en
Feedback
📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

Open in Telegram

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾 ➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና እንጊሊዘኛ ..... መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ። 📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️ B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር 100K ይደርስ ነበር ። For any comment @Meki3

Show more
2 263
Subscribers
+124 hours
+17 days
+7330 days
Attracting Subscribers
August '26
August '260
in 0 channels
July '26
+141
in 0 channels
Get PRO
June '26
+109
in 1 channels
Get PRO
May '26
+67
in 0 channels
Get PRO
April '26
+48
in 0 channels
Get PRO
March '26
+60
in 0 channels
Get PRO
February '26
+45
in 1 channels
Get PRO
January '26
+65
in 1 channels
Get PRO
December '25
+92
in 0 channels
Get PRO
November '25
+83
in 0 channels
Get PRO
October '25
+56
in 0 channels
Get PRO
September '25
+50
in 0 channels
Get PRO
August '25
+70
in 0 channels
Get PRO
July '25
+58
in 0 channels
Get PRO
June '25
+66
in 0 channels
Get PRO
May '25
+92
in 0 channels
Get PRO
April '25
+74
in 0 channels
Get PRO
March '25
+55
in 0 channels
Get PRO
February '25
+38
in 0 channels
Get PRO
January '25
+56
in 0 channels
Get PRO
December '24
+68
in 0 channels
Get PRO
November '24
+67
in 0 channels
Get PRO
October '24
+37
in 0 channels
Get PRO
September '24
+46
in 0 channels
Get PRO
August '24
+65
in 0 channels
Get PRO
July '24
+81
in 0 channels
Get PRO
June '24
+35
in 0 channels
Get PRO
May '24
+36
in 1 channels
Get PRO
April '24
+42
in 1 channels
Get PRO
March '24
+47
in 2 channels
Get PRO
February '24
+46
in 1 channels
Get PRO
January '24
+32
in 1 channels
Get PRO
December '23
+63
in 1 channels
Get PRO
November '23
+37
in 1 channels
Get PRO
October '23
+63
in 2 channels
Get PRO
September '23
+58
in 0 channels
Get PRO
August '23
+77
in 0 channels
Get PRO
July '23
+50
in 0 channels
Get PRO
June '23
+63
in 0 channels
Get PRO
May '23
+46
in 0 channels
Get PRO
April '23
+39
in 0 channels
Get PRO
March '23
+41
in 0 channels
Get PRO
February '23
+54
in 0 channels
Get PRO
January '23
+192
in 0 channels
Get PRO
December '22
+125
in 0 channels
Get PRO
November '22
+46
in 0 channels
Get PRO
October '22
+57
in 0 channels
Get PRO
September '22
+66
in 0 channels
Get PRO
August '22
+64
in 0 channels
Get PRO
July '22
+40
in 0 channels
Get PRO
June '22
+43
in 0 channels
Get PRO
May '22
+64
in 0 channels
Get PRO
April '22
+93
in 0 channels
Get PRO
March '22
+71
in 0 channels
Get PRO
February '22
+36
in 0 channels
Get PRO
January '22
+47
in 0 channels
Get PRO
December '21
+54
in 0 channels
Get PRO
November '21
+75
in 0 channels
Get PRO
October '21
+135
in 0 channels
Get PRO
September '21
+97
in 0 channels
Get PRO
August '21
+132
in 0 channels
Get PRO
July '21
+142
in 0 channels
Get PRO
June '21
+114
in 0 channels
Get PRO
May '21
+71
in 0 channels
Get PRO
April '21
+190
in 0 channels
Get PRO
March '21
+122
in 0 channels
Get PRO
February '21
+172
in 0 channels
Get PRO
January '21
+180
in 0 channels
Get PRO
December '20
+1 524
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
01 August0
Channel Posts
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣6⃣ ..........ብርክክ ብላ ወደቀችብኝ ። በፈጣሪ ስም ክው ነው ያልኩት። በፈጣሪ ስም ሲጀመር ለምን ከተኛችበት ተነስታ እንደተቀመጠችም አልገባኝም ። በሰአቱ የጮኩት በረጅሙ ስለሆነ  ዶክተሮች ነርሶች ቤኪን ጨምሮ እየተሯሯጡ መጡ ። እኔ ከድንጋጤዬ ብዛት ለእናቴ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ በእጄ አቅፊያት ቁጭ ብዬ ነው የቀረሁት ። ለስራቸው የሚተጉት ዶክተሮች ደግሞ ተረባርበው እናቴን አንስተው አልጋ ላይ አደረጓትና እኔንም አለምዬንም ከክፍሉ አስወጥተው የህክምና ባለሙያዎይ ብቻ ቀሩ ። የዛኔ እናቴን አጣዋት በቃ ብዬ በጣም ፈርቼ ነበር!!!!!! የዛኔ የምር እናቴን ያጣዋት መስሎኝ ድርቅ ብዬ አግዳሚ ወንበሮች ላይ ቁጭ ብዬ  እንባዬ መውረድ ሲጀምሩ ዶክተሩና ነርሷ በሩን ከፍተው ወጡ ። ከአለምዬ ሮጣ ሄዳ " ምንድነው ምን ሆና ነው ?? እ እህቴ ምን ሆነች .."  እያለች ትጠይቃለች። እኔ መጥፎ ዜና ለመስማት ዝግጁ ስላልነበርኩኝ እዛው ድርቅ ብዬ ቁጭ እንዳልኩኝ ቀረሁ። " አታስቡ በጣም ደህና ናት ምንም የተፈጠረ ነገር የለም ግን ረፍት ያስፈልጋታል የወደቀችውም የወሰደችው መድሀኒት የማዞር ባህሪ ስላለው በመተኛት ፈንታ ስለተነሳች ሰውነቷ  መቋቋም አቅቶት ነው " አለ ። የዛኔ ብንን ብዬ ተነስቼ ወደ ዶክተሩ ሮጥኩኝና የምርክን ነው  ዶክተር እናቴ ደህና ናት???  ብዬ ምንም በማያቀው ዶክተሩ ላይ ጥምጥም አልኩበት። ከዛ አለምዬም አቅፋ አባበለችኝ ። ከዛም እናቴ እስክትነቃ እዛው ቁጭ ብለን ጠበቅናትና ስትነቃ አወራናት ድካሟን አስረሳናት ምናምን !!!! ደስ የሚለው እዛ ሆስፒታል ደግሜ ላልመለስ እየተመኘው በሶስተኛው ቀን እናቴም ቤኪም ወጡልኝ። ስንወጣ ቀጥታ እነ ቤኪ ቤት ነበር የሄድነው ። እዛ ቤት ከእኔ እና ከእናቴ ይልቅ እንግዳው ሰለሞን ነው ማለት ይቻላል ነፃ የሆነ ህብረት ነበረን። አንድ ሳምንት አርፈን ወደየራሳችን ከተመለስን ቡሀላ ሁላችንም ወደየራሳችን ተመለስንደ ከዛ በፊት ግን የቤኪ አባት ለእነሱ ቅርብ የሆነ ቤት ፈልጋ  የእነሱ እንደሆነና ካሁን ቡሀላ እዛ እንደምትኖር ነገረቻት። ደሞኮ ፅድት ያለ ሰፊ ቤት ነው !!! እኔና ሰለሞንም እንደፈረደብን ወደ ዩንቨርስቲያችን ተመለስን ። ጄሪና ያቤፅ አንድም ሳይሰስቱ ፍቅራቸውን ጓደኝነታቸውን ሰተውኝ እንደምንም አንደኛ አመታችንን ጨርሰን ፊልድ መርጠን ወደ ሁለተኛ አመት አለፍን !!! በትምህርት አሪፍ ስለነበርኩ እና ፍላጎት ስለነበረኝ አርክቴክት መሆንን መረጥኩኝ ። አሪፍ ፊልድ እንደገባሁ ሰለሞን ስለነገረኝ ደስ ብሎኛል ማለቴ ለምን እንደሆነ አላውቅም በጣም አምነዋለሁ !!!!!"   እናም ደግሞ ቤኪ በራሱ መንገድ ቸፍ ተፍ እያለ ነው ከሱ በጣም ደስ የሚለኝ ነገር ቢኖር ብር ሴቭ ማድረግ ይወዳል ሁሌ በተገናኘን ቁጥርም ስለ ወደፊታችን ያወራል !!! ያማረ ህይወት እንደሚሰጠኝ ይነግረኛል እንደ አባቱ አይነት አባት መሆን እንደሚፈልግ ይነግረኛል .......!!!!! ብቻ ለኔ ልዩ ሰው ነው የኔ አባት !!!!!! በዚሁ ግን የሚገርመው አባቴ እንደታሰረ ቀርቷል ። የተያዘው በሰለሞን በኩል ስለሆነ ህጉም ጠበቅ ያለ ነው የሚሆነው !!!! ቀስ ቀስ እያልን መኖር ቀጥለናል ትንሽ አድካሚ ቢሆንም የእጅ ጥበብንና የጭንቅላቴን የማሰብ ፍጥነት ያዳበረልኝ ፊልድ ውስጥ ነው የገባሁት !!!! እናቴ ምንም ሳትሆንብኝ በሳምንት ወይም በወር እየሄድኩ እያየዋት  መኖር ቀጠልን እኔም እንደ ቀልድ የሶስተኛ አመት ተማሪ ለመባል በቃሁ። ጄሪና ያቤፅም በአጋጣሚ ተዋውቀው የሶስት አመት ፍቅረኛ ለመባል በቅተዋል ። በጣም ደስ የሚሉ እና ስርአት ያላቸው ፍቅረኛሞች ሆነዋል። ጄሪ እንደነገረችኝ ከሆነ ደግሞ ኢዩኤል የግል ስራ ጀምሮ ራሱን መቻልና ቤተሰቡንም ማገዝ ጀምሯል አለችኝ ። ታዲያ ግን የሆነ ቀን በረከት ደውሎ በቶሎ ወደ ቤት እንድመጣ ነገረኝ ። የትኛው ቤት ስለው እናቴ ያለችበት ቤት እንድመጣ ነገረኝ ። እኔም  ሳላንገራግር ቀጥ ብዬ እናቴ ቤት ሄድኩኝ ። በረከት ነጭ ልብስ ለብሶ በር ላይ እጁን ኪሱ ከቶ ቆሟል ። ዝቅ ብዬ ወደ መሬት ሳይ ከእናቴ ቤት የሚያስፈራ ጥቁር የሚመስል ደም እንደ ውለ እየወረደ ቀጥታ መቶ እግሬ ስር ሲደርስ ቆመ ። እኔ የማየውን ማመን አቅቶኝ ልቤ ደረቴን ከፍታ የምትወጣ ይመስል በእጄ ደግፌ ይዣት ቆሚያለሁ ...... . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣7⃣

2
