ch
Feedback
📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

前往频道在 Telegram

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾 ➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና እንጊሊዘኛ ..... መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ። 📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️ B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር 100K ይደርስ ነበር ። For any comment @Meki3

显示更多
2 276
订阅者
+624 小时
+107 夊
+1530 夊

数据加载中...

吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+39
在0个频道中
八月 '26
+86
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '26
+141
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+109
在1个频道中
Get PRO
五月 '26
+67
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+48
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+60
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+45
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+65
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+92
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+56
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+50
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+70
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '25
+58
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+66
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+92
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+74
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+55
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+38
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+56
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+68
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+67
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+37
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+46
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+65
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '24
+81
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+35
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+36
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+42
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+47
在2个频道中
Get PRO
二月 '24
+46
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+32
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+63
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+37
在1个频道中
Get PRO
十月 '23
+63
在2个频道中
Get PRO
九月 '23
+58
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+77
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+63
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+46
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+39
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+41
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+54
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+192
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+125
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+46
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+57
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+66
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+64
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '22
+40
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+43
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+64
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+93
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+36
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+47
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+54
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+75
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+135
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+97
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+132
在0个频道中
Get PRO
䏃㜈 '21
+142
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+114
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+71
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+190
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+122
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+172
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+180
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+1 524
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
15 九月+3
14 九月+6
13 九月+2
12 九月+2
11 九月+2
10 九月+1
09 九月+2
08 九月+2
07 九月+1
06 九月+3
05 九月+3
04 九月+3
03 九月+5
02 九月+2
01 九月+2
频道帖子
❤️ #ጥላቻ ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ ታሪክ❤️ ነገ ምሽት ጀምሮ በቴሌግራም ቻናላችን ይከታተሉን Join us: https://t.me/Ethioleboled

2
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 4⃣2⃣ የመጨረሻ ክፍል ......... ከስድስት ወራት ቡሀላ ግን ራሴን ያገኘውት በህይወቴ እደርስበት ይሆን የምለው ህይወት ላይ ደርሻለሁኝ !! ገንዘብ ላይ ሽቁንቁን ሆኜ ስድስ ወራትን አሳለፍኩኝ !!! ያለኝን ሳይ የበለጠ አጠነከረኝ !!! ከተጨማሪ ወራት ቡሀላ ግን ወደ ሀብታሞቹ መንደር ሄጄ ፅድት ያለ ቤት ገዛሁኝ !!!!!! ይሄ ለእኔ ምን ማለት እንደሆነ ......... የሆነ ትልቅ ማማ ላይ የደረስኩ ነው የመሠለኝ ራሱ  !!! ደግሞም ነው እንደዛ አይነት ቤት ገዛለሁ አደለም ቀርቶ ተከራይተን ወር እንቆያለን ብዬም አስቤ አላውቅም ነበር !!!! ዋናው ፈጣሪ ነው !!!!! እሱም በሳሚ ላይ አድሮ እኔን እዚህ አደረሰኝ !!!! አስታውሳለሁ ለመጀመሪያ ጊዜ አባቴን ፍለጋ ወጥቼ በስንት መከራ እና በስንት ጥቆማ አገኘውት ። ከዛም ለእናቴም ለአባቴም ልብስ ከቀየርኩላቸው ቡሀላ አንድ ላይ ወስጄ ነበር ቤቱን ያሳየዋቸው ። ወደ አዲሱ ቤት ስንገባ ልዕልቷ ቤት ድረስ መታ ሰላም ሳሚ ሆነው ኬክ ገዝተው ምናምን በቃ እኔ እናትና አባቴን ሳስደስት እነሱ ደግሞ እኔን አስደስተውኝ ነበር ! እናትና አባቴ አላመኑኝም ነበር የዛ ቀን የነበረውን ለቅሶ መቼም አረሳውም ሁሉም ሰው ነበር ያለቀሰው !!!! የቤት እቃዎችን ገና ባላሟላም ለእናትና አባቴ የሆነ ነገር እንዳደረኩ ነው የተሰማኝ !!! በጣም በራሴ ኮርቻለሁኝ !!!!! የነሱን ደስታ ሳይ ደግሞ የበለጠ ነው የሚያጠነክረኝ !!!! የበለጠ መስራቴን ቀጠልኩኝ ሳሚ ደግሞ በተገናኘን ቁጥር " ትንሹ ቢሊየነር ነው የምትሆነው " እያለ ያበረታኛል !!! በህይወቴ ከምደሰትባቸው ነገሮች አንደኛው  ከሳሚ ጋር መገናኘቴና መዛመዴ ነው !!!! ከስፖርት ትንሽ ብርቅም ባለኝ ነገር እየተደሰትኩ ቀስ በቀስ የእናት የአባቴን ቤት ማሳመሩን ተያያዝኩት !!! የሚገርማችሁ አዲሱ ቤት ስንገባ አባቴ በጣም ተቀይሯል !!! የመጠጥ ሱሰኛ አይመስለኝም !!! ሳስበው ከነገሮች ለመሸሽና ራሱን ለመደበቅ ከህሊናው ለማምለጥ ሲል ነበር የሚጠጣው !!! ሁልጊዜም ለኛ ምንም ባለማድረጉ እየተፀፀተ ነው የኖረው ለዛም ነው እናቴ ከሌላት ላይ ብር ሲወስድ ራሱን በጣለበት ታይም ቤት እንኳን እንደማይመጣ እያወቀች ራሱ ባለቤትነቷን የጠበቀችው !!!! ምንም እንኳን ቢጠጣ ቢቆሽሽ ቢሰክር ቢሳደቦ ውስጡ ነዋህ ነው በፍቅር የተሞላ !!! ሁል ጊዜ ይመርቀኛል ራሱን እንደሚወቅስ ይነግረኛል !! ያ ጢባራም የሚባለው አይነኬው የሚሉት ሀብታሙ ግን አሁን ላይ ኮራ ብሎ የሚኖር ወጣት ሆኗል !! በሀያ አመቴ ከህልሜ ግማሹን አሳክቻለሁ !!!!! ከዛ ቡሀላ ኮራ ብዬ ስሜን መናገር እችላለሁ !!! ምክንያቱም ስለሆንኩ!!! እናቴና አባቴ በህየውት ኖረውልኝ እነሱን መጦር በራሱ ትልቅ ሀብት ነው !!!!! ለካ ስሜን የጠላውት ያለቦታው ስለዋለ ነበር !!!! እንግዲህ እኔ ጎብዧለሁ !! ሁሉንም ነገር እያሳካሁ ኑሯችንን ቀጠልኩ የሚያስፈልገውን ሙሉ እያረኩ ቀሪውን እየቆጠብኩ ቆየሁኝ !! ብዙ ብር ሴቭ ማረግ ችያለሁ !!! ህይወት ቀጥላለች ልዕልቷም በእራሷ መንገድ የወደፊት ህይወታችንን ለማሳመር እየጣረች