ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስፋት ለዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ኩነቶች የምትመረጥ፣ ንፁህ፣ አረንጓዴ ውብ ሥፍራን የተላበሰች፣ አሰራሯን ያዘመነች ህብረ ብሄራዊነቷን የጠበቀች ሰላም ያላት ውብ ከተማ መሆን ችላለች።
በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሰው ተኮር ልማቷ የብዙ ነዋሪዎቿን እንባ ያበሰች፣ መደገፊያ መጠጊያ የሆነች፣ ተስፋን የሰጠች የተጣሉትን ያስታወሰች ፣ የተራቡትን ያጎረሰች፣ የነገ ህፃናቶቿን የደገፈች፣ተማሪዎቿን ያስታወሰች፣ ማዕድ ያጋራች፣ የኑሮን ጫና ለማቃለል ሸክምን የተጋራች ፣ሌማት እንዲሞላ ያበረታታች እንደ አዲስ የተፈጠረች ከተማ ለመሆን በቅታች፡፡
ድንበርና ዘመን ያልገደበው የዐድዋ ድል፦ የፔንስልቬንያ ምክርቤት ያሳለፈው ውሳኔ የኢትዮጵያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ዳግም ከፍ አድርጓል!
የአሜሪካው የፔንሲልቫኒያ ሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት የዐድዋ ድል መታሰቢያን እውቅና የሚሰጥና ማርች 2 የድል በዓሉ
በፔንስልቬንያ እንዲከበር የሚፈቀድ H.R 441 የሚል ስያሜ የተሰጠውን የውሳኔ ሀሳብ አጸደቀ።
ምክርቤቱ ባስተላለፈው የውሳኔ ሀሳብ ኢትዮጵያውያን በወቅቱ አፍሪካን ለመቀራመት ሲደረግ የነበረውን የኮሎኒ እንቅስቃሴን በጋራ በመሆን በማሸነፍ ኢትዮጵያ ብቸኛዋ የአፍሪካ ሀገር መሆን መቻሏን በከፍተኛ አድናቆት በማውሳት፣ ዐድዋ የዓለም አቀፍ የነጻነት፣ የክብር እና የአንድነት ምልክት መሆኑን አንስተዋል።
የውሳኔ ሀሳቡ አኩሪ የሆነው የዐድዋ መታሰቢያን ብቻ ሳይሆን በፔንስልቬንያ እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በጤና፣ በንግድ፣ በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር፣ በትምህርት እና በአገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪ ይበልጥ እንዲጠናከር እንደሚሰራ አረጋግጧል።
ከዚህ ምን አይነት ትምህርት እንቀስማለን?
ዛሬም እንደትናንቱ ጠንክረን ከሰራን፣ ከተባበርን፣ ቀጣይ ትውልዶች የሚዘክሩት ድሎችን በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ዘርፍ ማስመዝገብ እንችላለን። ይህ ትውልድ በከተማም ሆነ በገጠር እያመጣ ያለው ሁለንተናዊ ለውጥ ወደቀጣይ ድሎች እያመራን ስለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለንም።
ኢትዮጵያ በልጆች መስዋዕትነት ተፈርታና ተከብራ ለዘላለም ትኖራለች!