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣5⃣ ............የሚገርማችሁ ይሄ ሁላ ነገር እንደተደረገች  ቁጭ ብዬ እየሰማሁኝ ነበረ። ለኔ ግን በጣም ከባድ ነገር ነው !!!! ለደቂቃዎች ምን አይነት መበደል እንደሆነ አላቅም ኤጭ ምን አረኩ ፈጣሪዬ ..... እያልኩ ያላደረኩት ነገር ያለ ይመስል !!!!????....... በአንድ ሰአት በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ሁለት የምወደቻው የኔ የምላቸው ሰዎች በሆስፒታል አልጋ ላይ ተኝተዋል!!!! እናቴን የሚዬወራት ነገር መስማት ስለከበደኝ ለአለምዬ ትቻት ወደ  ቤኪ ጋራ ሄድኩኝ! በመስከኮቱ ሳይ  ከተኛበት ተነስቶ ቁጭ ብሎ ነበረ ። ምን ሆኖ ነው ብዬ ደንግጬ   በሩን ክፍት አርጌ ገባሁኝ። ገና አጠገቡ እንደደረስኩ ጥምጥም አለብኝ። ምነው ምን ሆንክብኝ አልኩት የዛኔ ሀሳቤ ላይ የመጣው የሆነ መጥፎ ነገር ተፈጥሮ ነበር የመሰለኝ። " ጥለሺኝ አትሂጂ !!!" አለኝ በአሳዛኝ ንግግር። እኔም ጥዬው የመሄድ እቅድ የለኝም ፈጣሪ ይመስገን ። አነጋገሩ አሳዝኖኝ ወሬው ስላሳቀኝ በህልምህ አየከኝ እንዴ አልኩት ፈገግ ብዬ ። " እኔኮ ከልቤ ነው እናቴ ልክ አጠገቤ ስትሆኚ ሁሉም ሰላም ይሆናል ። ነገ ከዚ ትወጣለህ ተብያለሁ አንቺ ካለሽ ሁሉም ሰላም ይሆናል ተመልሼ ወደዚ ቦታ መግባት ስለማልፈልግ አትለይኝ !!....." ብሎ ውስጤን ነካው ። ነገ ልትወጣ ነው አልኩት ሰስላልሰማሁ ተገርሜ። ይሄን ሁለት ቀን በእናቴ ጉዳይ ተወጥሬ ረስቼው ስለነበረ ይመስለኛል እንደዚህ የሚለውም!!! ከዛም ተነስቶ ጥምጥም ብሎ አቀፈኝ። ልክ እቅፉ ውስጥ ስገባ ያሳለፍኩትን ነገር በተለይም ያለ ፍላጎት የተወለድኩ ልጅ እንደሆንኩ ሳስብ የሆነ ነገሮች ይገለባበጣሉ ከሱ እቅፍ ውስጥ መሆኔ ሲጨመር ቀጥታ ወደ እሜ ገጋ ሄደን። ቤኪ ወደኳ መቅረበ ፈርተቀ ዳር ላይ ቀሞ እያየን ነበረ። ገብቼ ሳይ  በጥልቀት ገብተው እየመከሯት እሷና አለምዬ አጠገብ ለአጠገብ ሆነው ዐምን እንደተባሉ ሳላቅ ሁለቱም እያለቀሱ ነበረ ። ገና እንዳየዋቸው አሳዘኑኝና ሁለቱንም ምንም ሳልላቸው ተመልሼ ወጣሂኝ። ከዛም ከቤኪ ጋር ሆነን ጊቤውን ዞሮነው ቢያንስ እሱ በጣም ደህና ነው ያንን ማየት ራሱ ለእኔ ደስ የሚል ዜና ሆነ። ከቤኪም ጋር ተለያየንና ወደ እናቴ ሄድኩኝ ። በጣም ለእረጅም ሰአትና ደቂቃ ያህል ስታወራ ስለነበር ቀለል እንደሚላት ተስፋ አደርጋለሁ። እግሮ ስር ቁጭ ብዬ ነገሮችን እሰክትነግረኝ መጠባበቅ ጀመርኩ ። እናቴ በዝምታዋ ግራ መጋባት ስጀምር አለምዬ ወደኔ ቀርባ " አታስቢ ደህና ናት እሺ ከሆስፒታሉ ነገ እንወጣለን እሺ !!!!" እያለችኝ እያለ እናቴ ሳላስበው መሬት ላይ ብርክክ ብላ ድፍት አለች??????🥶🥶🥶🥶🥶......... የዛሬው አጥሯል ነገ እረዘም እናደርገዋለን ይቅርታ ቤተሰብ . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣6⃣
116
3
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣4⃣ ...........በምላሿ የተደናገጥኩት እኔ ክው ብዬ አየዋት። እናቴ አይን ውስጥ የሆነ የተደበቀ ስቃይ አለ። እናቴን በደንብ አቃታለሁኝ በእኔ ወይ በሆነ ነገር ካላስፈራራት በቀር እንዲህ አትልም !!!! አንኗ ውስጥ ያለውን ሀዘን ያነበበው ሰለሞንም በእጁ የሆነ ምልክት ተናገረ ። ወዲያው ፖሊሶቹ  መሣሪያቸውን አቀባበሉ። ከነሱ መሀል አንዱ " በሰላም መለቀቅ ከፈለክ በግድያ ሙከራ እንዳትጠረጠር ጩቤውን ጣል " ብሎ አስጠነቀቀው ። " እኔ እንደዛ የማድረግ ድፍረቱ የለኝም እኔ ንፁህ ሰው ነኝ " ብሎ እጁን ባነሳበት 🙌 ቅፅበት ከየት መጣ ሳልል አንዱ ፖሊስ ጭምድድ አድርጎ ያዘው። ከዛም እጁን ወደ ዃላ ጠፍንጎ ይዞ በካቴና አሰረው ። " ባለቤቴ እኮ ናት በግል ጉዳይ ላይ ጣልቃ አትግቡ " እያለ  ለህግ አስተማሪውች ህግ ሲያስተምር አሳቀኝ !!!!! ወዲያው ከዛ አካባቢ ይዘውት ሲሄዱ እናቴ ተነፈሰች ። ግን በጣም ጎድቷታል ስቅቅ ብላ አለቀሰች። የኔ እንስፍስፍ ሮጬ ሄጄ አቀፍኳት ። የዛኔ የምር አለቀሰችብኝ እኔም አብሪያት መሬቱ ላይ ድፍት ብዬ  ተቃቅፈን ስናለቅስ አለምዬም ተጨመረችልን ። ደስ የሚለው ወዲያው አንፑላንስ መጣ። እውነትም ያስፈልገናል እኔ ውስጤ እየተጎዳ ነው ያለው ። እሷ ደግሞ ስነ ልቦናዋ ተነክቶብኛል የኔ እናቴ እኔ ልንገላታላት በጣም ከመሰቃየቷ የተነሳ አቅሟ ተሞጣል ። በመሀል አለምዬ ሁለታችንንም አቅፋ እንደ እናት አባበለችን !!!! ከዛም ተረባርበው እናቴን መኪና ውስጥ አስገቧት። እኛም በሰለሞን መኪና ተከትለናቸው ወደ ሆስፒታል  ሄድን። ምርመራ ተደርጎላት ታይታ የተለመደ ማንነቷ ላይ እስክትመለስ ጠበኩኝና ተመርምራ ልብሷ ተቀይሮ ስትጨርስ አለምዬ ስላለች ብዬ ሁለቱንም ስሚያቸው ወደ ጊቢ ሄድኩኝ። ሰለሞንም ወደ ስብሰባ ሄደ ። ልክ ብቻዬን ስሆን ቋጥሬ የያዝኩት እንባዬ አመለጠኝ። ከስንት ሰአት ጀምሮ ኮ እናቴ ደህና ትሁን መጀመሪያ ብዬ ነበር ። ዶርም ስገባ ማንም የለም !!!! ሁኔታውን ተጠቀምኩበት ። ያለ ምንም ከልካይ እሪ ብዬ አለቀስኩ!!!! እናቴ ተጀፍራ ነው የተወለድኩት ብሎ ማመኔ ቀርቶ ሳስበው እንባዬን ለቀኩት ። ወዲያው ከየት መጣች ሳልላት ጄሪ በሩን ክፍት አርጋ ገባች ?!!! እንዳየችኝ በድንጋጤ ፊቷን አጨመደደችና ተንበርክካ አቀፈችኝ ። በሰአተ በጣም ከፍቶኛል !!!! አይምሮዬ ተረብሿል ማረገውን ባላቅም ሳለቅስ ሳለቅስ ቆየሁኝ። ወደዚች ምድር የመጣሁበት ቀን እየረገምኩ ቆየሁኘ። ሁኔታዬ ያስጨነቃት ጄሪ አይኔ ሚያማትርበትን አብራ እየተከተለች ስትጨቀጭከቀኝ ሁሉንም ነገር አውጥቼ ነገርኳት ። እሷም ከእኔ እኩል ደንግጣለች ያለጠበኩት ነገር ስለሆነ ከብዶኛል ። ጄሪ ግ ካልሄድን ብላ ውጥር አድርጋ ስትይዘኝ ተያይዘን ወደ ጤና ጣቢያ ሄድን ። አለሜዬ አጠገቧ ቁጭ ብላ የተኛችው እናቴን እያየች ትክዝ ብላለች ። አጠገቧ ያሉት ፖሊሶች እናቴን እያወሯት መሠለኝ ። እሷ ፊት ላለማልቀስ ራሴን ተቋቁሜ ስሄድ ፖሊሱ እያወራ ነበር " ስለዚህ እየንደሰማሽው በብዙ ነገር መክሰስ ትችያለሽ !! ደፍሮሻል  ደብድቦሻል  ጎድቶሻል አስፈራርቶሻል ያለ ፍላጎት ወስዶሻል ........ በምን መክሰስ ትፈልጊያለሽ?? ""* ብሎ ጠየቃት ። የሚገርማችሁ................ . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣5⃣
104
4
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣3⃣  ............... " ተደፍሬ ነው የወለድኩሽ ልላት አልችልም !!!" ስትል ጆሮዬ ውስጥ ጥልቅ አለ ። በፈጣሪ ስም ጆሮዬ ነው ብዬ ነበር ልቤ ለመተንፈስ እየተናነቀኝ በእጆቼ እየደገፍኩኝ ማዳመጤን ስቀጥል " ያለፈ ታሪክ ለምን ታነሻለሽ ???" አላት እሱ በቁጣ ። የለቅሶ እና የሲቃ ድምፅ ይሰማል .... "  ላንተ ያለፈ ታሪክ ነው ለእኔ ግን የማይረሳ ቁስል ነው ። እኔ ለልጄ አላንስም !!! እንኳንም ወለድኳት ለበጎ ነው የተሰቃየሁት የምታስብል ልጅ አለችኝ !!!! ነገር ግን እኔ ያን ቁስል ያንን ህመምና ጭካኔ መርሳት አልችልም !!!!!!!! አንተን የልጄ አባት ብዬ መሠየምን አልችልም !!!!!! አንተን እንደ ባል መቀበል አልችልምምምም !!!!!! አይገባህም እንዴ " ብላ ትጮካለች በአሁኑ በድንጋጤና በንዴት ፈዝዤ አልቀረሁኝም ይልቁንም በአይኔ ዞር ዞር ብዬ እሱን የምገድልበት ነገር ስፈልግ ነበር !!!! አለምዬና ሰለሞን ደግሞ በድንጋጤ ፈዘው እኔን እያዩኝ ነው !!!!! መጀመሪያ ላይ እንዳያስቆሙኝ የተረጋጋሁ ሰው መስዬ ዝም አልኩኝ ። አይኔ ግን ማማተሩን አላቆመም። በስተመጨረሻም አሮጌ ቤት ስለሆን ከስሩ የቆርቆሮ ግንጣይና ትልቅ እና ወፍራም የበር መቀርቀሪያ የሚመስል ዱላ ላይ አይኔ አረፈ ። መጀመሪያ ላይ ምን እንደማደርግ መዘጋጀትና ማሰብ ጀመርኩኝ ። ሙሉ እቅዴን ከጨረስኩ በሀላ  ሁሉንም በየተራ አይኔን እያማተርኩ አየዋቸው ። ሰለሞን በጥቂት ጊዚያት በደንብ አውቆኛል !!!!! የሆነ ነገር እንደማደርግ ስለሚያውቅ እኔን ለመያዝ ዝግጁ ሆኖ እየጠበቀ ነበረ ። ክፋቱ ደግሞ ሰይጣን እኔን ለማሳሳት በውስጤ እያቀረታታኝ ነበረ ። የእናቴን ንግግሮች ደጋግሞ በጭንቅላቴ እያመላለሰ ጭካኔ ላይ እንዳተኩር ይነግረኛል !!!! ከዛ በላይ ያልቻልኩት እኔ ቀስ ብዬ ወዳየውት መምቻ ሄጄ አነሳሁትና  ሮጬ ወደ ቤቱ ልገባ ስል በተጠንቀቅ ሲጠብቁኝ የኘበሩት ሰለሞንና ፊቱን ማያሳየው ጠባቂው ጭምድድ አድርገው ያዙኝ። ልቀቁኝ በማያገባችሁ አትግቡ .... እያልኩ እሪ ብዬ ጮኩባቸው !!!!! ሰለሞን ግን ቀስ ብሎ በተደጋጋሚ " ተረጋጊ ትንሽ ደቁቃ አትታገሺም እንዴ ነገሮችን አታበላሺ " ሲለኝ ነበር ። በሰአቱ የጋለ ንዴት ላይ ያለሁት እኔ መረጋጋት ተስኖኝ በባዶ ሜዳ ሳንባርቅ ከውስጥ በኩል በዛብህ ያንን ፊቱኝ ከስክሶ ወጣ ከዛ ያለምን እፍረት ፊት ለፊታችን ቆሞ መለፍለፍ ጀመረ። " ምን ታረጋላችሁ እዚህ??" አለን የሚገርም ነገር ነው ። እማዬ እስከዛ ሰአት ከውስጥ አሎወጣችም። ነይ ውጪ ብዬ ስጮክ ፊቷን እየጠራረገች ከቤት ወጣች። ምን ያህል ሰአት እንዳለቀሰች ማወቅ አልቻልኩኝም አይኗ ደም መስሏል አብጧል በድጋሜ እንባዋን እያፈሰሰች ነው ???? በማይገባ ሁኔታ ከላይ ልብሷ ተቀዶ ፀጉሯ ልክ ያልሆነ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ  ....... ብቻ በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ ሆና ተመለከትኳት ?????😭😭😭 እናቴ ሆና ማየት የማልፈልገው ሁኔታ ስለሆነ መታገስም አልቻልኩኝም እንባዬ ዱብ ዱብ እያለ መወራጨት ጀመርኩኝ ። ከነሱ አንፃር እኔ አልታይም ሁሉ ለመፈንከት ስንፈራገጥ ሳላስበው  በያዝኩት ቆርቆሮ የራሴን እጅ  ቀደድኩት !!!!!! እውነት ለመናገር በሰአቱ የእጄ ቁስል ምንምአልተሰማኝም !!!!!! ነዛገ ብረት ስለነበረ ግን እጄ ደም መድማት ጀመረ ። እንኳን ራሴ ላይ በዛ ልክ ይቅርና የመርፌ ደም ራሱ ይረብሸኛል ። እጄን ያነችው የኔ የዋህ እናት ልታግዘኝ ልትመጣ ስትል ጋም አድርጎ ያዛትና በእጁ የደበቀውን ቢላ አውጥቶ " እረፊ ቁሚ " ብሎ አስፈራራት ። የዛኔ ከአቅሜ በላይ ሆነ ። እናቴን እንዲ ሲያሰቃያት ቆሜ ማየት ለእኔ ህመም ነው !!!!! አለምዬም እንባዎቿን ከአይኗ እየጠራረገች በየዋህ አይን ታየኛለች ። እባክህ ፍቀድልኝ እናቴን እንዲ ማየት አልችልም !!!! እያልኩት እያለ በሩ በእግር ተመቶ  ተከፈተ ።  ክው ብዬ ስዞር የሚያስፈራ መሣሪያ የያዙ የመአት ሰዎይ ከውጪ ገቡ ። እኔ የቤኪ አባትና ራሱን የሚደብቀው ጠባቂ ጉዳይ ምንም አይገባኝም በምን ሰአት ተነጋግረው ፖሊስ እንደጠሩ አላውቅም !!!!!! ሰዎቹ ክብብ አደረጉን በሰአቱ በነገሮች የተደናገጠው በዛብህ ደግሞ እናቴ ላይ ስለቱን ደቅኖ እንዳትጠጉኝ ብሎ እንደማስፈራሪያ ሊጠቀምባት ሞከረ ። " ስህተት አትስራ መሣሪያውን አውርድ " አሉት ። ምን አይነት ድፍረት እንደሆነ አላውቅም " ምንም አላደረኩም ካላመናችሁ ጠይቋት " አለ ኮራ ብሎ ። እኔ ፍጥን ብዬ የሚፈስ ደሜን በአለምዬ ሻርፕ እየቋጠርኩ እማዬ ቶሎ ተናገሪ እንጂ ያደረገሽን ፍጠኚ አልኳት በተስፋ ተሞልቼ " የተነጋገርነው አትርሺ " አላት ፈገግ ብሎ ምን እንዳደረጋት ሳላቀው እማዬ አጎንብሳ " ምንም አላረገኝም " አለች ??????????????????😣😣😣 . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣4⃣
116
5
