ar
Feedback
📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

الذهاب إلى القناة على Telegram

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾 ➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና እንጊሊዘኛ ..... መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ። 📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️ B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር 100K ይደርስ ነበር ። For any comment @Meki3

إظهار المزيد
2 270
المشتركون
+324 ساؚات
+67 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
سبتمبر '26
سبتمبر '26
+11
في 0 قنوات
أغسءس '26
+86
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '26
+141
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+109
في 1 قنوات
Get PRO
مايو '26
+67
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+48
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+60
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+45
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '26
+65
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+92
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+83
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبع '25
+56
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+50
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '25
+70
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+58
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+66
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+92
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+74
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+55
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+38
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+56
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+68
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+67
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبع '24
+37
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '24
+65
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+81
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+35
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+36
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+42
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '24
+47
في 2 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+46
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '24
+32
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+63
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+37
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبع '23
+63
في 2 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+58
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '23
+77
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+50
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+63
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+39
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+41
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+54
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+192
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+125
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبع '22
+57
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+66
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '22
+64
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+40
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+43
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+64
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+93
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+71
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+36
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+47
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+54
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+75
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبع '21
+135
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+97
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '21
+132
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+142
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+114
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+71
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+190
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+122
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+172
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+180
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+1 524
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
04 سبتمبر+2
03 سبتمبر+5
02 سبتمبر+2
01 سبتمبر+2
منشورات القناة
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል3⃣0⃣ ..........ስትመጣ አየዋት ። በሰአቱ ሳናስበው ከልዕልና ጋር ተቀራርበን  ነበር ።ከቤቱ ስንወጣ ራሱ እየተሳሳቅን ነበር ። እና ፊት ለፊቴ እሷን ሳያት ያገጠጠው ጥርሴ ባንዴ ሽሽግ አለ ። ፊት ለፊት ስንገጣጠም የማያ ፊት ላይ ያየሁት ድንጋጤና የመሰበር ስሜት አስተውዬዋለሁ ። ከእኔ በላይ ደግሞ ልዕልናን በሆነ አስተያየት ተመለከተቻት !!! ምን ሆና ነው ብዬ ፈራሁ ። ከዛ በፈጣጣው ወደኛ መጣች ። ልዕልና ከዚህ በፊት አይታት ስለማታውቅ መታ ፊት ለፊቴ ስትቆም ግራ በተጋባ ፊት ዞራ አየችኝ ። እኔም ግራ ገብቶኝዐበዝምታ ስመለከት ነበር ። እሷ ናት ልጅቷ ?" አለችኝ ። ጭራሽ ደግሞ ከኔ መልስ እየጠበቀች ነበር ። ምን ማለት እንዳለብኝ እንኳን የማላቀው እኔ ሁለቱንም በየተራ ተመለከትኳቸው ። አይናቸውን እኔ ላይ ተክለው ምላሽ ይጠብቃሉ ። በዝምታዬ መፅናቴን የተመለከተችው ማያ " ንገረኛ እሷ ናት አይደል እኔን ሳታድነኝ ጥለህ የመሄድህ ምክንያት  ??. እሷ ናት አይደል በፍቅር የጣለችክ ከእኔ ያራቀችክ ?? እሷ ናት ማለት ነው ክብሬን ማንነቴን ልስጥህ ባልኩኝ እንቢ እንድትል ያደረገችህ ........." የሆነውንም ያልሆነውንም ቀባጠረች ። የእኔ መልስ አሁንም ዝምታ ቢሆንም ልዕልና ግን በሰማችው ነገር የተደሰተች ይመስል ፍልቅልቅ እያለች ነበር  ወይኔ ማያ !!!! ከእኔ መልስ አለማግኘቷ ሲገባት ራሷ መልሳ ለነገሩ ልክ ነህ እሷ ከእኔ በላይ ቆንጆ ናት አይደል በዛ ላይ የሚያምር አለባበስ አላት የሀብታም ልጅ መሆኗን እገምታለሁ በዛ ላይ ደግሞ አንተ እንደምትወዳት እሷም  እንደምትወድክ በእይታዋ ያስታውቃል !!! ግን እምልልሀለሁ አክስቴ ራሱ የእኔን ያህል እንደምትወድህ እጠራጠራለሁ !!!!" ብላኝ አረፈችው ። አክስቴ የምትለው እናቴን ነው ። ንግግሯ የሆነ ደስ ሚል ነገር ቢኖረውም ግን ልዕልና ትኩረቷንና እምነቷን እኔ ላይ እንድትጥል አድርጓት ነበር ። እንደምወዳት መተማመን ጀምራለች ። በጣም የምፈራው ነገር አሁን ባለሁበት ሁኔታ  የምሯን ነው ትወደኛለህ ? የሚል ጥያቄ ከልዕልና አፍ መስማት ብቻ ነው !!!!! ምክንያቱም እንደዛ አለችኝ ማለት ፈጣሪ የሰጠኝን ዳግመኛ እድል ገደል እንደመክተት ነው ። ብትጠይቀኝ ልክ ማያን እንዳጣዋት እሷንምአጣታለሁ ። ምክንያቱም እኔ ስሜቴን መግለፅ አልችልምምም!!!! ወደ ማያ ስመልሳችሁ ግን ሳታስበው እንባዋ አመለጣት ። እሷ ስታለቅስ ማየት አልፈለኩም አንገቴን ደፋሁ ። ተጨማሪ ንግግር ሳታደርግ መልካሙን ሁሉ እመኝልካለሁ እሺ ትገባሀለች ያዝልቅላችሁ " አለችኝ ። ወዲያው ደግሞ ወደ ልዕልና ዞራ " አዎ ቆንጆ ነሽ አምናለሁ ግን ፀባይሽም እንደመልክሽ ይሁን እሺ ገባሽ አይደል !!! ሀብትሼን በምንም ነገር ብታስከፊው አንቺ አትኖሪም ምክንያቱም ሁሌ በቅርብሽ አለሁ " ብላ ዝታ በመሀላችን አልፋ ሄደች ። ምን ማረግ እንዳለብኝ አላውቅም ልክ ማያን ተከትዬ ልሄድ ስል ልዕልና በሚያሳዝን ፊት እያየችኝ ሚኪ አትወደኝም እኔን ?" አለችኝ ። ወዲያው ማያ ወደኔ ዞራ ታየኝ ጀመር ።  በሁለቱ ሴቶች መሀል ሆኜ በየተራ አየዋቸው ። ልክ ልሁን አልሁን ባላውቅም የግድ መወሰን አንዷን አጥብቄ መያዝ ነበረብኝ ግን መወሰን ከብዶኝ መሀል ላይ ቆሜ ስወዛገብ ነበር ።