https://www.facebook.com/share/p/18zPpywme1/
ከቱሪስት መተላለፊያነት ወደ ቀዳሚ መዳረሻነት የአዲሷ አዲስ አበባ ቱሪዝም ሽግግር
ቀደም ሲል የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል በመሆን ብቻ የምትታወቀው የአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ፣ ዛሬ ላይ የውበት፣ የጥንካሬ እና የዘመናዊነት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን በክብር መጋበዝ ጀምራለች።
የከተማዋን ገጽታ በዋናነት ከቀየሩት ሥራዎች መካከል የኮሪደር ልማቱ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
እግረኞችን፣ ብስክሌተኞችን እና አካል ጉዳተኞችን ያማከሉ ሰፋፊ መንገዶችን ያካተተ በመሆኑም ከተማዋን በእግር ለመጎብኘት እጅግ ምቹ አድርጓታል።
ከዚህ በተጨማሪም ቀደም ሲል በቆሻሻ ተሸፍነው የነበሩት የወንዝ ዳርቻዎች በሸገር ፕሮጀክት አማካኝነት ዛሬ ወደ ውብ የአረንጓዴ መናፈሻነት ተቀይረዋል።
እንደ ወዳጅነት አደባባይ፣ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ታላቁ ብሔራዊ ቤተመንግስት፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአድዋ ሙዚየም ያሉ ታላላቅ የቱሪስት መስህቦች መገንባትም የከተማዋን ድምቀት አሳድገውታል።
እነዚህ አዳዲስ ስፍራዎች ዓለም አቀፍ እንግዶች በከተማዋ የሚያሳልፉትን ጊዜ እንዲያራዝሙ በማድረጋቸው፣ በሆቴልና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፉ ላይ ከፍተኛ የገበያ መነቃቃት ፈጥረዋል።
የቱሪስቶች የቆይታ ጊዜ መራዘምና የጎብኚዎች ቁጥር መጨመርም የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ፍሰት በከፍተኛ ሁኔታ ከፍ አድርጎታል።
እነዚህ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ከተማዋን ስማርት እና ውብ በማድረግ፣ የአፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ ትላልቅ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን እና ሁነቶችን ይበልጥ እንድትስብ ተጨማሪ አቅም ፈጥረውላታል።
የልማት ሥራዎቹ ከቱሪዝም ዘርፍ ባሻገር ዘላቂ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም ሰፊ ሚና አበርክተዋል።
በተለይም በፓርኮች ጥበቃ፣ በጽዳት፣ በአስጐብኝነት እና በተለያዩ የንግድ ሱቆች ውስጥ ለብዙ ሺህ ወጣቶችና ሴቶች አዲስ የገቢ ምንጭ መሆን ችለዋል።
ቀደም ሲል በከተማ አስተዳደሩ በቀረበው የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ እንዳመላከተው አዲሷ አዲስ አበባ የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት ባረጋገጠ እና የቱሪዝም መዳረሻነቷን ባሳደገ መልኩ የዘመናዊነት ተምሳሌት ሆና ትቀጥላለች።
AMN
የአዲስ አበባ የ3 ዓመት የፊስካል ማዕቀፍ (MTEF) ዕቅድ የከተማዋን የገቢ አቅም እንደሚያሳድግ ተገለፀ፡፡
#########################################
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ከሁሉም መስሪያ ቤቶች፣ ማዕከላትና ክፍለ ከተሞች መረጃዎችን በማሰባሰብ የ2019-2021 የመካከለኛ ዘመን የውጪና ገቢ ማዕቀፍ (MTEF) ረቂቅ እቅድ ዝግጅትን ማጠናቀቁን ገለፀ።
ይህ የሶስት ዓመት እቅድ በከተማዋ ውስጥ የሚደረጉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን መነሻ ያደረገ ሲሆን፣ በዘንድሮ ለየት የሚያደርገው በውጭ አማካሪ የተጠናው የከተማዋ የገቢ አቅም ጥናት እንደ ዋና ግብዓት ጥቅም ላይ መዋሉ ነው። ከተማዋ አሁን ላይ በቱሪዝም፣ በስፖርትና በኮንፈረንሶች ዓለም አቀፍ ትኩረትን እየሳበች መሆኗ እንዲሁም የተገነቡት የኮሪደር ልማቶች፣ ፓርኮችና የቤት ግንባታዎች ለቀጣይ የገቢ ትንበያው ትልቅ መሠረት ሆነዋል ሲሉ የቢሮዉ የፊስካል ፖሊሲ እና ገቢ ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ የሆኑት አቶ በለጠ ሞገስ ገለፁ።
የከተማዋ ገቢ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣ ሲሆን በ2014 ዓ.ም ወደ 70 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 350 ቢሊዮን ብር እቅድ ተይዞ ስራ ዉሏል። በአሁኑ ወቅት ከ70 ፐርሰንት በላይ የሚሆነው የከተማዋ ገቢ ከታክስ የሚሰበሰብ ቢሆንም ወደፊት የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢዎችን አሰባሰብ ለማሳደግ ጥናቱ ትልቅ እገዛ እንደሚደርግ አቶ በለጠ ገልፀዋል።
