fa
Feedback
BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

رفتن به کانال در Telegram

AACABOF PUBLIC PAGE

نمایش بیشتر
2 904
مشترکین
-324 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
የሕ/ተ/ም/ቤት አባላት የ5 ዓመት የአገልግሎት ዘመን ማጠቃለያን በተመለከት የተላለፈ ምስጋና #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
የሕ/ተ/ም/ቤት አባላት የ5 ዓመት የአገልግሎት ዘመን ማጠቃለያን በተመለከት የተላለፈ ምስጋና #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የውጭ ጉዳይና ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦ ዓለም ሊካድ በማይችል ሁኔታ ተለዋዋጭ በሆነችበት በዚህ ወቅት፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ የውጭ ፖሊሲ እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር በስትራቴጂካዊ ራስን መቻል
የውጭ ጉዳይና ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦ ዓለም ሊካድ በማይችል ሁኔታ ተለዋዋጭ በሆነችበት በዚህ ወቅት፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ የውጭ ፖሊሲ እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር በስትራቴጂካዊ ራስን መቻል ላይ የተመሠረቱ ሦስት ዋና ዋና መርሆችን እንከተላለን፤ የመጀመሪያው መቋቋም ሲሆን፤ ይህም የውጭ ተጽዕኖዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ አቅምን መገንባት ላይ ያተኩራል። ሁለተኛው መጠቀም ሲሆን፤ ይህም ማንኛውንም የሚያጋጥም ፈተና ወደ ስትራቴጂካዊና መልካም የልማት ዕድል የመቀየር ብቃትን ያካትታል። ሦስተኛው ደግሞ መግራት ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ የራሷን ብሔራዊ አጀንዳ ቀርጻ ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በልበ ሙሉነት እንድትጋፈጥና እንድትመራ ያስችላታል። በእነዚህ ሦስት ምሰሶዎች በመመራት በማንኛውም ብሔራዊ ውሳኔያችን ላይ የትኛውንም የውጭ አካል ጣልቃ ገብነት ፍጹም አንፈቅድም። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

ሠላምን በሚመለከት #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
ሠላምን በሚመለከት #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የትምህርት ዘርፍ ጥራት እና ለውጦችን በተመለከተ፦ የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው። ባለፉት ዓመታት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ፈተና የሚወስዱበት አሰ
የትምህርት ዘርፍ ጥራት እና ለውጦችን በተመለከተ፦ የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው። ባለፉት ዓመታት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ፈተና የሚወስዱበት አሰራር ተተግብሯል፤ በዚህም የኩራጃ ባህልን ማስረቀት ተችሏል። ትምህርት ከታች ካልተሠራ ከላይ መሥራት ውጤታማ አያደርግም፤ ለመዋዕለ ህጻናት ማስፋፊያ በተሰጠው ትኩረት 35 ሺህ መዋዕለ ሕጻናትን መገንባት ተችሏል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ኩረጃን ለማስቀረት፣ ትምህርትን በቴክኖሎጂ ለማስፋፋት እየተደረገ ያለው ሙከራ ተስፋ ሰጪ ነው። የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ አበረታች ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የጤና ጉዳዮችን በሚመለከት፦ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረት አቅማችንን ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማሳደግ ችለናል። ለአጠቃላይ መድኃኒት ግዢ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ደ
የጤና ጉዳዮችን በሚመለከት፦ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረት አቅማችንን ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማሳደግ ችለናል። ለአጠቃላይ መድኃኒት ግዢ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ደግሞ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርገናል። ባለፉት ወራት በርካታ ሆስፒታሎችን መርቀን ለአገልግሎት ያበቃን ሲሆን፣ በሚቀጥሉት ወራት የሚመረቁ ሌሎች ተቋማት ይኖራሉ። ለግንባታ ሂደት ትኩረት ከተሰጣቸው መካከል የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን የአልጋ አቅም በአንድ ሺህ ያሳደገው አዲሱ ሕንፃ ይጠቀሳል። በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ተደርገው የተሰሩ ናቸው። ቀጣዩ ትኩረታችን በውጭ ሀገራት የምናያቸውን ዘመናዊና ደረጃቸውን የጠበቁ ሆስፒታሎችን በሀገራችን መገንባት ነው። በሌላ በኩል፣ የወባ በሽታን ለመቀነስ በተደረገው የተቀናጀ ጥረት 14 ሚሊዮን አጎበር የተሰራጨ ሲሆን፣ በ3 ሚሊዮን መኖሪያ ቤቶች ላይ ደግሞ የጸረ-ወባ ኬሚካል ተረጭቷል። በተጨማሪም፣ ቀደም ሲል የክትባት ተደራሽነት ባልነበረባቸው 58 ወረዳዎች ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ክትባት መስጠት ተችሏል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የኢትዮጵያን ጽናት በሚመለከት #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
የኢትዮጵያን ጽናት በሚመለከት #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