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣2⃣ ............ፍጥጥ እንዳለ ተገጣጠምን !!! ቀና ብዬ እንዳየውት አጠገቤ ድንጋይ ቢኖር ምነኛ ደስ ባለኝ ነበረ መሠላችሁ። እሱም ምን ሊያደርግ እንደመጣ አላውቅም እሱም ሲያየን ክው ነው ያለው ። አምሳል እንዳየችው " አብዬ ያውና አባትሽ " ብላ እጇን ጠቆመች። ሁሉም ዞር ዞር አሉ ። እናቴ የት ናት ???? ብዬ ወደሱ መሄድ ልጀምር ስር ተመልሶ እየሮጠ መሄድ ጀመረ ። እኔ ልከተለው ልሮጥ ስል የቤኪ አባት  እጄን ያዘኝ ። እናቴን እሱኮ ነው የወሰዳት  እንያዘው እንጂ ልቀቀኝ ብዬ ላመልጠው ስሞክር በጠንካራው ያዘኝ ። ሹፌሩ እና ሰለሞን ተያዩና እንደተለመደው ተግባቡ። ወዲያው ሹፌሩ ሩጫ በሚመስል ርምጃ ተከትሎት ወጣና መኪና ውስጥ ገባ። ለምን እንደሆነ አላውቅም በሱ ተማመንኩበት ???ሁለቴም ሳላስብ በቃ አሁን አንጠልጥሎ ይዞት ይመጣል ብዬ ተኩራራሁኝ ። የሚገርመው በአንድ ጊዜ ሁሉንም ረስቼው ባይሆንም በሰለሞን ላይ ከመተማመኔ ብዛት ከደቂቃዎች ቡሀላ እናቴ ትመጣለች ብዬ ተኩራራሁኝ ። ከዛም ቀለል ብሎኝ ወደ ቤት ሳይ በሩ ተዘጋ እንጂ አለመቆለፉን አስተዋልኩኝ ። ከዛም ደስ ብሎኝ በሩን ከፈትኩትና አማትቤ ወደ ውስጥ ስገባ ቤቱ እንዳልሆነ ሆኖ ተዘበራርቋል እቃው መሬት ተዝረክርኳል የተቀደደ ልብስ አለ ???  አልጋው ምኑ ብቻ ሁሉም ዝብርቅርቅ ብሏል የዛኔ ደግም ልቤ በከባዱ ተረበሸ ግን እናቴ ላይ እንደሟሟረት ቆጠርኩትና ምንም ነገር ላለማሰብ ወሰንኩኝ ። ደግሞ ለካ የመንግስተ ሰማይ የሚመስል ቤት ውስጥ የሚኖሩ ባለ ትዳሮች በር ላይ ቆመዋል ። አለምዬን እንግዳ ማለት አልችልም ቤቱን ከእኔ እኩል ታቀዋለች ። ለእናቴ እንደ አለምዬ አይነት ሰው የሰጠ አምላክ ምን ይሳነዋል !!!! ግራ ገብቶኝ ዞር ብዬ አለምዬን አየዋት ። ሙሉ ተፈጥሮዋ ገራሚ ነው በተለይ ደግሞ ሳትነገር የምታውቀው ነገር !!!!!!!! ወዲያው ቶሎ ወደኔ መጣችና ቤቱን አየችው ። እን ግራ ተጋብቼ የቆምኩትን አልፋኝ ወደ ውስጥ ገባችና ራሷ የገዛቻትን ወንበር ይዛ መታ ከበሩ ራቅ አርጋ አስቀምጣው ሰለሞንን እንዲቀመጥ ነገረችው ። ከዛ አብራኝ ወደ ውስጥ ገባች ። ቤቱን በደንብ አየችውና " ችግር ተፈጥሮ ነበር አቡ መስኪዬን ይጠብቅልኝ የኔ አባት !!!!" አለች እጆቿን ዘርግታ ወደ ላይ እያንጋጠጠች ። ከዛ እቃውን አነሳስተን በትንሽ ደቂቃዎች ውስጥ ቤቱን ፏ አደረገነው ። ከዛ ቡና አቀራረበችና ከሰል አያያዝኩላት ። ከዛ ወደ ውስጥ እንዲገባ አደረገችው ። እንደ ጎደኛ ቁጭ አርጎ ያን ሁላ ነገር አውርቶኝ  ቤቱ ጠባብ ነው ምናምን ብዬ አልለውም ያለፈበትን ነገር ስለማውቅ መሠለኝ !! ከዛ ገብተን ቁጭ ብለን አለምዬ ቀስ ያለ ጭስ የበዛበት የሚገርም ቡና አፈላች ። ሁለተኛ ላይ ደርሰን እያለ በቀስታ በር ተነኳኳ። እናቴ መጣች ብዬ ሰፍ ብዬ ስጠብቅ  የሰለሞን ሹፌር ነው ። ማውራት መቻሉን እጠራጠራለሁ በዝምታ ተመለከተኝ ። ግራ ገብቶኝ ሰለሞንን ሳየው ሁለቱ ተያይተው ተግባቡና ተነስቶ ወጣ ።😂😂 ከምኖረው ህይወት ጋ በዚህ ልክ ብግባባ የት በደረስኩ ነበረ !!!!!! ከዛም ሁለቱ ተያይዘው ሲወጡ አላስችል ያለኝ እኔ ቸከትያቸው ወጣሁኝ ። የእኔ አፍ ዝም እንደማይል ያወቀችው አለምዬ ደግሞ ከትላኝ መጣች ። ከዛ ወተን አራታችንም ተፋጠጥን ። ለካ በዝምታው ውስጥ ራሱ ከሰለሞን ጋ እያወሩ ነበረ መሠለኝ .......... " ችግር የለውም ቀጥል " እስከሚለው ጠብቆ ዝምታውን ሰበረ ። ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፁን ልሰማው ስለሆነ በጣም ቸኩያለሁ አልዋሽም ። !!!! " ተከትዬዋለሁ አላወቀም " ብሎ በአጭሩ ወሬውን ቋጨው ። ድምፁ ያምራል ግን የጠበኩት ንግግር ይሄ አልነበረም ። ስለ እናቴ አንድም ቃል አልተናገረም ለምን ????? እናቴስ አልኩት አይን አይኑን እየተመለከትኩኝ ። እሱ በዝምታ ወደዃላ ሲሸሽ ሰለሞን ፈጠን ብሎ " ይዘናት እንመጣለን እወቂ ግቡና ጠብቁን"  ብሎ  መንገድ ሲጀምር አይ አኔም እመጣለሁ ብዬ እሪ አልኩ አማራጭ አልነበረውም ሁለታችንንም ይዘውን ሄድን ። በመኪና ትንሽ ተጓዝንና  የሆነ ቦታ ሲደርስ መኪናውን አቆመው ። እዛ ምን ልናረግ እንደሄድን አልገባኝም???በዝምታ ወደ ውስጥ ልንገባ ስንል " ተደፍሬ ነው የወለድኩሽ " ማለት ..... . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣3⃣
226
6
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣1⃣ ........ ወጡና እንዳዩኝ ክው ብለው ተመለከቱኝ ። በእናቴ ጉዳይ በጣም ደካማ ነኝ !!!! በዛች በአንድ ቅፅበት በአስተያየታቸው ብቻ ብዙ ነገር አስቤ በአንድ ጊዜ አይምሮዬን አሳመንኩት ። ሰለሞን ነገሩን እንደኔ በአንዴ መፍረድ አልፈለገም  የኔን ዝምታ ለመስበር በሚመስል መልኩ " ወ/ሮ .." ዞር ብሎ አየኝ ። ሲያየኝ መልሼ ፍጥጥ ብዬ አየሁት ። " ስማቸው ማን ነበር ?" አለኝ ። እ የማ  መስከረም ማለቴ መሰረት  እያልኩ ስርበተበት እሱ ቀልጠፍ ብሎ " ወ/ሮ መሠረት  የሉም እንዴ " አላቸው ። በጣም ትልቅ ሰው ነው ።!!!!! ትልቅ ሰው ሆኖ ባለ ስልጣን ሆኖ የጊቢው አስተዳደር ሆኖ እንኳን ያልሰጠሁትን አክብሮት ለእናቴ ሰጠልኝ !!! ጎረቤቶቻችንም ከመመለስ ይልቅ በዝምታ ተመለከቱን ። ነገሩ የበለጠ ረበሸኝ ። ስደነግጥ ራሴን መቆጣጠር ስለማልችል  እጄ መንቀጥቀጥ ጀመረ ። " ተረጋጊ እንጂ ልጄ ህይወትን መጥፎ ብቻ አርገሽ አትሳያት ከመፍረድሽ በፊት ጠይቂ " ብሎ በእጆቹ ትከሻዬን እያሻሸ አበረታታኝ ። " ወዴት ሄዳ ነው የሚመልስልኝ የለም ?" አለ መልሶ በትህትና ። የኛ ሰፈር ሰዎች አሁንም ዝም አሉ ። በእርግጠኝነት ባለ ስልጣንና ባለ ሀብት እንደሆነ ቢያውቁ እሩቅ ቆመው ባላዩት እንድል አደረጉኝ !!🙌🙌( እኔ አላልኩም )!! የዛኔ ዝምታቸው ከኔ ዝምታ ጋ እንደማይገጥም የተረዳሁት እኔ  ወደ ውስጥ አየር ስቤ እናቴን የምትቀርባት ሴት ላይ አፍጥጬ አምሳል እናቴ የት ናት ? አልኳት ። ስናደድ በደንብ ስለምታውቀኝ " መጀመሪያ ተረጋጊ ቆይ ያምሻል የኔ ቆንጆ ተረጋጊ " አለችኝ ። ከአቅሜ በላይ ከሆነ መንቀጥቀጥና ማልቀስ ነው የሚያረጋጋኝ ። ለዛ ትክክለኛ ሰአት ስላልሆነ ራሴን ለመቅጣጠር ሞከርኩኝ ። እሺ ንገሪኝ ደህና ነኝ !! አልኳት ለማወቅ እየተዘጋጀው ። " ትላንት አባትሽ መቶ ነበር ..." ንግግሯን አላስጨረስኳትም ። አባቴመ እናቴም እሷ እንደሆነች ታቂያለሽ እኔ አባት የለኝም !!!!ብዬ መለስኩላት ። በአሳዛኝ እይታ ተመለከተችኝና ንግግሯን ቀጠለች። " እና ትላንት በጣም ተጣልተው ሲጨቃጨቁና ሲመታትም ነበረ ከዛ ሲመሽ ሄደና ገና ወፎች ሳይንጫጩ መቶ እየጎተተ ይዟት ሄደ " አለችኝ እንደ ቀላል ነገር ???????? ንግግሯ ግልፅ አደለም ለእረጅም ደቂቃዎች ያህል ስታወራ ተሳስታ ነው ብዬ ነገሮችን ለመረዳት ስሞክር ነበረ ። ማለት አልኳት ግራ ገብቶኝ ። ጭራሽ ይባስ ብላ "  ይዟት ሄደ ይሄው እስካሁን ስንደውል አታነሳም ሰው እንዳይሰማ ብለን ዝም አልን "" ብላ ንዴቴን አባባሰችብኝ ። የዛኔ ከልጅነት እስከ እውቀት በትህትና በእርጋታ በሰከነ ማንነት በሰው አክባሪነት ...... የምትታወቀው  ጨዋዋ አብላካትን ደበኳትና እንዴት ማንም መቶ ሲወርዳት ዝም ትላላችሁ ????......እንዴት እናቴ ስትመጣ ዝም ትላላችሁ ????...... እናቴ ለአንቺ ስትል እንባዋን እስከማፍሰስ አልደረሰችም የምር እንደዛ አይነት ሰው ነሽ !!!!!!?????ብዬ አበድኩባት ። ሀገር አማን ብላ ባዶ እጅ የማታቀው አለምዬ በሁለቱም እጇ ፌስታል አንጠልጥላ ያ ድንቡሽቡሽ ጉንጯ ፈገግ እንዳለ ወደ ውስጥ ስትገባ አይን ለአይን ተገጣጠምን ። ድርቅ ብላ ነው የቀረችው ። ሴት መሆን እንዲህ ነው በእይታ ነገሮችን እናውቃለን ። ከዛም በፍጥነት ወደኛ መታ ፌስታሎቹን መሬት በትናቸው " አባ ...... አቡ " እዚህ ምን ታደርጋላችሁ ምን ተፈጠረ መስኪ ምን ሆነች ????....." ብላ የጥያቄ መአት አዘነበችብኝ ። እሷ ውስጥ የእናቴን የዋህነትና እናትነት አየሁ የዛኔ የሆነ አካሌ ተቆርሶ ሊወሰድ መስሎ ተሰማኝና ድካሜን ከዛ በላይ መደበቅ አቅቶኝ እንባዬ አመለጠኝ ። ካለቀስኩ እንደሚያመኝ ስለምታውቅ አምሳለ የምትባለው ሴት ወደኛ እየቀረበች " ያምሻል እንዳታለቅሺ እባክሽ " ብላ ልታረጋጋኝ ሞከረች ። በሰአቱ ለእናቴ የሚደርስ አንድ አካል ማጣቴ ለኔ አስከፍቶኛል !!! በዛ ላይ እናቴ ብትሆን እስከ ሞት ተከትላቸው እንደምትሄድ ሁሉም ያውቃሉ !!!! ሴትዮዋ እንዳትጠጋኝ ጮኩባት ። እንደመደንገጥ ብላ ወጀ ዃላ ሸሸች ። አለምዬ እቅፏ ውስጥ አስገብታ እንባዬን ተጋራችኝ ። !!!!!የኔ የዋህ !!!!! የዛኔ ሰለሞን ቀና ብሎ ሹፌሩን ሲያየው ወዲያው ወደ አለምዬ መጣና መኪና ውስጥ እንድትገባ ምልክት ሰጣት ። " አይ መስኪን ሳናገኝ የትም አንሄድም !!! የሆነ ነገር አድርግ እንጂ !!" ብላ ሰለሞን ላይ አፈጠጠችበት ። ዝም ብሎ ትንሽ አሰላሰለና "  የሆነ የሰማችሁት ስም የለም ነቦታ ስም ።???? ሰውዬው የት እንደሚኖር አታውቁም ?" ብሎ ሁሉንም በየተራ አያቸው ። ወሪያቸው ካላለቀ ከአቦል እስከ አራተኛ የሚያፈሉ ሰዎች በዛ በችግርና በጭንቀት ሰአት ሁሉም አፋቸውን ዘግተው ይመለከቱኛል ። ከዛ በላይ መቆጣጠር አቅቶኝ ለመሳደብ ስነሳ አባቴ የሚባለው ሰውዬ ፊት ለፊት ግትር ብሎ በድንጋጤ  ፍጥጥ እንዳለ ተገጣጠምን ???????..... . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣2⃣
340
7
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣0⃣ .......... ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ ። ከሆነ ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም ድምፅ የረብሻና የችግር ድምፅ መስለው ነው የሚሰሙኝ !!! ነርሷ የቤኪን ሁኔታ ለማየት በሩን ስትከፍት እኔ እንደ ጦርነት ድምፅ አይቼው በጣም ተረብሼ ነበረ ። በድንጋጤ ብርግግ ብዬ ስነሳ እንቅልፍ አልወስድ ብሎት የሚቁለጨለጨው ቤኪ በሚያሳዝን ፊት እያየኝ ነበር የኔ አባት ። በጣም እንደደከመው ፊቱ ላይ ይነበባል !!! ቀስ ብላ ገብታ የሆነ የሆነ ነገር አየችና በፈገግታ ተሞልታ " በጣም ደህና ነህ እንኳን ደስ አለክ  " አለችው ። አንድ ቦታ ለሰአት መቆየች የማይችለው ልጅ ተኝቶ መዋል  ሰለቸው መሠለኝ " ነገ ከዚ መሄድ እችላለሁ ነርስ በእናትሽ  "  አላት በሚያሳሳ ድምፅ ። ብችልና ህመሙን ተጋርቼው ከዛ አልጋ ላይ ወርዶ ቢንጎማለልብኝ ደስ ባለኝ ነበር!!!! ከዛ መልሼ ብተኛም እንቅልፍ እንደማይወስደኝ ስላወኩኝ ወርጄ ወደ ቤኪ ጋር ሄድኩና  እጁን ይዤ ቁጭ አልኩኝ ። ነርሷ ግሉኮሱን እየነካካች ቀና ብላ አየችንና " እህት እኮ ሁሌም ከጎን ናት ማነው ታላቅ ?" አለችን ። ሁለታችንም በፈገግታ እየተመለከትናት ማን ይመስላል አልኳት ቀስ ብዬ " ወንዶች እየረዘሙ ስለሆነ በቁመት ብቻ እድሜ አይገመትም ብዬ ነው እኮ " አለችን ። ደስ የምትሕ ሰው ናት በአንዴ ተቀራረብን ማለት ይቻላል ቀለል ብላ ነው የምታወራው ። ቤኪም ቀጠል አድርጎ " ከሁለታችን ማነው ቆንጆ " አላት ። " የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ለእናንተ ቤት አይሰራም መሠለኝ ሁለታችሁም በጣም ነው የምታምሩት እኮ " አለችን በአድናቆት እየተመለከተችን ። እናመሰግናለን ብዬ ዝም አልኩኝ እኔ ። ነርሷ ጨራርሳ ልትወጣ  ወደ በሩ ስትጠጋ " ለማንኛውም እህቴ ሳትሆን ፍቅረኛዬ ናት በቅርብ የምንጋባ ይመስለኛል " ብሎ የኔንም የሷንም ቆሌ ገፈፈው !!!!! ነርሷ ቀልድ መሠሏት መሠል ፈገግ ብላ ልትወጣ አለችና መለስ ብላ የምርህን ነው ??? አለችው ። " አዎ ማርያምን " አላት ። ደስ የሚለው እሷም አልተመቀኘችም በፍቅር አይን እያየችን " ያዝልቅላችሁ አረ ክፉ አይያችሁ !!!"