ቢሮው የገቢ ትንበያውን ተከትሎ የገቢና ወጪ ማመጣጠን ስራዎችን ያከናወነ ሲሆን የተቋማት የወጪ ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ አብዛኛው በጀት (ከ70 ፐርሰንት በላይ) የህብረተሰቡን መሰረታዊ ጥያቄዎች ሊመልሱ ለሚችሉ እንደ ውሃ፣ መንገድ፣ ትምህርት እና ጤና ላሉ የካፒታል ፕሮጀክቶች እንዲውል ተለይቷል ብለዋል።
ከ2013 ዓ.ም በፊት መደበኛ እና የካፒታል በጀት ተቀራራቢና ለዕለት ተዕለት ወጪዎች (Recurrent) የሚዉል የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ለልማት የሚመደበው በጀት በመጨመሩ ከ70 በመቶ በላይ በመሆኑ የከተማዋን እድገት እያፋጠነው እንደሚገን ገልፀው ሆኖም በተቋማት የወጪ ፍላጎት እና በታቀደው በጀት መካከል ልዩነት (Gap) በመኖሩ በቀጣይ ጥብቅ የወጪ ቁጠባ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ዳይሬክተሩ አመላክተዋል።
ይህ ረቂቅ እቅድ በቀጣይ በከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ከፀደቀ በኋላ ተቋማት በሲስተም በጀታቸውን እንዲያቀርቡ ይደረጋል። በመጨረሻም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ተደርጎበት በከተማው ምክር ቤት በህግ ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማ
የከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪት ክምችት ብቻ ሳይሆን፣ ነዋሪዎች በክብር፣ በምቾትና በደህንነት በሚኖሩበት ዘመናዊ ሥርዓት ይለካል።
ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስከ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ በተዘረጉት አምስት ዓመታት፣ የመደመር ትውልድ የከተሞቻችንን የትላንት ገፅታ በመቀየር፣ ከተሞችን ከድህነትና ከጥግግት አውጥቶ ለነዋሪዎቻቸው የተመቹ የብልፅግና ማዕከላት እንዲሆኑ አስደናቂ ስራዎችን በመንግሥት መሪነት አከናውኗል።
በእነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች ጎልቶ ከሚታየው ስኬት አንዱ የቤት ልማት አብዮት ነው። ቀደም ሲል ዘላቂና ውጤታማ ያልነበረውን የቤት ልማት ፕሮግራም በአዲስ መልክ በመቃኘት ታላቅ የቤት አቅርቦት ንቅናቄ ተደርጓል።
መንግሥት በዋነኝነት ሲያከናውነው የነበረውን ልማት ከግል ዘርፉ እንዲሁም ከመንግሥትና የግል አጋርነት (PPP) ጋር በማስተሳሰር የቤቶች ልማት በከፍተኛ ፍጥነት እንዲከናወን ተደርጓል። በዚህም ከ2013 እስከ 2017 በጀት ዓመት ባሉት ጊዜያት ብቻ ከመንግሥት፣ ከሪል ስቴት አልሚዎችና ከግል ቤት ሠሪዎች አቅም ጋር ተደምሮ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ቤቶች ተገንብተዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም፣ ዐቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ቤት ፈላጊዎች በመንግሥት በኩል የሚከናወኑ የቤት ልማት ፕሮግራሞች ሳይቋረጡ ቀጥለዋል።
የመደመር ከተሜነት ሰውን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ፣ ማኅበረሰብን በማስተባበር ዐቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች 166,207 ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል። ከተሞችን ከእርጅናና ከድህነት ገፅታ ለማላቀቅ፣ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቤቶችን ደረጃ የማሳደግ ሥራ በስፋት ተከናውኗል። በ2013 ዓ.ም ከ75 በመቶ በላይ የነበረውን ከደረጃ በታች የሆኑ (substandard) ቤቶች ድርሻ፣ በ2017 ዓ.ም ወደ 52 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል። ይህ ዜጎችን ከማይመችና ኋላቀር አኗኗር ወደ ዘመናዊ የኑሮ ሁኔታ በፈቃደኝነት ያሸጋገረ የክብር ጉዞ ነው።
ይህ ታላቅ የከተማ ትራንስፎርሜሽን የሲቪል ሰርቪሱንና የከተሞችን አገልግሎት ከማዘመን ጋር ተጣምሮ የተጓዘ ነው። ከተሞች ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው በማድረግ፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ለዜጎች በተሻለ ቅልጥፍና እንዲቀርቡ ተደርጓል።