በዛ መሀል ከየት እንደመጣ አላውቅ የማያ አይኖች እንባ አዝለዋል አሳዛኝ የልዕልና ፊት ደግሞ እግሬን እንዳላንቀሳቅስ አስረውኛል ። አዝናለሁ ሀብትሽ እድልክ አልቋል " አለችኝ ። ማለት ማያ እስኪ ልትረጂኝ ሞክሪ እያልኩ አይን አይኗን ስመለከታት ፈገግ አለች ። ምንድነው ብዬ ግራ በተጋባ ፊት እየተመለከትኳት እያለ ችግር አለ ?" የሚል ድምፅ ሰምቼ ዞር ስል ቀጥታ ወደ ማያ ሄዶ ግንባሯን ሳማት ። ሰውዬው ፊቱ አዲስ ሆነብኝና ግራ ገብቶኝ ቆሜ እስክታስረዳኝ መጠበቅ ጀመርኩኝ አረ ምንም ችግር የለም ጓደኞቼ ናቸው ላስተዋውቅህ " ብላ ወደኔ ይዛው መጣችና ሀብታሙ ይባላል እንደ ወንድሜ በለው ጓደኛዬ ነው እሷ ደግሞ የሱ ሚስት ናት ያው አልተጋቡም ግን በቅርቡ ሰርጋቸውን እንበላለን " አለችው ። እሱም እጁን ለሰላምታ እየዘረጋ በላይ እባላለሁ ባለቤቷ ነኝ " አለ ። ጭራሽ አልጠበኩኝም የሰርጉ ቀን ትኩረት ሰጥቼም አላየሁትም ከዚ በፊት በሱፍ ምናምን ተወጣጥሮ አይቼው አቃለሁ ግን በኖርማል አለባበስ ሳየው የተለየ ሰው ሆነብኝ ። እኔ ሳስብ የነበረው የሆነ ከባድ ሰው ትልቅና የሚያስፈራ ሰው አርጌ ነበር ። በዛ ላይ አባቱን በደንብ ስለማቀው ልክ እንዳባቱ በገንዘብ የሚያምን ጉረኛ እና አፈር አይንካኝ የሚል አይነት ሰው መስሎኝ ነበርጰ። አልዋሽም ማያ በጣም ትበዛበታለች !!!!!!! ማያ እና እሱ አይገናኙም በርግጥ በዛ ላይ በእድሜ ቢያንስ አምስት አመት በላይ እንደሚበልጣት እገምታለሁ ግን እንዳሰብኩት አያስጠላም !!! " በቃ አሁን እንሂዳ ለፈተና ማረፍ አለብሽ ነገ ትሄጃለሽ እኮ " ብሏት እጇቿን ይዞ መሄድ ጀመረ ። ሲጀመር እኔ ነኝ ጥፋተኛ በሰአቱ አዝኜላት እንጂ አፍቅሪያት አልነበረም ማለት ነው??? ብዬ ማሰብ ጀመርኩኝ !!!! ከደቂቃዎች በፊት ልትሄድ ስትል ልከተላት እየቃታኝ ነበር የቆየው አሁን ግን አጇን ይዟት ሲሄድ ሳይ ምን አልባት የደስታ እንጂ ሌላ ስሜት አልተሰማኝም ነበር !!!! አትሂጂ ብዬ ልለምናት ላስቆማትም ሆነ ልከተላት አላሰብኩም ሁላ !! ለነገሩ ለምን ብዬ ???!!! ሳስበው ትክክለኛ ነገር እንደሆነ ልቤ ስለሚያቀው ይመስለኛል ያልተከፋሁት !! በሰአቱ ልጁን ሙሉ በሙሉ በአባቱ አይን ስላየሁት ይጎዳታል ትምህርቷን እንድታቋርጥ ያረጋታል በገንዘብ እንደገዛት ቢሰማውስ ?? እያልኩ እፈራ ስለነበር እንዲሁም ማያ በጣም ቆንጆ እና ጨዋ ምርጥ ባህሪ ያላት ሴት ስለሆነች የማይመጥናት እጅ ላይ ወደቀች ብዬ ስላሰብኩኝ እንዲሁም ደግሞ አሱን ያገባችው በእኔ ጥፋት ነው ብዬ ስላሰብኩ ይመስለኛል ያመመኝና የተጎዳሁት !!! እንደውም ሳስበው ሴት ልጅ የምትወደውን ብቻ ሳይሆን የሚወዳትን ማግባት በጣም የተሻለ አማራጭ ይመስለኛልም !!! ቢያንሱ እሱ እንዳየሁት ከሆነ ያከብራታል ያስብላታል ይንከባከባታል በሰው ፊት አያዋርዳትም በዛ ላይ በገንዘብም ቢሆን ሀብታም የሀብታም ልጅ ነው እኔ በስም ብቻ ከተሸከምኩት ይልቅ የተሻለ ነው !!! ስለዚህ እንኳንም ከሱ ጋር ሆነች እንኳንም አልተሳሳትኩ እንኳንም ስሜት አልኖረኝ ብዬ ፈጣሪዬን አመሰገንኩ ደ በዛ ሁላ ሀሳብ መሀል ግን ለማያ ብዬ ጥያት ልሄድ የቃጣኝና ማያ ስትሄድ ወደሷ ልመለስ ያሰብኩት ልዕልና ትዝ አለችኝና ወይኔ ጉዴ ብዬ ስዞር በሆነ አይነት አስተያየት እያየችኝ ነበር ። ይቅርታ ልዕልና ብዬ ወደሷ ስዞር  ....... ....... . . ይቀጥላል ክፍል 3⃣1⃣

2
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣9⃣ ..........ያሳየችው ፊት ደስ አይልም ነበር!!! ደስ የሚለው እኔም አፀፋውን እየመለስኩ ፊቴን ከሷ በላይ ከስክሼ ምነው ልዕልና ? አልኳት ። ዞር ብላ አባቷን ተመለከተችና " አይ ገርሞኝ ነው " ብላ በቅጡም ሳትጨርስ ለምን ? ብዬ ቆሌዋን ገፍፈኳት !!!