ሰላምና መረጋጋትን በተመለከት “በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ለመፍታት መንግሥት ከ4000 በላይ የምክክር መድረኮችንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታ
ሰላምና መረጋጋትን በተመለከት “በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ለመፍታት መንግሥት ከ4000 በላይ የምክክር መድረኮችንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁን የብሔራዊ መግባባት ምእራፍ ተሻግረናል። ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናክረ ውይይት ብቻ ነው።” #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የሃይማኖት መቻቻልን በተመለከተ፦ ‎ ‎ኢትዮጵያ በጋራ እሴቶች እና በተቋማት የምትገነባ ሀገር እንጂ በግጭት የምትፈርስ አይደለችም። በአብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚከተላቸው እምነቶች የተቀራረቡ እና
የሃይማኖት መቻቻልን በተመለከተ፦ ‎ ‎ኢትዮጵያ በጋራ እሴቶች እና በተቋማት የምትገነባ ሀገር እንጂ በግጭት የምትፈርስ አይደለችም። በአብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚከተላቸው እምነቶች የተቀራረቡ እና የሰላም ተምሳሌቶች ለመሆናቸው፣ በታሪክም አብረው የመኖራቸው እውነታ ለዚህ ምስክር ነው። ወቅታዊ ግጭቶች የሃይማኖት ወይም የብሄር ሳይሆኑ፣ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ጥቅምን ለመደበቅ በነውጠኞች የሚቀሰቀሱ ናቸው። በመሆኑም ሀገርን በዘላቂነት ለማጽናት ህዝቡ የጥላቻ ቅስቀሳዎችን በመመከት፣ እንደ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ያሉ የሀገር ህልውና ጠባቂ ተቋማትን በሰለጠነ መንገድ ማክበር እና መደገፍ ይገባዋል። ‎ ‎#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የዘንድሮን ምርጫ በሚመለከት #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
የዘንድሮን ምርጫ በሚመለከት #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ ለኢትዮጵያ ልጆች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ላለፉት አምስት ዓመታት በፓርላማ ቆይታቸው ኢትዮጵያን ላገለገሉ የብልጽግና ፓርቲ አባላት እና የሌሎች ፓርቲ አባላትን በከፍተኛ አክብሮት አመስግነዋል። በተለይም በዘንድሮ በሚመሠረተው መንግሥት አካል ለማይሆኑት የፓርላማ አባላት በሌላ የመንግሥት ኃላፊነት እንዲያገለግሉ የመንግሥታቸው ፍላጎት መሆኑን ጠቁመዋል። “አንዳንዶቻችሁ በሚቀጥለው ምክር ቤት ከእኛ ጋር የማትቀጥሉ መሆኑን የዘንድሮ ምርጫ ያሳየ ቢሆንም ክቡር አቶ ደሳለኝ ጫኔ የመጨረሻ ያሉት ንግግር የመጨረሻ ባይሆን የመንግሥትት ምኞት መሆኑን እና ከምክር ቤት ውጪ እነዚህ አባላት ከመንግሥታችን ጋር በጋራ ሆነን ኢትዮጵያን እንድናገለግል በተከበሩ ምክር ቤት ፊት ጥሪ ላቀርብላችሁ እፈልጋለሁ” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። “መንግሥትታችን እናንተን አካትቶ ኢትዮጵያን ማልማት ይፈልጋል። ኢትዮጵያ የጋራ ሀገራችን ናት። እኛም፣ እናንተም ልጆቿ በምክር ቤት ብቻ ሳይሆን በተለያየ ዘርፍ ተባብረን ኢትዮጵያን እንድናበለጽግ አብረን እንድንሠራ ጥሪ ላቀርብላችሁ እፈልጋለሁ” ብለዋል።

በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተነሡ ጥያቄዎች፦ ***** 👉 የወደብ የኅልውናችን ጉዳይ ነው፤ የወደብና የባህር በር ጉዳይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቢገልጹልን? 👉 የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት በተያዘለት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ተጠናቅቆ የታለመለትን ሀገራዊ ዓላማ እንዲያሳካ መንግሥት በቀጣይ ምን ዓይነት የሎጂስቲክስ፣ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ድጋፍ ያደርጋል? 👉 ተጀምረው ላልተጠናቀቁ እና ታቅደው ላልተጀመሩ ፕሮጀክቶች ምን የታሰበ ነገር አለ? 👉 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለመንግሥት ሠራተኞች የኑሮ ጫናን ለመቋቋም ምን ታስቧል፤ ከሚመሠረተው አዲሱ መንግሥት ምን እንጠብቅ? 👉 የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ስለሆነ ለሁሉም ክልሎች አስገዳጅ ሆኖ ቢቀርብ? 👉 የመንግሥት መዋቅር ተጠቅሞ በዜጎች ላይ ምዝበራ የሚፈጽሙ አካላት ላይ ገዥው ፓርቲ መዋቅሩን የማጽዳት እና ተጠያቂነትን የማስፈኑን ጉዳይ እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል? 👉 ከፀጥታ አኳያ እየተሻሻሉ ያሉ ጉዳይ ቢኖርም፣ አሁንም አንዳንድ ቦታዎች ችግሮች አሉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን መፍትሔ ለመስጠት ታስቧል? 👉 ከነዳጅ ጋር በተያያዘ፦ መንግሥት ለነዳጅ ድጎማ ቢያደርግም የነዳጅ ሽያጭ እና ስርጭት ከብልሹ አሠራር ሊድን አልቻለም። በዚህ ላይ መንግሥት የያዘው መፍትሔ ምንድን ነው? 👉 በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የትግራይ ሕዝብ የሰላም እንዲያገኝ በመንግሥት በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ቢያሳውቁን? 👉 ሰላምን ወደ ዘላቂ መሠረት ለማሸጋገር ከምሁራን፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከህዝቡ ምን አይነት ንቁ ተሳትፎ ይጠበቃል? 👉 በትላልቅ ፕሮጀክቶች ምክንያት የሚነሡ ዜጎች መብት በአግባቡ እየተጠበቀ አይደለም የሚል ቅሬታ አለ። ፍትሐዊ የሆነ የካሳ አከፋፈል እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ምን ይደረጋል? 👉 የጠቅላይ ኦዲተር ሪፖርቶች ተደጋጋሚ የፋይናንስ ጉድለቶችን ቢያሳዩም፣ ተጠያቂነትን በማስፈን ረገድ ክፍተቶች አሉ። መንግሥት ተቋማትን ከሙስና እና ከመዝባሪ ኃይሎች ለማጽዳት ምን አዲስ አሠራር ይዘረጋል?

ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ቀዳሚ መሆኗን አይኤምኤፍ ገለፀ! ኢትዮጵያ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት (Purchasing Power Parity - PPP) ስሌት ከምስራቅ አፍሪ
ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ቀዳሚ መሆኗን አይኤምኤፍ ገለፀ! ኢትዮጵያ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት (Purchasing Power Parity - PPP) ስሌት ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ መሆኗን የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) አስታወቀ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ በዚሁ የመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ሚዛን 558 ነጥብ 93 ቢሊየን ዶላር የሚያህል ግዙፍ ዓመታዊ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (GDP-PPP) ማስመዝገቧን ጠቅሷል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ከኬንያ እና ታንዛኒያ በመቅደም ከምስራቅ አፍሪካ በአንደኝነት እንድትቀመጥ አስችሏታል። እነዚህ ሦስቱ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ) በጋራ 1 ነጥብ 35 ትሪሊየን ዶላር ዓመታዊ የመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ጥቅል ዓቅም ማስመዘገባቸውን የአይኤምኤፍ ሪፖርት አመልክቷል፡፡ ይህም ከደረጃ 4 እስከ 19 ላይ የሚገኙ በርካታ የቀጠናው ሀገራት በድምሩ ካስመዘገቡት የኢኮኖሚ አቅም የተሻለ ሆኖ መገኘቱን የሪፖርቱ ትንታኔ አመልክቷል።

የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር አሰራሮችን በማዘመን በበጀት ዓመቱ ስኬታማ አፈፃፀም ማስመዝገቡን ገለፀ። ######################## ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ የፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት (ከሐምሌ 01 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም) የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል ። ዳይሬክቶሬቱ በተሰጡት ቁልፍ ተግባራትና ኃላፊነቶች ላይ ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ አመርቂ ውጤቶችንና ጥንካሬዎችን ማስመዝገቡን አስታውቋል። የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ እያሱ መረሳ በከተማ አስተዳደሩ ለትልልቅ ካፒታል ፕሮጀክቶች በተሰጠ ልዩ ትኩረትና የክፍያ አፈጻጸሙን ሲያብራሩ በበጀት ዓመቱ ለሴክተር መሥሪያ ቤቶች፣ ለክፍለ ከተሞች፣ ለተለያዩ አካላት ድጋፍና ድጎማ በአጠቃላይ ብር 271,087,576,407.98 (ሁለት መቶ ሰባ አንድ ቢሊዬን ሰማኒያ ሰባት ሚሊዬን አምስት መቶ ሰባ ስድስት ሺ አራት መቶ ሰባት ብር ከ98/100) ክፍያ መፈፀሙን ጠቁመዋል።  ከተከፈለው አጠቃላይ ክፍያ ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ የሚይዘው 70% (ብር 188,820,883,886.99) የተከፈለው ለካፒታል ሥራዎች ነው። ይህም ቢሮው በከተማዋ ውስጥ ለሚከናወኑ ትላልቅ የካፒታልና የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያሳይም አብራርተዋል። የበጀት ዕድገት ንፅፅርም የዘንድሮው የ11 ወራት አፈጻጸም ከባለፈው በጀት ዓመት (2017 ዓ.ም) ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 85,835,253,524.69 ወይም የ46.33% ብልጫና ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱ ተመላክቷል። የሂሳብ አያያዝን የማዘመንና የማሳለጥ ስራዎች በሚመለከትም የኢንተርኔት ባንኪንግ ጅማሮ በከተማ አስተዳደሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የፋይናንስ ክፍያዎችን ይበልጥ ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ በ11 ተቋማት እና በ3 ክፍለ ከተሞች በፓይለት ደረጃ በ internet Banking online ክፍያ መፈጸም መጀመሩን አቶ እያሱ ጠቁመዋል። የሂሳብ አመዘጋገብና አዘጋግ ላይ በዳይሬክቶሬቱ በተደረገው የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ መሠረት ከ100 ሪፖርት አቅራቢ ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ 92ቱ (92%) እስከ ሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ድረስ ያለውን ሂሳባቸውን ሙሉ በሙሉ አናብበውና አስታርቀው መዝጋት ችለዋል። የውዝፍ ሂሳቦች ቅናሽ እስከ 2017 በጀት ዓመት የነበረውን የውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ለማስቀነስ በተደረገ ከፍተኛ ክትትል የ9 ወራት ዕቅድ 30% የነበረ ቢሆንም፣ በተጨባጭ ግን 31.2% በማስቀነስ ከዕቅድ በላይ ማከናወን ተችሏል። ይህም የሆነው ትልልቅ ፕሮጀክቶች የከፈሏቸውን ቅድመ ክፍያዎች በፍጥነት በማወራረዳቸው ነው ። በተመሳሳይ የውዝፍ ተከፋይ ሂሳብንም 29.4% ማውረድ መቻሉ ተጠቁሟል። በተጨማሪም በተቋማት ጥያቄ መሠረት 56 አዳዲስ የባንክ ሂሳቦች እንዲከፈቱ፣ 4 ሂሳቦች እንዲዘጉ እንዲሁም 248 የፈራሚዎች ለውጥ ተደርጎ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በወቅቱ የማሳወቅሥራተከናውኗል ። ዳይሬክቶሬቱ ባጠቃላይ በዚህ የ11 ወራት የስራ ሂደት ያሳያቸውን ጥንካሬዎችና የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ በቀሪዎቹ ወራትም የሂሳብ ሪፖርቶችን በጥራት የመዝጋት እና በፓይለት ደረጃ የተጀመረውን የኦንላይን ባንኪንግ ክፍያ ወደ ሁሉም ተቋማት የማስፋፋት ስራ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል። ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !! ዌብሳይት:- aabof.com.et ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ። ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀፅ 17 እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 81 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 3 መሠረት፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለሥልጣናትን ለጥያቄ የመጥራትና የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው። በዚሁ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌና የምክር ቤቱ ደንብ መሠረት፤ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ በሚያካሂደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ በአካል ተገኝተው የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ የሚሰጡ ይሆናል። በተያያዘም ምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች የሚገኙ ሲሆን፤ የጉባኤው ሙሉ ሂደትም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ በቀጥታ ሥርጭት ለሕዝብ የሚተላለፍ ይሆናል።