ይሁን እንጂ፣ መንግሥት ከተሞችን በተቀናጀ አግባብ ሲያለማ፣ አንዳንድ ኃይሎች ይህንን የልማት አቅጣጫ ባለመረዳት የተዛባ አመለካከት ሲያራምዱ ቆይተዋል። ዜጎችን ወደ ተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለማሸጋገር የሚሰሩትን የመልሶ ማልማት ስራዎች "ማፈናቀልና ማህበራዊ ኢንጂነሪንግ" ብለው ሲስሉ፣ የከተማን ይዞታ ስርዓት ለማስያዝና አረንጓዴ ቦታዎችን ለመጠበቅ የሚወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን በሌላ ስም ለማጠልሸት ሞክረዋል። አልፎ ተርፎም ከተሞቻችን ባህላችንንና ታሪካችንን እንዲያንፀባርቁ ለማድረግ የተሰሩትን የውበት ሥራዎች "ታሪክን እንደ ማውደም" አድርገው አቅርበዋል።
ሆኖም እውነታው በተግባር ሊደበቅ አይችልም። ዜጎቻችን የስራዎቹን ፋይዳ አውቀው ምስክርነታቸውን ሲሰጡ፣ የውጭ ሀገራት ሚዲያዎችና ዜጎች ሳይቀሩ በከተሞቻችን ላይ የተመዘገቡትን አስደናቂ ለውጦች እያደነቁ ይገኛሉ። የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የሲቪል ሰርቪሱን ውጤታማ ለማድረግ የሚከናወኑ ሪፎርሞችንም አሉታዊ ስም በመስጠት ለውጡን ለማደናቀፍ የተሞከሩ ሙከራዎች ከሽፈዋል። በአጠቃላይ እነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ መንግሥት ከተሞችን የነገው ዘመን የሥልጣኔ ማዕከላት ለማድረግ ያለውን ግልጽ አቋምና የማድረግ አቅም በተግባር ያረጋገጡ፣ እንዲሁም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን የፈጠሩ ደማቅ ታሪካዊ ምዕራፎች ናቸው።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
ታላቅ ወንድሜ እና ውድ ወዳጄ ክቡር ናሬንድራ ሞዲ፣ የዓለማችንን ትልቁን እና እጅግ ንቁ የሆነውን የዲሞክራሲ ማህበረሰብ ዘላቂ እምነት በማግኘት፣ ህንድን በራዕይ እና በቁርጠኝነት በተከታታይ ሶስት የዲሞክራሲያዊ የስልጣን ዘመናት በመምራት ላስመዘገቡት ታሪካዊ ስኬት የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ።
የእርሳቸው አመራር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከድህነት ያወጣ፣ የዲጂታል ሕዝባዊ መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ያስፋፋ እና ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ የመሰረተ ልማት እድገትን በማምጣት ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ያስገኘ ነው። በተጨማሪም በተከታታይነት ለደቡቡ የዓለም ክፍል (Global South) ጠንካራ ድምጽ በመሆን አገልግለዋል።"
አዲስ አበባ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስህበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች!
ዛሬ ከጤና ሚንስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና ከአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዦን ካሴያ ጋር በቀጣይ ኖቬምበር ወር ላይ ከተማችን አዲስ አበባ 5ኛውን አለምአቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማካሄድ መመረጥዋንና ኮንፈረንሱን በጋራ ለማዘጋጀት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬአማ ውይይት አድርገናል።
አዲስ አበባ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በመሰረተ ልማት በሰራናቸው ስራዎች ፣ በነዋሪዎቻችን እንግዳ ተቀባይነት፣ሰላሟ የተረጋገጠ ከተማ በመሆኗ እና የተለያዩ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ለማካሄድ ምቹ ከተማ መሆን በመቻሏ “የአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነት እና ደህንነትን ማላቅ/...to advance Africa’s health soverignity and security agenda./ በሚል 5ኛውን ዓለምዓቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዝግጅቶች በስፋት በጋራ በመከናወን ላይ ነው፡፡
5ኛውን ዓለምዓቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ የሃገራት መሪዎች ፣ሚኒስትሮች ፣የህብረተሰብ ጤና መሪዎች፣ፖሊሲ አውጭዎች ፣ተመራማሪዎች እና ባለድርሻ አካላትን የሚሳተፉበት ትልቅ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ነው ።
ፊጣሪ ኢትዮጵያና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