። ብላን ከክፍሉ ወጣች ። ወዲያው ቤኪ ወደ እቅፉ ስቦ ግንባሬን ሳመኝና ደረቱ ላይ አስተኛኝ ። መልሶ እንቅልፍ ይወስደኛል ብዬ  ባልገምትም ጠዋት በሰለሞን ጉትጎታ ነው ከቤኪ እቅፍ ውስጥ ከወሰደኝ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰደኝ ። ዛሬ ቤኪም ነቃ ብሎ ነው የነቃው ። በትንሹ የተሻለው ይመስል ነበረ !!! የሚደራረጉ ነገሮች ተደርገውለት ዙሪያውን ክብብ አድርገን ቁጭ ብለን እያወራን ነበረ !!! ቀኑ ረቡዕ ነው በድንገት የሰለሞን ስልክ ጠራ ። ድክም ዛልልል ባለ ድምፅ አነሳ " ሀሎ " አለ በጎረነነ ድምፁ ከዛኛው ወገን ምን እንደተባለ አላውቅ " ወይኔ ዛሬ ነው እንዴ ስንት ሰአት " አለ ከተቀመጠበት እየተነሳ ። ትንሹ እሱን ዝም የሚያስብሉ የሰከነ ንግግሮች አካሄደና እሺ እሺ ብሎ ስልኩን ዘጋው ። ወዲያውኑ ከኔ ቀድማ አለምዬ " ምነው አባዬ " አለች። " ዛሬ ረቡዕ መሆኑን ረስቼዋለሁ እኮ በእናታችሁ በሉ በሉ ልጆች ሶስታቹም ፍጠኑ ወደ ጊቢ ተመለሱ " ብሎ  አዘዘ ። አይ እኔ ከቤኪ ጋር ነው የምቆየው አልኩ ኮራ ብዬ ከነሱ በመቅደም ። " እኛ  እዚሁ እንሆናለን " አለ ያቤፅም ቀጠል አድርጎ ። " ተነሱና ሂዱ አልኩ እኮ ዛሬ ፋይናል ፈተና እንደሚጀምር ረስታችሁታል አይደለ አሁን ግን አስታወስኳችቱ ስለዚ ምንም ጎበዝ ተማሪ ብትሆኑሞ የሆነ ነገር እዩና አስታውሱ ጥሩ ውጤት እንጠብቃለን!!!!! እውነት ለመናገር ሙሉ በሙሉ ረስቻለሁኝ ። ከዛ አማራጭ ስለሌለኝ እስክመለስ ጤነኛ ሆነክ ጠብቀኝ !!! ብዬው ወደ ጊቢ ሄድኩኝ ። የሚያስጠላው ደግሞ ሀሳቤን መሠብሰብ ይከብደኛል እንዴት ብዬ እንደምሰራውም ሳላቅ ዶርም ሄጄ አየት አየት አረኩትና ተመልሼ ወጣሁ ። ከዛም ፈተናዬን ተፈተንኩና ተሰብስበን ቢኪ ጋር ሄድን ። ልክ ስገባ " እናትዬ ናፍቀሽኝ ነበር እኮ "ብሎ እዛ ሁላ ሰው መሀል አሳፈረኝ ። በትንሹ ፈገግ ብዬ በዝምታ አለፍኩት ። ከዛም ስናወራ ስንቃለድ ቆይተን ሰአቱ ሲሄድ ጊዜ እናቴ ጋ መሄድ ነበረብኝ ። ቃል ገብቼላታለሁኝ ። ብቻዬን መሄድ አልፉኩኝም !!! ሰለሞንን አድርሰኝ አብረን  እንሂድ  ብሎ መጠየቁ ስለደበረኝ ፊት ለፊቱ ቆሜ ስለ እናቴ ሳወራ ነገሩን የተረዳው የቤኪ አባህ ተነስቶ አብሮኝ ወጣ ። ሹፌሩ እየነዳ ከዃላ ተቀምጠን በፀጥታ መንገዳችንን ቀጠልን ። ፈተና እንዴት ነበር ???አለኝ ። እንደፈራሁት ስላልነበር  ቀላል ነው ብዬ ነው የመለስኩት ። ከዛ ከጉዞ ቡሀላ እናቴ ጋ ደረስን ። በጣም ናፍቃኝ ስለነበረ እየሮጥኩ ሄጄ በሩን አንኳኳው ። አይከፈትም ??? ደጋግሜ ሳንኳኳ ከኛ ጎረቤት ያሉ ሰዎች ወጡና እንዳዩኝ ክው ብለው ተመለከቱኝ ????? . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣1⃣
380
8
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣8⃣   .............ግራ የሚያጋባ ጥያቄ ጠየቀኝ ። በሰአቱ ማለት ምናምን ብዬ ጥያቄውን ማራዘም አልፈለኩኝም ። እኔም የዋዛ አይደለሁምና ደቂቃዎችን ሳላባክን ተጣጥፌ ምርኩዝ እሆነዋለሁ ብዬ የሚገርም መልስ ሰጠሁኝ ። በመልሴ የተደነቀ የሚመስለው ሰለሞንም ትክ ብሎ ተመለከተኝ ። እኔም ትንሽ ግራ መጋቢትን ስለፈጠረብኝ  ግን ለምን እንዲህ አይነት ጥያቄ ጠየከኝ ብዬ በመርማሪ ኤይታ አየሁት ። በሰአቱ እሱም ሊነግረኝ የፈለገ አይመስልም ነበር ወዲያው አስተናጋጁ  ቆንጆ  ቆንጆ ሲታዩ  በአይን የሚያጠግቡ ምግቦችን ከዚ በፊት አይቼ በማሚማቀው አቀራረብ ለየት ባለ ሁኔታ ማቀራረብ ጀመሩ ። አንደኛ ንፅህናቸው ሁለተኛ የእቃቸው ጥራት መስተንግዷቸው .......... ብቻ የማገርም ነገር ነው ያየሁት ። በህይት ውስጥ በተደጋጋሚ እያየ የመጣሁት ነገር ቢኖር ብር እያለሽና ሳይኘኖረሽ የሚፈጠሩ ልዩነቶችን በደንብ ማየትና ማስተዋል ችያለሁኝ ። ሰው የዋለበትን ይመስላል ይባል የለ እኔም ከደህና ሰው ጋ በመዋሌ እነሱ የሚያገኙትን ፍቅርና እንክብካቤ ማየት ቻልኩኝ ። ቤቱን ለየት ከሚያረገው ነገር አንዱ ደግሞ  ሁሉም በተቀመጠበት ወንበር አቅራቢያ ፅድት ያሉ የእጅ መታጠቢያዎች አሉ ። ተነስተን በየተራ ታጥበን ተመልሰን ቁጭ አልን ። ደስ የሚለው የቤኪ አባት እንደ ሀብቱና እውቅናው አይደለም ቅድሚያ ለፈጣሪ ይሰጣል ። ከመጀመራችን በፊት ፀሎት አድርጎ አማትቦ ቆርሶ ከእጁ ሰቶኝ  ምናምን መብላት ጀመርን ። በጣም የሚጥሙ ምግቦችን ከአድካሚና አሰልቺ የድካም ቀን ቡሀላ ጥግብ እስከምሕ ድረስ በላሁኝ !!! በልተን ጨርሰን ምግቡ ተነሳስቶ እስኪያልቅ ድረስ አንድም ቃላት አልተመላለስንም በዝምታና በእርጋታ ተመግበን ጨረስን ። እንደ ማወራረጃ ስፔሻል ጁስ መጣልንና የዛኔ ወሬያችንን ለመቀጠል ተመቻቸልኝ ። ለማወቅና ለመስማት በጣም  ጓጉቼ ነበረ !!!!!! ፊቴንጰበደንብ ተመለከተና ፈገግ ብሎ " ለማወቅ በጣም የቸኮልሽ ምመስለኛል " አለኝ ። አዎ በጣም ሁሉንም ነገር ንገረኝ ። በመጀመሪያ  ግን ለምንድነው እንደዛ አይነት ጥያቄ የጠየከኝ ???? ቤኪ ምኑን ታሞ ነበር እንዴት ዳነ?? ብዬ በጥያቄ አጣደፍኩት ። " የዳነው በፈጣሪ እርዳታ ነው ።!!!!!! ሌላውን ራሱን መጠየቅ አለብሽ መንገር ከፈለገ ይነንገርሽ እኔ ልነግርሽ አልፈልግም "" አለችኝ ። " ለማንኛውም ግን እኔ ክፉ ሆኜ ወይም የልጄን ስሜት መረዳት ከብዶኝ አይደለም !!!!y ማፍቀርን በጀንብ አውቀዋለሁ !!!! ከፍቅር ለመለየት መሞከርም ጥፋት መሆኑን በደንብ አውቃለሁ !!!!! እንደምታቂው ቤኪ በጣም ቆንጆ  ተማሪ ነው  !!! ( የማይካድ እውነታ ) በዛ ላይ የሀብታም ልጅ ነው ተብሎ ነው የሚወራበት ። የሚገርምሽ በሱ ምክንያት የኔ ልጅ መሆኑ ሳያስጠላው ሁሉ አይቀርም !!! ለማንኛውም ግን እሱ ደህና ሲሆን ሊነግርሽ ከፈለገ ሙሉውን ይነግርሻል " አለኝ ። ከዛ  በላይ ላስጨንቀው ስላልፈለኩኝ እሺ በቃ ብዬ ዝም አልኩኝ ። ድንገት ስልኩን አውጥቶ ያቤፅ ጋር ደወለለት ። በአንድ ጥሪ አነሳው ። " አቤት ጋሼ " አለ ፈጠን ብሎ። " አለም ተኛች እንዴ ፍቅረኛህስ ምን አዲስ ነገር  አለ " አለው ። " አለምዬ እና ጄሪ ተኝቸዋል ። ቤኪ ደግሞ ፍጥጥ ብሎ ቁጭ እንዳለ ነው ተጨንቋል። ማለት ከሄዳችሁ ጀምሮ  ስላልደወላችሁ ... " ብሎ የተንጠለጠለ ሀሳቡን ተወው ። " እሺ እሱ ደህና ነው አይደል " አለው ። " አዎ ደህና ነው " አለ ። ስልኩ ስፒከር ስላረገው ሁሉንም እየሰማሁ ነበረ ። " አትመጡም እንዴ ?" አለ ያቤፅ ። የእኔም ጥያቄ ስለነበረ እሰይ ነው ያልኩት ። " አይ አንመጣም ዛ "" ሲለው ልቤ ቀጥ ድው ነው ያለችብኝ ........... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣9⃣
286
9
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣9⃣ .............ልቤ ቀጥ ድው ነው ያለችብኝ። ስልኩ እስከሚያልቅ መጠበቅ ስላልቻልኩኝ አንሄድም እንዴ ?? ብዬ አፈጠጥኩበት ። ስልኩን እንደያዘው ሳይዘጋ " መሽቷል በዚህ ሰአት እንዴት እንሄዳለን ብዬ ነው " አለ ለሁለታችንም እየመለሰ ነበር ። አረ ብንሄድ ነው የሚሻለው ቅርብ አይደለ ምን ችግር አለው ብዬ ቀለል አድርጌ አወራሁት። ደስ የሚለው ቤኪም ስልኩን ተቀብሎ ፈጠን ብሎ " አባ ብትመጡ በጣም ደስ ብሎኛል ግን እ አቡ ናፍቃኛለች እኮ " አለው ። ገና ድምፁን ስሰማ ፈገግ የምለው ነገር አለኝ  ። የቤኪ አባትም በትንሹ ፈገግ አለና " እሺ መጣን በቃ " ብሎ ስልኩን ዘጋው ። ከዛ ወሪያችንን ቀጠልን በጣም ብዙ ነገር ነገረኝ ። መሸ ብለን ስናወራ የበለጠ እንዲመሽ አደረግነው ። ገና መጣን ስላንን ጨራርሰን ወጣን ። በመኪና እየሄድን ራሱ ስናወራ ነው የሄድነው። ወደነ ቤኪ ጋር እየተቃረብን ስንመጣ ግን " ስላዳመጥሽኝ በጣም አመሠግናለሁ ከማንም ጋ በዚህ  ልክ ተቀራርቤ አላውቅም !!! ሁል ጊዜ ስራና ስራ ላይ ብቻ ስለማተኩር ማንም ቀርቦ አውርቶኝ አያውቅም ስገምት ግን አብዛኞቹ ማውራት የምችልም አይመስላቸውም መሠለኝ " ብሎ ሳቀ ። ለፈገግታው ምላሽ ቁጥብ ፈገግታዬን እያሳየሁት ምን አልባትም ቀርበን ባናወራ እኔም እልክ ነበር እንቅስቃሴዎችክ እንዳለ የምልክት ናቸው እኮ !!!!! ስገምት ግን ስልጣኑ ሀብትክና ዝናህ ወጣ ስለሚያረግህ ነው ። ማለት ማንም ቢሆን እንደማንኛውም ሰው ቀርቦ ሊያወራክ አይችልም !!! እኔም የኔነት ስሜት አዳፍሮኝ ነው አልኩትና ሁለታችንም ተያይተን ከትትት ብለን ሳቅን ። ሁሉም ሰው ከላይ እንደሚታየው አይደለም ። አንዳንዱ ከላይ ስታዩት ንፁህ የዋህ ይመሰክራሉ ልና ስትቀርቡት ግን ምን ያህል ሰይጣን እንደሆነ ይታወቅበታል አንዳንዶቹ ደግሞ ከላይ ክፉ ኮስታራና መጥፎ ይመስሉና ልክ ስትቀርቧቸው ምን ያህል መሳቅ የሚያምርባቸው የዋህና ጥሩ መልካም ሰዎች መሆናቸውን ትረዱበታላችሁ  !!!! የቤኪ አባት ማለት ልክ ያ ሰው እንደማለት ነው ከላይ አይቼው ለልጁ የማያስብ ኮስታራ ገንዘብ የሚያሳድድ ሰው ጨካኝ ........ ብቻ በጣም ብዙ የማይመጥኑትን ማንነቶች ሰጥቼው ነበረ ስቀርበው ግን ፍፁም የተለየና ምርጥ ሰው ነው ።!!!!!!! ከደቂቃዎች ቡሀላ ሆስፒታሉ ደረስን ። ለሊት ሆኖ ራሱ  ውስጡ ቀን ነው የሚመስለው ነርሶች አሉ ፅዳቶች አሉ የደመቁ መብራቶች ብቻ ሁሉም ነገር አለ ። ቀጥታ ወደ ቤኪ ክፍል ሄድን ። ከፍተን ስንገባ አለምዬና ቤኪ እጅ ለእጅ ተያይዘው የሆዳቸውን እያወሩ ይመስላሉ ። ክፍሉ ውስጥ ሁለት የተለያየ አልጋ ተጨምሯል አንዱ ላይ ጄሪ አንዱ ላይ ያቤፅ ልጥጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ገብተዋል ። ከፍተን እንደገባን ሁለቱም እየተመለከቱን  በአንድ ድምፅ  " ቆያችሁ እኮ " አሉን ። እኔና ሰለሞን ደግሞ ተያይተን ሳቃችንን ለቀቅነው ። እነሱ በግርምትና በጥያቄ ፊት ትክ ብለው ሰከሩ እንዴ በሚመስል አስተያየት ያዩናል ። እነሱ ምን አስበው እንደዛ እንደሚያዩን ስናስብ ደግሞ የበለጠ መሳቃችንን ቀጠልን ። የኛ ከት ብሎ መሳቅ የተኙትን በአንዴ ቀሰቀሳቸው ። ከተኙበት ቀና ብለው ፍጥጥ ብለው ተመለከቱኝ የዛኔ የምር ከአቅሜ በላይ ሆነብኝና መቆም እስኪያቅተኝ ድረስ ከትትትትት ብዬ ሳኩኝ ። በሁለታችን ያልታወቀ የሳቅ ምንጭ አራቱም ግራ በመጋባት ቆመው እያዩን ነው ። ከዛ በላይ እነሱን ግራ ላለማጋባት ብለን እንደምንም ወደራሳችን ተመልሰን በየተራ ደህና መሆናችንን ነገርናቸው ። " አባ ምን  ተፈጥሮ ነው ንገረኝ " አለ ቤኪ ግንባሩን እየሳምኩኝ  ምን ይፈጠራል ምን አስደነገጠክ ግን ደህና ሆንክልኝ አ አልኩት ። " እኔ ሀያ ሰባት አመት ሳቀው እንደዚህ ሲስቅ አይቼው አላውቅም  እኮ " ብላኝ በትንሹ ፈገግ ብላ ተመለከተችኝ። ከኔ ጋር መዋል እንደዚህ ነው እንግዲህ ብዬ ራሴን ቆለል አደረኩኝ ። ስንወጣ ከነበረበት ነገር አንፃር እንደዚህ ስላልጠበቁ ይመስለኛል ግን እንደዚህ የሚሉኝ እና ሁሉም ሰላም እንደሆነ አሳመናቸው ። አለምዬ አቅፋ ግንባሬን እየሳመች " ከድሮም እኮ መልአክ የሆንሽ ልጅ ነሽ የኔ ልዕልት " አለችኝ ። ከዛም ትንሽ እያወራን ተሳሳቅንና ተከፋፍለን ተኛን ። በጣም ደክሞኝ ስለነበረ  ወዲያው ነው እንቅልፍ የወሰደኝ ። ከተኛሁ ቡሀላ ግን ጓ የሚል ድምፅ ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ ............ . . ይቀጥላል #ክፍል_5⃣0⃣
382
10
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣7⃣ ......... በድጋሜ በእናቴ ስልክ ተደወለ ። በሰአቱ ስልክ ማውራት ቀርቶ  ወደ ጎን አርጎ ማንሳትም ከበደኝ ። እጄ መንቀጥቀጡት ያስተዋለው የቤኪ አባት ዞሮ መጥቶ ስልኬን ተቀብሎኝ አንስቶ ላውድ ላይ አደረገው ። " ሄሎ እናትዬ " አለች ። የእናቴን ድምፅ ስሰማው በአንዴ ተረጋጋሁኝና ስልኩን ተቀብዬው እማ ደህና ነሽ ??? አልኳት ። " አዎ አበባዬ ደህና ነኝ እሺ አታስቢ የኔ ቆንጆ " አለችኝ ። እማ ምን ተፈጥሮ ነው ንገሪኝ  እባክሽ ጎዳሽ እንዴ እ ምን አርጎሽ ነው ??? አልኳት መጥፎ ነገር ለመናገር ተዘጋጅቼ ። " አታስቢ የኔ ወርቅ ምንም አላረገኝም ሰክሮ መቶ ትንሽ ተናገረኝ ታቂ የለ በሆነ ባልሆነ እንደሚከፋኝ " አለችኝ ፈገግ ያለ ድምፅ እያሰማችኝ ። በሆዷ ብዙ ቁስልና ህመም የያዘች ይመስል በሆነ ባልሆነው ነው  እንባዋ የሚፈሰው ከዛ ለምን ታለቅሻለሽ ስላት ከት ብላ ትስቃለች !!!????። በዛች ቅፅበት በጣምምምም ብዙዙ ነገር አስቤ ስለነበር በረጅሙ ተንፍሼ እንዳስደነገጠችኝ ነገርኳት ። እሷ ደግሞ ድርቅ ብላ ደህና መሆኗን እንዳምን አድርጋ አወራችኝ !! እኔም በቀላሉ አመንኳትና ነገ እመጣለሁ ብዬ ቃል ገብቼላት ስልኩን ዘጋሁትና መኪናውን ተደግፌ በረጅሙ ተነፈስኩኝ ። ከእኔ ባልተናነሰ ሁኔታ ተጨንቆ የነበረው ሰለሞንም በአንድ እጁ ወገቡን ይዞ በአንድ እጁ  ደግሞ ከረቫቱን እያላላ ተነፈሰ ። ምን ያህል ሊረዳኝ ዝግጁ እንደነበረ በአይኔ ያየሁት ነገር ስለሆነ ከተደገፍኩበት ቀና ብዬ በጣም ነው የማመሰግነው እናም በጣም ይቅርታ አልኩት እጆቼን እያሻሸሁኝ ። "ምንም አይደል ልጄ ነይ ከብርድ ላይ ጊቢ ወደ ውስጥ " ብሎኝ ሊገባ ሲል የቤኪ አባት ብዬ ጠራሁት ። ለምን እንደሆነ አላቅም ሰለሞን ማለትም አንቱ ማለትም ይከብደኛል ። በጣም ወጣት ነዎ እኮ ቤኪን በስንት አመት እንደወለደውም አላውቅም ። እሱም ወደኔ ዞር ብሎ ምነው በሚል ፊት አየኝ ። ትንሽ ፈጣጣ ሆንኩኝ መሠለኝ ፈገግ ብዬ አንዴ እንደ አባት ልቀፍህ ?? ብዬ በአሳዛኝ ፊት አየሁት ። በነገራችን ላይ እንዲህ ያልኩት ያለ ምክንያት አይደለም !!! ከደቂቃዎች በፊት ልጄ ብሎ ጠርቶኝ ነበረ ። በምላሹ እሱም ፈገግ አለና  እጁን ዘረጋልኝ እኔም ቶሎ ብዬ በዛ ግርማ ሞገስ ባጀበው እቅፍ ውስጥ ገባሁኝ !!! የምር በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ !!!! በትክክለኛ አባቴ እንደታቀፍኩኝ ነው የተሰማኝ ሁላ  !!!!! ምናለ እኔም እንደሱ አይነት አባት በኖረኝ ብዬ እንድመኝ አደረገኝ !!!!!!! ከዛ እንባዬ መምጣት ሲጀምር አንዴ ከጀመረኝ ማቆሚያ የሌለኝ መሆኔን ስለማውቅ ቶሎ ከእቅፉ ወጥቼ በጣም አመሰግናለሁ ብዬ አሳጠርኩት ። " ነይ ወደ ውስጥ ግቢ " ብሎኝ እኔን አስቀድሞ ተከትሎኝ መጣ ። ከዛ ተመልሰን ቦታችን ጋር ተቀመጥን ። ወዲያው አስተናጋጁ መጣና እሱን አየው ። በአይኑ የአወንታ ምልክት እየሰጠ አንገቱን ሲነቀንቀው ወደኔ ዞር ብሎ " ምን ይምጣልሽ እመቤት " አለኝ በትህትና ጎንበስ ብሎ ። ምን እንደሚባል የማላቀው እኔ ዞር ብዬ ሰለሞንን አየሁት ። በአንድ እይታ ሰውን መረዳት የሚችል ሰው ነው !!!! ጎንበስ ብሎ ወደ ሜኑ አየና የሆነ የሆነ ነገር ብሎት አስተናጋጁ ሄደ ። ሰውዬው እስኪመለስ ልብ አንጠልጣይ ታሪኩን ለመስማት ጉጉት አደረብኝና አላስችል ቢለኝ ለወሬ ማስጀመሪያ እና ቤኪ ምኑን አሞት ነው ? ብዬ ወደ ወሬው መለስኩት ። ለትንሽ ደቂቃዎች በዝምታ ተውጦ አሰበ አሰበና ጥልቅ ሀዘን ውስጥ ገባ ። እኔ አይን አይኑን እያየሁኝ ምላሽ እየጠበኩ እንደሆነ አሳየሁት ። ያየኛል አየዋለሁ ያየኛል አየዋለሁ ።።!!! ከደቂቃዎች መፋጠጥ ቡሀላ  ግን ሰለሞን ጉሮሮውን እንደመጠራረግ አለና " ልጄ በጣም ታሞብኝ ነበር በጣም " አለኝ ። ምኑን ታሞ ነው ይሄን ያህል እ ምን ሆኖ ነበር ?? አልኩኝ ይበልጥ ለማወቅ እየጓጓሁ ። " እስኪ ከዛ በፊት አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ እውነታውን ትነግሪኛለሽ  ?" አለኝ ። እሺ ደስ ይለኛል ምንድነው አልኩት መልሼ " አያድርገውና ልጄ በረከት አይኖቹ ማየት ቢያቆሙ ምን ታደርጊያለሽ ??3" የሚል እጅግ ግራ የሚያጋባ ጥያቄ ጠየቀኝ ???......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣8⃣
357
11
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣6⃣ .............. ቦታውን አላቀውም የት እንዳለን እዚህ ምን እንደምናደርግ እንኳን አላውቅም የቤኪ አባት ስለሆነ ብቻ ተከትዬዋለሁ ። የመኪናውን በር እንደከፈተ " ውረጂ !" ብሎ ዝም ብሎ ተመለከተኝ ። እዛ ድረስ ተከትዬው መጥቼ አልወርድም ብል ጥቅም አልባ ንግግር ነው ብዬ ስላመንኩ ቀጥ ብዬ ወርጄ ከመኪናው ጋር ተለጥፌ ቆምኩኝ ። የት እንዳለን አላውቅም ??? ከፊት ለፊቴ ሆቴል እንዳለ ብቻ ይታየኛል !!! ግን ጭር ያለ እና በዝምታ የተዋጠ ቤት ነው ። የመኪናውን በር ዘጋውና መሄድ ጀመረ ። እኔ እዛው ቆሜ ቀረሁኝ ። " ነይ ጊቢ " አለኝ ዞሮ ግን እዚህ ምን እናደርጋለን ? አልኩት እንደምንም ተዳፍሬ ። " ምን እንዳላደርግሽ ፈርተሽ ነው እኔ ሰለሞን እኮ ነኝ አፈየበለጠ አታናጂኝ ክብር እየሰጠውሽ ነው  የሌለኝን ትዕግስት አታስጨርሺኝ "አለኝ ጭምድድ ባለ ፊት ። በፈጣሪ ስም ቀይ ስለሆነ ትንሽ በተናደደ ቁጥር ፊቱ እንደ ቲማቲም ይቀላና ግንባሩ ይጨማደዳል !!!! ብቻ በጣም ነው የሚያስፈራው ምነው ባልተናገርኩ እንድል አደረገኝ !!!! ተጨማሪ ቃላትን ሳላባክን ተከትዬው ወደ ውስጥ ገባሁ ። የሚገርማችሁ ሌሎች ቦታ ካየሁት በላይ የሆነ ክብርን  ገና ከበር ማየት ጀመርኩኝ ። ገና ከበሩ ሞቅ ያለ ሰላምታ ጎንበስ ቀና የበዛበት መስተንግዶ ....... ብቻ ብዙ ነገር ። ...!!!!!! የዛኔ የምር አልቻልኩም !!! ሀብታሞች እንዲህ ነው የሚኖሩት ?? እንድል አደረገኝ ። በዛውም ደግሞ ከባለ ስልጣን ልጅ ጋ ማን ፍቅር ውስጥ ጊቢ አለሽ !!! እያልኩ ራሴን ወቀስኩኝ ። ወዲያው ደግሞ መልሼ በዚህ ልክ የሀብታም ልጅ ሆኖ እኛ ትምህርት ቤት ማን ግባ አለው ??? እያልኩኝ ጥፋቱን ወደ ቤኪ አዞረዋለሁ ። ጨዋታው ቀጠለ ለብቻችን ተቀመጥን ። አስተናጋጁን ቀና ብሎ አይቶት አንድ እጁን ከፍ አድርጎ መዳፎቹን ዘርግቶ አጠፋቸው ። ወዲያው አስተናጋጁ ጎንበስ ብሎ ተመልሶ ሄደ ። ሁሉም ነገር ለበጎ ነው ይባላል ምን አልባት ይሄን ህይወት ሊያሳየኝ ነው እንዴ ??!!ብዬ በሆዴ እያወራሁ ብቻዬን እስቃለሁ !!!! " እሺ እንቀጥል "አለኝ እ ምኑን ማለቴ እሺ አልኩኝ ከገባሁበት የልጅ ቀልድ ለመውጣት እየታገልኩኝ። " አውቃለሁ አንተዋወቅም ቁጭ ብሎ ለማውራትም ገና ነን ግን ስለ ቤኪ በደንብ እንድታቂልኝ እፈልጋለሁ !!! እኔ ክፉ ሆኜ አይደለም ግን ልጄን ይነጥቁኛል ብዬ እፈራለሁኝ   አንቺ ስለሱ ምን አታቂም  አምሮ ተውቦ ልዑል ሆኖ የምታይውን በረከትን ነው የምታውቂው ተሳሳትኩ ??" አለኝ ከላይ የለበሰውን ኮት አውልቆ ወንበሩ ላይ እያስቀመጠ ። ቃል ማውጣት አቃተኝ መሠለኝ በአወንታ ብቻ አንገቴን እየነቀነኩኝ  ። " እሺ ለማንኛውም እዚ ያመጣሁሽ እንድናወራ ስለፈለኩ ብቻ ነው ። አሁን ላይ አንቺ ፍቅር ውስጥ የከተሽው በረከት  ማለት እኔና ባለቤቴ ብዙ ያየንበት ብዙ ያጣንበት ብዙ ያገኘንበት ልጃችን ነው ። ከእኔ ጋ ብዙ ባንገናኝም አለምዬ ብዙ ነገር እንደምታቂ ነግራኛለች ። እና አሁን ያሉት ማንኛውም ነገር ድሮ ላይ አልነበረም ። እኔና እናቴ ( አለምዬን ማለቱ ነው  ) ከቤት ስንጠፋ  አንድ ነገር አልነበረንም !!. ገና ልጅ እያለን ነው በፍቅር የወደቅነው ። ቤተሰቦቻችን በከባዱ ሲያስፈራሩን ሁሉንም ለመቻል ወስነን ከቤት ጠፋን ። ሁለታችንም በየሆነ ቦታ ተበታትነን ስራ ለምስራት ሞከርን ። እናቴ አሁን እንደምታያት አልነበረችም ተሞላቃ ያደገች የሀብታም ልጅ ትመስላለች እንጂ በብዙ የተፈተነች ሴት ናት ። በሰአቱ እኔ ስራ ሳጣ እሷ እየሰራች በምታመጣው ብር ለመጀመሪያ ጊዜ በት ቸከራይተን ኬሻ አንጥፈን ለመተኛት እንድበቃ አደረገችኝ ። በሰአቱ በትምህርቴ በጣም ጎበዞ ተማሪ ነበርኩኝ ። የመማር እድሉን ሳላገኝ ቀርቼ ነበር ። ነገር ግን ሰው ቤት እየሰራች ትምህርቴን እንድጨርስ አደረገችኝ ። በጣም በትልቅ ነጥብ አለፍኩኝ ። ብታምኚም ባታምኚም ዩንቨርስቲ ገብቼ ትምህርት ጨርሼ እስክወጣ ድረስ በፅናት ብር እያጠራቀመች ጠበቀችኝ ። ያ ነገር ለኔ ብርታት ሆነኝ ። በተማርኩበት ስራ እስካገኝ ድረስ ጎን ለጎን መስራት ጀመርኩ ። አንድ ላይ ሆነን እየኖርን ልጅ መውለድ ተስኖን ነበር ። እኔ ደግሞ በጣም ወንድ ልጅ እመኝ ስለነበር ቅዱስ ሚካኤል ደጅ ሄጄ ወንድ ልጅ እንዲሰጠኝና ካሳካልኝ ብዬ መሳል የሌለብኝን ስለት ተሳልኩኝ ። ፈጣሪ ይመስገን  በዛው ወር አረገዘችና በመጀመሪያ ወንድ ልጅ ሰጠኝ ። የሱ መወለድ ያቺ ጠባብ ቤታችንን ስለሞላልን በረከት ብዬ ስም አወጣሁለት ። ከተወለድ አራት አመቱ አካባቢ ማታ በሰላም ተቃቅፈን ተኝተን ለሊት ላይ ድንገት ትንፋሹ ተቆራረጠች " ሁኔታው ትዝ ብሎት መሰለኝ እንባው መውረድ ጀመረ ። ለምን እንደሆነ አላውቅም ወንድ ልጅ  ሲያለቅስ ማየት በጣም ከባድ ነው !!! አባት የለኝ ይሆናል ግን አባትነትን በደንብ አነውበት !!!!! ልክ እንደ ከዚ ቀደሙ  ምን አለ አባት ቢኖረኝና የአባትነት ፍቅርን ባየው ብዬ ተመኘው !!!!!( ለካ አባት አለኝ 🧐🧐)...... አንዱ አባት ልጁን ይክዳል አንዱ ለልጁ እንባውን ያፈሳል ....... ህየወት ተቃራኒ ናት !!!! ምን ማለት እንዳለብኝም ሳላውቀው  አፌ ላይ የመጣልኝን ዋናው አሁን ላይ ከጎንክ ነው ለምን ታለቅሳለክ ብዬ ታሪኩን እንዲቀጥልልኝ ሰፍ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ ። ለመረጋጋት አየር እየሳበ እያለ እናቴ ደግማ ደወለች ። አሁንም ከጎን ነክቼ ዝም ልለው ስል የእናቴ መሆኑን አየና " አንሺው አንሺው እኔም ለመቀጠል ልዘጋጅ"  አለኝ ፈገግ ብሎ ። ውጩ እንደሆንኩ ካወቀች ጥያቄ ታበዛለች ብዬ ለመዋሸት ድምፄን ቀንሼ ሄሎ እማ ስላት ዝም አለችኝ ። ሄሎ ሄሎ እማ ስል የሚያለቅስ ድምፅ ሰማሁኝ ። ከደቂቃዎች በፊት ድምፄን መቀነሴን ረስቼው በድንጋጤ ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ እማ ሄሎ ሄሎ አልኩኝ በጩኸች ። ምንነቱንም ያላወቀው የቤኪ አባት ከኔ እኩል ከተቀመጠበት ተነስቶ ያየኛል ። " ሀ ሀ ሀ ሀ ...." የሚስቅ የወንድ  ድሞፅ ። የአባቴ ድምፅ ነበር እናቴ እያለቀሰች እሱ እየሳቀ ?????? ነገሮችን አሰብኩና እየሮጥኩ ከሆቴሉ ወጣሁ ። እሱ ደግሞ " ምንድነው ምን ተፈጠረ " እያለ ይከተለኛል ። እናቴ እናቴ ችግር ውስጥ ናት አልኩ እየተርበተበትኩኝ ። " እሺ መኪና ውስጥ ጊቤ እንሄዳለን ፍጠኚ " ብሎኝ ወደ መኪናው ስንገባ ድጋሜ በእናቴ ስልክ ተደወለ ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣7⃣
314
12
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣5⃣ ........ልጄን የወጋውና የስለት ልጄን ደም ያፈሰሰው ያንቺ አፍቃሪ ነው !!! የዛ ቀን ምሽት በዛ በምሽት ምን እንዳወራችሁ አላውቅም ልጄን እንዲጎዳ አደረግሽብኝ ለዛ ነው አሁን ገባሽ " አለኝ ። ኢዩኤል እንዲህ ያደርጋል ብዬ አልገምትም አላስብምም ነበረ !!! ቀና ብዬ ጄሪን ተመለከትኳት ከኔ በላይ ደንግጣለች እጆቿን አፏ ላይ ደራርባ በጥፋተኝነት ስሜት ተውጣ ፈዛ እያየችኝ ነበረ ። እውነት ለመናገር በሷ አልተናደድኩም ምክንያቱም  እሷ ምንም አታቅም በዛ እርግጠኛ ነኝ ። በሰአቱ ልመልስ የምችለው ነገር ስለሌለ በዝምታና በጥፋተኝነት ስሜት ሁሉንም አየዋቸው ። የውስጤን የተረዳችኝ አለምዬም አንዴ እኔን አንዴ ባለቤቷን ለማረጋጋት እየሞከረች ነው !! እኛ እዛ ቆመን ስንጨቃጨቅ ቤኪ በዝምታ ሲያዳምጥ ቆየና " አባ ራሴ ነኝ ነገር የፈለኩት ምንም ነገር ቢፈጠር እሷ ጥፋተኛ አይደለችም እሷን አትናገርብኝ " እያለው ነበር ። በሰአቱ ምን ያህል እንደሚወደኝና እንደሚያስብልኝ ለማወቅ ቀላል ነበር !!!!! መጥፎ ሁኔታ ውስጥ  ከትቼው ራሱ በዛ ሁኔታ ላይ ሆኖ ስለኔ እያሰበ ማየት ለኔ እንደ ጥንካሬ ነው !!!! እልና... ነገር ግን የቤኪን አባት ሁኔታ ሳይ የጥፋተኝነት ስሜቴ ያገረሽብኝና ሽምቅቅ እላለሁ!!!!! ቆመን እየተፋጠጥን እያለ ዶክተሩ ከነርሷ ጋር መጣ ። " መድሀኒት ሊወስድ ነው እና ትንሽ ረፍት ማድረግ አለበት ብቻውን ተውት ትንሽ ደቂቃ " አለ ። የሚገርማችሁ ዶክተሩ የቤኪን አባት ሲያወራ ያለው ክብርና እርጋታ በጣም የሚገርም ነው !!!!!!! ለነገሩ እንዴት አያከብረው ........ ለማንኛውም ግን ተያይዘን ከዛ ክፍል ወጣን በሩ እስኪዘጋ ድረስ ቤኪ የሆነ አስተያየት እያየኝ ነበር !!!! እንደወጣን ጄሪ ፊቴን እስካዞር ጠብቃ " አቡ በጣም ይቅርታ እሺ ለዚ ሁላ ጣጣ እኔ ነኝ ጥፋተኛ " አለችኝ ። እሷን ቀለል እንዲላት ብዬ በሰአቱ የሌለኝን ፈገግታ እያሳየዋት አንቺ ምን አደረግሽ ያምሻል እንዴ ቀውስ ደሞ ለበጎ ይሆናል  ብዬ ፈገግ አስባልኳት ። ወዲያው አለምዬ ወደኔ መታ አቀፈችኝና " እንዳትከፊ እሺ ብዙ የተፈተንበት ልጃችን ስለሆነ የሱ ደካማ ጎን ስለተነካበት ፈርቶ ነው እሺ " አለችኝ ። የዛኔ ከልቤ ስለ ቤኪ የማወቅ ጉጉቴ ጨመረ ። እስከዛሬ ስላለፈ ህይወቱ ስለቤተሰቡ ስለ ሀብታቸው ...... ስለምንም ነገር አስቤም ሆነ ጠይቄው  አላውቅም !!!!! አባቱንም ከልቤ ተረዳሁት !!!! አለምዬ ወደ ባለቤቷ ተመልሳ ከሱ ጋር ማውራት ጀመረች ። የዛኔ ያቤፅና ጄሪ መተው በየተራ እንደ እህትና ወንድም አቅፈው አባበሉኝ ። " ሰሌ በልጁ ቀልድ አያቅም !! በርግጠኝነት የምነግረሽ ነገር ቢኖር ቤኪ ምን ያህል እንደሚወድሽ ስለሚያውቅ ነው እንጂ ሌላ ሰው ቢሆን የነካው አንድ ደቂቃም አይገኝም !!!!! ኢዩኤል ደግሞ ከጊቢም ለቆ ጠፍቷል የት እንዳለ ማወቅ ስላልቻለ ነው ዝም ያለው " አለኝ ያቤፅ ቀስ ብሎ ። እስካሁን ካየዋቸውና በንግግሮች እንደተረዳሁት  ከሆነ ቤኪ በሆነ ችግር ላይ ያለፈ ሰው እንደሆነ ግልፅ ነው !!!! ለቤቱ ምን ያህል አስፈላጊና ውድ ልጅ እንደሆነ ገባኝ !!! ብዙም ሳይቆይ ከአለምዬ ጋር ምን እንዳወሩ ባላቅም የቤኪ አባት ወደኔ መጣ ። ገና አጠገቤ እንደደረሰ ሌላ ነገር ከማውራቱ በፊት ብዬ ምንም ነገር አላወኩም ነበር በጣም ይቅርታ አልኩኝ አይኔን መሬት ላይ ተክዬ ። ለትንሽ ደቂቃ በዝምታ ተመለከተኝና " ነይ ተከተይኝ " አለኝ ። ቀጣይ ምን እንደሚፈጠር ያላወኩት እኔ በድንጋጤ ቀና ብዬ በየተራ ተመለከትኳቸው ። የአለምዬን ፊት ሳየው ፍፁም የተረጋጋ ፊት ስለነበረ ትንሽ ተረጋጋሁ ። በሰአቱ ሌላ አማራጭ የለኝምና እሺ ብዬ መንገድ ስጀምር ጄሪም አብራኝ ለመምጣት ስትሞክር " አይ አይሆንም ሁለታችን የምንጨርሰው ነገር ነው " አላት " ግን እኮ ...." ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ያቤፅ ጎተት አድርጎ ወደ ራሱ ሳባትና ቀስ ብሎ አትጨነቂ አላት ። ከዛ ትልቅ ሆስፒታል ስንወጣ በእርግጠኝነት ከአራት ሰአት በላይ ሆኗል ። አለምዬ ለክፉ አትጥለኝም ብዬ እንጂ ማንን አምኜ በዛን ሰአት ከተናደደ ሰው ጋ እወጣለሁ !! ገና በሩን ጨርሰን ዞር እንዳልን ሹፌሩ እየሮጠ መቶ በሩን ሲከፍት የቤኪ አባት እጁን ዘረጋ ። የሚገርመው ሰውዬው ፈጥኖ በእጁ የያዘውን የመኪና ቁልፍ አውጥቶ ሰጠው ። ምን አይነት መግባባት እንደሆነ አላቅም ???? እጁን ሲዘረጋ ምንድነው ብዬ በግርምት እያየሁ እያለ እነሱ ተግባብተዋል !!! ከዛ እሱ መኪናውን ውስጥ እንድገባ አርጎኝ ወዴት  እንደሆነ ባላቅም መሄድ ጀመረ። እናቴ ጉዷን አልሰማች በዛ ሰአት ትደውላለች ። እኔ በዛ   ማንሳት ችግር ነው ብዬ ዝም አልኩኝ ከደቂቃዎች ጉዞ ቡሀላ ደረሰን ወረደና በሩን ከፍቶ ውረጂ አለኝ ። ቦታውን አላቀውም ...... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣6⃣
463
13
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣4⃣  ............ በረከት እየደከመ ነው አሉኝ ። በፈጣሪ ስም እንዴት እንደደነገጥኩ እኔ ነኝ የማቀው !!! ስልኩን ከአባቱ የበለጠ ወርውሬ የት እንደምሄድም ሳላውቅ በዛ ምሽት ዝም ብዬ ወጣሁኝ ። " ቆይ ተረጋጊ ተረጋጊ " ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረኝ ። የሀብታም ቅንጡ ስልኩን እየነካካ ከቢሮ ወተን እሱን እየተከተልኩ ስሄድ ጭራሽ ሹፌር ሳይቀር አለው ። በሰአቱ እንደዚ አይነት  ነገር አላስብም ነበር እንጂ ይሄ ቅብጠት ነው እል ነበር !!!! ብቻ ግን ሰሎሞን ቤኪን ምን ያህል እንደሚወደው እንደሚያሶብለትና እንደሚጨነቅለት ያወኩት የዛን ቀን ነው !!!!! ወንድ ልጅ በአደባባይ አያለቅስም የሚል ተራ ተረት ይዞት እንጂ እንባው አቅሮታል። እኔ ሴት በሁሉም ቦታ ማልቀስ ህብረተሰቡ ፈቅዶላታልና እንባዬን መቆጣጠርም አልቻልኩኝም !!!!! በሰአቱ የሰውዬው ንግግር ደከመ የሚለው ቃል ያጣሁት ያህል እንዲሰማኝ ነው ያደረገኝ !!!! " አፍጥነው ንዳው ፍጠን "" እያለ በተደጋጋሚ ይጮክበታል ሹፌሩ በሚያስፈራ ፍጥነት እየበረረ ነው ማለት ይቻላል !!! በሰአቱ ራሴን ላረጋጋ እሱን ላረጋጋ ግራ ገባኝ ። ለሰው ቅድሚያ መስጠት የህይወት መርሄ ስለነበረ  እንደምንም ራሴን አሳምኜና አረጋግቼ ቤኪ ለሚወዳቸው ሰዎች ሲል ይጠነክራል ምንም አይሆንም ብዬ ለማረጋጋት ስሞክር አመድ የለበሰውን ፍም ነካክቼ ቀሰቀስኩት " አንቺ እንደምታስቢውና በፊልም እንደምታይው ቀላል አይደለም የተወጉ ሰዎች ሁላ ይድናሉ ማለት አይደለም ገሀድ አለም ላይ እንዳለሽ አትርሺ !!!! ልጄ የሆነ ነገር ከሆነ ግን እመኛኝ በከባዱ ነው የምጎዳሽ !!!!"  አለኝ በሚያስፈራና በተናደደ ፊት !!! የተናገረው ንግግር ልክ እንደሆነ ገብቶኛል !!! ነገር ግን  ቤኪ የተጎዳው በኔ ምክንያት አይደለም እኮ ለምን እኔ ላይ ይሄን ያህል ተናደደ የሚለው ጭንቀት ሆኖብኛል !!!! ስንደርስ ግን ባለፉት ቀናቶች የነበረበት ቦታ ሳይሆን ትክክለኛ ሆስፒታል ነው የገባው ??? በቃ በጣም ታሞ ነው ብዬ በስንት ስቃይ የመለስኩትን እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩኝም !!!! የቤኪ አባት ሲሄድ በዝምታ እሱን እየተከተልኩ ገባሁኝ ። እንዴት እንዳወቀ ባላቅም ቀጥታ  ቤኪ ያለበት ክፍል ውስጥ ሄድን ። እጁ ላይ የተለያዩ ነገሮች ተሰካክተው አፉ ላይ መተንፈሻ ተደርጎ ምናምን ....በህይወቴ ላየው በማልፈልገው ሁኔታ ውስጥ  ሆኖ ተኝቶ አየሁት ። እሱን እያየሁ እንዳላጣው እየፈራሁ አለቅሳለሁ በዛው ሰአት እናቴ ደጋግማ ትደውላለች ???? በመሀል ላብድ ምንም አልቀረኝም ማለት ይቻላል !!!!!!!   የቤኪ አባትም በጣም ፈርቶ ምን እንደሚያደርግ ራሱ ግራ ገብቶት ሲንቆራጠጥ ቆይቶ ዶክተሩ ሲመጣ " ተናገር " አለ ቀጥታ ። " አሁን ደህና ነው ደም በብዛት እየፈሰሰው ስለነበር ለእርሶ መደወል ነበረብን እና በፍጥነት ደም የሚሰጠው ሰው ያስፈልጋል " ብሎ ሀሳቡን ሳይጨርስ እኔ እሰጣለሁ ከዚ በፊት አበረን ተመርምረናል የደም አይነታችን አንድ አይነት  የደም አይነት ነው ያለን እና በሽታም የለብኝም ምንም እ ቶሎ ስጠውና አድነው !!! አልኩት በአንዴ እጄን ሰብስቤ ደም  ለመስጠት  እየተዘጋጀሁ ። ዶክተሩ አንቱ እያለ እኔ አንተ ብዬ ጭራሽ በቁጣ ማውራቴ ትዝ ሲለኝ መቀራረባችን ይሆናል ብዬ ለራሴ ነግሬው ዝም አልኩኝ ። ወደ ውስጥ ገብቼ  ድጋሜ ቀለል ያለ ምርመራ አደረጉልኝና ደም ሰጥቼ እኔም እዛው ተኛሁ ። መዳፎቼኖ እጥፍ ዝርግት እያደረኩ እንደነበር አስታውሳለሁ ከዛ ግን ስነቃ ከቤኪ አጠገብ የተመቻቸ አልጋ ላይ ተኝቼ ሰለሞን አለምዬ ጄሪ ያቤፅ ቤኪና ዶክተሩ ጭምር ፍጥጥ ብለው እያዩኝ ነበር !??? ሁኔታው የመሠለኝ ሞቼ የተነሳሁ ያህል ነው የሆነብኝ !!!!! ተደናግጬ ሁሉንም በአይኔ እየማተርኩ ሳያቸው ቤኪ እዛው እንደተኛ በአሳዛኝ ፊት እያየኝ " ለምን እንደዛ አደረግሽ ለኔ መድሀኒቴ ነሽ ዝም ብለሽ አጠገቤ ብትቀመጪ እድን ነበረ እኮ " አለኝ ። " ብዙ ሰአት ስትቆይብን እኮ ፈራን አቡ " አለችኝ ጄሪ እጆቼን ደግፋ ይዛ ። የቤኪ አባት ትኩር ብሎ ተመለከተኝና " በአንቺ ምክንያት ያፈሰሰውን ደም መልሰሻል ጥሩ ነው ቢያንስ አሁን ንዴቴ አንቺ ላይ አይደለም " አለኝ ። የኔ ተቆርቋሪ ጓደኛ ጄሪ ቀደም ብላ " አብላካት ምን አደረገች እሷ እንዴት ለቤኪ መጎዳት መንስኤ ትሆናለች ?? " አለች ። በጣም ንዴት ላይ ነበር " ምክንያቱም  በሷ ምክንያት ነው ልጄን የጎዱብኝ " አለ በቁጣ ። " እኮ እንዴት እሷ ምን አደረገች ???" አለችው መለስ አርጋ "" ምክንያቱም ልጄን የወጋው ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣5⃣
582
14
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣3⃣ ....... እያየኝ ነበር ። ነገሮች የበለጠ እያናደዱኝ ነው !!! እስከማቀው ወንድ የሴት ዶርም መግባት ሳይሆን መቅረብ አይችልም !!! አልኩኝ በፌዜ አፌን አጣምሜ ። አንዳንዴ መቀራረብ ያናንቅ የለ !!! ለትንሽ ጊዜ ብንቀራረብ ይኸው አፍ ለአፍ መካፈት ጀመርኩ ። እንደ አለቃ እንደ ጊቢው አስተዳደርነት ከማክበር ይልቅ ሰው ፊት በንቀት ስላናገርኩት ክብሩን እንደወሰድኩ አሰበ መሠለኝ ቀይ ፊቱና ጆሮው ለብቻ ቲማቲም መሠሉ ። "" ወደ ቢሮ ሂጂ ነይ ውጪ ፍጠኚ !!" አለ በጣም በተቆጣ ድምፅ !! ከዛ በላይ እልህ ውስጥ መግባት ጥሩ መስሎ አልታየኝም ለሱ ብዬ ሳይሆን ለእራሴ ብዬ ተነስቼ ጃኬት ደረብኩኝና አልፌው ወጥቼ ወደ ቢሮ ሄድኩኝ ። ብዙም ሳይቆይ ተከትሎኝ መጣ እና በሩን ከውስጥ ቆለፈው ። የዛኔ የምር ፈራሁኝ !!! ለምን አፈቀርክ ብሎ ልጁን ትምህርት አቋርጦ ውጪ እስከመላክ የሚያደርስ ጭካኔ ያለው ኮስታራ ሰውዬ እና እኔ የእናቷ ብቸኛ ልጅ አንድ ክፍል ውስጥ ተቆልፎብናል ማለት ለኔ ከባድ ነገር ነው ። ላዬ ላይ ተከምሮ የነበረው ኮፍጣናነት ወኔና ደፋርነት በአንዴ ከኔ ራቁ !!!! ስሜቶች እንደዚ ናቸው!!!!! ማንኛውም ስሜት ቅፅበታዊ ነው !!!!! በስሜት መመራት በጣም መጥፎ ነገር ነው ለዛም ነው ስትናደድ አትናገር የሚባለው !!! ውጪ ላይ እያለው ገንፍለው የወጡ ብዙ ቃላትን ያስባከኑኝ እነዛ ሁላ ስሜቶች አሁን ላይ የሉም ከኔ ርቀዋል !!!!! " ተቀመጪ " ሲለኝ እንደ ከዚ ቀደሙ አላንገራገርኩኝም ቁጭ አልኩኝ !!! እጄን እያፋተኩኝ ጠረንጴዛው ላይ አይኔን ተክዬ ቀረሁ ። "  የገዛ ልጄን ራሱ እንደዚ ታግሼ አላቅም !!!!! ማንም ሰው እንዲህ በንቀት ተናግሮኝም አያውቅም !!! ነገር ግን ልጄ ላንቺ ያለውን ፍቅር ስላየሁ ነውዐየሌለኝን ማንነት እየታገስኩሽ ያለሁት ሰከን በይ!!" አለኝ ረጋና ቀስ ባለ ንግግር !!!! መረጋጋቱ ረበሸኝ !!! ቀስ ብሎ ሲያወራኝ ይበልጥ አስፈራኝ !!!! ምንም ማለት አልቻልኩኝም በዝምታ ቆየሁ ። " ሀሳብ ካልሰጠሽበት ነገሮችን በእራሴ መንገድ መረዳት ይኖርብኛል ማለት ነው  "  አለ ። የዛኔ በረጅሙ ተነፈስኩኝና ለማውራት ራሴን አነቃቃሁኝ !! እናንተም እንደኛ ሰው ናችሁ ። !!!! አዎ ምን አልባት ብዙ ነገሮች አንገናኝ አንቀራረብም ጭምር ይሆናል ግን እንደተረዳሁት ከእናንተ ይልቅ እኛ ጋር ጥሩና እውነተኛ ፍቅር አለ !!! በረከትንም በገንዘብ እየመረዝከው ነው !!! በእርግጠኝነት ከዚ ቡሀላ ሰው ሲቀርበው የሀብታም ልጅ ስለሆነና ገንዘብ ስላለው እንደሆነ ማሰቡ አይቀርም በእርግጠኝነት !!!! እኔ የተዋወኩት አንድ ትምህርት ቤት እየተማርን ነው ስለሱ የማቀው አንድም ነገር የለም ማለቴ አልነበረም እኔ የሀብታም ልጅ መሆኑን ሳላውቅ እሱ የደሀ ልጅ መሆኔን እያወቀ ነው ፍቅር ውስጥ የገባነው !!! እኔ እሱን ሳስብ አንድም ቀን አብሮ ሀብት ትዝ ብሎኝ አያውቅም ተምሬ የመቀጠር እና ሰርቼ የማግኘት ፍላጎት እንጂ ቁጭ ብዬ በሰው ገንዘብ የመቀለብ ፍላጎትም የለኝም !!!! አንተ እንደ አለምዬ አደለክም !!!እሷ ምርጥ ናት በገንዘብ አትመራም አትመካምም!!! አልኩት። " እባክሽ መሥመር አትሳቺ እኔ እንደዛ ለማለት ፈልጌ አንደለም በማታቂው ነገር በርግጠኝነት አታውሪ !!!!. በረከት ለኔ ብዙ ነገር ነው !!!! ለኔም ለአለምም ትልቅ ነገር ነው ! የልጅነት ልጃችን ነው በብዙ የተፈተንበት ነው !!!! እኛም ም ከእናንተ በላይ በድህነትና በችግር ውስጥ ሆነን ነው የተዋደድነው !!! ቢያንስ እናንተ ቤት አላችሁ እኛ እንኳን ቤት ይቅርና ከዝናብ የምንጠለልበት ሸራ እንኳን አልነበረንም !!!!! እንደመሸ አውቃለሁ !! ልታዳምጪኝ ከፈለግሽ ሁሉንም ነገር ልነግርሽ ዝግጁ ነኝ እንደምታስቢው አይደለም እዚ የደረስነው ....." እያለ እያስረዳኝ እያለ ስልኩ ጠራ ። አየውና ኮስተር ብሎ አነሳው !! " ምን ለምን ???" ብሎ ስልኩን ጠረንጴዛ ላይ አስቀመጠው ። ምንድነው ምን ተፈጠረ ምንድነው ....... እያልኩ ብጠይቅም የሚመልስለኝ አልነበረም !!!!!! ቶሎ ስልኩን አንስቼ ምንድነው ?? አልኩኝ ። " ቶሎ መምጣት ይኖርባችዃል በረከት እየደከመ ነው " አሉኝ ????? . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣4⃣
565
15
20 like or emoji I will send at next part 43 🫠
601
16
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣2⃣ ...........ተመልሼ ስገባ ተከትሎኝ መጣ ። " አስቢበት የምትፈልጊውን ያህል ነው ለቁጥሩ አልጨነቅም " አለኝ ። በሰአቱ በጣም ብከፋና ባዝንም ግን ለቤኪ ብዬ ታግሼ ዝም አልኩኝ !!! ፊቴን ከስክሼ ክፉ ቃል ላለማውጣት ጥርሴን ነክሼ ቦርሳዬን ለማንሳት ስዞር ጄሪ ኮራ ብላ ቆማለች ። ቤኪና ያቤፅ የታፈነ ሳቅ የያዙ በሚመስል ፊት ያዩኛል???? የተፈጠረውን አላወቁ ብዬ ንዴቴን ተቆጣጥሬ እግዚአብሔር ይማርክ !! ብዬ ከቤቱ ልወጣ ስል የቤኪ አባት ያጨበጭባል ሌሎቹ ይስቃሉ ???? ነገሮች ሊያሳብዱኝ ነበረ !!!! " ለፈተና እንደማትወድቂ እርግጠኛ ነበርኩ " አለች ፈገግ ብላ ። ቤኪ ቀበል አደረገና " ካንቺ ጋ አምስት አመት ብቻ ሳይሆን ህይወቴን እንደኖርኩ ነው የሚሰማኝ በደንብ አቅሻለሁኝ እርግጠኛ ነበርኩ " አለ ። አያልቅባቸው ያቤፅም ቀጠለና " ረጅም ጊዜ ባላቅሽም ከሚስቴ ጎን ነበርኩ " ይላል  ይባስ ብሎ የቤኪ አባት ለጥቆ "  እኔ እንኳን እንደማንኛውም አባት ትንሽ ተጠራጥሬሽ ነበረ ግን ልጄን ስላላሳፈርሽው አመሰግናለሁ ...!" አለ ። የሚያወሩት ነገር በማላቀው ቋንቋ ተረት እንደመስማት የሆነብኝ እኔ ፈጥጬ አያቸዋለሁ ????!!!!! ብቻ የበለጠ ተናደድኩኝና በሩን ወርውሬው ትቻቸው ወጣሁኝ ። የምር በጣም ከፍቶኝም ተናድጄም ነበር !!!!! መቼም እኛ ሰዎች ስንባል ስንከፋ እንጂ ስንደሰት የማናስታውሳት መሸሸጊያ የሀይማኖት ቦታ አለችንና እኔም ቀጥታ ወደ ቤተክርስቲያን ሄጄ እስኪበቃኝ ንዴቴን ተወጣሁኝ!!!! ሳለቅስ ለቀቀኝ እና ቀለል ብሎኝ ወደ ዶርም ተመለስኩኝ ። ራሴን በነገሮች ለመወጠርና ችግሬን ለመርሳት ብዬ ላይብረሪ ገብቼ ማንበብ ጀመርኩኝ!!! ስልኬ ላይ ማንም እንዳይደውል ስለፈለኩኝ ዘግቼ ቁጭ አደረኩት !!! ለሰአታት ራሴን ደብቄ ሳጠና ቆየሁኝ ። ስንት ሰአት የገባሁ ልጅ መሽቶ ነው የወጣሁትም ስልኬንም የከፈትኩትም። በጣምምም ብዙ የማላቃቸው ስልኮች ሁላ ሳይቀር የአሳውቁኝ መልእክት ገባልኝ ። መርጬ እናቴ ጋ ደወልኩ ። " አበባዬ እናቴ ምን ሆንሽብኝ እ ሳታወሪኝ ውለሽ ስልክሽን አጠፋሽብኝ እኮ ችግር  አለ እንዴ " አለችኝ ። በጣም አስጨንቂያት እንደነበር ድምጿና ንግግሯ ግልፅ ነው !!!!! እማ ይቅርታ እሺ መብራት ጠፍቶ ስልኬ ዘግቶብኝ ስለነበረ ነው ብዬ ላረጋጋት ሞከርኩኝ ። ብዙ ልታወራኝ እንዳሰበች ሲገባኝ እማ ነገ ፈተና ነኝ ልተኛ ነው  ብዬ ዋሸዋትና ስልኩን ዘጋሁት ። ዶርም ባልገባ በጣም ደስስስ ይለኝ ነበር !!!ሌላ የምሄድበት ቦታ ቢኖርና በሄድኩ ደስ ባለኝ ። አማራጭ ስላልነበረኝ ቀጥታ ወደ ዶርም ሄድኩኝ ። እንደፈራሁትም ጄሪ  በር ላይ ቁጭ ብላ ጠበቀችኝ ። " የት የበርሽ ያምሻል እንዴ ያልፈለግንሽ ቦታ የለም እኮ አስጨነቅሽን ...." እያለች ትለፈልፍ ጀመር ። ይቅርታ ማውራት አልፈልግም ደህና እደሩ ብዬ አልጋዬ ውስጥ ገብቼ ለጥጥ አልኩኝ ። እሷ ግን ያለማቋረጥ እየተከተለችኝ ታወራለች ትለፈልፋለች !!! " እኔ አይሆንም ብዬ ነበር ደግሞ እንደማታደርጊው እርግጠኛ ነበርኩ ለዛ ነው እንጂ ክፋት አስቤ አደለም " እያለች ልታስረዳኝ ሞከረች ። አሁንም የኔ መልስ ዝምታ ነበር ። " ቀልድ አይገባሽም እንዴ ተይ እንጂ "አለቾኝ። ቀና ብዬ ከቻልሽ ዝም በይ ብያት ተመልሼ ተኛሁኝኝ ። " እሺ በቤኪ ሞት ተነሺና አውሪኝ " አለችኝ ። በውስጤ ጠላቱ ይሙት ብዬ ለጥ አልኩኝ ። " እሺ በመስኪ ሞት " ስትል መታገስ አልቻልኩም ብድግ ብዬ የእናቴን ስም ከአሁን ቡሀላ ብጠሪ እንጣላለን ገባሽ የኔ እናት በእንዳንቺ አይነት ውሸታም ሰው አፍ አትጠራም እወቂ ። እንዳንቺ አይነት ጓደኛም ሆነ እህትም አልፈልግም  እኔ !!!! ብዬ ጮኩባት። " አቡ ጠላሽኝ እንዴ " አለችኝ በአሳዛኝ ድምፅ ። እኔም ድንገት ግንፍል አለብኝና አዎ  ሁላችሁም አስጠላችሁኝ ስወድም ስጠላምእንዲ ነኝ ..... እያልኩ እያወራሁ ሀሳቤንም ሳልጨርሰሰ  በሩ ክፍት አለ ። የበረከት አባት ፊቱን ጭጋጎት አድርጎ ፊቴ ተገት ሮ እያየኝ ነበር ............????? . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣3⃣
660
17
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣1⃣ ........ክው ብየ ደርቄ ቀረሁ ። በሰአቱ ራሴን የትም ሆነ እንዴትም ልደብቅም ሆነ ከአቶ ሰለሞን ልደብቀውም ሆነ እንዳያየኝ ላደርግ አልችልም!!! በሰአቱ ያለኝ አማራጭ ቆሞ መጠበቅ ነበር !! ልክ አባቷን በጉጉት እንደምጠብቅ ህፃን ልጅ በር በሩን እያየሁ ቆሞ መጠበቅ ነበር !!! የልጁን ጤንነት ለማየት ተቻኩሎ የመጣው አባት ከዶክተሩ ጋር እያወራ በሩን ክፍት አድርጎ ገባ ። ያቤፅ ደግሞ ከዃላ በድንጋጤ ቆሞ ምን ላርግ??? በሚል ፊት ይመለከተኛል !!!! እኔ ከደነገጥኩት ባልተናነሰ ሁኔታ እሱም ደንግጧል ። ለምን እንደዛ ሊለየን እንደፈለገ ባላውቅም የአመታት ጠላቱን እንዳየ ደመኛ ቀጥ ብሎ ቆሞ ፊቱን አጨማዶ ያየኛል !!???? ምን እንደማረግ ምን እንደምል የማላቀው እኔ አሁንም ግራ በመጋባት ስሜት ተሞልቼ ቆሜ እያየዃቸው ነው !!!!! መፍትሄው እንደሆነ ሳናወቅ በመፋጠጥ ብቻ ደቂቃዎችን አባከንን !!! ከዛም በቀስታና ግርማ ሞገስ በተላበሰ አረማመድ ወደኛ መምጣት ጀመረ። ለዛ ቀን ሲባል የቤት ግድግዳ በአንድ በኩል ክፍት ቤሆን ኖሮ ብዬ ተመኘው !!!!! እሱም አልበቃ ብሎ ምን አለ መሬት መደበቂያ ቦታ ቢኖራትም ብዬ ተመኝቻለሁ !!!! ፊቱ ቀለል ያለ እና መልከ መልካም ቢሆንም ከዚ በፊት የተለያየንበት ሁኔታ ጥሩ ስላልነበረ እፈራዋለሁ !!! አጠገቤ እንደደረሰ በጥፊ የሚያጋጨኝ መስሎ ተሰማኝ !!!! ያቺ ትንሽ ቤት ራቀችብኝ ። !!!!!! ከበሩ እኔ ጋር እስከሚደርስ ያለው ርምጃ ረዘመብኝ !!!!!! ከስንት የልብ ምትና ፍራቻ ቡሀላ አጠገቤ ደረሰ ። በቤኪ በግራ በኩል ቆመ ። እኔ በቤኪ በቀኝ በኩል ቆሜ እያጎረስኩት ነበረ !!!! በስተመጨረሻም ፊት ለፊት ተፋጠጥን !! " እዚህ ምን ታደርጊያለሽ ??""  ብሎ ዝምታውን ሰበረው ። እ አይ እ ... እያልኩ የ አ ቤት ፊደላትን ጥሪ የተባልኩ ይመስል እ አይ እ እያልኩ እቀባጥራለሁ !!!! " ባለፈው ቀን አላደመጥሽኝም መሠለኝ !!" አለኝ ።   አሁንም የኔ መልስ ዝምታ ነው በኩራት ከጁ ላይ ሰአት እየተመለከት " ብዙ ሰአት የለኝም ግን እባክሽ ብቻሽን ላናግርሽ " አለኝ ????? አሁን የበለጠ ፈራሁኝ ። !!!!!ግን አሁንም ቃል አላወጣሁም ዝም ብዬ አየዋለሁ ። " እባክሽ " አለ እጁን ወደ በሩ እየዘረጋ ። ምን ያርገኝ ምን ይበለኝም ሳላውቅ ቀጥጥጥ ብዬ ወጣሁ ። ከዛ እጆቼን አጣምሬ አይኔን መሬቱ ላይ ተክዬ ቀረሁኝ ። ከዃላይ ቀስ ብሎ መጣና ፊት ለፊቴ ግትር አለ ። "  የምትፈልጊውን ያሆል ገንዘብ እሰጥሻለሁ ስንትም ይሁን የአንቺንም የእናትሽንም ህይወት የምትቀይሪበት ገንዘብ ልስጥሽ ብቻ ከልጄ ራቂ "" አለኝ ???!!!! ጭራሽ ያልጠበኩት ንግግር ነው ። ሰው ሲያከብረኝ ነው የማከብረው ። የነበረውን ሞገስ በአንዴ አጣ !!!! ለሱ የነበረኝ ክብር ዝቅ ሲል ቀና ብዬ ተመለከትኩት !!!!! ምን ማለት ነው ፍቅር በገንዘብ አይገዛም እሺ ?!!!!!!! አለምዬን በገንዘብ ነው የገዛሀት እንዴ እ !!!!! ሌላ ሰው እንዳይሰማ !!! እኔ ማንነቱን እንጂ ያለበት ደረጃን ወይ ሌላ ነገሮች አደለም የወደድኩት !!! ብዬ ተመልሼ ስገባ ........... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣2⃣
516
18
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣0⃣ .......እጄን መጎተት ሲጀምር ከዛ በላይ ዝምታን ያልቻለው ቤኪ አባዬ !!! ብሎ ጭክ አለ። የቤኪ አባት ኮስተር ሲል በጣም አስፈሪ ግዙፍ ነው !!! ግንባሩን አጨማዶና ቅንድቡን ሰቅሎ ወደ ቤኪ ዞረ ። እንዳይመታው ፈርቼ ነበር ግን በአባት እና በልጅ መሀል መግባት ስላልፈለኩኝ ግራ እየተጋባሁ እያለ ያቤፅ መቶ በአንድ እጁ እኔኔ በአንዱ እጅ ጄሪን ይዞ እየጎተተ አስወጣንና በር ላይ "ገና ወደዚ ከመመለሱ ድጋሜ እንዲሄድ አታድርጊው በእናትሽ !!!!! " አለኝ ። ምን አድርጌ ያቤፅ እ አልኩት መደበቅ የማይችለው አፉ ሁሉንም ነገር  ነገረኝ ። ቤኪ ወደ ውጪ የመሄዱና ትምህርት አቋረጥ የመቅረቱ ምክንያት እኔው መሆኔን ተናገረ!!! ለካስ  አባቱ ከእኔ ጋር አይቶት ነው ከአባቱ ጋር ተጣልቶ ጥሎኝ ለመሄድ የሞከረው ።!!!! እናም ያቤፅ በቀስታ አረጋግቶ ነገረኝ !! " ድጋሜ ችግር ውስጥ ከገባ ላይመለስ እንደሚልከው ተናግራል እሱ ደግሞ ካወራ አወራ ነው ።!!!" አለኝ ከዛ በላይ ችግር መፍጠሩንም ሆነ ቤኪ እንደዛ ሆኖ ማየት አልችልም !!!!!! ስለዛ ከጄሪ ጋር ተያይዘን ቀጥ ብይ ከዛ ቦታ ወጣሁኝ ። ሁሉም ነገር አስከፍቶኛል በጣም ከባድና አሳዛኝ ቀን ነው ያሳለፍኩት !! ከዛ ቀን ቡሀላ ቤኪን እንኳን በስርአት ማውራት አልቻልኩኝም !!! ልክ አባትየውና ዶክተሩ ከዛ ክፍል ሲወጡ ያቤፅ ይደውልልኛል ገብቼ ስሜው ናፌቆቴን ተወጥቼ ቁስሉን ዳብሼ ነካክቼ አውርቼው ለማስታወሻ እያልኩ ፎቶ  እያነሳሁት ......ብቻ በተመሣሣይ መንገድ እስስከ ሳምንት ድረስ በአንድ አይነት ሁኔታ ቀጠልን ። ቀስ በቀስ ቤኪ እያገገመ መጣ ። የኔ አካልም ልቤም ቀልቤም ሁሉ ነገሬ ቤኪ ጋር ሆኖ ትምህርቱን እየተውኩት መጣሁኝ ። ተደብቄ ገብቼ ስንጫወች ሰንስቅ እየቆየን ስለነበር መማርን ረሳሁት !!!! ፈተና እንደደረሰ ሰሰማ ብቻ የገረፍታ ንባብ እያነበብኩ ባለችኝ ጭንቅላት ፈተናውን ሰራሁት ። በቀጣዩ ቀን ሌሌት የቀሰቀሰኝ የእናቴ ስልክ ነበር ። ስለ ቤኪ ነግሪያት ስለነበረ ስለሱ አጥብቃ ጠየቀችኝ እኔም ደህና መሆንኑን  ነገርኳት ። እንደለመድኩት ሀገር አማን ብዬ ከጊቢ ወጥቼ የምገዛውን ገዛዝቼ ምግብ ቴክአዌ አድርጌ ወደ  ቤኪ ጋር ደረስኩ ። ሳየው የሚያሳዝን አስተያየት ተኝቷል ። ትንሽ ቆይቼ እቀሰቅሰዋለሁ ብዬ ምግቦቹን መብያ ወንበሮቹ ላይ እየደረደርኩ እያለ ስልኬ ጠራ  ቀጥታ አነሳሁት ። ሄሎ .... " አባትሽ ነኝ !!" አለ ። እባክህ ዛሬ ደስ የሚል ጅማሮ ላይ ነኝ እና ማዘኔ አልፈልግም!!!!!! አልኩት ። " ልጄ ተይ አረ ልቀርብሽ ስሞክር እንኳን ተረጂኝ !!!!!"አላኝ እሺ ቡሀላ ደውላለሁ ዘጋሁት ። በቀስታ  ቤኪን ቀስቅሼ  የተደተደረውን ምግብ አስተካክዬ ሰጠሁትና ሊበላ ተዘጋጅቶ ገና እጁን ሲሰበስበበሪ ክፍት አለ ???? በዛ ላይ ሰለሞን ነበር የበረከት አባት !!! ክው ብዬ ደርቄ ቀረሁ ........ . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣1⃣