ነው !!! ከማያ ሙሉ በሙሉ ርቂያለሁ ማለት ይቻላል !!! ብቻ ግን ወንድ ልጅ እንደወለደች ሰምቻለሁ ! መጀመሪያ ላይ ተናድጄ ነበር ግን ሳስበው ለሷ ጥሩ ነው መሠለኝ !!! ሁላችንም በየራሳችን መንገድ ህይወት ቀጥለናል ደስ የሚለው !!!! ከዛሬ ምናምን አመት በፊት ያለንበትና አሁን ያለንበት መንገድ ልዩነቱ ደስ ይላል !!!! ከአመታት ቡሀላ ብዙ ነገሮች የበለጠ ተቀይረዋል እኔ የሀያ ስድስት አመት ጎረምሳ ይሆን ጎልማሣ የምባለው ብቻ ሳሚ እንዳለው ወደ ቢሊየነር እየገሰገስኩ ያለሁ ወጣት ሆኛለሁ !!! ልዕልና የዩንቨርስቲ ቆይታዋን ጨርሳ የምትመረቅበት ቀን ደረሰ !! የሚገርመው በዛ ሁላ አመታት ልዩነት እንኳን የዛኔም ሳገኛት ለሷ ያለኝ ስሜት አንድ ነው ደካማ ጎኔ ሆና ቀርታለች !!! ለብዙ አመታት ከጠበኩ ቡሀላ ለምርቃቷ ትልቅ ስጦታ አዘጋጅቼላታለሁ !! ምርቃቷ የስለት ልጅ ሰርግ ነው የሚመስለው !! የሚገርም ድግስ ነበር !! ካለው ተጠጋ ትል ነበር እናቴ የሚወርድላት ስጦታዎች ይለያሉ !!!! የዛ ቀን ግን ከሁሉም የምትለየው የኔ ስጦታ ናት !!!!! ምክንያቱም በእነ ሳሚና በእናትና አባቴ ቤት መሀል ፈልጌ መርጬ ያቺ የወደቀች ቤት እያለሁ ያልጠላችኝ ፍቅሯ ቅንጣት ያልቀነሰባትን ውብ ሴት ፅድት ያለ ቤት ገዝቼ እቃ ሞልቼ ጨርሼ አሰማምሬ ስጠብቃት ስለነበር የቤቱን ቁልፍ የምርቃቷ ቀን ሰጠዋት !! ጭራሽ አልጠበቀችውም ነበር በጣም ኮርታብኛለች !!!! ከዛ የበለጠው ደግሞ ከሳሚ ጋር አውርተንበት አስበንበት የምርቃቷ ቀንና የቀለበቷን ቀን አገጣጠምነው !! የዛ ቀንም ሙሉ ቤተሰቡ በደስታ ሲያለቅስ ነበር !!! ሙሉ ቤተሰቡን ስላኮራሁኝ ደስ ብሎኛል !! የዛኔ  ደሀ ነው ብለው ያልናቁኝን አይቀየርም ብለው ያልተውኝ ሁሌ ባለውለታችን የሚሉኝን ያደረኩላቸውን እንጄ ያደረጉልኝን የማይቆጥሩትን ሳሚና ሰላምንም ስላኮራዋቸው ደስ ብሎኛል !!! ሁሉም ወዶና ፈቅዶ ልዕልቷን ለልዑሉ አሳልፈው ሰተዋል !! በጣም ደስተኛ ነኝ !!!! ከዛች ቀን ጀምሮ ነው እኔና ልዕልና አንድ ቤት መኖር  የጀመርነው !!! ደስ የሚል ህይወት ያማረ ኑሮ ፈጣሪ ምን ይሳነዋል!! ከትቢያ አንስቶ  አይደላቆ እያኖረኝ ነው !!! ከልጅነቴ ያደኩበት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሄደን ቃል ተገባብተናል !! ከዛም ኑሯችንን ቀጠልን ! አንዴ ስኬት ወደ እናንተ መምጣት ከጀመረ ሙሉ ህየውታችሁ ስኬት ይሆናል ! በደስታ ላይ ደስታ መደራረቡ ቀጥሏል አንድ ላይ መኖር በጀመርን በወሩ ምናምን ልዕልቷ ቤቱን አሳማምራ ጠብቃኝ አባት ልሆን እንደሆነ ነገረችኝ !! ማመን ሁላ ከብዶኝ ነበር !!!! ለሰው ወሬም ሳንጨነቅ ሰባት ወር ሞልቷት ምናም ሆዷ ገፍቶ ፅድት አድርገው ዳሩን !! ልዩነቱ ልዕልቷ የመጀመሪያ ልጇን ስትወልድ ማያ ሶስተኛ ልጅ መውለዷን ሰምቻለሁ !!! የእኔንም የሷንም ቤተሰብ አያት ማድረግ ችለናል ደስ የሚለው ደግሞ ሁለታችንም ብቸኛ ልጆች ነን ! አንዴ የኔ እናትና አባት ቤት አንዴ የነ ሳሚ ቤት አንዴ የኛ ቤት እያልን እስኪበቃን ደስታ በደስታ ሆነናል !!!!!!!!🙏🙏🙏🙏🙏🙏 በመጨረሻም ፈጣሪ ፈቅዶልን ደስ የሚል ህይወት ላይ ነን !!! ልዕልቷ እየሰራች ጎን ለጎን ልጃችንን እያሳደገች ነው !.እኔም በስራዬ ስኬት ቀጥያለሁኝ !!! ሳሚና ሰላም እናቴና አባቴ ደስ የሚል ኑሮ ላይ ናቸው ማያም ልጆቿን እያሳደገች ነው !!!!!..... . #ተፈጸመ ሁሉም ነገር ቆንጆ መሆኑን እየነገርኳችሁ ህይወት ይቀጥላል የጣረ ይሳካለታል ተስፋ የማይቆርጥ የሚፈልገው ቦታ ይደርሳል ፍቅር በሀብት አይለካም !!!! እላችዋለሁ ። ለሁላችሁም እንደዚህ ታሪክ ያማረ መጨረሻ እንዲኖራችሁ እየተመኘሁ ቸር ሰንብቱ 🙏🙏🙏. ሀሳብ አስተያየት ካላችሁ comment ላይ አሳውቁን በቅርቡ በአዲስ ታሪክ አንመለሳለን ሰላም ቆዩን   
163
3
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 4⃣1⃣ ..........ደግሞ እጁን ዘረጋለት ። አባቴ አሁንም ሰላምታውን ለመመለስ ፍቃደኛ ባለመሆኑ በጣም ከፍቶኝ የበለጠ አልቅሼ እንዳላስለቅሰው ብዬ እያለቀስኩ የሳሚ መኪና ውስጥ ገባሁ ። ሳሚም የኛን በር አንኳኳና እማ ስትከፍተው ወደ አባዬ ጠቆመና ወደኔ ተመልሶ መኪናውን አስነስቶ መሄድ ጀመርን ። ቀጥታ ስራ ቦታ ሊወስደኝ ባለመቻሉ ቀድሞ አማኑኤል ቤተክርስቲያን ወሰደኝ ። ለረጅም ደቂቃ እዛ ተቀመጥን ። ከዛ ግን ሰአት እንደሄደ ሲነግረኝ የልቤን ፀልዬ ተነሳሁ ። ከዛም ወተን ወደ ስራ ቦታ እየወሰደኝ እያለ " መበርታት መኩራት እያለብህ እንዴት እንደዚ ትደክማለህ ?? " አለኝ ። በምንድነው የምኮራው ምን የሚያስደስት ነገር ኖሮ ??አልኩት " በጣም ጥሩ ልጅ ነህ !!.አሁን ደግሞ የለውጥ  ጉዞውን ጀምረሀል ከሶስት ሳምንት ቡሀላ የመጀመሪያ ደሞዝክን ታገኛለህ ። ከዚ ቡሀላ ቢበዛ ሁለት ወር መታገስ ቢኖርባቸው ነው ከዛ የተሻለ ቤትና ኑሮን ትሰጣቸዋለህ !! ሶስታችሁም እስካሁን መኖራችሁ በራሱ ትልቅ ደስታ ነው አይደል እንዴ !!!" አለኝ ። ትንሽ ብርታት ሆነኝ የበለጠ ቶሎ ተቀይሬ አለማቸውን ማሳየት እንዳለብኝ ወሰንኩኝ !!! በዛ በታደሰ መንፈስ ሆኜ ወደስራ ገባሁ ። ከሳሚ ጋር አንድም የሚያቃቅር ባህሪ ሳይኖረን ስራችንን ቀጠልን ። አንድም ቀን ሰልችቶት አያቅም !!! እንደቀልድ አንድ ወር በስራዬ ላይ መቆየት ቻልኩኝ ። የዛኑ ቀን ሳሚ ይዞኝ ሄዶ ባንክ አስከፈተኝና ከዛ ጋዜ ቡሀላ ደሞዙ ለትንሽ ጊዜ እዛ እንዲቀመጥ ነገረኝ ። በዘመዳ ዘመድ ቢሆንም ትልቅ ስራ ነውና ያገኘውት በህይወታችን ሙሉ አይተነው የማናቀው የሚመስል ብር ተከፈለኝ ። እናቴ ከላዩ ላይ አስራቴን እንዳስገባ ስለነገረችኝ ለሳሚ ነግሬው በጣም ትንሽ ብር አወጣሁና አስራቴን አስገብቼ ለእናቴ አስቤዛ እና ፈሳሽ ዘይት ገዝቼላት ገባሁ ። አባቴ ከስንት አንዴ ነው ቤት የሚመጣው ሲመጣም ግን በራሱ ስለሚያፍር እኛን ላለማውራት ይተኛል በቀጣዩ ቀን ይወጣህ ዝም ብሎ ህይወት ነው እየኖረ ያለው !! ቀጣይ ወር ስራዬን በሰላም እንደጀመርኩኝ ልዕልቷ ለዩንቨርስቲ መጠራታቸውን ሰማሁ ። ምንም ስራ ቢበዛ እንኳን በሳምንት ሶስት አራት ቀን መገናኘታችን አይቀርም ። ቀን በቀን በቀረብኳት ቁጥር ምን ያህል ንፁህና ውብ እንደሆነች እየተረዳሁ ነው የመጣሁት ። ለሷ ያለኝ ፍላጎት ጨምሯል ። በፊት ላይ ያለንበት የኑሮ ደረጃ በጣም የተለያየ ስለነበር የሆነ የሆነ ልክ ያልሆነ ነገር ነበር ምክንያቱም እኔ በፊልም ላይ ያለ ህይወት አልመኝም እያልኩ ነበር ራሴን የማሳምነው ። አንዲት ቆንጅዬ የሀብታም ልጅ ልዕልት የደሀውን ልጅ ወደደችው ከዛ ልዑል አደረገችው ..... ብቻ የማይሆን የምለውን ታሪክ እንድኖረው ፈቀደልኝ !!! እሷእንዲህ ደስ የሚል ውጤት አምጥታ በዛ ላይ ለኛ ቅርብ በሆነ ዩንቨርስቲ መግባቷ ምናምን በጣም ደስ ይላል ግን እሷን ሳላይ መቆየት ደባሪ ያረገዋል ። ግን ሳስበው ደግሞ ተራርቀን ሁለታችንም የራሳችንን መስመር መያዝ አለብን ብዬ ስለወሰንኩ እንድትሄድ ገፋፋዋት ። ከዛም ከሳሚ ጋር ጊቢ ድረስ አደረስናት ። የሀብታም ልጅ ናት መቼም ያልገባ እቃ የለም !! ከሁሉም ጋር እንድትግባባ ነገርናት ። ደስ የሚለው በአምስት ቀን ቆይታችን ስለ ጊቢ ህይወት በትንሹም ቢሆን ተምራለች። ከዛን ቀን ቡሀላ አላማዬን ለማሳካት ወስኜ ተነሳሁ ። ሳሚ እንዳለው በሁለት ወር ለመቀየር አሮጥኩም ። ስራውን የበለጠ ስረዳው ደግሞ በጣም ቀለለኝ የስራ እድገትም አገኘው በጣም ደስ ይል ነበር !!! ማያን አልፎ አልፎ አያታለሁ ሆዷ ከገፋ ሁለት ቀን አይቻታለሁኝ !!! ልዕልቷ ጋር ደግሞ ሲመቸን ከሳሚ ጋር እየሄድን አይተናት እንመጣለን ! እንደዛ እያረግን ህይወትን ቀጠልናት ከስድስት ወራት ቡሀላ ግን .......... . . ይቀጥላል ክፍል4⃣2⃣ 
211
4
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 4⃣0⃣ ....... የእኔንና የሷን ውጤት አየሁት ። ጭራሽኑ አልጠበኩትም ነበር !!!!!! ልዕልቷ ነቅንቃዋለች ከሰባት መቶ ስድስት መቶ ሀምሳ ዘጠኝ ነበር ያመጣችው !!!! ከሷ በላይ ደግሞ እኔ አልፌ በዛ ላይ አምስት መት አንድ ማምጣቴ አልዋጥ አለኝ ። አንዳንዴ ከመከለስ ውጪ ስራዬ ብዬ እንኳን አጥንቼ አላቅም ?? ያው አንብቦ የመረዳት ችሎታ ስላለኝ መሠለኝ ያን ያህል አልከበደኝም ነበር ! የልዕልቷ ውጤል በጣም ደስ ይላል ወዲያው ለእናቴ ነግሪያት በዛ ምሽት ወደነሱ ቤት ሄድኩኝ ። የሚገርመው እኔ በዛ ምሽት  እየበረርኩ ሄጄ እነሱ ገና ውጤት ለማየት ሲዘጋጁ ነው የደረስኩት ። ገና በሩን እንደከፈተችው ጥምጥም ብዬ አቀፍኳትና ከልብሽ ነው ያኮራሽኝ !!! ብዬ አቀፎኳት ። ከዛም ወደ ውስጥ ገባንና ያመጣችውን ውጤት ስነግራቸው ልዕልና ባለማመን ጮኸች ሳሚ ኮራ ብሎ ፈገግ አለ !! ከዛም በደስታ ሁላችንንም አቀፍናቸው ። የሚገርመው እሷ በራሷ እውቀትና ልፋት ባመጣችው ውጤት ሳሚ ወደኔ ተጠግቶ " ያንተም ዋጋ ነው !" አለኝ ። ግራ ገብቶኝ ማለት ?? አልኩኝ ። ልዕልና ቀደም ብላ " በጣም ተስፋ ቆርጬ ነበር እኮ እናቴን ጥዬ አልሄድም ብዬ ማጥናትም አቁሜ ነበር አንተ ግን ከፈጣሪ ቀጥሎ ለዚህ አበቃኸኝ " አለችኝ ። ሳሚም ቀጠል አድርጎ " ስንቱ ወንድ አላማዋን ሊያስታት ሲሞክር ነበር ሁሉም የሚፈልጋት ለሌላ ነገር ነው ሁሉም ትምህርቱን ተይውና ላግባሽ ነው የሚሉት አንተ ግን ነግራኛለች አሪፍ ውጤት ከሷ እንደምጠብቅና ካመጣች እንደምትሸልማት ነግረህ አበረታሀት ተስፋዋን አበዛክኩክኝ የምር አንተ በጣም ልዩ ልጅ ነህ !!!!" አለኝ ። እውነት ለመናገር ደስ ብሎኛል እንዲህ መባልም ለኔ ኩራቴ ነው ደስ ብሎኛል !!!! እሷም በጣም ደስ ብሏት ነበር !!!! የምትሆነው አታ ነበር ሁላ !!! ቀጥሎ ደግሞ እኔ የማያን ውጤት ማወቅ ተመኘው ግን በዛ ሰአት አልችልም ። ደስታችንን መቋጨት ነበረብኝና ደስ ስላለኝ ለመናገርና ላቅፋት ስለፈለኩ ነው የመጣሁት ወደቤት ልሂድ በቃ አልኳቸው ። ሳሚም እኔ ነኝ የማደርስክ ብሎ ቤቴ ድረስ አደረሰኝ ። ከዛ ቀን ጀምሮ ህይወቴ እየተስተካከለ መጣ ። ጠዋት ስነሳ ራሱ በደስታ ተሞልቼ ነው የምነሳው በቃ ምን ልበላችሁ ። ስራዬን ደስ በሚል ሁኔታ እየሰራሁ ህይወቴን ቀጠልኩ ። ደስ በሚል ሁኔታ አንድ ሳምንት አስቆጠርኩኝ ። እንደሁሌው እሁድን በለሊት ስፖርት ቤት ሄጄ ሰርቼ ቤት መጣሁና ታጥቤ ወደ ቤተክርስቲያን ሄድኩኝ ። ተሳልሜ ፀልዬ ስመለስ በሩ ላይ ማያን አገኘዋት ። ፊቷን ሳይሆን ሆዷን ነበር ቀድሜ ያየሁት?? ግን ሆዷ ምንም አልገፋም ? ለነገሩ ገና በአንድ ወር ምን ጠብቄ ነው አይ የኔ ነገር ። እሷ አይታኝ እንዳላየ ለማለፍ ስትሞክር ባያትም ግን እኔ ሮጬ ደረስኩባትና ምንም እንዳልተፈጠረ ሰላም አልኳት ። ከዛም ደህንነቷን ከጠየኳት ቡሀላ ውጤቷን ጠየኳት ። " 602 ነው ምንሞ አይልም አይደል ? " አለችኝ ። አንዳንድ ልዩነቶች ስላሉ እንጂ ጎበዝ እንደሆነች አውቃለሁ ። እንዴ በጣም አሪፍ ነው እንጂ የት ዩንቨርስቲ ቢደርስሽ ደስ ይልሻል ? አልኳት ለማወቅ ጓጉቼ " አረ እኔ አልሄድም አትማሪም ብሎኛል ከቤት እንድወጣም አይፈልግም ?!" አለችኝ ። ለዚህ ነበር የተቃረንኩት በራሷ እንዳትተማመን ያግዳታል ይሄ !!!! በራሷ ሰርታ ብትለወጥ ምን ነበረበት ኤጭ !!!! እሷን ላለማስከፋት ግን አንቺ ምን አለብሽ ቁጭ ብለሽ ብዬ ምናምን ብዬ እየተቃለድን  አብረን ሄድን ሰፈር ድረስ ከዛ እሷ ወደ ሀብታሞቹ መንደር እኔም ወደ እናቴ ጎጆ ተቀነጠስኩኝ ። ቤት እንደገባሁ  ለእናቴ ሁሉንም ነገርኳት እሷም አዝናላታለች ግን የኛ ውሳኔ አይደለምና ዝምታን መረጥን !!! ከእናቴ ጋር ደስ የሚል ውሎ ሆነልኝ ከልዕልቷ ጋርም እያወራን ቀኑን አሳለፍን ። በቀጣዩ ቀን እንደሁሌው ፏ ዝንጥ ብዬ ከቤት ወጣሁኝ ። እንደዛ ለብሼ ስታይ እኮ ከዛ ጊቢ የምወጣም አልመስልም !!! የለውጥ ጉዞ ሲጀመር ነው መሠለኝ ቤቴን እየጠላዋት መጣሁ ። ስንት አመት አዘንብላ ሳትወድቅ ያሳደገችኝን ቤት እየሰለቸዋት ይመስለኛል ። ስራ ከጀመርኩ ከሳምንት ቡሀላ ነው እንግዲህ ወደስራ ለመሌሄድ ከቤት ስወጣ በር ላይ አባቴን አገኘውት ። አየኝና ግን ሳያውቀኝ ዝም ብሎኝ እንደማለፍ አለና መለስ ብሎ አፉን እያሻሸ " የኔ ልጅ ነህ እንዴ ?" አለኝ ። ሳይጠጣ  አይመጣ መቼስ አይ የኔ አባት ። " ምንድነው  የት ልትሄድ ነው ማነህ ለምን እንዲህ ለበስክ ከየት አመጣህ ?? " ብሎ የጥያቄ ናዳ አወረደብኝ ። አባዬ እኔ ስራ ጀመርኩ እኮ በቅርቡ ህይወታችንን ቀይረዋለሁ ደርሼላችዋለሁ እሺ !! አልኩት ። በፈጣሪ ስም የኔ ጠንካራው የኔ ኮስታራው ሰው የማይቀርበው ድንጋይ ልብ የሚባለው ሰው ምን እንደነካው አላውቅም ገና እንደዛ ከማለቴ ከየት እንደመጡ የማላቃቸው እንባዎች በአይኔ ላይ እንደጉድ ወረዱ ። ስቅስቅ ብሎ ማለቀስ ጀመረ ። ደንግጬ ወደሱ ቀርቤ አባዬ ምነው ምን ሆንክ ??? አልኩት 🥺🥺 በህይወቴ ከአባቴ አይን እንባ እንዳዛ ሲወርድ አይቼም አላውቅም !!!! " እኔ አንተን ከመውለድ ውጪ ምን አረኩልህና ልጄ ??? ለምን አሁንም አባዬ ትለኛለህ ?? ለምን አሁንም የኔን ህይወት ለመቀየር ትለፋለህ ?? ዘላለሜን አንድ ደህና ነገር ሳላደርግ ልሞት ነው አይደል ??? " አለ ። ሳላስበው በማልፈልገው ሰአት አስለቀሰኝ ። ከዛም ወደሱ ቀርቤ ከልቤ አቀፍኩት ። " እረፍ እረፍ ከኔ ራቅ " ብሎ ከእቅፉ አስወጥቶኝ ወደዃላ ሸሸ ። ለምን ?? አልኩት መልሼ እየቀረብኩኝ ። " አይ አይሆንም እኔ ቆሻሻ ነኝ እኮ ልብስክን አቆሽሽብሀለሁ ከኔ ራቅ " አለኝ ። የሆነ ነገር ቢያገኝ ለኛ እንደሚያረግልን አውቃለሁኝ !!! ግን ትንሽ ብር ይሰራና በዚህ ምን ላርግላቸው በሚል ሀሳብ ይመስለኛል እንደዚ የሆነው !!!!! እንደዛ ሲለኝ ራሴን መቆጣጠር አቅቶኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩኝ ። ወዲያው ሳሚ መጣ ። ሁለታችንም ስናለቅስ የተመለከተው ሳሚ ደንግጦ በፍጥነት ወደኔ መጣና " ምንድነው ልጄ ችግር አለ ምን ሆነሀል ?" አለኝ ። እሱ ልጄ ሲለኝ የአባቴ ፊት ላይ ህመም አየሁ !!!! ሳሚ አባቴን አያውቀውም እኔም ኮራ ብዬ እንባዬን እየጠራረኩኝ አባቴ ነው ሳሚ ተዋወቀው አልኩት ። ሳሚ መቼም ሲሳሳት አይቼው አላውቅም ይለያል  !!!!! ቶሎ ብሎ ወደ አባቴ ሄዶ እጁን ዘረጋለት ለሰላምታ ። አባቴ ግን ሊመልስለት ፍቃደኛ አልሆነም የሱን ያደፈ ያረጀ ልብስና የተሰነጣጠቀ እጅ ተመለከተና ሳሚን አይቶ ራሱን ከሱ አንድ እርምጃ አራቀ ። የኔ አባት !!!!!! ገንዘብ አንዳንዴ ....... ሳሚም የበለጠ አባቴን ቀረበና " እኔ ከሚኪ  አለቃ አንዱ ነኝ ግን የትንሽ  ትልቅና አስተዋይ ልጅ ወልደሀል ልትኮራ ይገባካል !!! ለኔ እንደጓደኛዬ ነው ። ሳሚ እባላለሁ "ብሎ ደግሞ እጁን ዘረጋለት ። ........... ላይኩ 100 ከሞላ አንድ ክፍል ይጨመራል . . ይቀጥላል ክፍል4⃣1⃣
181
5
#SHARE #LIKE
222
6
ከዛ ነፈጠነ ተነስቼ ታጥቤ ለባብሼ ቶሎ ወጣሁና ከዛ ሰፈር ይዣት ጠፋሁ ። ከዛ አብረን ስንዞር ዋልን ። ከሷ ጋር ሲሆን ቀኑ ቢሮጥም ደስ ይል ነበር የማይሰለች ቀን ነው ያሳለፍነው !!! ከዛም ወደቤት ስመለስ የእናቴን ሽሮዐበልቼ ለጥ ። እንደምንም የማይደርስ የለ ቀኑ ደረሰልኝ ሰኞ ቀን ለሊት ተነስቼ ጂም ደርሼ ተመለስኩና ሻውር ወስጄ በስልኬ በተማርኩት መሠረት ፅድት ብዬ ለብሼ ሳሚን መጠበቅ ጀመርኩ ። እናቴ ቤቱን ፏ አድርጋ አሳምራ ቡና አፍልታ ነው የሸኘችኝ ። እኔ ግን ግፌ በስመአብ ስንት ነገር ማረጉ  እያለ ጭራሽ ደግሞ የግል ሹፌሬ አረኩት በሉት ብቻ ግን አማኑኤል ቤተክርስቲያን ደረስንና ተሳልመን በዛው ሄድን ። የመጀመሪያ የስራ ቀን በጣም ማራኪ ነበር ሁሉም ነገር ቀላል ነው በተለየሰ የኔ ስራ !!!!! ደስ የሚል ቀን ውለን ወደቤት ተመለስን ። ማታ ውጤት ለማየት ተዘጋጀን ። እናቴ አስቀድማ ስትፀልይ ነው ያመሸችው እኔ ደግሞ ከኔ በላይ የማያና የልዕልቷ ውጤት ያሳስበኛል ። እንደምንም ሰአቱ ሲደርስ የልዕልትን ኮድ አውቀው ስለነበር የእኔንና የሷን ውጤት አየሁ ........ . . ይቀጥላል ክፍል 4⃣0⃣
220
7
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 3⃣9⃣ ......... ያልጠበኩትን ነገር ነው ያየሁት ። በርግጥ ግድ ሊሰጠኝም አይገባም ግን ደግሞ እሱን እዛ ቦታ ላይ ማየት ለኔ ጥሩ ስሜት የለውም !!! እዛ እንደደረስን ሳሚ መጀመሪያ ሰላም ያለው የማያን ባለቤት አባት ነበር ???? ከነሱ ቤተሰብ ሙሉ በሙሉ መራቅ ነበር የኔ ፍላጎት ምክንያቱም እሱን ባየሁ ቁጥር ማያን አስታውሳታለሁ እሷን ሳስብ ደግሞ ለገንዘብ ብላ ማግባቷና በአንዴ ልጅ መፀነሷ ያናድደኛል!! ግን ምን አገባኝ ቆይ ???? እዛ ለትልቅ ስራ ልቀጠር ስሄድ የማስበው ነገር ይሄ መሆን አልነበረበትም !!!! " ተዋወቀው ሚኪያስ ይባላል " የሚለው የሳሚ ድምፅ ከገባሁበት ሀሳብ አነቃኝና ቀና ስል ሰውዬው እጁን ዘርግቷል ። ነገሮችን በማበላሸት በጣም ጎበዝ ከመሆኔ የተነሳ ራሴንም አላምነውም ማለት ይቻላል !!!! የዛኔ ነቃ ደንገጥ ብዬ ሰላምታ ተቀያየርኩኝ ። ከዃላ ከነበሩት ጋርም አስተዋወቀኝ ። አንዳንዴ መማር ምን ያደርጋል እልና ሳስበው ደግሞ መማር ያስከብራል ለካ !!! እኔም ምርጥ ባልሆንም ኢንግሊዘኛ ቋንቋ መቻሌ ግን በጣም ጠቅሞኝ ነበር !!!!! የሚያወሩት ይገባኛል እመልሳለሁም ። እንደሁሌው ምርጡ ሳሚ አላሳፈረኝም እኔን ፐርፌክት እይታ አላበሰኝ ። የሌለኝን እውቀት አጎናፅፎ አብራራኝ ። ኩል ሆኖ በመታየት ረገድ መቼም አንታማም እና ኮስተር ኮራ ብዬ ለመታየት ሞከርኩኝ  ተሳክቶልኛል !! ስለ ስራው እውቀት እንጂ ልምድ እንደሌለኝ ነግሯቸዋል ። የእናቴ " የሰው መውደድ ይስጥህ " የምትለው ምርቃት  በደንብ የተሳካች ይመሰል ሰዎቹ ትኩረት ሰተውኝ ነበር ። ፕሮቶኮል አጠባበቅ አሪፍ እንደሆንኩና ለስራው ብቁ እንደምመስላቸው ለሳሚ ሲነግሩት እየሰማሁ ሙቀት ለቀቀብኝ !!!!! ከዛም ፀሀፊዋ ጋር እንድጠብቃቸው ነግረውኝ ወደ መሠብሰቢያ ክፍል ገቡ ። ገና ቁጭ ከማለቴ ልዕልቷ ደወለች ። " ሄሎ " አለችች ቀስ  ብላ እንደተደበቀ ሰው ። ወዬ  ምን ሆነሻል ? አልኳት ምን ሆና ነው ብዬ ። " ስራ ላይ ከሆንክ ብዬ ነው እኮ " አለችኝ ። አይ አይደለሁም ባክሽ የምን ስራ ነው አልኳት ላናድዳት ፈልጌ " አልተሳም እንዴ ? ግን የራሱ ጉዳይ እሺ ምንም እንዳትጨነቅ ላንተ የተባለው ስራ ስላለ ነው እሺ ሚኪ ቶሎ ኑ በቃ አሁን የት ናችሁ ??" አለችኝ ። ሳታዳምጠኝ ብዙ ስታወራ አሳቀችኝና ራሴ ላይ እንዳላሟርት እየተሳቀኩኝ አዎ ጀባሪ ነው በቃ ከሳሚ ጋ እየመጣን ነው ቻው ብዬ ስልኩን ዘጋሁባት ። ከዛም ስልኬ ላይ ያወርድኳቸውን የሷን ፎቶዎች እየተመለከትኩ እየተመሣሠጥኩ እያለ ስራ ልቀጠር መሆኑ ትዝ አለኝ መሠለኝ ከሷ ወጥቼ ሰዎቹ ስላወሩት ነገር ማሰላሰል ጀመርኩኝ ። ከዛም ስልኬ ላይ ሰርች እያረኩ ማየት ጀመርኩኝ ። ለትምህርት ፍላጎት የለኝም እንጂ ብሞክር እንደምሰራ አውቀዋለሂኝ በደንብ !!!! እናም እያየሁ ሳላስበው አርባ ደቂቃ ቆይተው ነበር ። ሲጨርሱ ሲመጡ እኔም ስልኬን አስገብቼ ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ ። እነሱም ለስራው በጣም ሰው እንደሚያስፈልጋቸው ሳሚ እንደነገራቸው ከሆነ ለስራው ብቁ ነው ብለው እንደሚያስቡኝና ፍቃደኛ እንደሆኑ ቀጣይ ሰኞ ስራ እንድጀምር ነግሮ እጁን ዘረጋ ። በጣም ደስ ብሎኛል አቅፌ ሁሉንም ብስማቸው ደስ ይለኝ ነበር ግን ፈገግ ብዬ አመሠግናለሁ አልኳቸው ። ከዛም ከሳሚ ጋር ተያይዘን ወጣን ። ከዛ ሰፊ ጊቢ እስክንወጣ ዝም አልኩኝና ልክ መኪና ውስጥ ስንገባ ከልቤ አቀፍኩት !!!! አመሠግናለሁ አልኩት ያንሰዋል። ፈጣሪ በሱ በኩል ህይወቴን እያስቸካከለልኝ ነው ። ለእናቴ እንደደረስኩላት ተሰማኝ !!!!! ከዛም በደስታ እየቦረኩኝ ወደ ቤት ሄድን ። በሩን ገና ነካ ስናረገው ቆማ ስጠብቀን የነበረችው ልዕልቷ ቶሎ ከፍታ አቀፈችኝ ። " ችግር የለም እሺ አባ ሌላ ስራ ይፈልግልሀል አ  " ብላ ሁለታችንንም በየተራ ተመለከተችን ። ነገሩ ግራ የገባው ሳሚ " ምን ሆነሻል ሁሉም ወደው ነው የተቀበሉት የተባረከ ልጅ " አለ ። ከዛ ሳላስበው ሳቄ አመለጠኝ ። ስቀልድ እንደሆነ ሲገባት እሪ ነው ያለችብን ። ደብሯቸው ይመጣሉ ብላ የሚገርም ምሳ ሰርታ ነበር የጠበቀችን ። ከዛም ወደ ቤት ለመሄድ ስለፈለኩ ለእናቴ ለመናገር ስለቸኮልኩኝ ልሂድ በቃ አልኳቸው ።  " ወዴት ?? " አለች ልዕልና ቀደም ብላ ። ወደቤት መሄድ አለብኝ ብዬ ገና ሳሚን ለማመስገን ከተቀመጥኩበት ስነሳ " አይ ወደቤት መሄድ አትችልም !" አለኝ ሳሚ ። ግራ ገብቶኝ ደንግጬ  ማለት ? አልኩት ። " ቀድመን እኔና አንተ መሄድ ያለብን ቦታ አለ ብሎኝ ተያይዘን ወጣን ። ከዛም ወደ ሀብታሞች ልብስ መግዣ ቤት ሄድን ። ከዛ በጣም የሚያማምሩ ሱፍ ልብሶች ገዛልኝ ። ምክንያቱም እዛ ቦታ ላይ ፅድት ያለ አለባበስ ግዴታ ስለነበረ ነው ። ሳሚ ግን ከልክ ያለፈ ደግነት ይሆን የልጁ የወደፊት  ባል መሆኔን ታውቆት ባላውቅም ብቻ ግን ከልክ በላይ እያደረገልኝ ውለታ እየዋለልኝ ነው !!!! በጣም ብዙ ብር ነው ያወጣው ግን ደግሞ ምንም አልመሠለውም!!!! ከዛም በራሱ መኪና ወደ ቤት አደረሰኝ ። የሚገርመው እኔ የእነሱን ቤተሰብ ተቀላቅዬ ራሱ አንድም ቀን ግቡ ብያቸው እንኳን አላውቅም ። ለነገሩ ሳስበው የማለት ድፍረትም አይኖረኝም !!!!! ብቻ ግን እንደሁሌው በር ላይ አድርሶኝ ሊመለስ ሲል እማ ብቅ አለች ። ገና ስታየው በራ መታ አገላብጣ ሰላም አለችው ። ከዛ እማ ስራው እኮ ተሳካ ሳሚ ስራ ሊያስቀጥረኝ ነው ልጅሽ አደኩልሽ አልኳት በፈገግታ ተሞልቼ ። የኔ ህልሞ ለእናቴ መድረስ እና እንደልቧ የምትገባበት ትልቅ ቤት መግዛት ነው ። ማሳካቴን ሳላውቅ በእቅድ ብቻ ደስታዬ ከመጠን በላይ ሆኗል !!!!! የኔ ደስተኛ እልልታዋን እያሟሟቀች እኔንም ሳሚንም ሳመችን ። " የኔ ልጅ በምን ቀን አንተን እንደተዋወቀህ አላውቅም እንደው አማኑኤልዬ ሲሰማው እንጂ " አለች ። እኔም እስማማበታለሁ በደንብ !!!! ከዛ እማ እንዲገባ ብትጋብዘውም እኔ ስላልፈለኩኝ አይ መሽቷል ምናምን ብዬ ወደቤት እንዲሄድ አደረኩ። ከዛም ቤት ኘብቼ ብርቅ ሆኖብኝ የገዛልኝን ልብሶች አስር ጊዜ እየለካሁኝ ለእማ ሳሳያት ሳወልቅ ስለብስ ቆየሁኝ ! ከዛም ካርድ ሞልቼ online ስገባ  ልዕልቷ ልብሱን ስሞክር ያነሳችኝን ፎቶዎች ላከችልኝ ። ከዛ ራሴን እያየሁ በትንሹ ተደሳሰትኩኝና ወደቀልቤ ተመልሼ እኔ ያንቺ ባል እያልኩ አሽኮርምሚያት ስናወራ ቆይተን ተኛው ። ቀጣዮቹ ቀናቶች አመት ነው የሆኑብኝ ። የሆነ ጎኔ ማድረግ እንደማልችል እያሰበ እየነገረኝ ውስጤ እንዲረበሽ ያደርጋል ። ከዛ ግን ቀላል ነው እያልኩኝ ራሴን እያሳመንኩ ቆየሁ ። ደግሞ የሚያስጨንቀው ስራ የምጀምረው ሰኞ ውጤት የሚወጣው ሰኞ ማታ ሆኖ ተገኘ እኔም ቀኑን እንደምንም መግፋት ጀመርኩኝ በቀጣዩ ቀን  ተኝቼ አራት ሰአት ምናምን ሆኗል ስልኬን ሳየው አምስት ጊዜ ምናምን ደውላለች ልዕልቷ ። ምን ሆና ነው ብዬ ልደውልላት ስል  እናቴ ቶሎ ብላ ወደኔ መታ " ተነስ ተነስ  ቶሎ ተነስ " አለችኝ ። ምነው እናቴ ምን ተፈጠረ አልኳት ደንግጬ ያቺ የምታሳሳው ልጅ የምታምረው ቆንጆዋ ልጅ በር ላይ ቆማለች ቶሎ በል " አለችኝ ክው ነው ያልኩት ። ምንም ድህነቴን ብታውቅ ራሱ ያቺ ሞልቃቃዋን ልዕልት እዚ ቤት ላመጣ አልችልም
188
8
በአንዴ የተግባቡት ልዕልናም መታ እስከ አንገቴ ድረስ የቆለፍኩትን ሸሚዝ መክፈት ጀመረች ። በጣም ቀርባኝ ነበር !!! እንኳን በዚህ ልክ ቀርባኝ ገና ሳያት የምታሳስት ልጅ ናት ። እዛ ቤተሰቧ ፊት ሸሚዜን ስትፈታ ግራ ገብቶኝ እጇን ያዝኩትና ቀና ብዬ ተመለከትኳቸው ። የዛኔ ሁሉም ከት ብለው ሳቁብኝ ። ሳቁን ሳይጨርስም " ልታስተካክልልክ ነው " አለኝ ሳሚ በመሀል በመሀል እየሳቀ ። ከዛም ትንሽ ደረቱ ጋር ከፈት አደረገችውና ኮቱንም አስቸካከለችልኝ ። ከዛም በደንብ ተመለከቱኝ " አያችሁ አይደል ምን አይነት ቆንጆ ባል እንዳለኝ " አለች ቅብጥ እያለች ። እኔ እያፈርኩ አይኔን መሬት ተክላለሁኝ !!!.ራሴን በመስታወት ተመለከትኩት ። የምርም አስጠሊ ሰው አይደለሁም ገንዘብ ውበት ይሰጣል እንዴ በጣም ቆንጆ ሆንኩ ? አልኩኝ በልቤ  ፈገግ ብዬ ። ከዛ ቶሎ ቶሎ ምግብ በላንና ቶሎ መኪና ጨራርሰን ልንወጣ ስንል ልዕልና ቀወጠችው ። " ምን ሆንሽ ? " አልኳት ደንግጬ " እኔስ "? አለች ። " አይ ልጄ ዛሬ አይሆንም ደግሞ ቶሎ ነው የምንመለሰው " አላትና ወጣን ። አንድ ላይ ስንታይ በስራ ስኬታማ የሆኑ ሁለት ወጣቶች ነው የምንመስለው ማለት ይቻላል ። ደሞ በጣም ኮራ ብዬ ነበር ስሄድ የነበረው ። በርግጥ ስላለመድኩት ልብሱም ጫማውም ነፃነቴን ነፍጎኛል ግን ኩል ሆኜ ለመታየት እየሞከርኩ ነበር ። የሚያሳዝነው ግን እዛ ስንደርስ በጣም እድለቢስ ነኝ መሰለኝ ያልጠበኩትን ነገር ነው ያየሁት !!!!!??????🥺🥺 ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣9⃣
160
9
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 3⃣8⃣ .......... ማለት አልኳት ግራ ገብቶኝ ። " እንዴ አጎት ልትሆን ነዋ እህትህ አደለው " አለችኝ ። ያምሻል እንዴ ምንድነው የምታወሪው የምን እህት የምን አጎት ?? አልኳት ኩስትር ብዬ ። ምንም ቃል ሳትናገር ሆዷን ማሻሸት ጀመረች ። በሰአቱ ላለማመን ይመስል ጠግባ ሆዷን እያሸች ነው ብዬ ባምንም ደስ ይለኝ ነበር ። እኔ ሁኔታውን ለመረዳት ያህል ማያ ምንድነው አልገባኝም ?? አልኳት ። " አልገባህም ወይስ ማመን አልፈለክም " አለችኝ ። የዛኔ ደስ የሚል ቀን እየጀመርኩ ስለነበር ክፉ ደግ ላለመነጋገር ብዬ ደህና ዋይ ብያት መንገድ ስጀምር " አርግዣለሁ " አለችኝ ። በፈጣሪ ስም ክው ነበር ያልኩት ። ምክንያቱም ፈተና ከጨረስን ራሱ ሁለት ወርም አይሆነን ከመቼው እንዳረገዘች አላቅም ??? ማመንም ከብዶኝ ነበር በጣም ደንግጫለሂ ግን የደነገጥኩት ማያ ገና በጣም ትንሽ ናት ለመውለድ አልደረሰችም እሱም እንዴት ጨክኖ ነካት ብዬ ተናደድኩኝ !!! ማርገዟን ማመን አልቻልኩም በሆነ መንገድ ደግሞ በሷም ተናድጃለሁኝ እና ዞሬ መልካም ልጅ ውለጂ ብቻ ብያት መንገዴን ቀጠልኩኝ ። እንደዛ አይነት ምላሽ ስላልጠበቀች ደጋግማ ስሜን ስጠራ ነበር እኔ ግን ዝም ብዬ ቀጥታውን መንገድ ሄድኩኝና እጥፍ ስል ቆምኩኝ ። ተናደድኩም ደነገጥኩም እሷን አርግዛ ማሰብ ከበደኝ !!! ለደቂቃዎች ቆሜ ካሰላሰልኩ ቡሀላ ለነገሩ ምን አገባኝ እኔ ደግሞ አግብታ ነው አ እንዴ ብዬ መንገዴን ቀጠልኩኝ ። የነ ልዕልና ቤት እስክደርስ ድረስ ነገሩን ማመን ከብዶኝ ነበር !!! እያሰላሰልኩት እንሱ ቤት ደረስኩኝ ። ሳንኳኳ ልዕልቷ ቶሎ ከፈተችልኝ ከተገናኘን ስለቆየን እንደናፈኳት እየነገረችኝ አንገቴ ስር ሽሽግ አለች ። እቅፏን ሳገኝ ሁሉንም ረሳሁት !!! እዛው ተቃቅፈን ቆመን እያለ ሳሚ ሲመጣ ደንግጬ ቶሎ ለቀኳት ። ሳሚም ፈገግ ብሎ ተመለከተኝና " የእናንተን ፍቅር  ማስቆም አልችልም እኔ አይደል " ብሎ ፈገግ አለ። ከዛም ወደ ውስጥ ገባን እንደሁሌው የሚገርም ቁርስ ከቡና ጋር ቀራርቧል  ። ቁጭ ብለን ከሳሚ ጋር ማውራት ስንጀምር ልዕልና አሁን ካሁን አጠገቤ መታ ተቀመጠች ስል ቡናው ጋር ቁጭ አለች ። ግራ ገብቶኝ እያየዋት እያለ ሰላም መታ " ዛሬ ለሚኪ ቡና ካላፈላሁ ብላ ሳምንቱን ሙሉ ስትለማመድ ነበር " አለች እና ሰላም ብላኝ ቁጭ አለች ። አቀማመጧ ስርአቷ ምናምን በቃ ምርጥ ናት ብቻ ፈጣሪ ምን አርጌለት በዚህ ልክ እንደሚክሰኝ አላውቅም !! ሳሚ ለአስቸኳይ ነገር እፈልግሀለሁ ብሎ ስላመጣኝ በሰላም ነው የፈለከኝ ታዲያ ? አልኩት ከተቀመጥን አይቀር ብዬ ። " ለአንተ አሪፍ እድል ይሆናል ብዬ ስላሰብኩኝ ነው ፈጣሪ የሚልክልክን ቻንስ እንዳታባክን አስበክ መልስልኝ " አለኝ አስቀድሞ ። ባህሪዬን በደንብ የተረዳው ይመስለኛል ። እሺ ምንድነው ? አልኩት ። " እንግዲህ ውጤት ቢመጣም ዩንቨርስቲ መሄድ እንደማትፈልግ አውቃለሁኝ ። አንተ ደግሞ በራስክ ለፍተክ ማግኘት ነው የምቶፈልገው ስለዚህ እኔ ስራ እንድትገባ አመቻችቼልካለሁኝ ምን ታስባለህ " አለኝ ። ደቂቃዎችም አልፈጀብኝም በደስታ ነዋ ሳሚ ቀጣም ስራ ያስፈልገኛል በጣም !!!! እንደውም ፈልግልኝ ልልክ እያሰብኩኝ ነበር እኮ አልኩት ። በመልስ ተደስተዋል ሁሉም እና እንቢ እንዳልላቸው ፈርተው ነበር መሠለኝ ። ቡና ጠጥተን አወራን እና አመሻሹ ላይ ወደቤት ተመልሼ ፍልቅልቅ እያልኩ ስራ ማግኘቴን ነገርኳት ። ሌላ ጊዜ ብነግራት ልትሆን እንደምትችለው አልሆነችልኝም ደስ ይላል የኔ ልጅ ፈጣሪ ይርዳክ አለችኝ ። እማ ምነው ??? አልኳት ። " ልጄ የማወራክ አለ ቁጭ በል " አለችኝ ። ፊቷ ልክ ስላልነበር ደንግጬ ቁጭ አልኩኝ ደንግጬ ነበር ። እግሯ ስር በርከክ ብዬ እናቴ ምነው የተናደደ ፊት ነው ያለሽ አልኳት ግራ ገብቶኝ ። " አዎ ጨንቆኛል ልጄ ራሴን እየወቀስኩ ነው አንተም ስትሰማ እንደምትናደድ እርግጠኛ ነኝ " አለችኝ ። በፈጣሪ ስም በዛች ቅፅበት አይምሮዬ ስንት ነገር አሰበ  ምን ተፈጠረ  አባቴ ምን ሆነ ብዬ መጨነቅ ጀመርኩኝ። ቆይ ለምንድነው ራስሽን የምትወቅሺው ምን አረግሽ አልኳት እንድትነግረኝ ብዬ ። ኀ" አላቅም ልጄ ሰርካለም ደስ ብሏታል እን ግን ማስቆም እንደነበረብን ይሰማኛል በልጅነት መውለድ ከባድ ነው ማያ ያንተ ታናሽ ሆና በሆዷ ፅንስ ተሸክማለች " አለችኝ ። ብዙ ነገር አስቤ የማቀውን ነገር ስትነግረኝ ቀለል አርጌው ከእግሯ ስር ተነስቼ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጥኩኝ ። የኔ የዋህ  ተናድጄ መስሏት " ልጄ  አንተ ሞክረሀል እንዳትናደድ " አለችኝ ። እማ እኛ ስለሌላ ሰው ህይወት መጨነቅ ያለብን ሁኔታ ላይ አይደለንም !!! ፈልጋ ላረገዘችው ለምን አንቺ ራስሽን ትወቅሻለሽ እናቴ እ ??? በሰላም እንድትወልድ ፀልይላት አለቀ አንቺ ከሷ አንሰሽ አይደል የወለድሽኝ !!! አልኳት ። " አውቀሀል " አለችኝ በግርምት እያየች ። ሳሚ ጋር ስሄድ አገኘዋትና ነገረችኝ ከዛ ሰላም ተገላገይ ብያት ሄድኩ ። አሁን እኔ ህይወታችንን ለመቀየር እድል ተሰጠኝ እያልኩሽ በሷ ተጨንቀሽ ለኔ አለመደሰትሽ አናዶኛል አልኳት ። ከዛ ይቅናህ ብላ አቅፋ አባበለችኝ ። እኔ የሷንና የልዕልናን እቅፍ ሳገኝ ንዴት ይበርዳል ችግሬን ረሳዋለሁኝ !!!! አረጋግታኝ ራት በልተን ተኛን ። በቀጣዩ ቀን አላደርስ ያላት ልዕልና በለሊት ደውላ ቀሰቀሰችኝና ዘንጬ እንድመጣ ነገረችኝ ። ሳሚ ስራ ቦታ ወስዶ ሊያስተዋውቀኝ ስላሰበ ነበር እንደዛ ያለችኝ ። እኔም የደሀ ቅንጡ በኔ ቤት በውድ የገዛዋትን ልብስ ለባብሼ የእሜይን ምርቃት ተቀብዬ መሄድ ነዋ !!! እዛ ስደር ቀድማ ያገኘችኝ ልዕልና ፊቷን ቀየር አድርጋ እየተመለከተችኝ " ሚኪ ሰአት ደርሷል እኮ ገና ልብስ ልትቀይር ነው ? " አለችኝ ። ከፍቶኛሎም ግን አሳቀኝም ። ያለኝን ነው እኮ ለብሼ የመጣሁት አልኳት ። ደግነቱ ወዲያው ሳሚ መጣ ። ከዛም " ኑ ግቡ እንጂ ልጆች " አለ ። ነፃ ልጅ እኮ ናት ረስታዋለች ሁላ ወዲያው እጄን ይዛኝ ወደ ውስጥ ገባን ። አስተዋዩ ሳሚም ይዞኝ ወደ ክፍሉ ሄድን ልብስ አዘጋጅቾልኝ ነበር ለዛውም የሀብታሞቹን ሱፍ ልብስ !!!!! ምንድነው ?  አልኩት ግራ ገብቶኝ ። " ቶሎ ልበስና እንሂድ " ብሎኝ ከክፍሉ ወጣ ። እንዴት እንደምለብሰው ያን ያህል እውቀቱ ባይኖረኝም ዝም ብዬ መልበስ ጀመርኩ ሸሚዙን ቆልፌ ከላይ ኮት ደረብኩኝ ካልሲ እስከ ጫማው አዘጋጅቶልኛል !!!! ሲጀመር ሳሚ ይለያል ። እኔ ሰው በዛ ልክ ጥሩ ይሆናል ብዬ አስቤም አላውቅም !! ከእናቴ ውጪ የዋህ ያለም አይመስለኝም  ሁላ !!! ከዛ ለባብሼ ስወጣ ሁሉም ተሰብስበው እየጠበቁኝ ነበር ። ልዕልቷ ገና እንዳየችኝ አፏን ይዛ አየችኝና " እንዴት እንዳማረብክክክክ " ብላ በግርምት ተመለከተችኝ ። በየተራ ሁሉም አደነቁኝ !! ከዛ ሰላም ቀስ ብላ ልዕልናን ተመለከተቻትና " ደረቱ ጋር የወጣቶች አይመስልም " አለቻት ....
185
10
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 3⃣7⃣ .......የተጠቀለለ ነገር ሰጠኝ ። ምንድነው አልኩት ከፍቼ ከማየቴ በፊት " እየዋ " አለች ልዕልና ፍልቅልቅ እያለች ነበር ። ሳስበው የመጀመሪያ ስጦታውን ታውቀዋለች መሠለኝ አስክከፍተው ቸኩላ ነበር ። እኔም ፈገግ ብዬ ከፈትኩት ። በህይወቴ ኖሮኝ ከማያቀው ነገርች አንዱ ስልክ ነበር የሰጠኝ ። አስታውሳለሁ ትምህርት ቤት ሴቶቹ ስልክ ሲጠይቁ የለኝም ስላቸው ሁም ጢባራም ኩራቱ ላለመስጠት እኮ ነው ሲሉ ዝም ብዬ ፈገግ ብቻ ነበረ የምለው ። እኔ እንደዛ ትልቅ ስልክ ስይዝ የመጨረሻዬ ነበር ሁላ ቀድማ ያወቀችው ልዕልናም በደስታ ስትፈነጥዝ ነበር ። " ላንተ ከዚ በላይ ይገባሀል ግን በዚህ ስልክ እንደምትሰራበት እርግጠኛ ስለሆንኩ ነው ጊዜው የቴክኖሎጂ ነው እናም ብዙ የገሮችን ትማርበታለህ " አለኝ ። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር !!! ከሰው ምንም ነገር መቀበል ባያስደስተኝም ግን በሰአቱ በህይወቴ የተሰጠኝ የመጀመሪያ ጠቃሚ ነገር ነው !! ምክንያቱም በጣም ያስፈልገኛል በትምህርቴ ደካማ ባልሆንም ምንም አይነት ውጤት ቢወጣ ጊቢ እንደማልሄድ ግልፅ ነገር ነው ስለዚህ አንዳንድ ነገሮችን እመራመርበታለሁ !!! ሳሚን ከልቤ አመስግኜ ከማቀፍ ውጪጨየማረገው ነገር የለም!!! በዛ ስጦታ እየተደሰትኩ እያለ ሳሚ ፈገግ ብሎ " እንግዲህ ሁለተኛው ስጦታ .." ብሎ ወሬውን ሊቀጥል ሲል ልዕልቷ ጣልቃ ገብታ " አባቢ እኔን የሚመለከተውን አስቀድም በእናትህ !!!!" አለች ለመስማት እየጓጓች ። ምን ሊለኝ እንደሆነ አላቅም ዞር ብሎ ሁሉንም በየተራ ተመለከተና " እንግዲህ እኔና ሰላሜ ተመካክረን ነገሮችን አይተንና ቃኝተን አንድ ነገር አሰብንጨ...." ብሎ አጓጉቶን ንግግሩን አቆምን ። ቀጥል በሚል ፊት ሁላችንም ተመለከትነው ። ከዛም " እንግዲህ ሁለታችሁም ጋር ያለውን  ተመሳሳይ ስሜት እና የተለያዩ ድርጊቶችን አይተን ሳትሳቀቁ ፍቅራችሁን እንድቀጥሉ ፈቅደንላችዃል ያ ማለት ልጄን አደራ እየሰጠሁክ ነው ስለምተማመንብህ !!!" አለኝ ። በጭራሽ እንደዛ ይላል ብዬ አልጠበኩኝም!!! ለመስማት እንደዛ ስትቁነጠነጥ የኘበረችዋም የሳሚ ንግግር አሳፈራት መሠለኝ አንገቷን ደፍታ ዝም አለች ። ሁኔታዋን ያስተዋለው ሳሚም ወደራሱ ስቦ አቀፋት ። እንግዲህ ከሁለት ሰው አንደበት ምንም ቃል ሳይወጣ እንኳን ለነሱ እርስ በርስም ሳንነጋገር ሁሉም ተረድቷል ከእናቴ ውጪ ። ሁኔታው ባይገባትም ግን በኔ ሁሌም እንደኮራችብኝ ነውና ዝም ብላ ፈገግ ብላ ታየኛለች !! " በዚሁ የመጨረሻው ስጦታዬ እንግዲህ ለቤተሰቦችክም ጭምር ነው ። ይሄን ደሞ ሁላችንም አውርተኖበት የተቀበልነው ነገር ነው ። እንግዲህ በትንሹም ቢሆን ታቀናለህና ሰው እንደምንወድ መረዳት አይከብድህም እናም እናንተ አብራችሁን እንድትኖሩ እንፈልጋለን ። አባትህም በፈለገው ሰአት መምጣት ይችላል እናትህም የተሻለ ህይወት ይገባታል ለፍታለች ስለዚህ ዛሬውኑ እቃችሁን ማስመጣት እንችላለን " አለኝ ። ሲሰጥ ከልቡ ስለሆነ ፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ የማይፋቅ ነው !!! ግን እኔ የሚጠብቀውን ምላሽ አልሰጠሁትም !!!! ጥገኛ መሆን አንፈልግም !!! ነበር ያልኩት ። ደሀ እኮ ችግር አለብን !!! አጉል ክብር ክብር እያልኩ መሠለኝ የሆነ አለ አ ልርዳህ ያለኝ ነው የመሠለኝ !!! ምን እንዳናደደኝ አላቅም እሱ ሊረዳኝ በሞከረ እኔ በሰአቱ ሳላስበው ብዙ የማይመስሉ ነገሮችን ተናገርኩኝ !!! ሳሚ ይለያል የምለው በምክንያት ነው ልዕልናና ሰላም በማይሆን ፊት ማየት ሲጀምሩ ሳሚ ግን ረጋ ብሎ ቁጥብ ፈገግታ እያሳየኝ " አየክ አይደል እኛ ወንዶች በራሳችን ላብ መኖር ነው የምንፈልገው አይደል ቶሎ ተቀብለከኝ ቢሆን ደካማ ወጣት ነህ ብዬ አስብ ነበር " ብሎ ነገሩን እኔም ባላየሁት መንገድ አይቶ ሁኔታዎችን አረጋግቶ ሰላም አወረደ ። ልዕልቷም እሱ እንዳለው ነው ብላ ተቀይሮ ይቀይረኛል ብላ አስባ ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ ። ለሳሚ ቃል የለኝም እነሱ ተሰብስበው እዛው ሲቀመጡ ሁለታችን እንደ ወንድ ገንጠል ብለን ማውራት ጀመርን ደ ረጅምምምም ሰአት አወራን ። እኔ እንደሱ መሆን እንደምፈልግ ነገርኩት እሱ እንደኔ አይነት ልጅ መውለድ እንደሚፈልግ ነገረኝ !!!! ብቻ ደስ የሚል ቀን ነበር ። ከዛም እየመሸ ስለመጣ ሳሚ መኪናውን አወጣና ቤት ላድርሳችሁ አለን ። እኔና ልዕሉ ከዃላ እናቴና እሱ ጋቢና ሆነን ወደቤት መሄድ ጀመርን ። ከዛ ልዕልና ስልኬን ተቀብላኝ የራሷን ስልክ ሚስቴ ❤ ብላ ሴቭ አረገችው ቴሌግራም ከፍታም ገብታ ወደራሷ ሀይ ብላ ላከች ። ሳሚ ሁሉንም ነገር አዘጋጅቶና አሟልቶ ነው የሰጠኝ የተባረከ ሰው !!!!! ከዛም በር ላይ አድርሰውን ተመለሱ ። ቤት እንደገባን እናቴ ማልቀስ ጀመረች ። ክው ብዬ እማ ምንድነው ምን ሆንሽ አልኳት እግሯ ስር ተንበርክኬ ። " ልጄ የኔ ልዑል ላንተ የሚገባህን ህይወት አሎሰጠሁክም ይቅርታ አርግልኝ እባክህን በኛና በነሱ መሀል ያለውን ልዪነት ሳይ ከፋኝ አንተንም እንደኩዮችህ ማረግ አልቻልንም !!" አለችኝ ። የኔ እናት ጥምጥም ብዬ አቀፍኳት ከዛም ሁሉም እንደሚቀየር እየነገርኳት ልብሳችንንም ሳንቀይር ተኛን ። እኔ ስልክ ብርቅ ሆኖብኛል ልተኛ አልቻልኩም ። ከዛም ቴሌግራም ስገባ ከልዕልና በጣም ብዙ ፎቶ ተልኮልኛል ። የሁለት መቶ ብር ካርድ አለው ዳታ አብርቼ ሳይ መቼ እንዳነሳችኝም የማላቃቸው ብዙ ፎቶዎች ተመለከትኩኝ !! ከኔ ቀድሞ ስሜቱ እሷ ጋር እንደነበር አሰብኩኝ ደስ የሚለው ቤቴን ኑሮዬን ድህነቴንም አይታ አንዳች የተቀየረ ፊት የላትም !!! ሳስበው ኑሮዬ እናቴ በፊልም እንደምታየው ሊሆን ነው መሠለኝ !!!!!!🙄 ለተከታታይ ለአንድ ሳምንንት አካባቢ ከቤት አልወጣሁም ከልዕልና ጋር በስልክ እንጂ በአካል ተገናንተን አናቅም ! መቼም እኔ መመራመር እወዳለሁ ስልኬን ተመራምሬ ተረዳኋት በጣም ተላመድኩት ። አንዳንዴ እነ ሳሚ ቤት እየሄድኩ ቀሪውን ስልኬ ላይ እና ከእናቴ ጋር እያሳለፍኩ ውጤት እስኪመጣ መጠበቅ ጀመርኩኝ ። ቀኑ  ይሮጣል ውጤት የሚለቀቅበት ቀን እየደረሰ ነው ። ከዛም አንድ እሁድ ቀን ሳሚ ደውሎ እንደሚፈልገኝና ቶሎ ቤት እንድደርስ ነገረኝ ። እኔም ለእማ ነገርኳት ። እንደሁሌው መልካም እድል ብላ ሸኘችኝ !!!! እኔም ከቤት ወጥቼ መንገድ ከመጀመሬ ከማያ ጋር ተገጣጠምን ። ሰላም አልኳት ምንም እንዳልተፈጠረ ። ግን ሁኔታዋ ልክ አልነበረምና ግራ ገብቶኝ አዲስ ነገር አለ ? አልኳት ። ፈገግ ብላ " ወፈርኩብህ  " አለችኝ ።? ማለት ?? አልኳት መልሼ " እንኳን ደስ አለክ አጎት ላረግህ ነው " አለችኝ ማለት?????......... ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣8⃣
229
11
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 3⃣6⃣ .........ፊት ለፊቴ ያየዋትን ሴት ማመን አልቻልኩኝም ። ማናት እስከምል ድረስ የተቀየረች ውበቷ ተደብቆ የቆየች አንዲት ውብ ሴት አየሁኝ ። ልዕልና ካልሄድን ብላ ድርቅ ያለችው ቤት ልሂድ ስላት እንቢ ብላ የገጊችው ለካ ቀድመው አውርተውበት ነው ! እናቴ በሀበሻ ቀሚስ ዘንጣ ፀጉሯን ተስተካክላ በጭስና በማልቀስ የተጨማተረ አይኗን ተኩላ እንጨት በመፍለጥ የሰው ልብስ በማጠብ  የዛሉና የተፈገፈጉ እጆቿን የሚሸፍን ባይሆንም ጥፍር  ቀለም  ተቀብታለች ። ሳስበው እዚህ ምድር ላይ የማያምር ሰው ያለ አይመስለኝም ። ሁሉም ሲመቻችለት የተሻለ ሰው ነው የምሆነው ። እናቴን በደንብ አየዋትና የምር ግን  ገንዘብ ደስታ አይገዛም ብዬ አሰብኩኝ ??? ምን አልባት ጤናን አይገዛ ይሆናል እንጂ በደንብ ደስታን ይገዛል ብዬ አስባለሁኝ። ለነገሩ አንዳንዴ ከፈጣሪ ቀጥሎ ጤናንም ሊገዛ ይችላል ። መድሀኒት የሚገዛውም ያለው ነው እኛ ቢያመን ጤና አዳም እስኪያድን እንጠብቃለን ። አስታውሳለሁ የእናቴ ጓደኛ አለም እኔ ህፃን እያለሁ ታማ ሆስፒታል ገብታ ። አራት ወር ሙሉ ስትሰቃይ ቆይታ ለመታከሚያ ብር ስታጣ ነው የሞተችው ??? እናቴ በትንሽ ገንዘብ እንደዛ ፊቷ በደስታ ሊሞላ ከቻለ እኔን በደስታ ሊያስለቅስ ከቻለ እንዴት ደስታ አይገዛም ይባላል ። መንፈሳዊ ደስታን ላይገዛ ይችላል ግን ቢያንስ ፈጣሪን እንዳናማርር እና አመስጋኝ ሊያረገን ይችላል !!! የተጋነነ ሀብት መጥፊያ ሊሆን ይችላል አያያዙን ካወቅንበት ግን ከመጥፊያ ይልቅ መክበሪያ ሊሆን ይችላል አይደል !!!!! ብቻ ገንዘብ ይስጠኝ እንጂ አያያዙ አይከብደኝም ነበር ብሩ ጠፋ እንጂ 😂😂 ብቻ ግን እናቴን በዛ ሁኔታ ማየት ለኔ የደስታ ምንጭ ነው የሆነልኝ ። በጣም አምሮባት ነበር ፊቷ በዛ ልክ በደስታ ሲበራ አይቻትም አላቅም !!! እሷ እንደዛ ከመሆኗ በላይ ደግሞ የኔን ደስታ ለማየት ጓጉታ ስጠብቅ ቆይታለች !!! ስላሰቡ በው ግን ደስታዬን የገለፅኩት በእንባ ሆኖ አረፈው !!!! ከዛም እናቴ አቅፋ አባብላኝ ምናምን በመከራ ተረጋጋሁ ። ልክ እንደሳሚ ገንዘብን ጥሩ ቦታ ስናውለው እሱ ፊት ላይ የመጽሐፍ ታየውን አይነት በሰው ደስታ መደሰት ስሜቶች ይኖሩናል !!! ሙሉ ቤተሰቡ በስስት እየተመለከቱን ነበር ። በስተመጨረሻም ሳሚ " በሉ  ወደ ውስጥ እንግባ " ብሎ  ከገባንበት የሀሳብ ሰመመን ሰበሰበን ። ለኔና ለልዕልና አቀባበል ቤቱ ፏ ብሏል እንደሁሌው ድምቅ ያለ የምግብ ጠረንጴዛ ይታያል ። ሰላምም  በጣም ጤንነት ላይ ያለች ትመስላለች ። እኛ እዛ እያለን አሳክሟት ይሆን አላቅም ብቻ በጣም ጥሩ ስሜት ይታይባታል ። እንግዲህ በዛች በተባረከች ቀን ፈጣሪ እየመራ ወደ ሳሚ ወስዶ ከሱ ጋር አገናኝቶኝ እናቴ አይታ የማታቀው ህይወት እንድታይ አደረገልኝ ። ሽሮ ወይ ድንች ወይ ጎመን ከሶስቱ አማርጣ የምትበላውን እዛ ብዙዙ አይነት ነገር ስታይ ግራ ገብቷት ዝም ብላ ቁጭ አለች ። ይሄ ቤት እንዳለ የተባረከ   ቤተሰብ የሞላው ቦታ  ነው። የእናቴን ስሜት ለመረዳት ደቂቃ ያልፈጀባት ሰላም ተነስታ ከሁሉም አይነት አድርጋ አዘጋጅታ ሰጠቻት ። እኔና ልዕልቷም አራት ቀን የተበደልነውን እያካካስን ይመስል ጥግብ እስክንል በላን ። ምንድነው የማወራው ግን ሆይ እዛ እያለን የምንበላቸው ምግብ ለኔ ምርጥ ነበሩ እሷ ናት የተበደለችው እንጂ እኔ ተባርኬ ነው ማለት እችላለሁኝ ! ከዛም በልተን ስንጨርስ በታ እንቀይር ተብሎ በረንዳ ምንጣፍ ተዘርግቶ ምናምን  ቡና በሚያምር ሁኔታ ቀርቦ ወተን ቁጭ አልን ። በምን ቀን ያንን ቤተሰብ እንደተዋወኩ አላውቅም ። እናቴ ሁሌ " በየተሰ በኩል ልስጥህ " ይላል ፈጣሪ ስትል እስማ ነበር ። እኔም የዛ ቀን ብር አስፈልጎኝ ፈጣሪዬን ለምኜ ወጥቼ በትንሹ አስጀምሮ ብዙ ነገር አሳየኝ !!!!! እውነት ለመናገር ከዛ ቀን ቡሀላ በጣም በፀሎት ማመን ጀምሪያለሁ !! ክብ ሰርተን ቁጭ ብለን ማውራት ጀመርን ደ የኔ ደርባባ ተስተካክላ ተቀምጣ ብዙ ከማውራት እያዳመጠች ፈገግ ብቻ ትላለች ። ሰላምም ሁለታችንንም ተመለከተችንና " ዛሬ ሙሉ ቀኑን አብረን ነው የዋልነው በጣም የምትወድክ የምትሞትልክ ዋጋ የከፈለች እናት ናት ያለችክ ሚኪዬ ደግሞ ባንተ ላይ ያላት መተማመን ትልቅ ነው ። ጥሩ ልጅ ነክ ለካስ ካስተዳደግ ነው አይደል !" አለች ፈገግ ብላ ። አዎ እግዚአብሔር ይመስገን ብዬ ቁጥብ ፈገግታ አሳየሁ ። ሳሚም ለጠቅ አደረገና " እናንተ እዛ በመሄዳችሁ ሰላምዬ ዳነችልኝ " አለን " እንዴ አባ ሳትነግሩኝ ሆስፒታል ሄዳችሁ እንዴ ?" አለች ልዕልና ቀደም ብላ ። " አዎ ትክክለኛውን ሆስፒታል አገኘሁት ። እኔም ከእናንተ እኩል ለአንድ ሳምንት ቤት ሆኜ ነው የሰራሁት ጥያት አልወጣሁም ። ቤት ስንውል እንደድሮ አብረን ስንሰራ ምግብ ስናበስል ውሀ ስንረጫጭ ጊቢ ውስጥ ስንሯሯጥ  ...... ብቻ አንድ ወር አብረን እንዳሳለፍን ቁጠሩት ትንሽ ነበር እየተኛን የነበረው ። ለሊቱን ሙሉ ስናወራ ይነጋል !! ከድሮም የህመሟም ያለመዳኗም ምክንያት እኔ ነበርኩኝ እስከዛሬ ሳላግዛት ለካስ ሰው ርቧት ነበር ፍቅር ሽታ ነው " አለ ስሜታዊ ሆኖ ነበር ። ግን እኮ የመዳኗ ምክንያትም አንተ ሆነሀል ብዬ ፈገግ ብዬ አየሁት ቶሎ ወደ እናቴ ተመለከተና " በእውነት ፈጣሪ በልጅ ክሶሻል ሚኪ ማለት ለእኛ መልአክ በይው ። ከሰላም ጋርም ስላንተ ስናወራ ነው የቆየነው !! ለዚ ቤተሰብ ትልቅ ዋጋ አድርገሀል ። እናም እኔና ሰላም አውርተንበት ለአንተና ለቤተሰብክ እንዲሁም ብቸኛዋን ልጃችንንም ያማከለ ሶስት ልዩ ስጦታዎች አዘጋጅተንልሀል " አለኝ ። በደስታ ሊገሉኝ ነው መሰለኝ ሀሳባቸው ። " ምንድንነው አባቢ እኔንም ይጨምራል እ ንገሩና " አለች ልዕልቷ ቀና ብላ ። " አንዱ የሚሰጥ ሁለቱ ሚነገር ነው " ብሎ የሆነ የተጠቀለለ ነገር ሰጠኝ ............ ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣7⃣
227
12
https://t.me/Ethioleboled
https://t.me/Ethioleboled
215
13
የበአል ዋዜማ እንዴት ነው?