‎ በአዲስ አበባ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 98 በመቶ ከፍተኛ ውጤት ሆኖ ተመዘገበ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን በተሰጠው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልቀቂያ ፈተና 98 በመቶ ከፍተኛ ውጤት ሆኖ መመዝገቡን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ‎ ‎በ2018 የትምህርት ዘመን በከተማ አስተዳደሩ 84 ሺህ 257 ተማሪዎች በ199 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናው የተሰጠ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 82 ሺህ 137ቱ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት በማስመዝገብ ማለፋቸው ተገልጿል። ‎ ‎የቢሮው ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ በሰጡት መግለጫ ፈተናውን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 548 ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን ገልጸዋል። ‎ ‎98 ከመቶው ሁለት ተማሪዎች ማስመዝገባቸውን የገለፁት ቢሮ ሃላፊው 449 ተማሪዎች 95 እና ከዚያ በላይ፣ 5ሺህ 559 ተማሪዎች ደግሞ 90 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም 82 ሺህ 137 ተማሪዎች ማለትም 97 ነጥብ 48 በመቶ 50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎በሁሉም ትምህርት ቤቶች የቀን ተማሪዎች ከተፈተኑት ውስጥ 97 ነጥብ 83 በመቶ ማለፋቸውን የገለጹት ዶ/ር ዘላለም በግል ከተፈተኑት ውስጥ ደግሞ 96 ነጥብ 66 በመቶ አልፈዋል ብለዋል። ‎ ‎ይህም የቀን የመንግስት 96 ነጥብ 80 በመቶ፣ የቀን የግል 99 ነጥብ 15 በመቶ፣ የመንግስት የማታ 91 ነጥብ 19 በመቶ፣ የግል የማታ 78 ነጥብ 92 በመቶ ማለፋቸውን አብራርተዋል። ‎ ‎በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን የተሰጠው የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አጠቃላይ የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ መሆኑንም አስታውቀዋል። ‎ ‎በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከተማ አስተዳደሩ በአጠቃላይ 84 ሺህ 257 ተማሪዎች በ199 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸው ከእነዚህ ውስጥ 82 ሺህ 137ቱ 50 እና ከዚያ በላይ አምጥተው ማለፋቸውን ገልጸዋል። ‎መደበኛ ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ፣ የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች 45 በመቶ ፣ የኦቲስቲክ፣ ዳውን ሲንድረምና ኢንተሌክቹዋል ዲሴቢሊቲ ያለባቸው ተማሪዎች 40 በመቶ የማለፊያ ውጤት እንዲሆን መወሰኑንም አብራርተዋል። ‎በ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ከሌሎች ዓመታት የላቀ መሆኑን ያነሱት ሀላፊው የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከመደበኛ ክፍለ-ጊዜ ውጭ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት እንዲሁም ተማሪዎች በሒሳብና በእንግሊዘኛ ትምህርቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ መደረጉ ለተመዘገበው ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል።