ch
Feedback
📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

前往频道在 Telegram

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾 ➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና እንጊሊዘኛ ..... መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ። 📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️ B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር 100K ይደርስ ነበር ። For any comment @Meki3

显示更多
2 265
订阅者
+124 小时
+77 夊
+330 夊

数据加载中...

吸引订阅者
八月 '26
八月 '26
+70
在0个频道中
䏃㜈 '26
+141
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+109
在1个频道中
Get PRO
五月 '26
+67
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+48
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+60
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+45
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+65
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+92
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+56
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+50
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+70
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '25
+58
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+66
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+92
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+74
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+55
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+38
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+56
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+68
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+67
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+37
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+46
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+65
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '24
+81
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+35
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+36
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+42
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+47
在2个频道中
Get PRO
二月 '24
+46
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+32
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+63
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+37
在1个频道中
Get PRO
十月 '23
+63
在2个频道中
Get PRO
九月 '23
+58
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+77
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+63
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+46
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+39
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+41
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+54
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+192
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+125
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+46
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+57
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+66
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+64
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '22
+40
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+43
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+64
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+93
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+36
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+47
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+54
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+75
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+135
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+97
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+132
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '21
+142
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+114
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+71
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+190
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+122
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+172
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+180
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+1 524
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
26 八月0
25 八月+3
24 八月+3
23 八月+2
22 八月+3
21 八月+4
20 八月+3
19 八月+3
18 八月+2
17 八月+5
16 八月+3
15 八月+2
14 八月+4
13 八月+1
12 八月+1
11 八月+4
10 八月0
09 八月+2
08 八月+3
07 八月+2
06 八月+2
05 八月+4
04 八月+3
03 八月+1
02 八月+8
01 八月+2
频道帖子
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣7⃣   .........,እዛው ቁሜ ቀረሁ ; ከዛ ልዕልናን ዞሬ ሳያት እንዴት እንደተረዳችኝ ባላውቅም ከተቀመጠችበት እየተነሳች " እማ እሱኮ ሚኪ ነው አስተዋውቅሻለሁ ያልኩሽ ልጅ እሱ ነው ጥሩ ልጅ ነው በዛ ላይ  የአባዬ ጓደኛ ነው እኮ " አለቻት ልክ እኔ በያት ልላት አመት እዳሰብኩት ለዛውም የተሻለ አርጋ አሳመነችልኝ ። ቀስ ብላ ተረጋጋች አየር እየሳበችና እየተነፈሰች ራሷን አረጋጋች ። ይቺ ሴት እብድ አይደለችም !!!! ምን ማረግ እንዳለባትም ሆነ ምን እያረገች እንደሆነ ጠንቅቃ ታውቃለች ራሷን እንዴት እንደምታረጋጋ ሳየቀር ታውቃለች ። ሰው  ስለበደላት የሰው ጥላቻ ብቻ ነው እሷን የጎዳት  !!!! እና እሷን ለማረጋጋት በጣም ቀላል ነገር ነው !!! እኔም እድሌን ተጠቀምኩኝ እግሯ ስር በርከክ ብዬ እያረጋጋዋት ላንቺ ባይመጥንሽም ስለ አንቺ ስለነገሩኝ ትንሽዬ ስጦታ አምጥቼልሻለሁ ማየት አፈልጊም ?? አልኳት ። ተመቻችታ እየተቀመጠች ቁጥብ ፈገግታ አሳየችኝ ።ከዛም ብልጭልጭ ቢሆንም በምርጫ ጎበዝ ነኝ መሠለኝ ስጦታውን ሳወጣሁ ሁሉም ተገርመው አዩኝ ሳስበው አልጠበቁም መሠለኝ !! እሷም በጣም እንደወደደችው እንድገምት የሚያደርግ ፊት አሳየችኝ ። ከዛም ከማስቀመጫው ላይ አውጥታ እየወሰደች " በጣም ያምራል " አለችኝ በለሆሳስ ። ድምጿ በጣም ደስ ይላል !!! በዛ ላይ በጣም ቆንጅዬ ናት !!! በርግጠኝነት ሳሚ ራሱን ጥፋተኛ አደረገ እንጂ  በቁንጅናዋና በእድለኝነቷ የተነሳ በቅናት ተገፋፍታ እንዲ ያደረገቻት ይመስለኛል !!! ግን ምን አይነት ጭካኔ ነው በፈጣሪ የፈለገ ቢሆን እንዴት አብሮ አደግ ጓደኛዋን እንዲ ታደርጋታለች ሴትዮዋን ባቃትና የኔ እናት ብትሆን የምገላት ሁላ መስሎ ተሰማኝ !!! ብቻ ግን ቃሉ አትፍረድ !! ነውና ፈርጄ ከጨረስኩም ቢሆን አስታውሼ ዝም አልኩኝ ። እኔ ሀብታም ሰዎች አርቴፊሻል ነገር የሚጠቀሙም አይመስለኝም ነበር ፊቴ ላይ ትወረውረው ይሆን እንዴ እያልኩ እየፈራሁ ነበር የሰጠዋት ። ከጠበኩት በተቃራኒው ግን በጣም እንደወደደችው እየነገረችኝ በፍቅር አይን  እያየችኝ " አመሠግናለሁ በጣም " አለችኝ ። ኡፍፍፍ የኔ እናት እርጋታዋ ደርባባነቷ በጣም ነው ደስ የሚለው ። ረጅምና ለስላሳ ፀጉሯ ሁለት ቦታ እንደተሰራ የቆየ ይመስላል ። ያ ቀይ ፊቷ በቁስል እና በተቧጨረ ነገር ተሞልቷል ሲመስለኝ ሲያማት ራሷን ለማጥቃት ትሞክራለች መሠለኝ !!! ግን የተፈጥሮ ውበቷ ያስታውቃል በዛ ላይ ያን ያህል ትልቅ አይደለችም ወጣት የምትባል ሰው ናት !!! እኔ በሷ ተፈጥሮ እየተመራመርኩ ለካ ሳሚ እያወራ ምን እንዳለ ሳልሰማው " እናመሠግናለን  " ሲል ብቻ ሰማሁት ። ምን ይበል ምን ባላውቅም አረ አይባል ሳሚ ብዬ ፈገግ አልኩኝ ። ከዛ እዛ ሀብሉን ልታረገው ስትል አይ አይ እንደዚ አይደለም መጀመሪያ አንዱን ልዕልና አንዱን ሳሚ ፀጉርሽን ይፈቱታል ከዛ ረጅም ሰአት የሚፈጅ ሻውር ከባለቤትሽ ጋ ትወስጃለሽ ቀስ ብሎ ያጥብሻል ከዛ ልብስ ትቀይሪና ጌጥሽን አድርገሽ ዛሬ ከእኔ ጋር ነው ምሳ የምንበላዎ እንጠብቅሻለን አልኳት መልሷ ምንም ቢሆነን ለመጋፈጥ እየተዘጋጀሁ ። እንዳሰብኩትም ማልቀስ ጀመረች ስቅስቅ ብላ ካለቀሰች ቡሀላ ወደኔ ተጠግታ ጭምቅ አድርጋ አቀፈችኝና " የምር እንዳልከው ማረግ እችላለሁ እ ??" ብላ በጥያቄ ፊት አየችኝ ። እኔም በደስታ ተሞልቼ  አዎ አዎ በደንብ ትችያለሽ በጣም ቀላል ነገር ነው እኮ ትችያለሽ !!!! ብዬ ለማነቃቃት ሞከርኩኝ ተመቻችታ ተቀምጣ  ዞር ብላ ሳሚን አየችው ። እሱም እሺ የምትል ስላልመሠለው ችላ ብሎ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም  ስታየው በደስታ ተነስተው ሁለቱም እንደ እንቁላል እየተንከባከቡ በቀስታ ፈቷት ። በጣም ተጎድቶ ራሱ የሚያምር ፀጉር አላት ከዛም ወደ ሳሎን ተመልሰን እኔና ልዕልና ቁጭ ብለን ሁሉም ሰላም እንዲሆን እየፀለይን ቆየን ። ከዛም ቀራርቦ  የነበረው ምግብ አንዳንዶቹን እያነሳች ማሞቅ እና ሰላም በፊት ላይ ትወዳቸው የነበሩ ምግቦችና ጁስ መጨመር ጀመረች ። ልዕልና በጣም ጨንቋት ስትቆም ስትቀመጥ ስትነሳ ስትጨነቅ ነበር እውነት ለመናገር እኔም በጣም ፈርቻለሁ !!! የሆነ ነገር እንደሚቀየር እያሰብኩ ተጨንቄ ነበር ። እዛው ተቀምጠን ከ አንድ ሰአት ከሀምሳ ደቂቃ በላይ ቆየን !! አዲስ ነገር ብንጠብቅም ቆዩብን።እስከዛ ሰአት ሰላም መሆናቸው ትንሽ አረጋግቶኝ ልክ ቁጭ ስል የሚረብሽ ጩኸት  ሰማንና ሁለታችንም ለሩጫ እንደተዘጋጀ አትሌት በሩጫ ወደመታጠቢያ ቤት ሮጥን ......... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣8⃣

2
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣6⃣  ........ ከማያ ጋ ተገጣጠምኩ ። በፊት ላይ አግኝቻትም የማላቃት ልጅ አሁን በዚህ ልክ መገጣጠማችን በጣም እያስገረመኝ ነው ። አሁን አልተሳሳትኩም ራሴን እንደምንም ተቆጣጥሬ አለፍኳት ። የሆነ አካሌ ግን ያዛት ያዛት ይለኛል ?? ከዛም ምን እንደሚያያዝ ባላውቅም ሀብታም ቤት  ሙዝ ይዤ አልሄድም ብዬ ገበያ ውስጥ ስዟዟር የሆነ የሚያምር ጌጣጌጥ ቤት ተመለከትኩኝ ። አርቴፊሻል ቢሆንም የሚያማምር ሀብልና የእጅ ጌጥ አየሁኝ ። እና ሚኪ በጣም አስተዋይና አሳቢ ሰው ስለሆነ የሷን መንፈስ የሚያድሱና እሷን የሚያስደስቱ ነገሮች መግዛት ይሻላል ብዬ አሰብኩኝና በሌለኝ ብር መከራከር እንኳን አልችል የሚያምር ሀብልና የእጅ ጌጥ ገዝቼ በእቃ ላይ አስደርጌ ወደነ ሳሚ ቤት ሄድኩኝ ። ልክ እኔ ስደርስ የሳሚ  መኪና ስትገባ ተገጣጠምን ። ስራ ጨርሶ ምሳ ለመብላት መምጣቱ ነበር ። እኔም እግር ጥሎኝ እያልኩኝ በአይነት የቀረበው ምግብ ላይ ደረስኩኝ ። ሚኪ ከባድ የራስ መተማመን ተጭኖታል ። መኝታ ቤቷን ቆልፋ የምትኖረውን የልዕልናን እናት ሰላምን ጤነኛ ሰው ለማረግ ሀላፊነት ወስዷል ። ልዕልናም እጇን ተጣጥባ ስትመጣ ከኔ ጋ አይን ለአይን ተገጣጠምን ። እየሮጠች መታ ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ ። ደነገጥኩኝ ክው ብዬ እስክትለቀኝ መጠበቅ ጀመርኩኝ ። " ትላንት እኮ እናቴን አወራዋት ከስንት ጊዜ ቡሀላ አወራችኝ ስታለቅስ አየዋት በጣም  ነው የምናመሠግነው እሺ ደግሞ ስለ አንተ ነግሪያታለሁ እኮ አስተዋውቅሻለሁ ብያታለሁ  " ብላ ጉንጬን ሳመችኝ ። ክው ነው ያልኩት !!! ደንግጬ ፍዝዝ ብዬ ሳያት ምንም ሳትል ዞራ ምግቡ ጋ ቁጭ አለች ። ወዲያው አንድ የሚገርም ሀሳብ መጣልኝ ቀጥታ ወደ ሳሚ ዞርኩኝና አንድ ሀሳብ አለኝ !! አልኩ ፈገግ ብዬ " ምንድነው እሺ  " አለኝ ሳሚ ወንበሩ ላይ እየተቀመጠ ። ወደ ምግብ ከመግባታችን በፊት አንዴ ሰላምን እንያት አልኳቸው ። ቤቱ በአበቦች ነፈካ ስለሆነ ከማስቀመጫው ላይ አበባ ሳብ ሳብ አርጌ ሁለት አወጣሁ እና ይሄን ይዘን አልኳቸው ። " አሁን ምሳ ሊቀርብላት ነው ትብላና እናወራለን ከፈለክ " አለኝ ሳሚ በተጨናነቀ ፊት ። አይ አይ አይሆንም ምግብም አብረን ልንበላ እንችላለን ማን ያውቃል አልኳቸው ። በጣም ደስ እያለኝ ነው ሀሳቤን የነገርኳቸው !!! ሳስበው ሚኪ ጥሩ የስነ ልቦና ሀኪም መሆን የሚችል ይመስላል !!! በጣም አስተዋይ ሆኛለሁ ሲጀመር እዚህ ቤት ስመጣ ሌላ የማላቀውን ሰው ነው የምሆነው ። ብቻ ግን  መልሳቸውን ስጠብቅ ልዕልና ቀደም ብላ " ጥሩ ሀሳብ አይመስለኝም " አለች ሳሚም እሷን ተከትሎ " አዎ አትልፋ አይሆንም እሺ አትልም " አለኝ ከየት እንዳመጣሁት ባላቅም ይሆናል !!! ባይሆንም እንሞክረዋ ከሆነ ይሆናል ካልሆነ ቀጣይ ይሆናል ባለፈው ቀን እኮ አምንሀለሁ ብለከኛል እንደምታምነኝ አሳየኛ !!! አልኩት ። ሳሚም አላሳፈረኝም እሺታውን ለመግለፅ ከተቀመጠበት ተነሳ ። ልዕልና ሀሳቡን እንዳታስቀይረው ፈርቼ በእጄ ግትቼ ላነሳት ስሞክር ገና እንደያስኳት የሆነ የንዝረት ስሜት ስለተሰማኝ ደንግጬ ቶሎ ለቀኳት  ። ከዛም አበባውን ለሁለቱም  ሰጠዋቸውና እናንተ ግቡና እመጣለሁ ብያቸው ወደዃላ ቀረሁ ። ከዛም ወደ ልዕልና ጠጋ ብዬ ገብተሽ በደንብ አውሪያትና ከዛ እንግዳ ላስተዋውቅሽ ብለሽ ጥሪኝ አልኳት ቀስ ብዬ እሷም እሺ ብላኝ ወደ ክፍሏ ሄድን ። ሁለቱም ከመፍራታቸው የተነሳ በሩ ላይ ሲደርሱ ሁለቱም በረጅሙ ተንፍሰው አማትበው ወደ ውስጥ ገቡ ። ውጪ እያለች ልዕልና በጣም ፈርታ የነበረ ቢሆንም ቀበጥ መሆኗ ጠቀማት መሠለኝ ፍልቅልቅ እያለች " ማማ አየሽ ምን እንዳመጣንልሽ አበባ ላንቺ ነው እኮ ናፍቀሽን ነበር " አለቻት እቅፏ ውስጥ እየገባች። ሳሚ ቃላት ማውጣት ስለከበደው በፀጥታ ተውጦ ግንባሯን ሳማትና ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ ። ከዛም ልዕልና ቶሎ ብላ " እማ የማስተዋውቅሽ ሰው አለ " ብላ በምልክት  ጠራችኝ ። እስካሁን እነሱን ሲመክርና ሲያበረታታ የነበርኩ  ልጅ  ለመግባት ራሱ ፈራሁ ከዛ ግን ሳማትብ ለቀቀኝና ፈገግ ብዬ ገና እግሬን ሳስገባ ወደዃላ እየሸሸች መፍራትና መንቀጥቀጥ ጀመረች የሆነ መንፈስ እንዳየ ሰው አረጋት ። " ከነገርኩህ ጊዜ ጀምሮ ሰው ትፈራለች የማታቀውን ሰው አትወድም ትሸሻለች ነግሬህ ነበር እኮ እንደማይሆን " አለኝ ሳሚ ከተቀመጠበት ተነስቶ በቀስታ ። የነበረኝ ትልቅ በራስ መተማመን ይጥቀመኝ ይጉዳኝ ባላውቅም በራሴ ተማምኜ ሊሆን ይችላል ብዬ ወደሷ ቀርቤ ከአልጋው ስር በርከክ ብዬ ስቀመጥ በትልቅ ፍራቻ ታየኝ ጀመር ። እኔ በሌለኝ ብር አውጥቼ የገዛውት ስጦታ ልሰጣት ከሁዴዬ ውስጥ ፌስታሉን ሳወጣ እሪሪሪ ብላ ጮኸች መረበሽ ጀመረች ትራሶቹን ወረወረችብኝ ማልቀስ ጀመረች ......... በጣም ደነገጥኩ ሳሚ እጄን እየጎተተ እንደወጣ ቢነግረኝም እዛው ቆሜ ቀረሁ ....... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣7⃣
86
3
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የፍቅር የሰላም የጤና ያርግልን ❤️ @ethioleboled
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የፍቅር የሰላም የጤና ያርግልን ❤️ @ethioleboled
117
4
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣5⃣  ......... እጇን ጭምቅ አድርጌ ያስኩት ። ልጅቷ ስርአት ያላት ፈሪና ጭምት  ሰው ናት ። ስይዛት ከመደንገጧ የተነሳ እጆቿ እየተንቀጠቀጡ ነበር ። ግራ ቢገባት ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ " ምንድነው ችግር አለ ?" አለችኝ በታፈነና ቀስ ባለ ድምፅ ። ምን እያሰብኩ እንደነበር አላውቅም እንደመባነን ብዬ እጇን ለቀኳትና በጣም መርበትበት ጀመርኩኝ ። እ.... እ .... እያልኩኝ ወደፊት ወደዃላ መርበትበት ጀመርኩኝ ። ምን እንደሆንኩና ምን እየተሰማኝ እንዳለ ማወቅ አለመቻሌ የበለጠ ግራ አጋባኝና እረበሸኝ !!! ከዛ በላይ ከፊት ለፊቷ ቆሜ መጋፈጥ ስላልቻልኩኝ የሌለብኝን ከአንገቴ ጎንበስ ብዬ   ይቅርታ ብያት ፖሊስ እንዳባረረው ሌባ በሩጫ ከቦታው ራኩኝ ። ቀጥታ ወደቤት ሄድኩ ። ስገባ እናቴ ቡና እያፈላች ነበር ። " ምሳ ስጠብቅህ ቆየህብኝ እኮ ልጄ በሰላም ነው ሰሞኑን ከቤት መራቅ አበዛክብኝ " አለችኝ ። እውነት ለመናገር ልክ ናት ወይ ቤት አይደለሁም ወይ ደግሞ ቁጭ ብዬ ስለ ልዕልናና ስለ ቤተሰቧ እያሰብኩ አመሻለሁ በቃ !!! የዛሬው ለየት የሚያረገው ግን የእናቴን ስፔሻል ምግብ ድንይ በሽሮ ከበላሁና ድካም የሚያጠፋው ቡናዋን ከጠጣሁ ቡሀላ ገብቼ ስለ ማያ ማሰብ ጀመርኩኝ ። በርግጥ ስሟንም የማውቀው አንድ ትምህርት ቤትና አንድ ክፍል በመሆናችን ነው ። የክላሱ ቀለሜ እና ዝምተኛ የፊት ወንበር ወዳጅ እንደሆነች ባውቅም ትኩረት ሰጥቻትም ሆነ በስህተት እንኳን አውርቻት የማላቃት ልጅ አንድ ቀን በራሴ የፈጠርኳት ካራክተር ከመሆኗ ብሶ እንዴት ሆኖ አሁን ላይ የሚሰማኝ ስሜት እንደተፈጠረ አልገባ ብሎኛል ። ምሽቱን ሙሉ ከአይምሮዬ ማውጣት ከብዶኝ ተጨነኩ !!! ጠዋት በጠዋት ተነስቼ እንደተለመደው ተሳልሜ ኸደ ስፖርት ሄድኩኝ ። ሀሳቤን የሚያስረሳኝ ይመስል በጣም ለረጅም ሰአት ስሰራ ቆየሁ ። ረጅምም ሰአት ከመስራቴ የተነሳ በጣም ደክሜ ትንፋሼ መቆራረጥ ጀምሮ ነበር ቆይቼ አስተዋልኩት እንጂ  !! አሰልጣኙ መቶ እንዳቆሚ ስነግረኝ ነበር ትዝ ያስተዋልኩትም !!!! ከዛ ወጥቼ ቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩኝ ። መንገዱን ሙሉ ፊት ለፊት እንዳላገኛት እየፈራሁ እንደሰረቀ ሰው ዙሪያዬን እያማተርኩ በሰቀቀን ስጓዝ ከፈራሁት በበለጠ እናቴ መስከረም እና ማያ አንድ ላይ ፊት ለፊቴ ሲመጡ አየዋቸው ። ወደ ግራሞ ወደቀኝም ብመለከት መታጠፊያ የሚባል የለም መሀል ግድግዳዎች ናቸው ። ወደዃላ ተመልሼ ልሄድ እያሰብኩ እያለ ከሩቅ እናቴ ፈገግ ስትል አየዋት ደ ያ ማለት ደግሞ አይታኛለች ማለት ነው  ብዬ ስላሰብኩ ቀጥ ብዬ ቆምኩኝ ። የሚያናደው ደግሞ አጠገቤ እየቀረቡ ሲመጡ ነበር ያስተዋሉኝና የዛኔ ነበር የእናቴንና የመስከረምን ተገርሞ እኔን ማየትና የማያን ቀድንጋጤ ቀጥ ብሎ መቆም ያስተዋልኩት ። ምናለ ቀጥ ብዬ ብመለስ ያልኩት !!! ምክንያቱም ገና ሲቀርቡኝ ሌቤ መረበሹና እንግዳ ስሜቶችን ማስተናገድ የጀመርኩት ። አጠገቤ እንደደረሱ እንደሁሌው እናቴ አገላብጣ ሳመችኝና " ልጄ ስጠብቅህ ስትቆይብኝ እኮ ነው የወጣሁት " አለችኝ  ቀበል አድርጋም መስከረም እንደናቴ ከሰማችኝ ቡሀላ " ጎረምሳው አሁንማ እየጠገብክ ነው እንደልጅነትህም አይደለህ " አለችኝ ። እሷ ስታወራ ሲያስጨንቀኝ የነበረው ግን ሰላም ልበላት አልበላት እያልኩ ግራ ስጋባ ነበር !!! እጇን መንካት ፈራሁ ሁላ ብቻ አረ እንዴት እናንተ ላይ ይጠገባል አንድ ላይ አሳድጋችሁኝ ... ምናምን ብዬ ነገሩን ለመደባበስ ሞከርኩኝ ። "" የመስኪዬ ልጅ ናት እኩ ሰላም በላት እንጂ " የሚለው የእናቴ ንግግር ነበር ቆሌዬን የገፈፈው ። ምን እንደማረግ ግራ ገብቶኝ እናቴን ስመለከታት ቆየሁኝ ። በአይኗ ቁጣዋን ስታሳየኝ ደንግጬ እጄን ዘረጋሁላት እሷ ፈርታለች ቶሎ እጄን ነካ አድርጋ ሰበሰበችው ። ምንም ባላመጣው እኔን መንካት ደብሯት ነው ! በዬ ተናደድኩኝ ። ሳስበው ስናደድ ነው መሠለኝ ወደ እራሴ የምመለሰው ኮስተር ብዬ ሰላም ዋሉ ብዬ ማያን ገፍተር አድርጊያት አልፌ ሄድኩኝ ። ቤት ገብቼ ሻውር ወስጄ ጨርሼ ራሱ መናደዴን ማስቆም አልቻልኩኝም የሆነ ያለመከበር ያለመፈለግ አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ !!! በእራሴና በሁኔታዎች እየተናደድኩኝ  ነበር ። ከዛ ቁርሴን በልቼ ጨርሼ ለጥ አልኩኝ ። ደክሜ ስለነበር ቶሎ እንቅልፍ ወሰደኝ ለረጅም ሰአት ተኝቼ ተነሳሁኝ ። ከዛ ስነቃ ሳሚ ትዝ አለኝ ። ብር ማስቀመጫዬ ላይ ሳይ ትንሽ ብር ነበረችኝና ህመምተኛ ለመጠየቅ በሚል ሰበብ ለመሄድ አሰብኩ ከዛ ለባብሼ ከቤት ወጣሁ ልክ ስወጣ ከማያ ጋ ተገጣጠምኩ  ...... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣6⃣
171
5
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣4⃣ ......... ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ ። እሷም ክው ብሓ እርምጃዋን ገታችው ??? እየተፈጠረ ያለው ነገር ከኔ አልፎ ያስጨነቀው ሳሚ " ምነው ልጄ ችግር አለ ?" ብሎ እጄን ሲይዘኝ ከገባሁበት ሰመመን ባነን ብዬ ይቅርታ ሳሚ የሆነ ነገር ትዝ ብሎኝ ነው !! ብዬ ንግግሬን ገታ አደረኩት ። እሷም የበለጠ ነጠላውን እየተሸፋፈነች አንገቷን ደፍታ ቄሱን  ተከትላ ሄደች ። ምን እንደተፈጠረና ምን እንደሆንኩ ያልገባኝ እኔ በሀሳብ ተውጬ እያለ ነበር ሳሚ " ልትነግረኝ ካልፈለክ ተወው በቃ " ያለኝ ። ለካስ ስለ እራሴ እንድነግረው ሲጠይቀኝ ስለነበር ይሄ ድንጋጤ የተፈጠረው ማውራት ያልፈለኩ መስሎት ነበር ። እኔም አረ በጭራሽ እንደዛ አይደለምዐበምነግርህ ህይወት ለመገረም ተዘጋጅ እንጂ ነግርሀለሁ አልኩት ። በመጀመሪያ ትክክለኛ ስሜ ሚኪያስ አይደለም ሀብታሙ ነው ብዬ መናዘዝ ጀመርኩ ። ገና ሳልነግረው የተገረመ ፊት አሳየኝ ። እኔም ፈገግ ብዬ እኔ የደሀ ልጅ ሆኜ ስሜ ሀብታሙ መሆኑን ስለማልወደው ነው ያስቀየርኩት ። እና ደግሞ እናቴም አባቴም በጣም ደሀ ከተባለ ቤተሰብ ወተው ደሀ ቤተሰብ መስርተው ይኖራሉ ። የቤቱ ብቸኛ ልጅ ነኝ ። አባቴ የመጠጥ ሱሰኛ ነው አንድ ካቲካላ ጎንጨት ካላለ የሎብ ምት እንደቆመ ሰው ያረገዋል ። ሲጠጣ ደግሞ ታርዳ እንደተጣለች ዶሮ ያንፈራግጠዋል !!! ከልጅነቴ ጀምሮ በድህነት ህይወት ውስጥ ነው ያደኩት ። እናቴ ጉልት ሰርታ ነው ያሳደገችኝ አባቴ አልፎ አልፎ ይሰራል ችግሩ እዛው በካቲካላ ይጨርሳታል ። እናቴን ያን ያህል ጠባየ ግዛትም እንደገቢያችን ወጪም የለንም እኔ ከጠገብኩ አለም ሁሉ ሰላም ውሎ ያደረ የሚመስላት ምስኪን እናት ናት ያለችኝ ። " አልጠራጠርም " አለ ሳሚ ጣልቃ ገብቶ ። በቃ አሁን ላይ የምታነው ሀብታሙን የገነባችው እናቴ ናት ሚኪን ለመገንባት ደግሞ በትንሹ የራሴ ጥረትም አለበት ። እና አጋጣሚ ከእናንተ ጋር አስተዋወቀኝ እኔ መኖር አለመኖሩንም የማላቀውን አይነት ህይወት ነው የምትኖሩት ። ደግሞ በፈጣሪ ስም የምምልልክ እኔ በገንዘብ የምገዛ ሰውም አይደለሁም እና ለገንዘብ ብዬ የቀረብኳችሁ ምናምን እንዲመስላችሁ አልፈልግም እኔ በትምህርቴም ደካማ አይደለሁም በጉልበትም ጠንካራ ነኝ በራሴ ሰርቼ ማግኘት የምችል ሰው ነኝ ነገሮች አልመቻች ብለውኝ ነው አልኩት ። ከሱ ጋ ሳወራ  ከልቤ ነው የማወራው እና ለረጅም ደቂቃ በጣም ብዙ ነገር አወራን ከሱ የምደብቅበት ምክንያት የለኝም ለልዕልና ይንገራት አይንገራትም  አላሳሰበኝም ሁሉንም ነገር  ነገርኩት ። በጣም ለብዙ ሰአት ነው ያወራነው ደስ የሚለው እሱም በእኔ ላይ ሙሉ እምነት እንዳለው እስከመጨረሻው አብረን እንደምንዘልቅ እኔን እንደ ልጅም እንደ ጓደኛም እንደተቀበለኝ ሙሉ በሙሉ እንደሚያምነኝ ስለ ድህነት ስለ ሀብት እሱም በፊት ላይ ምን አምነት ህይወት እንደነበረው ብቻ በጣም ብዙ ነገር አወራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በዚህ ልክ የውጪ ሰው ሳወራ ። ከሰው ብጣላም ከአስተማሪ ብጣላም በድህነት ብከፋም ብቻ ምንም አይነት ነገር ቢኖር እናቴ እቅፍ ውስጥ ገብቼ ነው የማለቅሰው ሌላ የማወራውም የለኝም ። ከረጅም የግል ንግግር ስንነቃ ነበር ቤተክርስቲያን ውስጥ መሆናችንም የታወቀኝ ። ከዛ ተሳልመን ከዛ ወጣን ። እኔ ተመልሼ ወደነሱ ቤት መሄድ አልፈለኩኝም ። ሳሚ ደግሞ አብረን እንድንሄድ አስቦ ነበር ግን ስራ አለኝ ብዬ ግግም አልኩበት ። በስተመጨረሻም ቅዳሜ መጥቼ ጠይቃታለሁ ብዬ ቃል ገብቼ እኔም ወደቤቴ በእግሬ መሄድ ጀመርኩ ሳሚም በመኪናው ተመለሰ ። መንገድ ላይ ሆኜ በርካታ ሀሳቦች ሲመላለሱብኝ ነበር !!!!! ማያን ሳያት ለምን እንደደነገጥኩ ራሴን ጠየኩት   ። አይ ለልዕልና ያወራሁትንና እሷን ስላሰብኩ ስህተት ስለሆነ ነው ብዬ አሰብኩኝና ቀጥ ብዬ መንገዴን ቀጠልኩኝ ። ከሳሚ ጋር ስላወራሁ የሆነ ነገር ቅልል ብሎኛል ። ስለድህነቴ ለልዕልና ነገራት አልነገራት ብዬ አለመጨነቄ ግን ትንሽ አስጨንቆኛል !!! ዙሪያ ጥምጥም አድርጌ በሩቅ መንገድ አርጌ ብቻዬን እያወራሁ ነበር እየሄድኩ የነበርው ። የመጨረሻው የኛ ቤት መታጠፊያ ቀጭኗ መንገድ ጋር ስደርስ ግን ከየት መጣች ሳልላት ከፊት ለፊቴ ማያ ስትመጣ አየዋት ። ሳላስበው ቀጥ ብዬ ቆምኩኝ ። ለምን እንደሆነ አላቅም ሳያት ሰውነቴ መታዘዝ ያቆም ይመስል የማስበውን ማረግ ከብዶኛል ። ቅድም ለምን እንደቆምኩም ሆነ አሁን መራመድ ለምን እንደከበደኝ አላቅም !!! ስታየኝ እሷም መደንገጧ ደግሞ የኔን ሀሳብና ጭንቀት አጋጋለብኝ ። ከሩቅ ስትመጣ ጀምሮ እያየዋት ነበር !!! ያን ያህል ቆንጆ መሆኗን ያየሁት የዛኔ ነበር ቁመት አቋም ቀሚስ ለባሽ ከእርጋታ ጋር አነውባት ። ቀስ በቀስ ረጠገቤ ደረሰች እሷ አውርቻትም ሆነ ቼክ አድርጊያት ስለማላቅ እንደሁሌው አንገቷን ደፍታ እያለፈች ነበር ። ያቺ ቀጭን መንገድ ግን አቀራርባናለች እና እጄ አልታዘዝ ብሎኝ በሰላም እየሄደች የነበረችውን ልጅ ሳላስበው  ቀሚሶቿን ሰብስባ የያዘችበት እጇን ጭምቅ አድርጌ ያስኩት . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣5⃣
148
6
https://t.me/stars_oneklic_bot?start=_tgr_4t0oaJ40NDU0 Join us
188
7
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣3⃣  .......... ጭምድድ አርጎ አቀፋት ። አምልጦኝ እንደተቆጣጣሪ አባት  ማነው ምንሽ ነው ?? ብዬ ልሟገታት ምንም አልቀረኝ ማለት ይቻላል ግን እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ በዝምታ ከበሩ ገለል አልኩኝ ። መን ፈልጋ እንደሆነ አላቅም ዲቦራ ተብዬዋ ተከተለችኝ ። " አንዴ ስልክህን ስጠኝ " አለችኝ ። ደፋር እንኳን ቁጥሬን በዘዴ ልትቀበል ስልክም እንደሌለኝ ማን በነገረልኝ እያልኩ በውስጤ የለኝም ብዬ ንግግሩን በአጭሩ ለመቋጨት ሞከርኩኝ ። " ልደውል እኮ ነው ""አለች ላለማስነቃት ፊቷን አኮሳትራ ። በቅርቡ ሰረቁኝ የለኝም አልኩሽ እኮ አልኳትና ፊቴን ዘፈዘፍኩት ። ትንሽ ደቂቃ በሩ ላይ ቆመው ምን እንዳወሩ ባላቅም ቆየት ብለው ወደኛ መጡ ። ዲቦራንም አቅፎ ሰላም ካላት ቡሀላ " ሄይ ሚኪያስ እባላለሁ " ብሎ የራሴን ሁለተኛ ስም ደግሞ ነገረኝ ። ገና ሳየው አልወደድኩትም ከሱ ጋ ብዙ ላለማውራት እኔም ብዬ ሰላምታውን መልሼ ዝም አልኩኝ ። " ኑ ግቡ "" ብላ ልዕልና ከፊት ቀደመች እሱም ተከትሏት ሶፋው ላይ ተቃቅፈው ልበል ተዛዝለው ብቻ ተሸካክመው ተቀመጡ ። ምንም ያህል የምትወደው ፍቅረኛዋ ቢሆን እኛ ፊት የተጋነነ ሁኔታ ማሳየታቸው የምር አናዶኛል ከልቤ !!! ከዛ ግን ምንም እንዳልመሠለው ለመሆን የማረገው ሳጣ በጥሩ ሰአት ሳሚ ከክፍሉ ሲወጣ አየውት ። ኀለእኔ በጣም አሪፍ ነገር ነው ። ሳየው ከተቀመጥኩበት ብድግ አልኩኝ አመጣጡ ያስፈራል ነገር !!!! እኔ ምንም አይነት ጩኸት ስላልሰማሁ ነገሩ ሁሉ ሰላም መስሎኝ ነበር !!! ፈራሁ በማያገባኝ ገብቼ ነገር ያበላሸው መስሎኝ በጭንቀት ድፍት ልል ስል ቀጥታ መቶ ላዬ ላይ ተጠመጠመብኝ ። ይሄን እቅፍ አላውቀውም !!!!! bcha gn des mil neger alewu !!! ሲያቅፈኝ ተረጋጋሁም ተጨነኩም ግራ ገብቶኝ ነበር !!!! ለደቂቃዎች ካቀፈኝ ቡሀላ ለቀቀኝና በእጆቹ እጄን አጥብቆ ይዞ " የኔ ልጅ አንተ ማለት ከፈጣሪ  የተላክ ስጦታ ነክ ና እንውጣ ላወራክ እፈልጋለሁ ና " ብሎ እጄን እየጎተተ ሊወስደኝ ሲል ያ ሴታሴት " እንዴ ሳም " አለ ። የሚገርመው ያንን ያህል ሰአት ልጁን አላስተዋለውም ነበር ደንገጥ እያለ " እንዴ ናቲ " ብሎ ጨበጠውና  ሰላምታ ከተቀያየሩ ቡሀላ " ና በቃ ልጅ ሚኪ  " ብሎ ወደ ውጪ ገሰገሰ ። እናውራ ሲል ጊቢ ውስጥ መስሎኝ የነበረ ቢሆንም የውጪውን በር ከፍቶ መኪናውን አመጣና ውስጥ እንድገባ ነግሮኝ ይዞኝ ሄደ ። ቤት ውስጥ ምን እንደተፈጠረ አለመስማቴ እየረበሸኝ ነው ። ደግነቱ በጣም ቅርብ ቦታ ነው የሄድነው የሰፈራችን ድምቀት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ነበር የወሰደኝ ። የኔ ከጫጫታ ማምለጫዬ መደገፊያዬ መጠለያዬ የልብ ጓደኛዬ... ብቻእዛ መሄዳችን አስደስቶኛል !!! ሳሚ ተንበርክኮ ያለማቋረጥ ምስጋናን ያቀርባል !!!! ፀሎቱን እስኪጨርስ ሸሸች ብዬ የራሴን ፀሎት አደረስኩኝ ። ከዛም ከረጅም ደቂቃዎች ቡሀላ ወደኔ መቶ ከአጠገቤ ተቀመጠ ። ሰአቱ ቀትር አካባቢ ስለነበር ብዙም ሰው የለም እና ጥጋችንን ይዘን ተቀመጥን ። እስከሚያወራ እየጠበኩት ነበር !! " ታውቃለህ ልጄ አንተን ለምን እንደቀረብኩህ ከዚ በፊት ነግሬካለሁ !!! ታማኝነትህን ስለወደድኩትና ወንድ ልጅ እንዲኖረኝ ብመኝም ስላላገኘው አንተን ሳይህ ስለወደድኩህ ብቻ ነው !!!! በጊዜው ሌላ ሀሳብም አልነበረኝም ግን ታውቃለህ ሳስበው ፈጣሪ ነው ወደኔ የላከህም ሆነ ከኔ ጋ ያገናኘህ !!!!" አለኝ ደስታውጰፊቱ ላይ እየታየ ። ምን እንዳገኘና  ለምን በዚህ ልክ ደስተኛ እንደሆነ የማቀው ነገር ባይኖርም ፈገግ ሲል አብሬው ፈገግ እያልኩ ነበር ። ከዛም ተሳካልን እንዴ ?? አልኩት ምን እንደምል ግራ ገብቶኝ ። " በደንብብብ ከስንት ጊዚያት ቡሀላ እኮ አወራችኝ የሚስቴን ድምፅ ሰማሁት " አለኝ ። ተመስገን አልኩ በልቤ ። ከዛ ወዲያው መለስ አርጎ " ልጄ አንተ ልክ ነበርክ የሚያወራትና አዳማጭ ነበር ያጣችው ።!!! ገና ስታየን እሪ ስለምትል ስለምትጮኽ ስለምታለቅስ እፈራለሁኝ  ለዛ ነበር የማላወራት " አለኝ ። እኔ እንደማስበው መታ ካላየቻችሁና ካላወራቻችሁ በር ከፍታ ካልወጣች ገብታችሁ አታወሯትም አይደል ? አልኩኝ ። ከሳሚ ጋ ስሆን የሚመጣው አሳቢ አስተዋይና ቁም ነገረኛ ልጅ ማን እንደሆነ ባላቅም በንግግር የበሰለ ሰው እያረገኝ ነው ። ሳሚም ለጠቅ አድርጎ " እሷ ብዙ ጊዜ የእንቅልፍ ና ሌሎች መድሀኒቶች ትወስዳለች እና ስንገባ የምትታመም ስለሚመስለን ስለምንፈራ ፈልጋን ካልመጣች ዝም ነው የምንለው " አለኝ ። አየክ አይደል እንጀዛ ስትርቋት ደግሞ እሷዐስለታመመች የተዋችዋትና የጠላቹዋት መስሎ ይሰማታል እና ፈልገሀት ክፍሏን ከፍተህ ስገባ ያለመጠላትና የተፈላጊነት ስሜት ተሰምቷት ነው !! አልኩት ። " በጣም የሚገርም እይታ ነው ጎበዝ ልጅ ነህ " አለኝ ። የምርም ግን በእራሴ ንግግር ራሴ እየኮራሁ ነበር ። ለካ አዳማጭ ካለ ጥሩ ተናጋሪ ይወጣል ማለት ጀመርኩኝ !!! ከአምላኬና ከእናቴ ውጪ የማወራው አንድም ሰው ስለሌለ ማውራት እንደምችል ራሱ ራሴን እንድጠራጠረው ያደርገኛል !!! " ታውቃለህ ገና ስገባ እንደናፈቅት ነገረችኝ ብቸኝነት እንደጎዳትና ራሷን እንድጠላ እንዳደረጋት ነገረችኝ ( እንባውን ከአይኑ እየጠራረገ ) ታውቃለህ እኔ እንደማስበው እኔን ሳይሆን ራሷን ጥፋተኛ ነው የምታደርገው ቤተሰባችሁን ደስታችሁን ወጣትነትህን ስለነጠኳችሁ ይቅርታ አለችኝ እኮ ( ያለቅሳል ) የመጨረሻ ቃሏ ደግሞ እርዳኝ አለችኝ እኮ !!! ከፈጣሪ ቀጥሎ የአንተ እርዳታ ያስፈልገኛል እባክህ "  አለኝ ። እኔ በምን ልረዳህ እችላለሁ ሳሚ ?? አልኩት ግራ ገብቶኝ ። " አሁን እንደረዳከኝ እርዳኝ በቃ ፈጣሪ መርቆ ጥበበኛ ልጅ አርጎሀል እሲ ጥበቡን ይገልጥልሀል ብቻ የቤተሰቤን ጤና እና ደስታ እንድመልስ አግዘኝ " አለኝ በድጋሜ ፊቱ ላይ የሚያንዣብበውን እንባ እየጠረገ ። ወዲያው ማሰብ ጀመርኩኝ ። " ከዛ በፊት ግን ....." ብሎ ዝም አለ ። ግን ምን ሳሚ አልኩት እኔም " ስለ አንተ ሁሉንም ነገር ማወቅ እፈልጋለሁ እውነታውን !!" አለኝ ። ስለኔ አልኩት ደንግጬ እንኳን የሚወራ የሚነገር ታሪክ ሊኖረኝ በህይወት መኖሬም የአምላክ ስራ ነው !!!! እንዲህ ነው የምለው ታሪክ የለኝም ብዬው ቀና ስለ ከፊት ለፊቴ ከደብሩ አንድ አባት ጋር ረጅም ቀሚስ ሻሽና ነጠላ እንደለበሰች ወደኛ መስመር ሲመጡ አየዋቸው ። ሳላስበው ደነገጥኩ ልቤ ላይ የሆነ እንግዳ ስሜት ሲሰማኝ ነበር ። እንደዛ ሆና ሳያት ለካ እንደዚ ቆንጆ ናት እንድል አደረገችኝ ። የሚገርመው የልዕልናና የኔ የፍቅረኛ ማሳየት ውድድር ባይኖር እኮ ጭራሽ ልብ ብዬም አይቻት የማላቀው ልጅ ናት !!! ምን እንዳሏት ባላውቅም በነጠላው አፏን አፈን እያደረገች ስትስቅ አየዋት ። ልቤ ላይ ያለውን አላስፈላጊ የልብ ምትና ያልታወቀ ስሜት ግራ አጋባኝ ድንገት ቀና ስትል አይን ለአይን ግጥምጥም አልን !!! ክው ብዬ ሳላስበው ከተቀመጥኩት ተነሳሁ ???? . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣4⃣
193
8
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣2⃣ ........ ወደኛ ሲመጣ ተመለከትኩት ። አይኑ ያስፈራል ምን ያህል እንዳለቀሰ ግልፅ ነገር ነው ። ግን ከጀርባው ያለውን ነገር ማወቅ ስላልቻልኩኝ ግራ ተጋብቼ እያየሁት ነበር እሱም እንደምንም አጠገባችን ደረሰና " አባዬ ባሌ አለችኝ "።ብሎ ደረጃው ላይ ቁጭ ብሎ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ። እሺ አሁን ምን ብለካት ወጣህ አልኩት ደንግጬ " ትቻት ወጣሁ አልቻልኩም እያለቀሰች ማየት አልችልም " ሲል ልዕልና ተጨምራ አብራ ማልቀስ ጀመረች ። ሁለቱንም ማረጋጋት ሌላ ስራ ሆነብኝ !!! ደስ የሚለው እዛ ቤት ስሄድ ሀብታሙ ምም ያህል አስተዋይና አሳቢ እንደሆነ ለማየት እስኪያስችለኝ ድረስ ኢነርጂ ነበረኝ ። ቀጥታ ልዕልናን ወደ ዳር አደረኳትና እግሩ ስር በርክ ብዬ  አየክ ስትፈልግህ ጥለሀት መሄድ አታስለምዳት እንጂ ጠልቶኛል ብላ እንድታስብ አታድርግ !!! ጠንክረህ እሷን ማበርታት እያለብህ አንተ እንዲ ስትሆን ስታይህ እሷም ትደክማለች እኮ ምን ሆነሀል አስለቀሰኩት ብላ የበለጠ ራሷን እንድትወቅስና እንድትጠላ አታድርጋት አሁን 120 ሰከንድ ብቻ ነው ያለህ ቶሎ ፊትህን ጠርገህ ከሷ ጋ መቆየት እሷን ማበርታት ወይስ ያ በር ተዘግቶ እንደሁሌው እንድትውል ማድረግ ብዬ ልቡን ለማራራት ሞከርኩኝ። እንባውን መገደብ እስኪያቅተው ድረስ እያለቀሰ ነው ሊያወራኝ ራሱ አልቻለም ነበር ። " አልችልም "አለኝ እርግጥ አድርጎ ሌላ ተጨማሪ ቃላትን ከማባከን ብዬ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ሰአቱ መቁጠር ጀምሯል 119 ሰከንድ ሆኗል ብዬ ልዕልናንና ጓደኛዋን ይዜ ከዛ ዞር አልን ። ለትንሽ ሰከንዶች ራሱን  ለማሳመን ሲታገል ነበር ከዛ ድንገት ብድግ ብሎ ፊቱን አየጠራረገ እየሮጠ ወደ ውስጥ ገባና የክፍሉን በር ዘጋው ። በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ ። ምን እንደሚፈጠር አላቅም ግን የሆነ አስታራቂ እንደምሆን እየተሰማኝ ነበር !!!! ከዛ ልዕልናን ሁሉም ነገር እንደሚስተካከል አሳምኜ አረጋጋዋት ። ከዛ እዛው ጊቢ ውስጥ ቁጭ አልንና የቤት አጋዧን ጁስ አመጪልን ብላት መጠበቅ ጀመርን ። ከደቂቃዎች ቡሀላ በትልቅ ብርጭቆ ውስጡ እንደ ህፃናት ጁስ መጠጫ ተሰክቶ ግን በሚያምር አቀራረብ ይዛ መጣች ። በነገራችን ላይ በዛ ሰአት እዛ ክፍል ውስጥ በሩን ቆልፋ የምትውለው ከቤት ወታ የማታቀው ለአራት  አመት ሙሉ ከቤቷ ሳትወጣ ታሽጋ የኖረችው እንዲሁም ከወጣትነቷ ጀምሮ እየተሰቃየች ያለችው ያቺ ወጣት እና ውብ ሴት ለሳሚ ሚስቱ የልዕልና ደግሞ እናቷ ናት ። በታሪኩ ሳሚ እንዳጫወተኝ ሰላም ማለት በአይኔም እንዳየሁት በጣም ቀይና ውብ ሴት ናት !!! ረዘም ያለ ለስላሳ ብዙ ጥቁር ፀጉር የሚያምር አይን ከረጅም የአይን ሽፋሽፍት ጋር ያላት በዛ ህመም ውስጥ አንድ ጊዜ ብቻ ባያትም የሚታይ ውበህ ያላት ሴት ናት ። በልጅነቷ ሳሚ አይቶ እንደወደዳትና መጠበቅ ስላልፈለገ በአስራ ዘጠኝ አመቷ እንዳገባትና በዛ ውበቷ ላይ እንደ ሳሚ አይነት ውብ ወጣት እና የተሳካለት ሀብታም ሰው  ስታገባ ከሁለተኛ ክፍል ጀምሮ አብራት ያደገችው ጓደኛዋ ትቀናባት እንደነበረና ልዕለናን ወልደው በሰላም እያሳደጉ የልቧ መሻት የሆነውን ወንድ ልጇን እንኳን ሳትወልድ ቤቷ መታ በልታ ጠጥታ በዛው መርዛት እንደሄደች እና የዛኔ በልብሷም እንዳስደገመችባትና ከዛ ቡሀላ ሰላም ሆና እንደማታቅ ድንገት ቅይር እንደሚያረጋት ካለፉት አራት አምስት አመት በፊት ብሶባት ሰው ማየት እንደማትፈልግ ከሳሚ ጋር ማውራት እንደማትፈልግ ሰው እና ብርሀን ላለማየት መኝቷ ክፍሏን ቆልፋ እንደምትኖርና አስንት አንዴ ካልሆነ በረነዳ ራሱ እንደማትረግጥ ነግሮኛል ። ሳሚም ይሄ ሁሉ በእኔ ምክንያት ነው ብሎ እንደሚፈራ እና ሁሌም ራሱን እንደሚወቅስ ነግሮኛል ። ልዕልናም ግማሹ አመቷን ሁሉም ቢሳካላትም ያለ እናት እቅፍ በብቸኝነት እንዳደገች ሰማሁ ። ሁሉም ነገር አልታመን ብሎኝ ነበር ለዛ ነው ቤተሰቡ የያሳዘነኝም !!!! ሳሚ ሲነግረኝ ያለወሰዳት ጤና ጣቢያ ሆስፒታል ድረስ እንደተጓዙ ግን ምንም መፍትሄ እንደሌለው ነግሮኛል ። እኔ ግን እናቴ አዳኝ ፈዋሽ ስትል የምሰማትን የጅሩ አርሴማ ጀበል ላስሞክራት አስቢያለሁኝ !!! ሳሚ ከገባ በትንሹ አርባ ደቂቃ ቆይቷል የአራት አመት ናፍቆላቸውን የሚወጡበት ሰአት እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ። ረጅም ሰአት መቆየታቸው ደግሞ አስደሰቶኛል ።  እዛ ቦታ ቁጭ ብለን እኔ ሀሳቤ ሳሚጋ ነው ለካ ልጅቷ አይኗን ጥላ እስካወራት እየጠበቀች ትመስላለች ። እኔ ከውስጥ ሳሚን እየጠበኩ ከውጪ በሩ ጓ ጓ ተደረገ ። ሁለቱ ከውስጥ ስለነበሩ ቆይ እኔ ልክፈት ብያቸው ሄጄ በሩን ከፈትኩት ። በእድሜ ከእኔ ጋ የሚቀራረብ ሸበላ ና ዘናጭ ልጅ ከፊት ለፊቴ ቆሟል ። እንግዳ መሆኔን ላለመርሳት ዝም ስል ኮስተር ብሎ አይቶኝ ወደ ውስጥ ገባ ። ገና እንዳየችው እንደዛ ተጣጥፋና ደቃ ተቀምጣ የነበረችው ልጅ በሩጫ መታ ልጁ ላይ  ተጠመጠመችበት ። እሱም የዋዛ አልነበረም ጭምድድ አርጎ አቀፋት!!!!! ????? እስከ 3:30  ላይኩ 100 ከሞላ አንድ ክፍል ይለቀቃል . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣3⃣
201
9
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣1⃣ ...........ከደቂቃ ቡሀላ መልሳ " አውቄሀለሁ ወንድሜ " ብላ ላከችልኝ ። ደህና ሰላም የነበርኩትን እንዴት ወንድሜ ትለኛለች በሚል ደግሞ ሌላ ንዴት ጨመረችብኝ ከዛ በንዴት ዝም አልኳት ። " አትመልስልስም ሚኪ " ብላ ላከችልኝ መልሳ ። አቤት ብዬ ላኩ ለማናደድ አስቤ ነበር ። የኔን ፍቅረኛ ከፈለክ ነገ አስተዋውቅሀለሁ ያንተንስ " ብላ ላከች ። በዙሪያዬ ሴት እንደሌለ አቃለሁ ከሠርካለም ልጅ ከማያ ውጪ የማውቀው ሴት የለም እሷን ማውራት ራሴ ላይ ችግር መፍጠር እንደሆነ አቃለሁኝ ስለዛ ምንም ማረግ አልችልም ። ዝም ላለማለት ብዬ ያንቺን ካስተዌወቅሽኝ ቡሀላ አልኳት ። " እሺ ቤት ስትመጣ አስተዋውቅሀለሁ ከፈለክ ነገ ና ዳዲ ቤት ነው " ብላ ላከችልኝ ። በጭራሽ ቤታቸው መሄድ አልፈለኩኝም ግን ልጁን ለማየት በጣም ነው የጓጓውት እና ትንሽ አስቤ እሺ ምሳ ሰአት ወደናንተ አካባቢ መምጣቴ ስለማይቀር ጎራ እላለሁ ብዬ የመጨረሻ መልእክቴን ፅፌ ተጣጥፌ ለጥ አልኩኝ ። ጠዋት በጠዋት ተነስቼ ቤተክርስቲያን ተሳልሜ በዛው ስፖርት ቤት ደርሼ መጣሁኝ ። ከዛ ሻውሬን ወስጄ ፏ ብዬ ለብሼ ከቤት ልወጣ ስዘጋጅ እናቴ መጀመሪያ ምግብ አፍህ አርግ እንጂ ልጄ አለችኝ ። እነ ልዕልና ቤት ልሄድ እንደሆነ ሳስበው ራሱ ይቅር ይበለኝና ያደኩበት እዚህ የደረስኩበት የእናቴ ሽሮ ፈሰስ መብላት ቀርቶ ማሰብ ከበደኝ ።    " የደሀ ቅንጡ ያፏጫል በ**" አለች እናቴ ። ሆይ ጉድ እኮ ነው ነገ ከነሱ ቤት ስቀር ሌላ የምቀምሰው የለኝ ምን አስቦ እንዲያ እንደሚያሽቀናጣኝም አላቅም ። ብቻ የዛኔ ለእናቴ ሰበባ ሰበብ ደርድሬ ሳልበላ ወጣሁ ። ልክ በሩን ዘግቼ ዞር ስል አግኝቻትም አይቻትም የማላቀውን ሳስባት ያደርኩትን ማያን ፊት ለፊቴ አላገኘዋትም !!! ከመደናበሬ የተነሳ እሷ ምን እንዳሰበች ራሱ መገመት አልፈልግም !!!ብቻ አፌ በደመነፍስ ነው የሚጓዘው መቼም  ሳላስበው " ደህና ዋልሽ " አልኳት ። ክው ነው ያለችው ድንጋጤዋ ፊቷ ላይ ይታያል " ደ ደ ደህና አደርክ " ብላ እየሮጠች ወደ ቤት ገባች ። እኔስ እሺ እሷ ምንድነው ያስደነገጣትና ያርበተበታት ብዬ ተገርሜ ቶሎ ከዛ ሰፈር ጥፍት አልኩ ። አለባበሴ ሁኔታዬ ምናምን እኮ ከዛች ደሳሳ ጎጆ ሳይሆን ከነ ልዕልና ቤት የምወጣ ነው የምመስለው!!!!! ሌላ የምሄድበት ምክንያት ባይኖረኝም  በዛው እግረ መንገዴን ጎራ እንዳልኩ አስመስዬ ሄድኩኝ ። ሰላም ብለው ቸቀብለው ካስገቡኝ ቡሀላ " ለምን አልደወልክም ስደርስ " አለችኝ ልዕልና ስልኳን እየተመለከተች ። አይ ስልክ አልያስኩም አልኳት እንዴት እንዳወቀች አላቅም " ስልክ የለክም እንዴ አሁን ላይ " ብላኝ አረፈችው ። እኔም ላለማስፎገር ስልኬን ወስደውብኝ ነው ለጊዜው አልኳት ። ሳስበው ልጅቷ በራሷ መወሰን ትወዳለች መሠለኝ " እና ለምን በላብቶፕክ tg አትከፍትም ማታ ፎቶ ልልክልክ ነበር አትጠቀምም አለኝ " አለች ። በጣም ቀልደኛ ነገር ነች !!!! እውነት ለመናገር ሳቄ መቶብኝ ነበር እሷ የምታስበው ሚኪና የደሀ እናቱ ልጅ ሀብታሙ ያላቸውን ልዩነት አሰብኩኝና ሳቄ መቶ ሊያመልጠኝ ሁላ ነበር ግን እንደምንም ተቋቁሜ ለጊዜው አልፈልግም ! ብዬ አጭር ምላሽ ሰጠሁኝ ። " እሺ ና ወደ ውስጥ ግባ " ብላ ገባች ። እኔም በሩን ዘግቼ ተከተልኳት ። ከሳሚ በተጨማሪ የሆነች ቆንጅዬ ልጅ ከሳሚ አጠገብ ቸቀምጣለች እኔም ሁለቱንም ሰላም ብዬ ተቀመጥኩኝ ። ልጅቷ የምር ቆንጆ ናት ለኔ ከልዕልና ባትበልጥም ። ደግሞ ሀብታም ለሀብታም ነው የሚወዳጀው መሠለኝ እሷም ልጥጥ ያለች በጥ የሀብታም ልጅ እንደሀነች በአንድ ንግግር ነው ያወኩት ። እኔ እንደሁሌው በእርጋታ ከሳሚ ጋሮ እያወራሁኝ እሷ ለተደጋጋሚ ጊዜ ስትቅበዘበዝ እያየዋት ነበር !!!! የፊቷ አክትና ትኩረት ለመሳብ የምታረገው ነገር ስላልተመቸኝ ፊቴን ኮስተር አርጌ ተቀመጥኩኝ ። ሳሚ በጣም ደስ የሚል ሰው ነው ቀለል ያለ ሰው ከወጣቱ ጋ ወጣት ከልጅ ጋ ልጅ ከስራ ባልደረባ ጋ አለቃ ብቻ ሁሉም ቦታ ፐርፌክት የሆነ ሰው ነው ። ከሱ ጋ ማውራት ደስ የሚል ነገር ነው ። እኔ ሀብታም ሰዎች ክፉ ኮስታራ ከደሀ ጋ የማይቀመጡ መስለው ይታዩኝ ነበር እሱ ግን የተለየ ነው !! ብቻ ደስ እያለኝ ነበር ። ምግብ በላን ቡና ተፈላ ጠጣን በሁለት በሶስት ግንኙነት የምርም የቤተሰቡ አካል እንደሆንኩ ነው የተሰማኝ ። ከዛ ሳሚን ቤት ውስጥ ያለችውን ሴት እንድናያት ቀስ ብዬ ጠየኩት " አይ ይቅርብኝ ቢነሳባትስ ቢያማትስ ደግሞ እኔን ማየት አትፈልግም እንድቀርባት አትፈልግም !!" አለኝ ። ፈርቷል ፍራቻው ፊቱ ላይ ይታይ ነበር !!! " አይተካታል ከዚህ በፊት ተጠግተህ አውርተሀታል?? አልኩት ። " አረ በፍፁም ከነገርኩህ ቀን ጀምሮ ቀርቢያትም  አውርቻትም አላቅም በዛ ላይ እንባ ስለሚቀድመኝ ..  " ብሎ ሊመጣ የሚታገለውን እንባ ይዞ ፀጥ አለ ። ምን አልባትም እኮ ናፍቀሀት ይሆናል ምን አልባትም እኮ መድሀኒቷ አንተ ሆነክ ግን ስላላወክ ሊሆን ይችላል !!! አልኩት ። በርግጠኝነት ሚኪ ነው እያወራ የነበረው እንጂ ፊተ ከስክስ የሆነው ሀብታሙማ ሰው በዚህ ልክ አይመክርም እያልኩ ነበር በውስጤ ። ምክንያቱም ከሰው ጋ በዚህ ልክ ቀርቤ አውርቼ ራሱ አላውቅም እኔ  !!!! ሳሚም አላሳፈረኝም " ልክ ልትሆንም ላትሆንም ትችላለች ግን ቢያንስ ሞክሬ አልቻልኩም ልበል " ብሎ በረጅሙ እየተነፈሰ ከተቀመጠበት ተነሳ ። " ወዴት ነው አባ " አለችው ልዕልናም አብራው እየተነሳች " ሰላሜ ጋ " አላት ዞር ብሎ ። ክው አለች ኮስተር ብላ " እንዴ ለምን አባ አይ አይሆንም እያወክ " ብላ ድፍረቱን ገደለችብኝ ። እሺ ብሎ የተስማማው ሰው ራሱን መጠራጠር እንዲጀምር አደረገችው ። እኔ ምን እንደሆንኩ ባላውቅም ውጪ ጠብቁን እናንተ ቶሎ በይ  ብዬ አዘዝኳት ። በንግግሬ እሷም ግራ የተጋባች የሚመስል ፊት አሳየችኝና አባቷን ተመለከተችው እሱም በፊቱ እንድትወጣ ሲነግራት ጓደኛዋን ይዛት ወጣች ። ሞክረው ምን አልባትም መፍትሄው እጅህ ላይ ሆኖ እያሸሸክባት ሊሆን ይችላል ብዬ መልሼ አነቃቃሁት ። ደስ የሚለው አመነኝና ቀጥ ብሎ ወደ ተዘጋው ክፍል  ገባ ። እውነት ለመናገር እኔም ፈርቻለሁ ግን የሆነ ነገር ተሰምቶኛል እና በምክንያት ነው እዚ ያመጣህ ይለኛል የሆነ ህዋሴ የኔ ድብቅ ህዋስ  ደሞ አይዋሸኝም ። የሚፈጠረውን ነገር ራቅ ብዬ ባይ ይሻለኛል ብዬ ወጣሁ ። ገና ወጥቼ ከመቆሜ ልጅቷ ወደኔ መታ " ዲቦራ እባላለሁ"  ብላ እጇን ዘረጋች ። ቀና ብዬ ልዕልናን አየዋት ። እሷም በግርምት እያየቻት ነው ። ሚኪያስ ብዬ ሰላምታዋን መልሼ ፊቴን አዞርኩ ። ለደቂቃዎች ሳሚ ውስጥ ቆየ ። ምንም ጩኸት አለመሰማቱ ቢያስደስተኝም በርግጠኝነት የሆነ ነገር አለ እያልኩ እያለ አይኑ ደም መስሎ እንባው እንደጉድ እየወረደ ወደኛ ሲመጣ ተመለከትኩት ......... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣2⃣
189
10
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣0⃣ ...........ከፍቅረኛዬ ጋ ነው የምኖረው አልኳት ። መልሳ ያንን የሚያምር ኩርፊያዋን አሳየችኝ ። መልሼ ለምን እንደዛ አልኩ ብዬ መፀፀቴ አልቀረም !!!!! " አውቀህ ነው አይደለ ?" አለችኝ መንገዱን ገታ አድርጋ ። ውሸቴን ከዛ በላይ መቀጠል ስላልፈለኩኝ ዝም አልኩ ። " እሺ ፍቅረኛከን አስተዋውቀኝ እ ማየት ፈልጋለሁ " አለችኝ ። የኔ ምክንያት  ድህነቴን እንዳታየው የወደቀ ቤታችንን እንዳታያት  ነው እንጂ እናቴን ለማስተዋወቅ አፍሬ አይደለም ። በሰአቱ  የነበረኞ አማራጭ ስሌለ ጊዜው ሲደርስ አስተዋውቅሻለሁ አልኳት ። ያ ቃል የምርም አሳመናት መሠለኝ  በሰአቱ ያልጠበኩትን ንግግር ነው የተናገረችው ቀና ብላ አየችኝና በቀል በሚመስል መልኩ " የአንተን ካስተዋወከኝ የኔንም ፍቅረኛ አስተዋውቅሀለሁ " ብላኝ አረፈችው ። አልዋሽም ደንግጫለሁ ክው ብዬ ፈዝዤ አየዋት " ምነው አታምነኝም ነገ ካሳየከኝ እኔም ነገ አሳይሀለሁ ከፈልክ ig ላይ ልክልሀለሁ የtg ፕሮፋይሉንም ማየት ትችላለህ እሺ ...." እያለች ብዙ ለፈለፈች ። እንኳንስ ig እና tg  ስልክ የሌለኝ እኔ አሁንመሰ መልሴ ዝምታ ነበር !!! ለደቂቃዎች ፈዝዤ ካየዋት ቡሀላ በቃ ቀጣይ ስንገናኝ አስተዋውቅሻለሁ አልኳት ። ወሬውን ማመንና ለራሴ ደግሜ ማሰብ ስላልፈለኩ ፈተና ደርሷል ተዘጋጂ ብዬ ወሬውንም ሀሳቤንም ለማስቀየር ሞከርኩኝ። ተሳክቶልኝ ነበር  ግን መልሷ " አው ደርሷል ግን እሷን ጥዬ መሄድ አልችልም ምን አልባት እዚሁ ከቀጠልኩ ነው " አለችኝ ። በርግጥ መልሷ አስደስቶኛል መሠለኝ ። ምክንያቱም እኔም ውጤቱ ምንም ቢሆን እዚሁ ሰርቼ ተቀይሬ እናቴን መቀየር ነው የኔ እቅድ እና እድሜ ላለማባከን እንደማልሄድ አቃለሁኝ ። ምን አልባትም ከሷ ሊያርቀኝ የሚችል አንድ እንቅፋት እንዳቃለልኩ ተሰማኝ የሆነ ህዋሴ ደግሞ ፍቅረኛ ያላት ሴት ያንተ ያልሆነች ሴት ናት ምን አገባህ የምን ደስታ ነው ??? እያለ ይጨቃጨቀኛል ። ብቻዬን ማሰብ ስለፈለኩ በቃ ተመለሺ አልኳት ። " እሺ ስልክህን ስጠኝ ልክልሀለሁ እሺ ደግሞ ነገ ነው የምታስተዋውቀኝ እወቅ " አለችኝ ። በሰአቱ ልሰጣት የምችለው ቁጥር ስለሌለኝ የእናቴን ቁጥር ፅፌ ቴክስት ላኩኝና ቁጥሩን መልሼ አጠፋሁት ከዛ እመጣለሁ ብያት ተለያየን ። ከሷ ጋር እያለሁና ከሷ ትንሽ እንደራኩኝ ያለው  ስሜቴ የተለያየ ነበር። ከሷ በራኩኝ ቁጥር የሆነ ነገር እንደጣልኩኝ ቅር ቅር ይለኝ ጀመር ??? ዞሬ ላለማየት ታግዬም ቢሆን ቀጥ ብዬ ወደ እናቴ ቤት ሄድኩኝ ። በር ላይ ስደርስ እናቴ ከቡና አጣጮቿ ጋር ሆና በሩ ላይ ቁጭ ብላለች ። ደግሞ ምን ተፈጠረ ብዬ ወደ ውስጥ ስገባ ገና እንዳዩኝ ህዝቤ  ግማሹ እልል ይላል እናቴ ሮጣ መታ ተጠመጠመችብኝ ምናምን ??? ነገሩ ግራ ያጋባኝ እኔ ግትር ብዬ ቆሚያለሁ ። " ምነው ልጄ ምን ሆነክብኝ ነው ለሊት የወጣህ ቃልም ሳትለኝ እስካሁን የምትቆየው ከማን ጋር ተጣላ ምን በላብኝ ብዬ ወዴት ልጩኽ ???" አለችኝ እንባ እየተናነቃት ። ምንድነው እማ ምን ተፈጠረ አልኳት ። " ሳትነግረኝ ሙሉ ቀን እየጠፋህ ምን እንዳስብ ጠብቀህ ነበር ??" አለችኝ በቁጣ ። ሠርካለም የምትባለው ጎረቤታችንም ለጠቅ አድርጋ " ተው እንጂ ሀብታሙ እናትክን እያወካት አስጨነከን እኮ ምን ሆነሀል ጨዋ ልጅ ነው ስንልክማ እንዳትበላሽ " አለችኝ ። የሚገርማችሁ ተይዣለሁና እንዳትፈርዱብኝ እንጂ እሷ ስትናገር ከሷ ይልቅ በክፍል እኩያዬ የሆነችው አንድ ትምሀርት ቤት ሆነን ግን ተነጋግረንም የማናቀው ልጇ ማያ ላይ ነበር ትኩረቴ ። በሳምንት አንድ ቀን ባያት ነው እሱም እሁድ ጠዋት እሷ ከቤተክርስቲያን ስተመለስ እኔ ወደ ስፖርት ስሄድ ከተገጣጠመን ነው ። ብቻ ቆንጅዬ ልጅ አለቻች እያለች እናቴ አንድ ሁለቴ ልታስከጅለኝ ሞክራለች ። ወዲያው ነበር የልዕልናን ፍቅረኛ ለማየት ልጠቀምባት ያሰብኩት። አንድ ቀን ተሳስቼ ሰላም ብያት የማላቀውን ልጅ እንዴት እንደፍቅረኛ መቀበል እንደምችል ባላቅም ብቻ በቅርቤ ያለች ብቸኛዋ ሴት እሷ ናት ። ምን አልባትም የህይወቴ ትልቁ ስህተት ያንን ያሰብኩበት ቀን ሊሆን ይችላል ግን በሰአቱ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም !!!! ይቅርታ ሁላችሁንም ስራ እየፈለኩ እኮ ነው ለዛ ነው የቆየሁት ብዬ ዋሽቼም ቢሆን የእናቴን ደስታ መመለስ ቻልኩኝ ። እንደዛ ያልኩት ልጄ ደረሰልኝ ብላ እንደምትኮራ ስለማውቅ ነው !!! ንዴቷን ረስታ ወዲያው ፈገግ አለች። ከዛም እነሱም ወደቤታቸው ሄዱ እኛም ወደቤታችን ገባን ። ከዛም ለእናቴ ቤት ገብቼ ውሎዬን እውነታውን ነገርኳት ። ስለነ ሳሚ ቤተሰብ አጫወትኳት ስለ ሀብታቸው ሁሉንም ከነገርኳት ቡሀላ ረፋዱ ላይ ስለተፈጠረውና ሳሚ ስለነገረኝ አሳዛኝ ታሪክ ነገርኳት ። " ድሮም እኮ ሀብታሞች ጤና እና ሰላም የላቸውም ይባላል !!! ግን እንደው ሲያሳዝኑ እረ አየህ ለዚህ ነው ማንንም አትመን የምልህ ሰው እንዳታምን ልጄ !!!" እያለች የተሰማትን ሁሉ አወራች ። እኔም እሺ ብዬ ዝም አልኩኝ ። " እረ ደሞ ልጄ ና እስኪ ከባንኩ ይሁን ከማን አላቅም ይሄ ምንድነው የሚለው ?" ብላ ቅድም በልዕልና ስልክ የላኩት ላይ አድርጋ ሰጠችኝ ። የኔ የዋህ ሳትማር ያስተማረችኝ !!!! በሰአቱ ስለ ልዕልና እንድታውቅ ስላልፈለኩኝ ከቴሌ ነው ተያቸው ብዬ እዛው ስልኩን ያዝኩት ። ከዛ ተመቻችቼ ተቀምጬ አውጥቼ አውርጄ  ለመመለስ ፅፌ ስልክ ካርድ የለውም ። ሰአት ከሄደ ከቤት እንደማታስወጣኝ ስለማቅ ተደብቄ እየሮጥኩ ሄጄ ካርድ ገዝቼ ተመለስኩ ። ከዛም ቶሎ ብዬ  ገና ሳልከው እስክትመልስ እየጓጓሁኝ በፍራቻም ቢሆን " ሰላም ልዕልና "ብዬ ላኩላት ። ልጅቷ የምጠብቀው ስልክ ወይ እያወራች በሌላ የተቋረጠባት ይመስል ሁለት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ " ወዬ አባቴ " ብላ መለሰች ??? በፈጣሪ ስም በአንዴ ደስታዬ  ጉጉቴ ሁላ ከፊቴ ጠፋ !!!! ፍቅረኛዋን በሌላ ስልክ አውርታ ካርድ ያለቀባት መስሏት ነው ብዬ ቱግ ብዬ እንደምንም ራሴን አረጋግቼ   " አወቅሽኝ ?" ብዬ ላኩላት ። የዛ ቀን እኔን ለማናደድ ቆርጣ የተነሳች የመስል መልሳ ...... ይቀጥላል #ክፍል_1⃣1⃣
237
11
በሰላም እየሄድን ፍቅሬን እያጣጣምኩ እያለ የደስታ ነበልባሌ ላይ ውሀ ከለበሰችበት ። በሰአቱ እሷን ብቻ እያሰብኩ ስለነበረ ነው ሰላማዊ የሆንኩት ግን ሀሳብ ከየት እንደመጣላት አላቅላትም " መቼ ነው እናንተ ቤት የምትወስደኝ ግን እ ቤተሰቦችክን አታሳየኝም እና ያንተን ክፍል ሳስሰበው ጥቁርር ይመስለኛል  ገንጠል ያለ ክፍል ነዋ ..." እያለች የሌለ ነገር መቀባጠር ስጀምር ተናድጄ ከፍቅረኛዬ ጋ ነው የምኖረው አልኳት ! ይቀጥላል #ክፍል_1⃣0⃣
176
12
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 9⃣ .........ምንድነው ብዬ ቀና ስለ ከዚህ በፊት አይቻት የማላቃት ሴት ፊት ለፊቴ ቆማለች ። ከዃላ ደግሞ ልዕልና " አባቢ ....ዳዲ "  እያለች እየተጣራች ወደኛ መምጣት ጀመረች ?? በነገሩ ግራ የተጋባሁት እኔ ሁለቱንም በየተራ እመለከት ጀመረ ። ከዛ ግን ልዕልና ቶሎ ብላ ሴትዮዋን አቅፋ እንደ ህፃን ልጅ እያባበለች ይዛት ገባች ። ሳሚ ደግሞ ኮፍጠን ለማለት እየሞከረ ነበር ግን መቋቋም አቅቶት የፊቱ ደም ስሮች ሁሉ ተወጣጥረው  አይኑን እያሸ ቆየ ። በዛ ሁኔታ ውስጥ ልሂድ ማለት ስለከበደኝ ዝም ብዬ አጠገቡ ቁጭ አልኩኝ ። ጩኸቱ ካለቀ ቡሀላ ያ ተንኮለኛ ልጅ እየሮጠ መቶ " አጎቴ " ብሎ ሳሚን ተመለከተው  ። ምንም ቃላትን ሳይጠቀም አንገቱን ብቻ ሲያነቃንቅ በአንዴ ተግባቡ እሱም እየሮጠ ወደ ሌላኛው ክፍል ገሰገሰ ። በመሀል እኔ የማረገው ጠፍቶኝ ግራ ስጋባ ቆየሁ ። ለረጅም ደቂቃዎች ማንም ሰው ቃል ሳያወጣ ቆየን ። ሳሚ ፊቱን ወደታች እንደደፋ ጭንቅላቱን ይዞ ስለቆየ ማውራት ከብዶኝ ዝም አልኩኝ ። ከቆይታዎች ቡሀላ ግን ልዕልና እንባዋን እየጠራረገች ልጁ ደግፏት ወደኛ መጡ ። ወዲያው የአባቷ እግር ላይ ድፍት   ብላ ማልቀስ ጀመረች ?? ሁለቱም እሷን ለማባበል ሳሚ አቅፎ ያኛው ፀጉሯን እያሻሿት ነው ። እኔን ከነመፈጠሬም የረሱኝ ይመስላሉ !!! ለረጅም ደቂቃ እሷን ማባበል ራሱ አድካሚ ሆኖ ነበር በዛ ላይ በጣም የከፋት ትመስላለቸሰ እንባዋ ያለስስት ነው ሲወርድ የነበረው ። በስተመጨረሻም እየተረጋጋች መጣች  ። ውሀ አጠጥተዋት ምናምን ተረጋጋች ። " አባ ግን ለምንድነው  እ እኛ ምን ባጠፋን እሷ ምን አደረገች ደግ ናት እኮ " ትላለች ። ሳሚ በጣም የደላው ጭንቀት የማያቅ ሙሉ ሰው ቢመስልም ውስጡ ያለውን ሀዘን የዛኔ ነበር ማስተዋል የቻልኩት ። ለካ በውጪ ሲስቁ ሲደሰቱ የምናያቸው ሁሉ ሙሉ በሙሉ ደስተኛ አይደሉም አልኩ በልቤ ። የሚያሳዝነው ነገር የኔ ስነ -ልቦና በጣም እንደተጎዳ የምታቁት   በዛን ጭነቀት ሰአት ... " ሀብታሞች ደስተኛ አደሉም የሆነ ነገር ይጎላቸዋል " የሚባለው የምር ነው ማለት ነው እንዴ ??? እያልኩ እየተብሰለሰልኩ ነበር ። በፈጣሪ ስም ወዲያው ራሴን አንድ ሁለት የማንቂያ ጥፊ አቅምሼው ወደነሱ ስሜት ተመለስኩኝ ። ቀጥሎም ሳሚ " ቃለአብ በል ይዘካት ውጣ ብዙ እንዳቆዩ ግን " አለው የልዕልናን ፊት በእጆቹ እየጠራረገ ። እንኳን ጉንጬን ሊነካ ከተያየን ቀናቶች ያለፉት አባቴን አስታውሼ መልሼ ተከዝኩ ። ወዲያው ይሁን ለበጎ ነው ብዬ ራሴን እያነቃቃሁ ዝም አልኩ ። ነገሩ የሆነ የተለመደ ነገር ይመስል በትንሽ ንግግርና ቃላት ብቻ ሁሉም ይግባባሉ ። ወዲያው ጃኬት ይዞ መጣና አልብሷት ይዟት ወጣ ። እስከ ውጪ በሩ ድረስ አደረሳቸው ። እነሱ እስኪወጡ ሁሉንም ተቋቁሞ የቆየ ቢሆንም በሩ ከመዘጋቱ የበሩ ደረጃ ላይ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ጀመረ ። እኔ በህይወቴ ትልቅ ወንድ ሲያለቅስ ሳይ የመጀመሪያዬ ነው ። የኔ አባት ማለት ተቸግሮ ሳይበላ ሲያድር የሚስቅ ሰው ነው ከዛ ውጪ የሚያለቅሱም እስኪማይመስለኝ ድረስ ነው አይቼ የማላቀው ። ምን ያህል እንደከፋው ስለተረዳሁ ወደሱ ቀረብ ብዬ በማያገባኝ ከገባው ይቅርታ ግን በቃ ተረጋጋ አትዘን እ አልኩት ። ምን ተብሎ ሰው ማረጋጋት እንደሚቻልም አላቅም ግን አፌ ላይ የመጣችልኝ  ያቺ ቃል ያፀናናችው ይመስል አንባውን ከፊቱ በቀስታ እየጠራረገ ትንሽ ደቂቃ ተከዘና " እኔ ይሄን ያህል ፈጣሪን አስከፍቼው ነው ??? እኔ ትዛዙን ከመከተል ውጪ ምን የማቀው ነገር ኖሮ ነው ?? ምን አረኩህ አምላኬ ምን በድዬ ነው በእንዲህ አይነት ነገር የምትፈትነኝ " እያለ ምርር ብሎ ከፈጣሪ ጋር ሲሟገት ነበር ። በእርግጥ  ምን አረኩህና ማለት አንችልም !!! ምን ያላረግነው አለና ነው !! ነገር ግን በማላቀው አልፈርድም ብዬ ይቅርታ ግን ምንድነው ችግሩ አልኩ እየፈራሁም ቢሆን ። ስለቤተሰቤ ምን አገባህ ይለኛል ይጮኽብኛል ብዬ ብፈራም እዛችው ደረጃ ላይ እንደተቀመጥን የማልጠብቀውን መራር እውነታ ነገረኝ !!! ከልጅነቱ ጀምሮ አመጣጡን እንዴት ሀብታም እንደሆነ ከዛ ቡሀላም እንዴት ችግሮች እንደተደራረቡበት እምዲሁም አሁን ላይ እቤት ውስጥ እስካለችው ሴት አሁንም በመድሀኒት እንደተኛች እኔን ለምን እንደቀረበኝ ሳይቀር ሁሉንም ነገር ነገረኝ ።!!! እጅግ በጣም አሳዛኝ ህይወት ላይ ናቸው !!!! በተለይ ለሳሚ በጣም ከባድ ነው ለሁሉም ነገር ራሱን ተጠያቂ ነው የሚያደርገው !!! እኔ በጭራሽ ያልገመትኩት ነገር ስለነበር ደንግጫለሁ !!! ምን አልባትም ከአቅሙ በላይ ቢሆን ነው ከፈጣሪ ጋር የሚሟገተው ብዬ አመንኩኝ ። ነገር ግን ያ አጋጣሚ እና የሰማሁት ታሪክ ለእኔ ያልተነገረ ፍቅሬ የመጀመሪያው የታሪክ መነሻ ሊሆን ይችላል !!!! የፍቅሬም የሀዘኔም የብዙ ነገሮች መነሻ ያቺ ቀን ናት አረሳውም ግንቦት ወር የኔ ህይወት መጀመሪያ ናት !!! ወጣትነቴ በህይወት ላይ ያለኝ አመለካከት የተቀየረበት ወር .......!!!! ሳናስበው ረጅሞ ሰአት ቁጭ ብለን ስናወራ ልዕልትና ዘመዷ ቃለአብ ተመልሰው መጡብን ። በህይወቴ በስርአት ቁጭ ብዬ ያዳመጥኩበት የመጀመሪያ ቀኔም ነው ። ሲመለሱ ግን የሆነ ውበት ጨምራ የመጣች ያህል እስከሚሠማኝ ድረስ ሳቢ ሆና ነበር ። ግንባሬን ቋጥሬ ላለማስነቃት ባስብምዐአይኔ ከሷ ላይ መንቀል እስኪያቅተኝ ትቆጣጠረኛለች !!?? ሳሚ " ኑ ወደ ውስጥ እንግባ " ሲል ነበር ብንን ብዬ አይኔን የነቀልኩት ። እ አይ እኔ ልሂድ አመሠግናለሁ  ለሁሉም ነገር !!  አልኩኝ ። ልዕልት ቀደም ብላ " ተመልሰህ አትመጣም ማለት ነው ?" አለችኝ ። " አረ ይመጣል እንጂ እገዛህ እንደሚያስፈልገኝ ታቃለህ " አለኝ ። እኔም ያወራኝን አስታወስኩኝና አረ በፍፁም እመጣለሁ በየቀኑ ከፈለጋችሁኝ ብዬ ቁጥብ ፈገግታ በሁሉም ላይ ፈጠርኩ ። ሁሉንም ከተሰናበትኩ ቡሀላ ምን አባቴ እንደነካኝ አላቅም አትሸኚኝም አመት እዳልጠፋ አልኳት ። ሰከንድ አላሰበችም በፈገግታ እሺ ብላ በእጇ የያዘችውን ቃልን ለቃ ወደበሩ ሮጠች ። ስትመለስ የነበረችው ልዕልና አሁን ላይ የለችም !!! ከዛ ወተን ገና መንገድ ከመጀመራችን " አባቢ ምን ብሎህ ነው ወይስ ዛሬ ምን ተገኘ " አለችኝ ። ፈልጌ ነዋ ከደበረሽ ተመለሺ ብዬ ንግግሯን አስቀየርኳት ። ለምኖ እንደሆነ ባላውቅም ከሷ ጋር ስሄድ አንድ እርምጃ ተራምጄ መንገዱ ይፈጥንብኛል ። እንደዛው እየተጓዝን ብንውል ደስ እስኪለኝ ደረስ ከሷ ጋ መሆን የደስታ ስሜት አለው !!! በቃ ምን ልበላችሁ ያ የሚያምር መአዛዋ ቅላቷ ቁመቷ ፍቅሯ ብቻ ሁሉ ነገሯ ማራኪ ነው ። ሳላስተውለው በጣም ወድቄላታለሁ ። ለምን ሁሌ ከማላገኘው ነገር ፍቅር እንደሚይዘኝ ባላቅም በህይወቴ ከሷ ውጪ ማየት የማልችል እስኪመስለኝ ድረስ ወደድኳት !!!!
222
13
https://t.me/ethioleboled
256
14
4 any comment DM @Meki3
306
15
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 8⃣   ........ በሰአቱ ልዕልናን እያየሁ ስለነበር ሳልፈልግ በሷ ተስፋ በመቁረጤ ብቻ  እሷም እንድተውኝ አስቤ አዎ ! ብዬ ተስፋዋን ቆረጥኩት ። አሰፍስፋ እና ፊቷን በፈገግታ ሞልታ መልሴን ስጠብቅ የቆየችው ልጅ አዎ እንዳልኩ ፊቷን ከስክሳ እና ግንባሯን ቋጥራ ከተቀመጠችበት ተነስታ ሄደች ። ልቤ እሷ ጋር ሆነ ተሰምቶኝ የማያቁ ስሜቶች በአንድ ቅፅበት ተፈራረቁብኝ ። ክብሬንም ድህነትንም ምኔንም ትቼ አትሂጂ ልላት እየቃታኝ ነበረ። ግን እንደምንም ስሜቴን ተቆጣጥሬ አሁን መሄድ አለብኝ እቸኩላለሁኝ ብዬ ሳሚ ላይ አፈጠጥኩበት ። " እሺ ግን  ስልክልን ብታስቀምጥልኝ ደስ ይለኛል እኔ ወንድ ልጅ የለኝም እንዳየከው አንድ ሴት ልጅ ብቻ ናት ያለችኝ እና አንተ ጥሩ ልጅ ነክ ቤተሰባችንን ብትቀላቀል ደስ ይለኛል " አለኝ ። ከመጀመሪያው ንዴት ላይ ያለሁት እኔ ንግግሩ አናደደኝ መሠለኝ እኔ ግን ቤተሰብ አለኝ !!! አልኩት ከተቀመጥኩበት እየተነሳሁ ። " ትንሹ ልጅ ተረጋጋ እንጂ አትገንፍል ምን ሆነሀል " አለኝ በሁኔታዬ የተደናገጠ ይመስላል  !!! ። እኔም ምን እንዳናዳደኝ ባላውቅም ቱግ አልኩኝ ። ይቅርታ ግን ስለኔ የምታቀው ነገር የለምና ምንም ባትል ደስ ይለኛል አልኩኝ ኮስተር ብዬ ። " በተሳሳተ መልኩ ነው የተረዳከኝ " አለኝ ለመረጋጋት እየሞከረ ። እኔ ግን የዛኔ ዝቅ ብዬ ስሰራ ስላየኝ ስለተሸከምኩለት ምናም ሰው የለውም ብሎ ያሰበ ስለመሰለኝ እና እናቴን የረሳብኝ መስሎ ስለተሰማኝ ነው የተናደድኩት ። ምንም ያህል አንቀባራ ባታሳድገኝ ብር ባይኖራትም ባይተርፋትም እናት ያው እናት ናት ፈልጋው ስላልሆነ በድህነት ብናደድም በሷ ግን አልፈርድሞ !!! ስለዛ ማንም በሷ እንዲመጣብኝ አልፈልግም !!! ንዴቴን ያስተዋለው የልዕልና ዘመድ ፈጠን ብሎ ከቦታው ጠፋ ። እኔና ሳሚ ብቻ ስንቀር ሁለታችንም  መፋጠጥ ያዝን ። የዝምታ እይታው የሆነ ነገር ሹክ አለኝና ጭንቅላቴን እያሻሸሁ ወንበሩ ጎተት አርጌ ተቀመጥኩ ። " ካስከፋሁህ ይቅርታ " አለኝ ቁጥብ ፈገግታ እያሳየኝ ። አወራሩ ስለገባኝ ጉሮሮዬን ጠራርጌ ስለተናደድኩ ነው ይቅርታ አልኩት በለሆሳስ ። " ምንም አይደል ተረጋጋ ውሀ ጠጣ " አለኝ ወደተቀመጡት ብርጭቆዎች እየጠቆመ ። ቃሉን ለመስማት በሚለው ሳይጠማኝም ቢሆነ ቀድቼ ጠጣሁ ። ከዛ ትንሽ ዝም ካልኩ ቡሀላ በቃ መታወቂያዬን ስጠኝና ልሂድ ስለሁሉም ነገር አመሠግናለሁ አልኩኝ በቀስታ " እሺ ግን እኔ እንዲሁ ቀልቤ ስለወደድክ እንጂ ...... " ብሎ ንግግሩንም ሳይጨርሰው ከመቀመጨው እየተነሳ " በቃ ላምጣልህ" ብሎ ወደ መኝታ ቤት መሠለኝ ሄደ ። ብቻዬን መቀመጥ ቢጨንቀኝም ቁጭ ብዬ ጠበኩ ። ትንሺ አስጠብቆኝም ቢሆን መታወቂያዬንና በሌላ እጁ ደግሞ ምንነቱ ማይታወቅ   ነገር ይዞ መጣ ። " የተገናኘነው በአጋጣሜ ቢሆንም መልካምና ታማኝ ልጅ መሆንህን አይቻለሁ ። የዛኔ የነበረክ ታማኝነት ልዕልናዬ ብር ስሰጥክ አልቀበል ማለትህ ጊቢ ገብተህ ከፊት ለፊትህ የተቀመጠውን ብር ራሱ አለማየትህ እዚህ ክፍል ውስጥ ብቻህን ጥዬ ወጥቼ ቀና ብለህ ነገሮችን አለማየትህ በጣም አስደንቆኛል " አለ በመገረም እየተመለከትኝ ። አስተዳደጌ ይሆናል እናቴ ስርአት በሞላበት ሁኔታ ነው ያሳደገችኝ አልኩ እኔም ኮራ ብዬ " አይ አይ አትሳሳት አስተዳደግ ብቻ አይመስለኝም ቀኞ ግራ እጅ ከቀኝ እጅ በሚሠርቅበት በዚህ ዘመን እንዳንተ አይነት ልጅ ማግኘት ደስ ያሰኛል በተለይ በወጣት ወንድ ሲሆን " እያለ በእጁ የያዘውን መታወቂያዬን ሰጠኝ ። ልክ መታወቂያዬን ስቀበል ግን የልቤን ድብቁን ፍቅሬን እየተሰናበትኩ ነበር ። የሚያስፈልገኝን ስቀበል የምፈልገውን እያጣሁ ነበር !!!!!! ከዛች መታወቂያ ሌላ ከሷ የሚያገናኘኝ ነገር እንደሌለ እያሰብኩ ልቤ እየተሰበረም ቢሆን ከመቀመጫዬ እየተነሳሁ መታወቂያዬን ተቀብዬ ኪሴ ከተትኩ ። " እንግዲ ልጅ ይሄ ደግሞ ...." ብሎ በእጁ የያዘውን ነገር ሊሰጠኝ ወደኔ ሲያስጠጋ ከቤት ውስጥ ቅውጥ ያለ የሴት ጩኸት ሰማን ። ክው ብዬ ተነስቼ የማረገው ሳጣ ሳሚ ግን አንገቱን ወደ መሬት ደፍቶ በእጆቹ አይኑን እያሸ ነበር ??? ድጋሜ ቅውጥ ያለ ጩኸት ሳሚ ሳሚ እያልኩ ቀና እንዲል አደረኩት ። ሳየው አይኖቹ በእንባ ተሞልተው ያዘነ ፊት አሳየኝ ። ምንድነው ተነስ እንጂ ብዬ እሱን ጠይቄ ቀና ስል ...... NB: እስከ 3:30 ላይኩ 100 ከሞላ አንድ ክፍል ይለቀቃል :: ይቀጥላል #ክፍል_9⃣
297
16
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 7⃣ ..........ግን ምንድነው የሚያስፈራኝ ከኔ ምን ሊያገኙ ሆ ? እያልኩ ስመለከት ሌላ በተለያዩ ምግቦችና መጠጦች ያሸበረቀ ረዘም ያለ ጠረንጴዛ ነበር ። ለምንድነው ተደብቀው የሚበሉት ?? እያልኩ በልቤ ሲቀመጡ አብሬ ተቀመጥኩኝ ። በነገሮች ላለመሳሳት ሁሉንም ሳደርግ የነበረው ከነሱ ቀጥዬ ነበር ። ሰሀን አነሱና የሚፈልጉትን ነገር ያደርጋሉ ። ልዕልና አንድ ቁርጥ እንጀራና አንድ ቁርጥ ዳቦ አርጋ አቀረበች ሌሎቹ   ሁለት ሁለት ቁርጥ ሲያደርጉ ወንድ ልጅ አደለሁ ብዬ ሀገር ለት ቁርጥ አንስቼ ሳየው ቀለል ያለኝን ምግብ አነሳሁ ። ሳሚ በስመአብ ብሎ ሲጀምር ልጁ ግን እንደቀድሞው  ዘው ብሎ መብላት ጀመረ ። አንዳንዴ ሰዎችን ለመምሰል መጣሪ ከማንነታችን ያርቀናል!!!!! እኔም ስፀልይ ቢያዩኝስ ብዬ አርጌ ማላቀውን በስመአብ ብቻ በማለት እናቴ ያለማመደችኝን እነዛን የሚያጠግቡ ፀሎቶች ሳልፀልይ በላሁኝ ። እኔ የለመድኩት የቀረበችልኝን የእናቴን ሽሮ ቶሎ ቶሎ ጠረግ ጠረግ አርጌ በልቼ መነሳት ነው እነሱ ደሞ ሁለት እንጀራ የያዙ ይመስል አደሩበት ። ከዛ ግን እነሱን መጠበቅ ሲሰለቸኝ እንደሙዴ በመጠኑ ሳብ ሳብ አድርጌ ጎረስኩኝና መአዱን ሳምኩኝ ። ድንገት " አምሳለ.... አምሳለ" ብሎ ተጣራ ሳሚ " አቤት ጋሼ " አለች ፈጠን ብላ መታ "መፀዳጃ ቤቱን አሳይው እዛው ይታጠባል " አላት ። እሷ መሄድ ስትጀምር ተከተልኳት ። የቤቱ ነገር አስገርሞኝ እንደሚያጠና ሌባ በግርምት ስመለከተው ነበር !!!! ሽንት ቤቱም በመብራቶች ያሸበረቀና አንድ ሙሉ እና አንድ አጠር ያለ መስታወት አለው ። በስመአብ ፅዳቱ ይለያል ። ሳስበው ከሁሉም ነገሮች የተቆጠብኩ ልጅ መሆኔ ጎድቶኛል ። ሀብታም ጓደኞች ቢኖሩኝም ከሄዱ መምጣት አለ ብዬ ስለምፈራ እነሱ ቤት መሄድ አልፈልግም ደርሼም አላቅም ፊልም ከስንት አንዴ እናቴ ስታይ ካየሁ እንጂ አድናቂ አይደለሁም ደ ወይ ወደ ሀብታም ሰፈሮች የምዞር አይደለሁ እና ከነገሮች መቆጠቤ ነገሮችን እንዳላቅ የያዘኝ ይመስለኛል ። !!!! ያንን ቤት ሳይም በዛ ልክ ስላልጠበኩ ነው የገረመኝም ። ከዛ የኔ ጓደኞችም እንዲህ አይነት ቤት ውስጥ ይሆን የሚኖሩት ??? እያልኩ ራሴን እየጠየኩ ፈጣሪን እንዳላማርርጰደግሞ ብዬ ቶሎ ወጥቼ ወደታች ተመለስኩኝ ። ያ ችግር የሆነ ቃለአብ የተባለ ልጅ ግን ከኔ ችግር ያለበት ይመስል ልክ ቁጭ ከማለቴ " ግን አጎቴ ከዚ ልጅ ጋ ምንድነው ያገናኛቹ ለምን ይሄን ያህል ትኩረት ሰጠከው ??" ብሎ ጠነቀው ። ተነስቼ አንዴ ቴስታ ባቀምሰው ደስታዬ ነበር ግን ራሴን ላለማስገመት በዝምታ ተቀመጥኩኝ ። ያስደነገጠኝ ነገር ግን ሳሚ ፈገግ ብሎ ልዕልናን ሲያያት ፈጠን ብላ " አባቢ የበአል እቃ ገዛዝቶ ሲመለስ የሚያግዘው አቶ ከዛ ሚኪ ጥሩ ልጅ ስለሆነ እቃውን በታማኝነት ቤት ድረስ አደረሰለትና ብር ጎሎት ነበር ከቤት ብር ይዞ ወስዶ ለአባቢ ሰጠው ከዛ አባቢ የእሱን መታወቂያ ሲያገኘው አንስቶ አመጣለት ደግ ሰው ስለሚወድ ወደኛ እያቀረበው ነው አለቀ " አለይ ፈገግ ብላ ። ማለት ስለምን እና ስለማን ነው የምታወራው ከመፅሀፍ ጋ የሚመሳሰል ታሪክ ኖሮኝ ነው ?? አልኩ በልቤ ። ምክንያቱም ካወራቻቸው ወሬዎች ውስጥ ልክ የሆነ ነገር ቢኖር የበአል እቃ ገዝቶ የምትለዋ ብቻ ናት ። ግራ ስለገባኝ ቀና ብዬ ሳሚን ሳየው የሆነ የአራዳዳዳ ልጅ አስተያየት አየኝ ። ከዛ እኔን ላለማሳጣት የፈጠረው ታሪክ እንደሆነ ገባኝ ። ድሮም እኮ የደሀ ልጅ መሆኔን ብታውቅ እኔን ለመቅረብ እንደማትሞክር አቅ ነበር !!! በቃ የሀብታም ልጅ መስያት ነው ልትቀርበኝ እየሞከረች ያለችው እንጂማ .......!!!! ብቻ ግን የሰለሞን እርድና ቢያስደስተኝም  ነገሮችን ሳስባቸው ግን አስከፊ ነገር ናቸው ። ለነገሩ ምን አገባኝ ብዬ ስለ ግብዣው አመሠግናለሁ አሁን መታወቂያዬን ስጡኝ ልሂድ ስራ አለኝ አልኩ ሳሚን  እየተመለከትኩ ። "እህ ለምን አትቆዬም ትንሽ እ " ብላ አይን አይኔን ተመለከተችኝ ። ልጅቷ ልቤን ለማቅለጥ ቆርጣ ተነስታለች ። ቀና ብዬ ባየዋት ቁጥር የሆነ ነገሬን ይወጋኛል ??? ልቤን ከሷ ለማራቅ በሞከርኩ ቁጥር ትጎትተኛለች ። በዛ ሰአት ግን ሳሚ የማይሆን ጥፋት አጠፋ ድንገት ጉሮሮውን ጠራርጎ " እኔ ምለው ግን ፍቅረኛ አለህ አይደለ ? " አለኝ ። ለምን እንደሆነ ባላቅም ክው ነው ያልኩት ። ከሱ በላይ ልዕልና መልሴን ለመስማት አሰፍስፋ እየጠበቀችኝ ነበር ። በሰአቱ ምን ማለት እንዳለብኝ ራሱ ግራ ገባኝ ። ግን በሰአቱ ልዕልና እያየሁ ስለነበር ሳልፈልግ ........ ይቀጥላል #ክፍል_8⃣
241
17
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 6⃣ .........ሳላስበው ጩኸቴን አቀለጥኩት ። በጣም ነበር የደነገጥኩት ። የኔ  ጩኸት ያስደነገጠው ሳሚ ዞሮ እየሮጠ ሄዶ አነሳት ። እኔ ያሰብኩት የነበረው ። እናቴ እንደምታየው ፊልም ወድቀው ጭንቅላታቸው ደምቶ ሞተው ሲቀበሩ ስላየሁ እንደዛ አይነት ነገር ስላሰብኩ ነበር በህይወቴ አውጥቼ የማላቀውን አይነት ድምፅ  አውጥቼ የጮኩት ። ደስ የሚለው ግን ምንም ሳትሆን በትንሽ ጉዳት ነው  ያለፈልን ። እሷ ግን ከህመሙ በላይ እኔ ፊት መውደቋ ነበር ያሳሰባት ። እንደማፈር እያለችም ቢሆን ለሁለት ይዘናት ገባን። በተለያየ ሰበብ ከነሱ ጋር የሚያቀራርበኝ ነገር እየበዛ ነው ። ስመጣ ለእራሴ የገባሁትን ቃል ሙሉ ሽሬ  ቤታቸው ውስጥ ገባሁ ። ያለምንም ማካበድ ውጪው በጣም ነው የሚያስጠላው ከውስጡ አንፃር ማለት ይቻላል ። እንደዚ አይነት ቤት እንዳለ እንኳን አላቅም ነበር ። ለምን ከነሱ ጋ እያቆራኘኝ እንደሆነ ባላቅም ፊትና ጀርባ የሆነ ተቃራኒ ህይወት ላይ ነው  ያለነው ። በስተት እንኳን በህልምም ሆነ በቅዠት አይቼ የማላቀው አይነት ህይወት ነው። ማለት እኛም እነሱም እየኖርን ነው እንላለን ????? ለነገሩ ሁላችንም በፈጣሪ ዘንድ ያለንን ቦታ እያሰብን መፅናናት አለብን ። በዛ ራሴን እያነበረታታሁ ውሎዬን በነ ሳሚ ቤት አደረኩኝ ። ልዕልና ራሷን አደፋፍራ " እውነት ለመናገር ያማል አባ ግን አልተጎዳሁም አሁን ወደ ፕሮግራሙ እንሂድ ይመጣል ብዬ ስላላሰብኩኝ  ነው እንደዛ የለበስኩት መብራትም ስለጠፋ ሰአቱን አላስተዋልኩኝም ይቅርታ ይደረግልኝ " ብላ ለብሳ መጣች ። የሚገርመው እኔ የተገላለጠ ልብስ ስለማልወድ እንጂ ያቺ ብጣሽ ልብስ ራሱ ታምርባት ነበር ። ገብታ ለባብሳ ስትመጣ ደግሞ የበለጠ አማረባት ። አጋዣቸው ቶሎ አፀዳድታ ጨረሰችና እኛ ከነበርንበት ቦታ ጠፋች ። ቦታው ጭር ሲልብኝም ግብዣው ዝምታ ነው እንዴ ሆይ እያልኩኝ ተቀመጥኩ ጀ ሳሚ ተነስቶ ወደ ሌላ አቅጣጫ ልዕልና ተነስታ ወደ ሌላ አቅጣጫ ስታፀዳ የቀየችው ሴትም ወደሌላ ብቻ ሶስቱም ወደተለያየ አቅጣጫ ሲሄዱ ግራ የተጋባሁት እኔ ወዴት ወዴት ነው እያልኩ እጠይቃለሁኝ ። ብዙም ሳይቆይ ግን ልዕልና ከባለፈው ገገማ ልጅ ጋር እጅ ለጅ ተያይዘው መጡ ። እንደነገረችኝ አላወቀም መሠል እንደፍቅረኛዋ ሲያስመስል ቆየ ። ትንሽ ቆይቶ ሳሚ ልብሱን ቀይሮ ወደኛ መቶ ተቀላቀለ ። ከየት ከየት ነው የሚመነጩት እያልኩኝ ብቻዬን እያወራሁ ግን አድናቆቴን ከመግለፅ ይልቅ ደብቄ ያዝኩት ። ልጁ በጣም ያወራል ??? በጣም ነው የሚለፈልፈው ምን አስቦ እንደሆነም አላቅም በንግግሩ ሁላ እኔን ለመንካትና ለማናደድ እየሞከረ ነው እኔ በጣም ችላ ብዬ እያለፍኩት ነው ያለሁት ። ለነገሮች አዲስ እንዳልሆንኩ ማስመሠል አልፈለኩም ኮራ ብዬ ነው የተንደላቀቀው ሶፋ ላይ የተቀመጥኩት ። ዝምታ ሰፍን የራሴ ሀሳብ ላይ ሳለሁ " ጋሼ ጨርሻለሁ ሁሉንም " ብላ ተመልሳ ሄደች ። ስለምን እንደሚያወሩ ያልገባኝ እኔ ሁለቱንም በየተራ አየዋቸው  ። ሳሚ ቶሎ ተነስቶ ተከትሏት እየሄደ " በሉ ልጆች ፍጠኑ ኑ " ብሎን መንገዱ ቀጠለ ። ቤቱን ከጥንስሱ አንስቶ ያልወደድኩት እኔ የሆነ ነገር ሊያደርጉኝ መስሎ ስለተሰማኝ ፈራሁ ። ግን ምንድነው  ......???? ይቀጥላል #ክፍል_7⃣
254
18
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 5⃣ ...........ዞሬ እያየዋት ሳላስበው እሷም ዞረች ። አልዋሽም ደንግጫለሁ ። ደስ የሚለው የሆነ ህዋሴ ረዶቶኝ ፊቴን አዙሬ ምንም እንዳልተፈጠረ መንገዴን ቀጠልኩኝ ። ከዛ ቡሀላ ብዞር ቆማ እያየች ቢሆንስ ብዬ ስለፈራሁ ቀጥ ብዬ ወደቤቴ ሄድኩኝ ። ፈጣሪ ይቅር ይበለኝ እንጂ  ቤቴ ስደርስ እየከፋኝ ነበረ ። ልዩነትን ማየት ማንነትህ ላይ እንድታተኩር ያደርግህና ሌላ ነገር እንድትመኝ ነው የሚያደርግህ!!! እኔም ያንን ቤት ጊቢ እና የአባትና የልጅ ፍቅርን ጨምሮ ብዙ ነገሮችን አይቼ መጣሁና ቤቴ ገብቼ በውርስ ከተገኘችው ያዘነበለች አንድ ክፍል ቤት እና ከሰው ተበድሮም ቢሆን አረቄ በጠጅ በጠላና በአንድ ጠርሙስ ሀረር ቢራ ከሽኖ ጠጥቶ እልሁን ምስኪኗ እናቴ ላይ ከሚወጣው አባቴ ጋር አነፃፀርኩትና አይ አለመታደል አልኩኝ ። የኔ አባቴ አንድ ሳምንት ሰይጣን አንድ ቀን መልአክ መሆን የሚያስደስተው ግሩም ፍጥረት ነው ። " ባለው ይመስገን !!" የምትለዋን የእናቴን ምክር ለእራሴ እየነገርኩ ወደ ውስጥ ገብቼ ቁጭ አልኩኝ ። እናቴ ገና ከመግባቴ ሮጥ ብላ ውሀ ይዛ መጣች ። " ቆየክብኝ እኮ ሀብቴ ርቦታል ብዬ ተጨነኩብህ እኮ " አለችኝ ለማስታጠብ እየተዘጋጀች ። የኔ የዋህ እህኔ እኮ እኔን እየጠበቀች ምሳ አልበላችም አልኩ በልቤ ። የት እንዴት የሚሉ ጥያቄ አጠይቀኝም ብዬ ስላሰብኩኝ በልቻለሁ እማ አንቺ ብይ አልኳት ። መቼም እዛ ያን የመሰለ ከቅቅል እስከ ዱለት ያን የመሠለ ምግብ በልቼ መጥቼ የእናቴን ሽሮ ፈሰስ ልጨምርብህ ብለው ሆዴም እሺ አይለኝም ብዬ አስቤ ነው ። " ቀጣፊ የት ነው የምትበላው ታጠብ ና ወይስ አመመክ እንዴ ልጄ " ብላ አንዴ ግንባሬን ጭንቅላቴን ጉንጮቼን ብቻ ሁሉንም በየተራ አገላብጣ አየችኝና " መፋጀት ደግሞ የለብህም ችግር አለ እንዴ እ ከሰው ተጣላህ " አለችኝ ከኔ የምትፈራው ነገር ነውና !!! በልቻለሁ ብዬ ተነስቼ ከቤት ስወጣ ምንም አላለችኝም ዝም ብላ የራሷን አቅርባ በርበሬ በቁጥር የተደረገበት የሚመስል ሽሮ ወጧን ጨው ጨው በሚለው የሱቅ እንጀራ በልታ ተነሳች ። የዛኔ ነበር ይበልጥ ከድህነት ጋር የተጣላሁት ። ለምን ህይወት ይሄን ያህል ተቃራኒ ሆነች ??? ለአንዱ ገነት ለአንዱ ምድራዊ ሲኦል ለምን ሆነች ??? የሌላው እናት ስንቱን አማርጦ እየለበሰ እየተዝናና እየበላ የኔ እናት ለምን እድፍ በምትችለው ሙሉ ቀሚሷ እና ያንን ሀር የመሠለ ረጅምና ለስላሳ ፀጉሯን በደበቀው ጥቁር ሻሽ እና በማትቀየረው ሽሮ ወጥ ተዘፍቃ ለመኖር ማን ፈረደባት ??? ፈጣሪ አያዳለም አይደል እንዴ ??? እያልኩኝ ከእራሴ ጋር መሟገቴን ቀጠልኩበት  ። ከዛም ድህነትን እበቀለዋለሁ ብዬ ለእራሴ ቃል ገባሁ !!! ሀብታም ሆኜ  እናቴን ቀን በቀን ስጋ እንድበላ ካላረኳት አባቴን ሱፍ ካላለበስኩ እኔ ሰው አይደለሁም !!! እያልኩ እየዛትኩበት ዋልኩኝ !! ቀን በቀን እልህ ተናነቀኝ !!! ሳምንቱንም የቻልኩችን ያህል ሳቅድ አሳለፍኩት የቻልኩትን ያህል ደግሞ ለመስራት እየሞከረኩ ነው ። ደስ የሚለው በሰአቱ ስራ አልንቅም ብቻ ክብር ክብር እያልኩ ስለምጨማለቅ ራቅ ወዳለ ቦታ ሄጄ ተፍ ተፍ ብዬ እየመጣሁ ኑሮዬን ቀጠልኩኝ ። ቀኑ ይፈጥናል እኔ በጠዋት ተነስቼ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሜ ስፖርት ሰርቼ ተጣጥቤ ቁርስ ልበላ ስዘጋጅ ነበር ቀኑ እሁድ መሆኑንም ሆነ የልዕልና አባት ጥሪ እና እንዳላረፍድ የተሰጠኝን ማስጠንቀቂያ ጭምር ያስታወስኩት ። መጀመሪያ ችላ ብዬ ልተወው አስቤ ነበር ነገር ግን  ልዕልና " መታወቂያክን ይቀደዋል " ያለችውና ከወር ቡሀላ የማትሪክ ተፈታኝ መሆኔ ሲገጣጠሙብኝ የእናቴን ሽሮም ሳልበላ ቶሎ ለባብሼ ከቤት ወጣሁ ። ወይ ሰአት የለኝ ወይ ስልክ የለኝ መርፈድ አለመርፈዱን በምን ልዬ ስለዚህ ረፈደም አረፈደም አያገባኝም እያልኩ ከእራሴ ጋር እያወራሁ ቀጥታ ወደነሱ ቤት መሄድ ጀመርኩ ። መንገዱን ሙሉ ምንም ቢሉኝ አያገባኝም ....! ቤት ግባ ቢሉ አልገባም ....!!!   ልዕልና ምንም ብትል አይጨንቀኝም ......!!! ፍቅር የሚባል ነገር የለም   ....!ደሀና ሀብታም አንድ ላይ አይሆንም መቼም ስለዚህ ራሴን አልጎዳም.....! እኮሳተራለሁ ....አልመልስላትም.... !!! እያልኩ ለእራሴ በርካታ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ እየነገርኩ ወደነሱ ቤት አመራሁ ። ብቻዬን ሳወራ ይሆን ባላቅም መንገዱ በጣም ቀረበብኝ ቶሎ ደረስኩ ። እንደደረስኩ በሩን ደወልኩ ። አልከፈት አለኝ ደግሜ ተጫንኩት አልተከፈተም ።??? ምን  አልባት ረጅም ሰአት ከፈለገስ ብዬ አሰብኩና ደግሜ ተጭኜው ቆየሁኝ አሁንም አልተከፈተም ??? ያማቸዋል እንዴ ብዬ በሩን ጓ ጓ ጓ አደረኩት ። ወዲያው በሩ ተከፈተ ክው ነው ያልኩት !!! ያስደነገጠኝ ወዲያው በሩ መከፈቱ ሳይሆን የልዕልና እርቃን ቀረሽ የሆነ አለባበስ ለብሳለች ። የእግሯን ቅላት የሚያጓላ ግልገል ሱሪ የምትመስል ትንሽዬና ስስ ቁምጣ ለብሳለች ከላይ ደግሞ ከጡቶቿ ውጪ ያለውን ሁሉንም ሰውነቷን የሚያሳይ የሚያስጠላ አለባበስ ለብሳለች ???? ስታየኝ እሷም ክው ነው ያለችው ግን እንደዛ መልበስ ለምን አስፈለገ ብላት ደስ ባለኝ ነበር ግን አሁንም በማያገባኝ አልገባም ብዬ መታወቂያዬን አቃብይኝ አልኳት ፊቴኔ ወደ ዃላ እያዞርኩ ። እሷም እንደመባነን ብላ በሩን ፊቴ ላይ ወርውራው ወደ ውስጥ ገባች ። ሁኔታው የበለጠ አናደደኝ መሠል በሩን መልሼ በሀይል መደብደብ ጀመርኩኝ ። " ልጅ ሚኪ " አሉኝ ከዃላ  እና ዞር ስል አባቷ ነበር ። ሰላም አደርክ መታወቂያዬን ፈልጌ ነው አልኩኝ ኮስተር ብዬ ። ሲጀመር ያገናኘን ስራ እስከሆነ ድረስ ምንድነው አላስፈላጊ ቅርበት ??? ለምን ይሄን ያህል ሊያቀርቡኝ ፈለጉ ?? ደግሞ እቃ ያመጣሁት በደግነት ሳይሆን ለገንዘብ ነው የደሀ ልጅ መሆኔ እንዴት አይገባቸውም ሆይ ???? አልኩ በልቤ ። " ሰላምታ አይቀድምም እንዴ ?" አለኝ መልሶ እንዴት አደርግ ሰሚ ይቅርታ ቸኩዬ ነው አልኩት ። ከዛም ከኪሱ ስልኩን አወጣና ተመለከተው ። " እኔ የምመርጠው አይነት ሰው መሆንክ እየበዛ ነው ባክህ ከተባባልነው ሰአት አምስት ደቂቃ ቀድመህ ነው የመጣኸው ይሄ ያስደስታል በል ና ግባ " ብሎ በሩን በያዘው ቁልፍ ነካ ነካ ሲያረገው በሩ ተከፈተ ። አይ አልገባም አመሠግናለሁ  እዚሁ ስጠኝ አልኩትና ወደ ውስጥ ሳይ ልዕልና በረንዳ እየተወለወለ ነበር መሠለኝ አንሸራቷት ውድቅ ስትል ሳላስበው ጩኸቴን አቀለጥኩት ????........ ይቀጥላል #ክፍል_6⃣
245
19
没有文字...
0
20
Join us 🫡
384