271
14
"Loyalty" ታማኝነት ምንድነው? ለናንተ አንድን ሰው Faithful ነው ብላችሁ የምትደመድሙት ምን ሲያደርግ አልያ ምን ቦታ ላይ ሲገኝ ነው... ? ሀሳባችሁነ comment ላይ ጫር ጫር አድጉልኝ ከ ርዕስ መውጣት አይቻልም #ᵐᵉʲⁿᵘⁿ 🥀𝖇𝖊𝖑𝖆✌️
326
15
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 3⃣5⃣ ........ ተገጣጠምን ። የተለያየንበት መንገድ ጥሩ ስላልነበር በዛ ላይ ከልዕልቷ ጋር ሆኜ ስታየኝ ይደብራታል ብዬ ፈርቼ ነበር ። እያሰብኩ ከነበረው በተቃራኒው ግን እሷ ፊቷ ሁሉ በደስታ ተሞልቶ ነበር ። የምር ይሆን የሴቶች ብልሀት ?? አላውቅም ብቻ እየሳቀች ሀብትሽ ብላ ጥምጥም አለችብኝ ። እጆቼን ወደሰማይ አንስቼ እያሳየሁ ልዕልናን ተመለከትኳት ። ብዙም ሳትቆይ ደግሞ እኔን ለቃኝ " የፍቅሬ ፍቅር እንዴት ነሽ? " ብላ ልዕልናንም አቀፈቻት ። ሴቶች የራሳቸው የመጣጣም ባህሪ አላቸው መሠለኝ እኔ ገና ይጣላሉ እርስ በርስ እንዳይጨቃጨቁ ፀብ እንዳይነሳ .... እያልኩ በፍርሀትና በጭንቀት ውስጥ ሆኜ  እያለሁ እነሱ እየተቃቀፉ ነበር ። ጭራሽ ይባስ ብላ ልዕልቷ መልሳ " የፍቅሬ አፍቃሪ እንዴት ነሽ ?" ተባብለው መሳሳቅ ጀመሩ !!?? ለደቂቃዎች በሀሳቤ ነው ብዬ ተጠራጥሬ ካየዋቸው ቡሀላ ግን የምር መሆኑን ሳቅ ወይ ሴቶች ብዬ አፌን ይዤ ቁጭ አልኩኝ ። ሴቶች ገራሚ ፍጥረት ናቸው ግን !!!!! " ታውቃላችሁ እዚህ ጊቢ ብቻዬን መሆን በጣም ደባሪ ነበር ስላገኘዋችሁ ደስ ብሎኛል " አለች ። እኔ ምንም ለማውራት አልፈለኩም ዝም አልኩኝ ። " አዎ ልክ ነሽ እረዳሻለሁኝ ሲደብር አሁን መገናኘታችን ጥሩ ነው ! ደግሞ እህል ውሀችን ተለያይቶ እንጂ በጣም ቆንጅዬ ነሽ ሄዋኑ እኔ ሆኜ እንጂ ሚኪ ይወድሽ እንደነበር እርግጠኛ ነኝ " አለች ልዕልና ። ጭራሽ መሞጋገስ ጀመሩልኝ ወይ ጉዴ ። " ካንቺማ አልበልጥም በጣም ቆንጆ ነሽ እኮ " አለች ማያ በተራዋ ። ከጨዋታው ውጪ እያደረጉኝ እያለ ደስ በሚል ሁኔታ ምግቡ መጣ እና ወሪያቸውን አቋረጠው ። " ይቅርታ አንድ ፖስታ በአትክልት  ጨምርልን ከለስላሳ ጋር  " አለች ማያ በትህትና ። ታጥበን እንምጣ ብለው ሁለቱም ሄዱ ። በጣም ከመጠራጠሬ የተነሳ እስካሁን ሲያስመስሉ ቆይተው መፀዳጃ ቤት ሲደርሱ ሚጣሉና ሚደባደቡ መስሎኝ ሮጬ ለማገላገል ተዘጋጅቼ ብቀመጥም ምንም ሳይፈጠር ተመልሰው መጡና ምግባችንን መብላት ጀመርን ። መጀመሪያ ያዘዝኘው ስንጨርስ ፓስታውም መጣልን እንቸ አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊ ወንድ ፓስታ ላይ ያን ያህል አይደለሁም ። ትንሽ ጎርሼ ተነሳሁና ታጥቤ ተመለስኩ ። ሁለቱም በልተው ጨርሰው ተመልሰው መጡና ለስላሳችንን እየጠጣን ቁጭ አልን ። ማያ ሰአት አየችና " ገና ሁለት ሰአት አለን " አለች ። በቃ ቶሎ ጨርሱና ላይብረሪ እንሂድ ብዬ ያፈንኩትን ዝምታ ሰበርኩት ። ከዛም ለአስተናጋጁ ሂሳብ እንዲያመጣ  ነገርኩትና ከዛው ከፈረደበት ሳሚ ብር ላይ ልከፍል ስዘጋጅ  ማያ ቀድማ  ብሩን ያሰላችው ይመስል " እኔ ነኝ ምከፍለው ግብዣ ነው እረፉ " ብላ አዘጋጀች ። እንም እንቢ ብዬ ብታገለም " አይሆንም ሰርኬ ትሙት " ስትል በቃ እሺ አትልም ብዬ ዝም አልኩ ! አንዳንዴ ህይወት እንዲ ናት !!! ነገሮችን በደንብ አስባቸውና " ወይ ካለው ተወለድ ወይ ካለው ተጠጋ "  የምትለው አባባል ትዝ ትለኛለች ። ብቻ ግን ከፍላ ወጣንና ላይብረሪ ገብተን አንብበን   ተመልሰን ወደ ፈተና ገባን ። ሶስቱንም ቀን በተመሳሳይ መንገድ አሳለፍን ። ላይብረሪ እንዲገቡ አረጋለሁ እኔ ትንሽ አነብና ከዛ ለጥ እላለሁ  እንፈተናለን ምሳ እንበላለን ድጋሜ እንፈተናለን !!... ሌሎቹን  ትምህርት ተፈተንንና ሀሙስ ጠዋት የመጨረሻውን ፈተና ለመውሰድ መዘጋጀት ጀመርን ። ሀሙስ አምስት ሰአት አካባቢ ሰባቱንም  ትምህርት ተፈትነን  ጨረስን ማለት ነው። የተባለው የዛ ቀን እስከ ነገ ቆዩና ጠዋት ትሄዳላቹ ነበር ልዕልቷ ግን ካልሄድን ብላ ድርቅ አለችብኝ ። እኔም እሷን ላለማስቀየም እሺ ብዬ ያመጣናትን እቃ ሸክፈን  ወደቤት ለመሄድ ማያንም ጠብቀናት ፈርመን ከዛ ወጣን ። ከዛም በር ላይ እያለች ቶሎ በጠባቂ ስልክ ደወለች ባለቤቷ ጋር ። ከዛም ታክሲ ጠብቀን ወደቤት ሄድን ። ልዕልናም ቤት ካላደረስከኝ ብላ ችክ አለች ። የዛ ቀን ስትቀብጥ ነበር !!! ማያ ወደቤቷ ሄደች እኛም እነ ሳሚን ለማስደንገጥ ሄድን ። ከፊት በር ባንኳኳ ብደውል ቆይቶ ተከፈተ ። የሚገርመው ደግሞ የከፈቱት ሰላምና ሳሚ ናቸው ። ሰላም ብለናቸው ወደ ውስጥ ስንገባ ግን ያየሁትን ማመን አልቻልኩኝም !!! ፊት ለፊቴ የቆመችው .......   ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣6⃣
333
16
❤️ ..........ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ ፀሀፊ  ፊደል                         ክፍል 3⃣4⃣ .......... ግን ለምን ??? ማለቴ ልዕልና ከሰው ጋር ችግር ውስጥ እንደማትገባ ግልፅ ነው ሰው ቀና ብላም የማታይ ልጅ ናት !!!! በጣም ተናድጄ ነበር ። አንደኛ  የሳሚ አደራዬ ናት ሲቀጥል የመጀመሪያ ከልቤ ያፈቀርኳት ሴት ናት !! ግን ሴት ወደድኩ ብዬ ሴት ላይ እጄን ለማንሳት አልደፍርም !! በማንኛውም እንደዚ አይነት ሁኔታዎች ላይ ምስኪናን እናቴን አስታውሳታለሁ አስባታለሁ !!!! በሰአቱም እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ ወደልጆቹ ሄድኩኝ ። የልዕልናን ፍራቻና ድንጋጤ ሳይ ልሳሳት ምንም አልቀረኝም ነበር !!! ምን እያረጋችሁ ነው ?? አልኳቸው አጠገባቸው ሄጄ ። ምን አይነት የውርጋጥ ስብስብ እንደሆነ አላውቅም እንዳለ መንጋጋቸው እስኪታይ ማስቲካ እያላመጡ ወደኔ ቀና ቀና አሉ ። እንፈራለን የሚሉ ጀማ ናቸው !! የሚያሳዩት ፊት አክታቸው የሌለ ነው የሚደብረው ። ሁሉም በየተራ ተመለከቱኝ ። የዛ መልክ ለምኔ የመሠለ ጀማ መሪ ነኝ ባይ መሰለችኝ " በለው ውበት አባቢ ተማሪ ነሽ እንዴ እ የሌለ ነው የምታምረዎ ነው የምልክ ምን ልሁንልህ በእናት ?????" ። እኔ እንኳን እንደሷ ዘቅጬ አውርቼ አላውቅም !!!! ሴት ልጅ ክብሯንና ስርአቷን ሴትነቷን ስትጠብቅ ነው እንጂ የአራዳ ቋንቋ ብለው የሚያስቡትን ቃላት በመጠቀም አራዳ መሆን የሚፈልጉ ለፀብ የቀረቡ ክብራቸውን ጥለው ወንድን በወረደ ቃላት የሚያወሩትን ሴት ለማለት ይከብዳል !! በእነዚ አይነት ውርጋጦች ምክንያት እንደነ ልዕልና እና ማያ አይነት ውብ ሴቶች ከጠቃላይ ሲሰደቡ የምር ይደብራል !!! በሰአቱ ከሷ ጋር ለማውራት ራሱ ነው የጨፈገገኝ !! እጄን ዘርግቼ ልዕልናን ከወደቀችበት አነሳዋትና ፊቷን እየጠራረኩኝ ተጎዳሽ እንዴ አመመሽ እንዴ ? ብዬ አቀፍኳት ። እሷ ያደገችበት መንገድ ፍፁም ከእኛ የተለየ ነው መመታት መጠላት እንዲህ አይነት ቃላትን አለመደችም በጣም ደንግጣለችም !!! " ምንሼ ባባዬ እኛ እያለን ከዚች ፋራ ጋር አይነፋም እሽ " ብላ ያንን ቀፋፊ ንግግሯን ቀጠለች ። የመጨረሻ ትዕግስት ላይ ደርሻለሁ ከመሳሳቴ በፊት ብዬ ትሰሙኛላችሁ አስባችሁት ሳይሆን ሳታስቡት እንኳን በፍቅረኛዬ አጠገብም እንዳታልፉ እሺ እንኳን እናንተ ሌላ ሰው ቢነካትም ፀቤ ከእናንተ ጋር ነው ለራስሽ ስትይ ጠብቂያት ያለበለዛ ግን ሴት ስጎዳ የመጀመሪያዬ ነው የምትሆኝው አገኘሽኝ ?? ሲቀጥል ሴት ሁኑ እሺ እሷ ጋር ለመድረስ ተጨማሪ ሀያ አመታትን ኑሩ !! በዠየሚል ኮራ ያለ ንግግር ተናግሬ ልዕልቷንም አኩርቼ እጇን ይዤ ከቦታው ሄድን !!! ለግቢው አዲስ ብንሆንም ያንን ሰፊ ጊቤ ዞር ዞር ብለን አንድ ቦታ ቁጭ አልን ። " ለምንድነው እንዲ የሚያረጉት ሚኪ " አለችኝ ። ግራ ገብቷታል የኔ እናት !! ቆይ ምን አርገሻቸው ነው ? አልኳት ግራ ገብቶኝ ። " ገና ከመለያየታችን ናፍቀከኝ ነበር ቶሎ ለመድረስ ስሮጥ ሳላቅ ልጅቷን ገፋዋት ከዛ ሶሪ ብያት ልሄድ ስል መሬት ገፈተሩኝ ከዛ በጥፊ መታችኝና ደግመሽ በኔ አጠገብ ብታልፊ እያለች ነበር ግን ጊቢ ውስጥ ጠባቂ የለም እ ??" አለችኝ ። ድንጋጤዋ አለቀቃትም አሳዘነችኝ ከዛም እንዲለቃት ብዬ ከራሷ አባት በተቀበልኩት ብር ካፌ ወስጄ ጋበዝኳት እራት በልተን ወደ ዶርም ለመግባት ልንለያይ ስንል " ሚኪ " አለችኝ በሚያሳዝን ድምፅ ወዬ እናቴ አልኳት አምልጦኝ " እንዲ ስትለኝ የመጀመሪያህ ነው አረሳውም ይሄን ቀን ደሞ የሆነ ስሜት አለው ደስ የሚል!! ልልክ የነበረው ደሞ ፈራሁ " አለችኝ እየተሽኮረመመች ። እኔም ወደኔ ሳብ አርጌ ግንባሯን ሳምኳትና አቅፌ ምንም እንዳትፈራና በቻለችው መጠን ከሰው ጋ እንድትግባባ ነግሪያት ዶርም አድርሻት ተመልሼ ለጥጥ አልኩ ። ቀጣዩ ቀን እሁድ ቀን ጠዋት ተነስቼ  ልጠብቃት ከመጣች ብዬ ስወጣ እዛው ቦታ ጋር በዛ ብርድ ቁጭ ብላ እየጠበቀችኝ ነው ። አቅፌ አዳሯን ከጠየኳት ቡሀላ መንገድ ጀመርን ። " ሚኪ ቁርስ እንብላ " አለችኝ ። እኔዴ ተረጋጊ እንጂ ትንሽ ወክ ይቀድማል ብያት ቤተ ክርስቲያን ተሳልመን ተመለስንና ቁርስ በላን ከካፌ ። እንድንዞር ፈታ እንድንል ብጠይቀኝም እንቢ ብዬ ላይብረሪ ወሰድኳትና እሷ ከኬሚስትሪ እኔ ከፊዚክስ ጀምረን ሙሉ ቀኑን ስናነብ ዋልን ። ሰአቱ መምሸቱንም ሆነ  ምሳ አለመብላቷን ያስተዋልነው ቆይተን ነበር !! የፈጠነ ወርደን ራት በላንና ቁጭ ብለን ብዙ አወራን !! ስለ ማህበራዊ ኑሮና ስለኛ የደሀ ልጆች አስተዳደግ በጥቂቱ ነገርኳት ። ከዛም ቅር እያለን ተለያየንና በቀጣዩ ቀን ጠዋት ቁርስ በልተነሰ  የመጀመሪያ ፈተናችንን ተፈተንን ። እንግሊዝኛ በጣም ቀላል ነበር ለኔ እንደዛ ከሆነ ለልዕልና አሰብኩት ። ከዛ ትንሽ ፈታ እንድትል ብዬ ካፌ ወስጃት ምሳ  አዘን እየጠበቅን ድንገት ቀና ስል ከማያ ጋር አይን ለአይን ተገጣጠምን.......🙄🙄 ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣5⃣
415
17