759
19
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣9⃣  ........አለ ቤኪ ክው ብሎ ። ዩንቨርሲቲ ውስጥ ከአንዴም አራቴ ያየሁት ሰው ነው ። ወፈር ብሎ ረዘም ያለ ኩል የሆነ አለባበስ ያለው የሚያምር ቀይ ሰው  ነው ግን ግንባሩ ጭምድድ ያለ ሰው ነው  ። የዚህ ሁሉ ልጅ አባትም አይመስልም !!! በሁለት እጄ  አጣምሬ የያስኩት እጁን ለቅቄ ወደ ዃላ እየደበኩኝ ፍጥጥ ብዬ አየሁት ያቤፅና ጄሪም በድንጋጤ አንዴ እኔን አንዴ የቤኪን አባት እየተመለከቱ ደርቀው ቀሩ ። " ምንድነው እዚህ ምን ታደርጋላችሁ ያቤፅ " አለው ግርማ ሞገስ ያለው ወፍራም የተረጋጋ ድምፁን እያሰማ። " አይ ቤኪ እኮ  ....." ብሎ ዝም አለ ። " ቀጥል በረከት  ምን ??? " አለው ወደኛ እየቀረበ ። " አረ ሶል ቤኪ ትንሽ አሞት እኮ አስደነገጠን እና ወደዚ ይዘነው መጣን አለ ወደ ቤኪ እየቀረበ ። ዞር ብዬ ሳይ ቤኪ ብርድ ልብሱን ጭምቅ አድርጎ ይዞታል ??? የቤኪ አባት በዝግታ እየተራመደ ወደኛ ሲመጣ ያቤፅ ከፊት ቀድሞ ቆመና " ሰሌ ደህና ነው አሁን ተረጋጋ እሺ እዚህ ጋ ቁጭ በል " አለው ወደ ወንበሩ እየጠቆመ ። " ያቤፅ አትልፋ ታቀኛለህ እኮ " ሲለው በአንዴ ተግባቡ ። መንገዱን ለቆ ጥጉን ይዞ ቆመ ። ከያቤፅ ጥሪ እንደተረዳሁት ከሆነ ስሙ ሰለሞን ነው መሠለኝ።  ሁላችንንም አልፎ ወደ ቤኪ ተጠጋና በእጁ ጨምቆ የያዘውን ብርድ ልብስ ገፈፈው ። ክው ነው ያልኩት የቤኪ ሆድ ከጎን ላይ ታሽጓል ። ምን ያህል ስሜቱን መደበቅ እንደቻለ አላውቅም እኔ  ሙሉ ቀኑን አብሬው ስውል ሆዱ ላይ ስተኛ ስነካካው ......... እንዴህ እንደተቆጣጠረው አላውቅም እኔ !!!!!! ምንድነው ምን ተፈጥሮ ነው ??? አልኩኝ አምልጦኝ ነው !!!!የቤኪ አባት ዞር ብሎ በሆነ በሚያስፈራ አስተያየት ተመለከተኝ ። " በዚች ልጅ ምክንያት ነው አይደለ !!! " ብሎ በሚያስፈራ አስተያየት አየኝ ። " አራ አባ እሷ ምንም የምታቀው ነገር የለም ስትሰማ ደንግጣ እየሮጠች መጣች አለቀ ብሎ ለኔ ለመሸፋፈን ሞከረ ። " ዶክተርክ ሁሉንም ነገር ነግሮኛል ከማን  ጋር ተጣልተህ ነው በል ተናገር ቶሎ ። "ፐብሎ ተናገረው ። " እንደዛ አይደለም አባ እሷ ምንም አታቅም !!!!!!!!" አለው ። " በሞትና ህይወት መሀል እያለህ ለሷ ትሟገታለህ ደደብ " አለው የአስተማሪ ነገር ። ወዲያው ዶክተሩ መጣ ። "እሺ አሁን ምን እናድርግ????" አለው  የቤኪ አባት ወደ ዶክተሩ እየቀረበ !!! እሱ ዞር ሲልልኝ ጠብቄ እጆቹን ይዤ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ እየጠየኩት እያለ  አባሁ ዞረ ። ቶሎ ለመልቀቅ ሞከርኩኝ ። ነገር ግን ከእይታው ማምለት የማይታሰብ ነው ። " ልጄን ልታስገድይብኝ ነዋ????....ብሎ አፈጠጠብኝ ። ምንም የማላቀው እኔ ቤኪና ያቤፅን በየተራ እያየሁ ጉዳዩን እንዲያስረዱኝ ጠብቃለሁ !!! ያቤፅ በሚያሳዝን ፊት አየኝና " ሶል እሷ ምንም የምታቀው ነገር የለም ዛሬ ገና ነው እንደታመም የሰማችው " ብሎ ለመሸፋፈን ሞከረ ። አሁንም ከኔ ጋ ምን እንደሚያገናኘው ግልፅ አልሆነልኝም ?????? ወደ ቤኪ ተጠግቶ እንደ ህፃን ልጅ ፀጉሩን አሻሸና ቀና ብሎ " ትሰሚኛለሽ የስለት ልጄ ነው በልጅነት የተፈተንኩበት ልጄ ነው እዚጋ አምሮበት ደምቆ ተውቦ ስላገኘሽው ብቻ አይደለም ብዙ ዋጋና ፈተና ተከፍሎበታል!!!! ትሰሚኛለሽ የብዙ ነገር ማስታወሻዬ ነው እንኳን እንደዚህ ሆኖ ላየው ይቅርና እንቅፋት ሲመታው ራሱ ያመኛል ገባሽ  " አለኝ ። ሳላስበው እንባዬ አመለጠኝ ። በተናገረው ንግግር ብቻ ሳይሆን የማላቀውን የአባትነት ፍቅር በሱ ላይ አየሁት !!!! የማላቀውን አሳየኝ አባት ለልጁ ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ ሳይ ...... ሁለት ልጄ ብለው ጠርተውኝ የማያቁ ድብደባ ጥላቻ ቁጣን አንዴም አባትነትን መካድን ቆይቶ መመለስን .....ብቻ የማይረቡ ነገሮችን እያሳዩኝ የነበሩት ሁለት አባት ከተባሉ!!! እሱን አሰብኩኝና የምር ከፋኝ !!!!! ሳላስበው እንደ ህፃን ልጅ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩኝ !!!!!!! አንዳንዴ የኔ ስጋ የምትለው ሲከዳህ በዙሪያክ መልካም ሰዎችን በመላክ ይክሳልና ጄሪና ያቤፅ ወደኔ መተው  አባበሉኝ ። ጄሪ እንባዬን ከፊቴ ላይ እየጠረገች " እረፊ እነሱ ፊት አታልቅሺ " አለችኝ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ ። ራሴን እንደምንም አሳምኜ እንባዬን ወደ ውስጥ መልሼ ተነፈስኩና ለእርሶ ልጆ ነው እኔ ደግሞ ልጆን እወደዋለሁ ከእርሶ እኩል አስብለታለሁ እጨነቅለታለሁ ከችግሮች ልመልሰው እንጂ መቼም ችግር ውስጥ እንዲገባ አላረግም አልኩኝ አፌን ሞልቼ !!! ሰው ቀና ብዬ ለማየት የምፈራ ልጅ ያንን ድፍረት ማን እንደሰጠኝም ላውቅም !!!??? ስገምት ግን አፌን ብዘጋ የተሻለ ነበር መሠለኝ የበለጠ ተናደደ ። አንገቱ ላይ የተቋጠረውን ከረቫት እያላላ " አንቺ የልጄን ጠባሳ የፈሰሰውን ደም ትመልሻለሽ " ብሎ በጩኸት ቤኪ የለበሰውን ብርድ ልብስ ገፈፈው። በፈጣሪ ስም ከድንጋጤዬ ብዛት እዛው ቀጥ ልል ነበረ!!!!! ቤኪ ለመሸፈን ቢሞክርም አየሁት ሆዱ ጋር በስለት እንደተወጋ ሰው አራት መአዘን ቅርፅ ታሽጋ በብዙ ነገር ተሸፋፍናለች !!!! መጀመሪያ ላይ እኔ ዝም ብሎ ህመም ያመመው እንጂ እንደዚ አይነት ነገር አልጠበኩኝም !!! ከድንጋጤዬ ብዛት እጄ እየተንቀጠቀጠ አፌ ተያያዘ ። " እስካሁን ብዙ ነገር ስታወሪ አልነበር ምነው  ድንገት ዝም አልሽ ጥፋትሽ ገባሽ "......እያለ ያወራል ??? እኔ እሱን ረስቼዋለሁ ንግግሩ አይሰማኝም ቤኪ ምን ሆነክ ነው ማነው እንዲህ ያደረገህ  ማነው ምንድነው ........ምን እንደማወራም አላቅም ብቻ ድንገተኛ መርዶ እንደተነገራት እናት እጄን አንዴ  ጭንቅላቴ ላይ አንዴ እሱ ላይ እያደረኩኝ እርበተበታለሁ ። " ምን እንዳላወቀ ትሆኛለሽ ባንቺ ምክንያት እኮ ነው ከዚህ ቡሀላ ልጄ አጠገብ ባይሽ መጥፎ ችግሮች ይፈጠራሉ እወቂ!!!!!! ልጄ አጠገብ እንዳላይሽ አሁን ቀጥ ብለሽ ከነ ጓደኛሽ ከዚህ ሂጂ ላትመለሽ .....ገባሽ !!!!" ብሎ እየጮከ እጄን መጎተት ሲጀምር ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣0⃣
759
20
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣8⃣ ..........አይኑን ክድን አደረገው !!! በፈጣሪ ስም ለአራት ሰከንድ አይኑን ጨፍኖ ቢቆይ በዛች ሰከንድ አይኑን ጨፍኖ የሚቀር መስሎኝ ምን ላደርግ እንደነበረ ራሱ አላውቅም ???!!!!! ብዙ ነገር ከማሰቤና ከመናገሬ ቀድሞ መሎሶ በዝግታ አይኑን ገለጠነ " አቡ " አለኝ ። ሞቼ ተነስቼ ቃላትን እየሰማሁ ነው የመሰለኝ ማለት እችላለሁ !!!! ሁለት ፊደላት አረጋጉኝ !!! ከድንጋጤዬ ብዛት ግን መናገርም መንቀሳቀስም ከብዶኝ ነበር !!! የሰማያዊት እናቴን  ስም እየጠራሁ ደጋግሜ አማትቤ ራሴን አረጋጋሁኝ ። ወደራሴ ስመለስ ቀረብ አልኩኝና እጆቹን አጥብቄ ይዤ ቤኪ የኔ አባት እኔ አንተን አጥቼ መኖር አልችልም የኔ አባት እንዴትስ እችላለሁ " ፀጉሩን እየነካካሁ .እጆቹን እነሳምኩ ) አንተ ለኔ ፍቅርን ያስተማርከኝ ሰው ወዳድ ያደረከኝ ያበረታከኝ ፅኑ ሴት ያረከኝ ነገሮችን በተግባር ያሳየከኝ ሁሉ ነገሬ ነህ የድሮዬ የአሁኔ የወደፊቴም ...........በስሜታዊነት ሳላስበው   በጣም ብዙ ከኔ ይወጣሉ የማልላቸውን ከየት እንዳመጣዋቸውም የማላቃቸው የፍቅር ቃላት ለፈለፍኩበት ። እውነት ለመናገር ብዙ እንዳወራሁ የገባኝ ራሱ ንግግሬን ጨርሼ ሳያቸው ሶስቱም ከንፈራቸው ለጠጥ አድርገው በፈገግታ እየተመለከቱኝ እንደነበር ሳውቅ ነው !!! " የኔ እናት  እንደዚህ ያማሩ ንግግሮች ካንቺ መስማት ለኔ ፈውስ ነው እኮ " ብሎ አጥብቀው የያዙት እጆቼን ስሞ አንገቱን አስደገፈበት !!! የቤኪ የግል  ዶክተር የተባለው ሰውዬ " ብዙ አታስወሩት ለቁስሉ ጥሩ አይደለም" ብሎን በነፃነት እንድናወራ ጥሎን ወጣ። አራት እብድና የፍቅር ሰዎች አንድ የተዘጋ ከፍል ውስጥ ተገጣጠምን ። ለወሬ እንዲመቸን አድርገን ወንበሩን አስቀምጠን መፋጠጥ ጀመርን ። ለወሬ ማስጀመሪያ ብዬ የቤኪ የዚህን ያህል ቅርብ ሰው ከሆንክ እንዴት አላቅህም ቆይ ???? አንድም ቀን አይቼክ አላቅም የት ነበር የምትማረው ?? አልኩት ያቤፅን አንን አይኑን በጥያቄ ፊት እያየሁኝ !! " እኔ ግን በደንብ ነው የማውቅሽ ካንቺ ቀድሜ ነው መፈቀርሽንም ያወኩት ( ፈገግ እያለ ) እኔ የተማርኩት እዚህ አይደለም የምኖረውም እዚህ አካባቢ አልነበረም "" ብሎ በስሥም ብቻ የማቀውን የሀብታም ትምህርት ቤት ስም ጠራልኝ ። ጄሪም እንደመንቃት ብላ ቆይ ግን ለምንድነው እነ አቡ ትምህርት ቤት የገባከው አለችው ። ቤኪ ብዙ እንዳያወራ ነፈለገው ያቤፅ ከእራሱ በላይ እንደሚያቀው ሰው በኮንፊደንስ ተሞልቶ ነገረን " ከአስተማራ ጋር እየተጣላ ትምህርት እያስደገሙት  በጣም ሲቸገር ዘጠነኛ ክፍልን ብቻ እዛ ተምሮ ይመለስ ብለውየመንግስት  ቢያስገቡት  የበለጠ ረብሾ አንድ አመት ደገመ በሰከንድ ግን ቅይር አለ እድሜ ለአንቺ !!" " ማለት " አለች ጄሪ ቀደም ብላ ። " ትምህርት በገባ በሳምንቱ ጠብ አደረገችው ተቃራኒ ባህሪ ስላላቸው አብረው እሱ ግንፍል ሲል አቡ እያበረደች ። እሱ ሊጣላ ሲል ፍቅር እየሰጠች ተንከባክባ በዛው እንዳቀጥል አደረገችዋ እንደዛ ተማሪ ያረገውን ጫማ አላደርግም የሚል በሽተኛ ልጅ ጠብ አደረገችው !!!!*" ብሎ ትንሽ ማጋነን የበዛባት ክሽን ያለች ቆንጆ ንግግር አደረገ !!! አንዳችን አንዳችንን እየተጠያየቅን ስንስቅ ስንስቅ እዛው አመሸን ። ሁላችንም ወደ ጊቢ የመመለስ እቅድ የለንም ደግነቱ ቁጭ ብለን ስናወራ ነበር ። በመሀል እናቴ ደወለች ። ብትሰማ ለአለምዬ እንደምትነግራትና እንደምትጨነቅ ስላወኩኝ ዝም እንዲሉ ተናግሬ ስልኩን አነሳሁት ። " አብዬ ሳጀውይልኝ ዋልሽ እኮ እናቴ ጨነቀኝ እና ነው የደወልኩልሽ " አለችኝ ። የኔ ኘዋህ እናት !!!!!!!❤❤❤ ድምፄን እያንሾካሸኩኝ ቀስ ብዬ እናቴ ጠዋት እደውልልሻለሁ አሁን እያጠናሁ ነው እሺ ደህና ነኝ እወድሻለሁ አልኳት ። እኔን ለማመን አታመነታም !!! እሺ እሺ እማ ብላ ስምኩን ዘጋችው ። ወዲያው ስልኩን ከመዝጋቴ " አንድ ጥያቄ አለኝ እኔ "  አለች ጄሪ ምንድነዎ ተረጋጊ እንጂ ቀስ ብለሽ አውሪ አልኳት መልሼ "  በመጀመሪያ  አራታችንም በአንድ ቀን ነው የምንጋባው !!!! ጥያቄው ግን መች ነው የምንጋባው ሁላችሁም ተናገሩ ። እኔ ከአራት አመት ቡሀላ ጥር ሀያ አንድ ላይ " አለች ፍልቅልቅ እያለች ። ደስታዋ ፊቷ ላይ ይነበባል ። እስካሁን በዝምላ ነቆየው ቤኪ "" እኔ የምመኘው ግን ....." ሲል በሩ ብርግድ አለ ። ያቤፅ የጄሪን እጅ ለቆ ብድግ አለ " አባ "  አለ ቤኪ ክው ብሎ ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣9⃣
743