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ፀሀፊ ፊደል                         ክፍል3⃣3⃣ ........ስቶ ሲመጣ ተመለከትን ። ልዕልና ደንግጣ እሪሪ ብላ ስትጮኽ ፍቅር ከመስጠት ውጪ ሌላ ነገር ላይ ጉብዝናው የተመሠከረለት ሳሚ  ምኑን እንደነካው ባላውቅም መንገድ ቀይሶ በሲኖው ፈንታ ከትንሽዬዋ የቤት መኪና ጋር ተነካክቶ ቆመ ። መኪናው አንዱ ጎኑ ከመመታቱ ውጪ ማናችንም ላይ አደጋ ሳይደርስ የምወደው አማኑኤል አባቴ ሁላችንንም ጠብቆ አዳነን ። እኔና ሳሚ ብንደናገጥም ደህና ነበርን ልዕልና ግን ከድንጋጤዋ ብዛት ማውራት ራሱ አቅቷት እጇም አፏ ሁሉ ነገሯ ሲንቀጠቀጥ ነበር !!!! ሳሚ ከራሱ በላይ በልጁ ደንግጦ ልጄ ልጄ ብሎ መኪና ውስጥ እንዳለች አቅፎ  ሊያባብላት እየሞከረ ነው ። በጭንቀት ልፈነዳ የደረስኩት እኔ ከመኪናው ወጥቼ ስንቆራጠጥ ሲኖው አሁንም ከሌላ መኪና ጋር ሊጋጭ ደርሶ ከነሱ ለማምለጥ ሲል መንገድ ለመቀየር ሲሞክር መንገዱ ዳር ወዳለው ጉድጓድ ተገልብጦ ሲገባ ተመለከትኩት !! ከልዕልና በላይ እጆቼ መንቀጥቀጥ ጀመሩ ከየት ከየት እንደመጡ አላውቅም በአንድ ጊዜ  ሰው ስብስብ አለ !!!!! ህዝቡ መጯጯህና መሰባሰብ ጀመሩ !😥😥 የሚገርመው  ግን በሰአቱ ከዳር ቆሞ ስልክ አውጥተው ቪዲዮ ሲቀርፁ ከአንድም ሶስት አራት ሰዎችን ተመለከትኩ ። ግን ለምን ???? የሰውን ልጅ ሂወት ለማትረፍ ለምን አልተሯሯጡም ታዲያ ??? ንዴቴን መቆጣጠር የማልችለው እኔ ሄጄ ስላከቸውን መሬት ልወረውርላቸው ስል ሳሚ " ሚኪያስ ቶሎ በል ቶሎ ግባ ፍጠን ልጄን ልጄ ደከመችብኝ መሠለኝ ብቸኛ ልጄን እንዳላጣት እባክህ አግዘኝ ....." እያለ እንደ እናት እያለቀሰ  ነበር ። እኔም ቶሎ ወደነሱ ተመልሼ ከሳሚ እቅፍ ተቀብያት አየዋት ። በአንድ ጊዜ እሳት ሆናለች ። ሳሚ መኪናውን አስነስቶ መሄድ ጀመረ ። በሰአቱ ሙሉ ሀሳቡ ልዕልና ጋር ሆነ እንጂ ያንን አደጋ ተመልክቶ ዝም እንደማይል እርግጠኛ ነኝ ። በሰአቱ ምን ማረግ እንዳለብኝ ባላውቅም ፀጉሯን እያሻሸሁ ደህና ነን እኮ ሶስታችንም አለን ተረጋጊ እና እየተጫወትን እንሂድ እያልኩ ወደራሷ እንድትመለስ ለማረግ ሞከርኩኝ ። ተሳክቶልኝ ነበር ከጥቂት ደቂቃዎች ቡሀላ ቀስ በቀስ አይኖቿን በፍጥነት እያርገበገበች መንቃት ጀመረች ። እንዳየችኝ የፈጠነ ተነስታ ተጠመጠመችብኝና ሳሚንም እየነዳ መሆኑን ረስታው ከዃላ ተጠምጥማበት " በህይወት አለን መኪናውስ የሞትን መስሎኝ ነበር ፈርቼ ነበር ..!!!" እያለች ተመልሳ እቅፌ ውስጥ ተወሸቀች ። ሳሚም መኪናውን አቁሞ መጣና አሻግሮ እያቀፋት በጣም ፈርቶ እንደነበር ነገራት ። ቀጥሎም እኔን አቅፎ ያመሰግነኝ ጀመር እኔ ምን አረኩ ከፈጣሪ ጥበቃ በተጨማሪ አንተ አስተዋይ ፈጣንና ጎበዝ በመሆንክ እኮ ነው የተረፍነው ቀጣም ጎበዝ ሹፌር ነህ !!!!! አልኩት ። ከዛም ሶስታችንም እንድንረጋጋ ብሎ ትንሽ ጥን ይዘን ቆምንና ከዛ ቀጥታ ወደ ካፌ ወሰደን ። ከአስጨናቂው ውሎ ቡሀላ ፅድት ያለ ምግብ ጋበዘን ከለስላሳ ጋር !!!! ተዳርሰንም ስለነበረ የምንፈተንበት ቦታ ድረስ አደረሰን ። እንዴት ሆኖ የባለ ስልጣን ልጆች የሚማሩበት ትምህርት ቤት እንደደረስን ባላውቅም ብቻ በር ላይ ቅብጥ ያሉ ራቁት ቀረሽ ልብስ የለበሱ ልጆችን ስመለከት ነበር !! ከዛ ከመኪናው ውስጥ ሁለታችንም ቦርሳችንን አወረድን ። ሳሚ ከልጁ መለየት የጨነቀው ይመስላል ከፍቶታል ። " አባ አቅፌ ቻው ካልኩህ ትናፍቀኛለህ !! ስለዚህ በሩቁ ቻው እናቴን አደራ ትናፍቁኛላችሁ !" አለች እንደ ህፃን ልጅ እንባ እየተናነቃት ። ከዛም ወደ ሴቶች ፍተሻ ሄደች እኔም በአጭሩ አመሠግናለሁ ሳሚ ብዬ ልሄድ ስል እጄን ያዘኝ ። " ልጅ ሚኪ በጣም ጥሩ ልጅ መሆንህን ስለማውቅ ስለማምንህ ትንሽ ቀለል ብሎኛል አሪፍ ውጤት እንድታመጣ እርዳት ለኔ ስትይ አርጊው እያልክ አበረታታት እባክህ በእናቷ ምክንያት አውቃ እንዳትወድቅ አደራ ! ከማንም ጋር እንዳትነካካብኝ አደራዬን ሰጥቼሀለሁ ደግሞ ..." ብሎ ንግግሩን ገታ አደረገና ከኪሱ ድፍን መቶ መቶ ብር ብዙዙ ብር አውጥቶ ደብቆ ኪሴ እየከተተ " ልዕልናዬ ትንሽ ቀበጥ እንደምትል አውቃለሁ የምትፈልጉትን አድርጉበት ካነሰ ደግሞ ዳይሬክተሩ ጋርም ቢሆን ሄዳችሁ ደውሉልኝ አደራ ልጄን አምንሀለሁ " ብሎ አቅፎ ትከሻዬን መታ መታ አረገው ። ለአንድ ሳምንት ይሄ ሁላ ብር ያንሳል ይለኛል አቤት ሀብታሞች ግን በስመአብ !! እኔም ኪሴ ከቀረችው መቶ አስር ብር ውጪ አንድ እንደሌለኝ ስለማውቅ አፌን ዘግቼ እሺ ብዬ ተቀበልኩ ። አገላብጠው ፈትሸው አስገቡንና ዶርም ለማየት ሊበታትኑን ሲሉ ልዕልና እየሮጠች መታ " እቃህን አስቀምጥና ቶሎ ና እዛ ጋር እጠብቅሀሉሁ " ብላኝ ሄደች ። እኔም ወደተነገረኝ የወንዶች ዶርም ገባሁ ። ወንዶች ለመግባባት ቅርብ ነን መቼም እዛው በዛው ሰላም ተባብለን ስም ተነጋግረን ሎከር ተከፋፍለን ጨረስን ። አራት ነን ሶስቱም ጥሩ ልጅ ይመስላሉ ግን ትምህርቱ ላይ የሉበትም ! ከዛም እቃዬን አስተካክዬ እንደጨረስኩኝ ና ወዳለችኝ ቦታ ለመሄድ ነጠላ ጫማ አርጌ ቀለል ብዬ ወጣሁ ። ልክ ያለችው ቦታ ልደርስ ስል ከሩቅ ሳይ ልዕልና በፍርሀት ተውጣ መሬት ላይ ወድቃለች ሶስት ሴቶች ደግሞ ከበው ምን እንደሚሉ አላውቅም በየተራ እጃቸውን ይቀስሩባታል ጭራሽ አንዷ ደግሞ በጥፊ ስትመታት ተመለከትኩ ግን ለምን ???? .......... ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣4⃣
342
18
ልዕልና በግርምት ተመለከተችኝና " እንዴ እቃህስ ይቺ ብቻ ናት በቃ ?" አለችኝ ። ሳሚም ቀደም ብሎ " እኛ ወንዶች እኮ እንደናንተ አስቸጋሪ አይደለንም " ብሎ ነገሩን አስቀየሰው ። ዃላ ግን ቦርሳዬን ለማስቀመጥ ኮፈኑን ሲከፍተው ወደ ውጪ የምትሄድ ይመስል ትልቅ የሚጎተት ቦርሳ ይዛለች ውስጡ ያለውን ነገር አሰብኩኝና ተውኩት ! ከዛ ሁለታችን ከዃላ ሆነን መንገድ ጀመርን ። አስታውሳለሁ ሰኞ ቀን በሀያ ስምንት ከቀኑ ስድስት ከአርባ አካባቢ  መሆኑን በሳሚ የመኪና  ሰአት አይተናል ። ልዕልና ያለ ስልክ ሳምንት መቆየት እንደማትችል እያወራች እያለ ሳሚ ስልኳን ሊሰጣት ወደኛ ሲዞር ከፊታችን አስፈሪው ቀይ ሽብር ( ሲኖትራክ )መስመር ስቶ ሲመጣ ............. ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣3⃣
274
19
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል3⃣2⃣ .................. መጮህና መሳደብ ጀመረች ። በጣም ደንግጫለሁ በጣም !!!! ያ ሁላ ፍቅር ሳቅ መግባባት የት ሄዶ ነው አልኩ ፈርቼ ። ማለት ከቀናቶች በፊት እኮ በጣም ተግባብተን ተመሰጋግነን ነበር የተለያየነው !! ግራ ገብቶኝ ሳሚን መመልከት ጀመርኩኝ እሱ ደግሞ በጣም ከመፍራቱ የተነሳ ሊያረጋጋት እየሞከረ አይደለም ??? እኔ እንደማስበው ከሆነ ደግሞ ሴት ልጅን ከሚያረጋጉ ነገሮች አንዱ የምትወደው ሰው እቅፍ ውስጥ መቆየት ነው ። ሳሚ ግራ በመጋባት ስሜት ይመለከተኝ ጀመር ከዛ እጆቼን እያጣመርኩ አቅፎ እንዲያባብላት ነገርኩት። ሳሚ በዛ ላይ ጎበዝ አልሆነም !!! በስራ በባህሪ በሌሎቹ ነገሮች ላይ ጎበዝ ቢሆንም ግን ፍቅር መስጠት ላይ ደካማ ነው !!! ስሜቱን መግለፅና ማሳየት ላይ የለበትም ! እንዴት እንደተጋቡ አላቅም በርግጠኝነት በሰላም የፍቅር ሰውነት ይመስለኛል !!! ለምን እኔን ስታይ እንደተናደደች ሊገባኝ አልቻለም !! ሳሚን ለማስረዳት ስለረቃኝ አጠገቤ ቆማ የለበስኩትን ጃኬት አጨማዳ ወደያዘችው ልዕልና ዞሬ እቅፍ ናፍቋታል ቶሎ በይ እሷን ማቀፍ አለብሽ አልኳት ። ነቄ ነገር ናት ቀልጠፍ ብላ ወደ ሰላም ሄደችና እናቴ እማ የኔ ቆንጆ እያለች እንደ ልጅ ፀጉሯን እየደባበሰች አቀፈቻት ። እውነትም ናፍቋታል መሰለኝ ተረጋጋች። ስድቡን መግታቷን የተመለከተው ሳሜም ከሰላም እቅፍ ተቀብሎ ያባብላት ጀመር ። ልዕልና ደግሞ ለአባቷ ካስረከበች ቡሀላ ወደኔ መታ ደረቴ ላይ ልጥፍ አለች ። በሰአቱ ደስታም ድንጋጤም ነበር በርግጥ ግን ሌላ አማራጭ የለኝም አቅፌ ላባብላት ግድ ነው !!!! ከስንት ቆይታዎች ቡሀላ ሰላም ተረጋጋችልን ። ሳሎን ተሰብስበን ቁጭ አልን ብዙም ሳትቆይ ወደራሷ መመለሷ ደስ  ይላል ግን ውስጧ እንደቸረበሸ ነው ። የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ እንዴ ?  አልኩኝ መልሳ ልትሰድበኝ እንደምትችል እያሰብኩኝ ! " የለም ግን ግን አልቻልኩኝም !!!" አለች ፊቷን ላይ ኮምጣጤ እንደጠጣ ሰው ጉምዝዝ አድርጋ ። ለምን ?? አልኳት መልሼ " መንፈሴን አስጨነቀቻት ቅርብ ናት አዎ ይሰማኛል እሷ ቅርቤ ናት ጨርቄን አስጥላኝም አረካችም መሠለኝ ቅርቤ ናት !!!!! ..........????" ማለት ጀመረች። ሁለቱም ግራ ገብቷቸዋል ደንግጠዋል !! ችግሩ ግን ምንም ልላቸው አልችልም እኔም ግራ ገብቶኛል ለምን እነዚህ ስሜቶች እንደተፈጠረ ማወቅ እፈልጋለሁ ። አሁን ላይ የማረገው ነገርና የምሰጠው መፍትሄ ስላልነበረኝ እና ነገ የጊቢ ጉዞ ስላለ ወጣሁ !!! በዛ ሰአት ላይ ጊብ እንደምንሄድ ሳስብ ወደቤት መሄድ ነበረብኝ ። በጨዋታ መሀል ለምን እንደተናደደችብኝም ነግራኛለች ። እ ኔም በቻልኩት አውርቻት ተነስቼ ወጣሁ ። ወደ ቤት ስመለስ ስጠብቀኝ የነበረችው እናቴን ጠርቻት መቅሰስ  በላን !! በቀጣዩ ቀን የት እንደምንላክ  እጣ ወጣና ለማየት ሁላችንም ወደ ትምህርት ቤት ሄድን ። የዛኔ ደግሞ የመንግስትና የግል አንድ ላይ ስለምንፈተን የምንላክበት ቀንና ቦታ ከነስም ተዘርዝረ። !! ከሁሉም የሚያስጠላው  ነገር ግን ስም ሳነብ የሶስት ሰው ስም ማንበቤ አስደነገጠኝ ። ምክንያቱም እንዴት እንዴት እንደተገጣጠምን እንጃ ሶስታችንም አንድ ጊቢ ለመፈተን ተመድበናል ። የሆነ ጎኔ ምን አገባህ ቢለኝሞ የሆነ ልቤ ግን አንድ ላይ መሆናችንን አልወደደውም!!!! በቀጣይ ቀን ያለምንም አማራጭ ለመሄድ መዘጋጀት ጀመርኩኝ ። ከእናቴ ተለይቼ አድሬ የማላቀው እኔ ገና ሳልሄድ እስከዘላለሙ የተለየዋት ይመስል ሆዴ እየባባ ነው ። ግን ደግሞ ከእኔ በላይ እናቴ እንደሚከብዳት አውቃለሁ ። ብቻዋን ነው የምታድረው ማንም የላትም አባቴ እንደሆነ አንዴ የተበላ እቁብ ሆኑዋል !!! እኔ የሚያሳዝኑኝ እናቴ እንደ ሚስት ወግ ሳታይ አባቴ የአባትነት ክብር ሳያገኝ እድሚያቸውን መጨረሳቸው ነው ። ብቻ ግን ለእናቴ ለአንድ ሳምንት ብቻ እንደምሄድ እየነገርኩ ላባብላት ሞከርኩኝ ። ከዛም ሳምንቱን ሙሉ በሰራቻት ብር ዳቦ ቆሎ እና ኩኪስ ገዝታልኝ መጣች ። አንዳንዴ የሷን ውለታ ሳልከፍል እሞት ይሆን እያልኩ እጨነቃለሁ !! ከሌላት ላይ ሳትቀንስ እንደሰጠችኝ ያለኝን ሙሉ ልሰጣት እመኛለሁ ! እንደሌሎቹ እናቶች ልብስ ላለብሳት ሀበሻ ቀሚስ ልገዛላት እፈልጋለሁ!!!!! አንዳንዴ የምር ራሴን አልወደውም ሁሌም ብር ሳገኝ ከራሴ ውጪ ለሷ ካልሲ እንኳን ገዝቼ አላቅም ። ??? ክብሯን ጥላ ሰርታ አስተምራኝ እኔ በማንም መንገደኛ ለመከበር ዘንጬ ለመውጣት ዋጋ እከፍላለሁ !!!" እውነት ለመናገር ድህነት የሚያኮራ ነገር የለውም ግን በእኔ ልክ ሊታፈርበትም አይገባም እላለሁ አንዳንዴ ሳስበው ግን ማንኛውንም ነገር ስንጠላው ነው ከሱ ለመራቅና ቆርጦ ለመጣል የምንነሳሳው !!! እኔም ድህነትን ለመቁረጥ ራሴን እያዘጋጀው ይመስለኛል ፈጣሪን የተደገፈዐአይወድቅም የምትል መርህ እየተከተልኩ ነበር ። ለማትሪክ ፈተና ትኩረት አልሰጠሁኝም አላነበብኩም የማለፍ ፍላጎትም የለኝም !!!! ወደኩም አለፍኩም ከእናቴ ስር ሆኜ ባገኘዋት እያገዝኳት መኖርን ነው የምፈልገው !! መጥፎ ውጤት ላለማምጣት በሚል ብቻ ማታ ማታ ትንሽ አንብቤ እየተኛሁ አው የቆየሁት ። እንግዲህ እኔ ለአንድ ሳምንት ስለሆነ ብዬ ሶስት ልብስ ያዝኩኝ ከዛ አንድ ነጠላ ጫማና አንድ ሽፍን ጫማ እና እናቴ የገዛችልኝን ቆሎና ዳቦቆሎ በጥቁሯ ቦርሳዬ ውስጥ ከትቼ እቃዬን አዘገጃጀሁ ። " የትራንስፖርት ስንት ነው የሚያስፈልግህ ልጄ ተቀብዬ ልመጣ ነው ንገረኝ " አለችኝ እናቴ ። ለኔ ሞራል እኮ ነው እንጂ እመልሳለሁ ብላ በአርባ አራቱ ታቦት ምላ ወይም ደግሞ እነዛን ጎረቤቶቿን ግማሽ ግማሽ ለምናልኝ ነው  የምታመጣው !!! እሄኔ እኮ በልቧ መጀመሪያ ማንን ልጠይቅ ? እያለች ይሆናል ፈጣሪ ግን ደግ ነው !!!! በዛው ሰአት በዛው ቅፅበት የውጪው ቆርቆሮ ተንኳኳ ። ከዛም እሷ በዛው ልትሄድ ሁለታችንም አብረን ወጣን። ሳሚና ልዕልና  ነበሩ ። በሰአቱ ግራ ገብቶኝ እዚህ ምን ታረጋላችሁ አልኳቸው ? " ሰላምታ አይቀድምም እንዴ ልጅ ማይክ " አለና እኔንም እናቴንም ሰላም አለን ። የኔ ቀበጥ  የዛኔ ጎብዛለች " ደህና አደሩ የሚኪ እናት ልቀፎት " አለች እጇን እየዘረጋች ። የኔ እናት ደስ ብሏት እቅፍ አረገቻት ። እሷ ከመምጣቷ ፈገግታን ጫረችብኝ የሆነ የደስታ ምንጭ ነገር አላት !!! " እንግዲህ ከፈቀዱልን ልጆትን ልንወስድ ነው የመጣነው " አለ ሳሚ በታላቅ አክብሮት ። እንዴ ሳሚ እሜይ እኮ ኑሮ አጎሳቆላት እንጂ ከሰላም ታንሳለች ገና ወጣት ናት !! አልኩት አንቱታው የክብር እንደሆነ ባቅም .. እናቴ ትንሽ ነገሩ አልገባትም መሠለኝ ቀና ብላ አየችኝ ። እማ ልዕልና ማለት እሷ ናት እሱ ደግሞ ሳሚ አባቷ እኔና እሷ አንድ ጊቤ ነው የምንፈተነው እና የትራንስፖርት ከምናባክን በመኪናው አድርሶን ሊመጣ ነው  ብዬ በአጭሩ አስረዳዋት። " ይሻላል ልጄ ?" አለችኝ ። የሆነ ደስ የማይል ፊት አሳየችኝ አላመነቻቸው ይሆናል ብዬ ቀለል አረኩትና አዎ እማ ችግር የለውም በቃ ብዬ ከቤት ቦርሳዬን ይዤ ወጣሁና እናቴን ቻው ብያት እንደምትናፍቀኝና ራሷን እንድጠብቅ ነግሪያት ከጊቢ ወጣሁ ።
360
20
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል3⃣1⃣ ....... ወደሷ ስዞር በዝምታ ተመለከተችኝ ይቅርታ እንደምታስቢው አይደለም አልኳት ወደሷ እየቀረብኩ ። ሂዳ ተከተላት " አለችኝ አንድ እርምጃ ወደዃላ እየሸሸች ። ይቅርታ የራሴ ጥፋት ነው እንድትጎዳ ስለማልፈልግ ብቻ ነው ብዬ ላስረዳት ሞከርኩ ። ለምን ትጎዳለች ራሱን የሚጠብቅ ኩል የሆነ ባል የሚያከብራት ሰው አላት ለምን ትጎዳለች ??" አለችኝ ። መጀመሪያ እንደዛ አልመሰለኝም ብዬ ላስረዳት እየሞከርኩኝ እያለ " ትወዳታለህ ?" የሚል ድርቅ ያለ ጥያቄ ጠየቀችኝ ።ማያ ማለት ከልጅነት የማቃት ግን የማላቃት ልጅ ናት ሽለሷ ሁሉንም ነግርሻለሁ ከፈለግሽ ግን እወዳታለሁ እንጂ በፍቅር አይደለም እምልልሻለሁ አስብላታለሁ ግን ላፈቅራት አልቻልኩኝም እሷ ጋር ያለው ስሜት ቀስ በቀስ እንደሚጠፋ እርግጠኛ ነኝ አልኳት ። ያን ያህል የተዋጠላት አትመስልም ። እውነት ለመናገር ከሆነ ከልቤ ነው ያወራሁት በዛ ላይ በራስ በመተማመን ስሜቴን መግለፄ የሆነ ደስ የሚል አይነት ስሜት አለው የሆነ ነገር ከላዬ ላይ እንደወረደ እየተሰማኝ ነው  !!! እዛ ጋር የነበረውን ድባብ መቀየር ፈልጊያለሁኝ ። ልዕልና ያን ያህል የምትጨክንብኝ አይመስለኝም ግን አላውቅም ። በሰአቱ ስሜቷን ለማስተካከል ስለፈለኩኝ ወደሷ ቀረብኩኝና አይን አይኗን መመልከት ጀመርኩኝ ።በሰአቱ  በጣም በራስ መተማመን ላይ ነበርኩኝ ። በልበ ሙሉንት አታምኚኝም እኔ ልሙት በፍቅር አላስባትም አልኳት። ከዛም ትንሽ የፍቅር ሰው ለመሆን ስለፈለኩኝ ግን አንቺስ ? አልኳት ፈገግ ብዬ በጣም እየቀረብኳት። እኔ ምን ? " አለችኝ ። ምንም ሳልናገር በሆነ መንገድ አየዋት ተግባብተናል ግን ላለማመን እየሞከረች ይመስለኛል ። ደግሞ ለምንድነው እንደሱ የምታየኝ " አለችኝ አይኖቿን ወደ መሬት እየተከለች ። ደስ የሚለው ቦታው ብዙም ሰው የማይተላለፍበት ስለነበረ እንጂ እንደዛ ከሴት ጋ ተቀራርቤ ሰው ቢያየኝ ኖሮ ......!!!ብቻ ግን ወደ ፍቅራችን ስመለስ  የሌለኝ ባህሪያትን እያወጣሁ ነው ። ከሷ ጋ ስሆን የሆኑ ስሜቶች አሉ ። ላቅፋት እንድታቅፈኝ እንድስማት እንድትስመኝ እጆቿን መያዝ ብቻ ብዙ ነገሮችን እመኛለሁ ። መቼም ሀብትሽ እንደዛ አያረግም ማያን የተዋወቃት ሚኪ የፍቅር ሰው መሆኑ ተዋቶለታል ። በእጆቼ አገጯ አካባቢ ይዤ ቀና እያደረኳት አይኔን እያየሽ ተመልከቺኝ እንጂ ምን ሆነሻል ? አልኳት ። አንተ እንደሱ አትመልከተኝ አትቀረበኝም " ብላ ድጋሜ አንድ እርምጃ ከኔ ራቀች ። ሚኪ ግን ከራሱ ጋ አልነበረም  የበለጠ  ወደሷ ቀረበና ለምን አላት ። ውስጤ ያለው ሌላኛው ማንነት ማለቴ ሚኪ በዛ ሰአት አልተቻለም እሷ ደግሞ ስቀርባት ትደነግጣለች ምክንያቱም ውስጤ እንድሳሳት ይገፋፋኛል ልቤ ይመታል እና እንደምትወደኝ ማሰብ እንድጀምር ያረገኛል እረፍ !!" አለችኝ ። ምን አልባት ልክ ብትሆኚስ እ አስቢ ምን ችግር አለው ደግሞ ለምንድነው ልብሽ የሚመታው እ ታፈቅሪኛለሽ እንዴ ??  አልኳት ጉፍጥጥ ብዬ ። " ሚኪ ዛሬ ምን ሆነሀል ቅድም አሞክ የነበረው ራስክን ነበር አበድክ እንዴ በዛው ?" አለችኝ ። አይ አሁን ላይ ከበፊቱ የተሻለ ጤነኛ ሆኛለሁ እሺ ብዬ ፈገግ አልኩኝ ። ትንሽ ዝም አለችና እንደማፈር እያለች " ታውቃለህ ሚኪ በቅርብ ስትታይ የበለጠ ቆንጆ ነክ እንድጎዳ ካልፈለክ አንድ እርምጃ ከእኔ ራቅ " አለችኝ ። ማለት ለምን ትጎጃለሽ እ እኔ ቆንጆ መሆኔ አንቺን ይጓዳል ? ብዬ ተመለከትኳት ። አዎ ምክንያቱም ልቤ በጣም እየመታ ነው " አለችኝ ። ከዛ ምን እንደሆንኩ አላውቅም ሊከተሉኝ የሚችሉትን  ጥፊ ጥሎ መሄድ  መጣላት ስድብ ሁሉንም ሳላስብ ስሜቴን መቆጣጠር አልቻልኩኝም ቀና አድርጌ በእጆቼ ጉንጮቿን አቅፌ በማይሆን መንገድ ሳምኳት ከዛ ግን ደስ የሚለው እኔ ከጠበኩትና ከፈራሁት የተሻለ ነበር ። ጥፊ የለውም ትንሽ የስስት ግፍተራ አለ ከዛ እጆቿን አፏ ላይ አድርጋ ዞር ዞር ብላ አየችና ምን ሆነሀል ሰው ቢያየንስ ደግሞ ድገመውና ገድልሀለሁ እሺ " የሚሉ የደስታ ቃላቶችን ተናገረች ። በጣም ሳቋን ለመቆጣጠር እየሞከረች ነበር ቢያን በሰአቱ ፊቷ ላይ ቁጣና የመዘግነን ስሜት አለመኖሩ ሰላም ሰቶኛል ። ሲጀመርም ግልፅ የሆነ ነገር ነበር ዝምታዋ መልስ ሰጠኝ ። እውነት ለመናገር ያንን ነገር ከየት እንዳሰብኩትም አላቅም ለመጀመሪያ ጊዜ የወንድ ልጅ ስሜት ያየሁባት ሴት እሷ ናት !!!ባለፈው ማያ በዛ ልክ አውርታኝ ራሱ ምንም ፍላጎትና ስሜት አልነበረኝም ለማያ ሲሆን ግን አመለጠኝ !!!! አሁን ላይ ሳስበው የዛኔ እንኳንም ተሳሳትኩ እላለሁኝ!!! በሰአቱ የሆነ አይነት ንዝረትና ከልብ የመነጨ የደስታ ስሜት በየተራ እየተመላለሱብኝ ነበር ። ለምን እንደሆነም አላውቅም በርግጥ ግን የምር ኩራት ተሰምቶኛል የዛኔ የምርም ወንድ የሆንኩ መሰለኝ ።!! ከዛም ወደሷ ቤት መሄድ ጀመርን ። እንደስከዛሬው አልነበረችም። አታየኝም አታወራኝም ቅብጥ ቅብጥ አትልም እጅ በደረት አርጋ ቀስ እያለች መሄድ ጀመረች ። ሳወራትም በጣም በርጋታ መመለሷ ግራ ቢገባኝ ደህና ነሽ ልዕልና ችግር አለ አስከፋሁሽ እንዴ ?? አልኳት ። እንዴ ማለት ምንም አልሆንኩም አረ " አለችኝ  ።እና ምንድነው በአንዴ የተቀየርሽው ? አልኳት ። ሳቋ አመለጣት ነገር ግን በነዛ የሚያምሩ እጆቿ ሳቋን ከፊቷ ላይ ተቆጣጠረችና " አይገባህም እንዴ እንደነገሮች እየተቀየርኩ ነዋ " አለችኝ ። ንግግሯ የበለጠ ግራ አጋባኝ ። ማለት እንዴት ብዬ መልሷን መጠበቅ  ጀመርኩ " ካሁን ቡሀላ ኩል መሆን አለብኝ ነገሮች ተቀይረዋል ጓደኝነት እና ፍቅር ላይ አንድ አንነት ሰው አልሆንም አንተም የፍቅር ሰው ሁን እስኪ አሁንም ልዕልና ነው የምትለኝ እኮ ???" አለችኝ ። የኔ አናት  ሁኔታዋ በጣም ደስ እንዳላት ፊቷ ላይ ይናገራል !!!! አልፎ አልፎ ለስላሳ እጇቿን እየያስኩ ወደቤት ሄድን ። ስንደርስ ሳሚ ምሳ የሚበላበት ጠረንጴዛ ላይ ቁጭ ብሎ በሀሳበ ተውጦ ነበር ደ ቀበጧ  ልጅ ደህና ነህ አባዬ እንዴት ዋልክ ችግር አለ? " አለችው ። ሳሚም በአፀፋው ፈገግታ እያሳየ ደህና ነኝ ልጄ ምነው ? አለ እሺ ታጥቤ መጣሁ " ብላ ወጣች ። ከዛም ሶስታችንም አንድ ላይ ተቀምጠን ማውራት ጀመርን !!! ከዛ ከሰአታት በፊት ሰላም ታማ እንደነበርና በስንት መከራ እንደተረጋጋች ነገረን ። ከዛም ቁጭ ብለን ልክ እንደ ጓደኛ ስናወራ ነበር። ሳሚን ባየሁት ቁጥር ትዝ የሚለኝ አባቴ ነው ። ረዝሜ ብልም ሰበር ብዬ ማቀፍ የልብን ማውራት እኛ ቤት እንደ ጎጂ ባህል ነው የሚታየው ። በሰአቱም ሰላም  ድብር ብሏት ወደኛ መጣች ። ምን እንደነካት አላውቅም ገና ስታየኝ እሪ ማለት ጀመረች ከስከዛሬው ተለየችብኝ እና በጣም መጮህ እና መሣደብ ጀመረች ???? ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣2⃣
369