አይይይይ....." ብላ ነገሩን አረዘመችው ። በጣም ንዴት  ላይ መሆኔን የተመለከተው ሳሚ ልዕልናን በአይኑ ዝም እንድትል እየነገራት ነበር ። እኔ ትክክል መሆኔን ስለሚያውቅ ምንም ለማለት አልደፈረም ነበር !! ለደቂቃዎች ያህል በመሀላችን ዝምታ ከሰፈነ ቡሀላ ልዕልና ቀልጠፍ ብላ እየተቁለጨለጨች ይቅርታ አንዴ ላውራ ?" ብላ ሁለታችንንም ተመለከተችን በሰአቱ ሳሚ ምንም እንድታወራ የሚፈልግ አይመስልም !! ሳስበዎ ነገሮችን እንዳታበላሽ  ፈርቶ ይመስለኛል !!! እኔ ደግሞ በተቃራኒው መጥፎ ንግግር ተናግራኝ እሷን መጥላት እፈልጋለው !!! ምክንያቱም ልጅቷ በጣም ቆንጅዬና የምታሳሳ ናት !!!የምጎዳው የምታመመው ለማያ ቢሆንም ሳስበው ግን ልዕልና ለእኔ የማትገባ አይነት የሆነች ልዕልት ትመስለኛለች !!!! ራሴን በደንብ አረጋግቼ አውሪ ምንም ችግር የለውም አልኳት ቀለል ካላት ብዬ ፊቴን ፈታ እያረኩኝ ። " ይቅርታ ሚኪ ..."ብላ ወሬዋን ስጀምር ቶሎ ጣልቃ ገብቼ ሀብተትሽ በይኝ ሀብታሙ ነው ስሜ አልኳት ቶሎ ጣልቃ ገብቼ ።በስሜ እንደማንኛውም ሰው ፈገግ ብላለች !!!ደስ የሚለው ቅልል ያለች ልጅ ስለሆነች አይ እኔ ሚኪ ብልክ ይሻለኛል " አለችኝ ! ሳልፈልግና ሳላስበው ፈገግታዬ አመለጠኝ ። ስኮሳተር ተጨንቆ የነበረው ሳሚም አብሮኝ ፈገግ እያለ ነበር !!! " ደሞ አንተን የመሰለ ውብ ልጅ ሀብታሙ የሚል ስም አብሮ አይሄድም እሺ በስመአብ " አለች ቀልድ መሆኑን ለማሳወቅ እየሳቀች !!! እኔም እኮ እሱን አስቤ ነው የቀየርኩት አልኳት ፈገግ ብዬ ። እሺ ወደ ሀሳቤ ልመለስና እኔ አንተ ምንም ብትሆን አይጨንቀኝም !! ካስቀየምኩህ ይቅርታ ግን እኔ አንተን የሳልኩበትና ያገኘውክ ቦታ ስላልተገጣጠመልኝ ብቻ ነው !!! እንጂ አንተን የወደድኩህ ማለቴ ( ክው ብላ እጆቿን እያወራጨች )የወደድንህ  አንተነትህን ነው !! እኔ አንተ ስለምትኖርበት ቤት ሰፈር መንደር ምንም አይጨንቀኝም !!! ሲጀመር ማንም ተንደላቆ የኖረ የለም አባዬ አንተ ካለህበት ሁኔታ የከፋ ቦታ ላይ አድጎ አሁን ላይ ....አንተ ደግሞ ፈጣሪ ሁሉን አሟልቶ ነው የሰጠቅ እኮ በጣም ውብ ነህ ፀባይክ ለመስራት ፍላጎት አለህ ቋንቋ ትችላለህ ቁመትና አለባበስህ ......." ብላ ዝም አለች ቋንቋ ያለችው እንግሊዝኛ ቋንቋን ቀለል አድርጌ መጠቀም እንደምችል አስታውላ ይመስልኛል !አለባበስ ቁመት ስትል ሞዴሊንግ እንድማር እየነገረችኝ ይመስለኛል !!! ግን በጣም ውብ ነህ ሁሉን አሟልቶ የሰጠህ እንዲሁም የወደድኩህ የሚሉት ቃላቶች እኔና ሳሚ ፈገግ ብለን እንድናያት ያደረገው ንግግር ይመስለኛል!!!! ሳላስበው በንግግሯ ተስቤ ነበር !!! ህመሜን የምርም ሙሉ በሙሉ የለቀቀኝ ይመስለኛል!!!!! ደስ እያለኝ ነበር !!!በተለይ ደግሞ እኔ ትለኛለች ብዬ የጠበኩት ነገር እና እሷ ላይ ያየሁት ነገር ምንም ስላልተገጣጠመ ደስ ብሎኛል !!! ሀብታሞች እንደዛ ያስባሉ ብዬ ስላላሰብኩኝ ተገርሜ ነበር ። ሳናስበው ሶስታችንም በፈገግተታ ተሞልተን ሳለ የሳሚ ስልክ ጠራ ......ሳሚም ቶሎ ከተቀመጠበት ተነስቶ ለማውራት ሄደ ። ንዴቴ በአንዴ ቀለል ብሎ በፈገግታ ስመለከታት አይኖተቿ እኔን ላለማየት ማማተር ጀመሩ !ለኔ ያለሽ ፍቅር አባትሽ ፊት እስከመናዘዝ ነው ማለት ነው ? አልኳት በፈገግታ ተሞልቼ  !! እ አረ እንደዛ  አይደለም " እያለች እያለ ሳሚ ወደኛ መጣ ። " ልጆች እንግዲህ ይቅርታ በጣም አስፈላጊ ስብስባ ረስቼ ነው መሄድ አለብኝ ስጨርሱ ደውሉልኝና መኪና እልክላይዋለሁ ወደቤት ሂዱ " ብሎን እየተቻኮለ ከኪሱ የሆነ ያህል ብር አውጥቶ ለእኔ ሰጠኝና የተጠቀምነውን ክፈሉ ካነሰ ደግሞ ደውሉ " ብሎን እየፈጠነ ሄደ ። ይሄ ማለት ደግሞ እኔና ልዕልና ብቻችንን አንድ ደስ የሚል አየር ያለው ካፌ ነግር ውስጥ ተቀምጠን እየተፋጠጥን ነው ። ታውቃላችሁ አንዳንዴ በጣም ራሴን እስከመጥላት የሚያደርስ በራስ አለመተማመን ውስጥ ከቶኛል !!! ልክ ከማያ ጋር ስሆን ሙሉ በሙሉ ማያን እንደምወዳት ይሰማኛል በማግባቷም ተከፍቻለሁ ግን ልክ ልዕልናን ሳገኛት ሁሉንም ነገር ጥርጣሬ ውስጥ ትከተዋለች !!!! ሁለታችንም ፋንታችንንም ጨርሰን ቁጭ ብለን ስንፋጠጥ የተመለከተን አስተናጋጅ ወደኛ መቶ የሚጨመር ነገር አለ ? " አለን ። ምንም አያስፈልግም ለማለት ገና ላወራ ስል ቀድም ብላ ለእኔ ማኪያቶ አምጣልኝ " አለችው ። በነገራችን ላይ ያን ያህል ውድ እንዳልሆነ ባውቅም ግን ቀምሼ የማላቀው እኔ እድሌን ለመጠቀም ያህል ለእኔም አልኩት ። ከትኝሽ ቆይታዎች ቡሀላ ይዞልን መጣና መልካም ጊዜ ብሎን ሄደ ። ሙሉ ሰአቱን ልዕልና አይኖቿን ከእኔ ለማራቅ  የምታረገውን ትግል እየተመለከትኩ ምስጥ ብያለሁ ። ሴት  ልጅ  የወደደችውን ወንድ ልጅ አይን በጣም ትፈራለች !! ሴት ልጅ ከወደደችክ ያንተን አይን ላለማየት አይኖቿን ገደልም ልትከት ትችላለለች !!!! በመሀላችን ያለውን ዝምታ ቀልድ ለማረግ ያህል እና ስለ ባልሽ ትንሽ ንገሪኛ ? አልኳት ። እ የምን ባል ነው ሚኪ " አለችኝ አሁንም እጆቿን የማኪያቶ ሚንኪያ ላይ አድርጋ ።ባል አለኝ ብለሽኝ ነበር እኮ አልኳት እኔም ለማወጣጣት ስለፈለኩኝ "አረ እኔ እየደዛ አይነት ነገሮች ላይ የለሁበትም እኮ " አለችኝ ። የዛን ቀን ምን እይደነካኝም አላውቅም በጣም ቀልደኜ ሆኜ ነበር ከቤት ስወጣ የበረኩበት ሙዶ እና እዛ እያሳየሁት ያለሁት ሙድ አይገናኝም ሁላ !!!! ጭራሽ ብሶብኝ እና እኔ የመጀመሪያሽ ነኛ እ !!! አልኳት እየሳኩኝ ። ማኪያቶው ጠረንጴዛ ላይ እንደተቀመጠ በመሆኑ ምንም ባጠጣም ምራቋ ያነቃት ይመስል ትን ብሏት ውሀ ጠጥታ የው የለቀቃት ሁላ !!! እንዴ ምየው ችግር አለ ?  አልኳት እሷም ቶሎ ብላ አረ የምን ችግር ጠጣና ቶሎ እንውጣ በቃ አለችኝ ። እሷ እንዳደረገችው አማሰልኩና ቀመስኩት ። ሀለት የምወዳቸው ነገሮች ድብልቅ ነው በጣም ይጣፍጣል !!!! ቶሎ መውጣት የፈለገች ትመስላለች ቶሎ  ቶሎ መጠጣት ጀመረች እኔም ቶሎ ጨርስኩና ሂሳብ መጣ ። የመጣው ብር ሳሚ  ከሰጠኝ አንፃር ትንሽ ነበር !!! በእኔ በኩል እናቴ በቀን ለአንድ ጊዜ ምግብ የወር ወጪዋን እንዳወጣን ብሰማ እንደማታናግረኝም አቃለሉ ከሳሚ ብር ላይ ብዙ መትረፉ ግን ደስ አላለኝም ። ከዛ ቲፕ ኘስቀምጠን ወጣንና በር ላይ እንኪ ለሳሚ ስጪው እሺ ብዬ ብሩን ስሰጣት ልትቀበለኝ ፍቃደኛ እየሆነች አልነበረም !!!! " አያገባኝም ራስክ ስጥ ሲቀጥል ደግሞ ገና ግብዛው መች አለቀ ትጋብዘኛለህ " ብላኝ አረፈች ። አስቡት በአባቷ  ብር  እኔ ስጋብዝ !!!! መኪና ጥሩ ብሎን ቢሄድም እኔ በየቀኑ በእግሬ የምመላለስበት መንገድ ነውና ቅርብ ነው በዛውም እያወራን እንሄዳለን ብያት መንገድ ጀመርን ። ልክ የሰፈራችን መተጣጠፊያ መንገድ ላይ ስንደርስ ከሷ ጋ እያወራን ከት ብዬ ስቄ ቀና ስል ማያን ከፊት ለፊቴ ወደኔ ስትመጣ አየዋት ......... ....... . . ይቀጥላል
114
3
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣8⃣ እኔ ግን እንቅልፍ ሊወስደኝ አልቻለም !!! ይልቁንም መድሀኒት ያጣ እብድ መሠልኩ እሷ ገና ከኔ ከመራቋ መታመም ጀመርኩኝ ። ቀኑም እየመሸ ነበር !! አልዋሻችሁም ከየት እንደሚመጣ እንኳን ሳላውቀው እንባዬ ዝም ብሎ መፍሰስ ጀምሯል ለሊቱን ሙሉ ሳለቅስ አደርኩ እናቴም ከእኔ እኩል ስታለቅስና ስትጨነቅ አደረች ሰካራሙ አባቴ ብሩ አላለቀችበትም መሠለኝ ቤት መቶም አያቅ የፈረደባት እናቴ ብቻዋን ስታስታምመኝ አደረች ። እናቴ ተስላልኝ ነው መሠለኝ ሲነጋጋ እንቅልፍ ወሰደኝ ።የነቃሁት ቀን ላይ ቢሆንም ስነቃ ተሽሎኝ ነበር !!! ማያ ሳትመጣ ሶስት ቀናት ያህል ቆየች ። ማትሪክ ፈተና አራት ቀን ቀርቶታል ። የተለያየ  ትምህርት ቤት ተልከን  ነው የምንፈተነው እና እኔና እሷ አንድ ላይ ቢደርሰን ደስ ይለኝ ነበር !!! ደግሞ ሶስቱንም ቀን ሳስበው የነበረው ከዛ ሰውዬ ጋር ተኝታ የሚለውን ሀሳብ እያሰብኩ መቀበል እስኪከብደኝ ድረስ ሳስበው ነበር !!ግን ሁለቴ አሳልፌ ሰጥቻታለሁ የሷ ጥፋት አይደለም !!ቀኑ ቀጥሎ ቅዳሜ ቀን ትምህርት ቤት እንድንመጣ አርብ ጠዋት ተነግሮ በወሬ በወሬ እኔም ሰማሁኝ ። ቁጭ ብዬ ስለዛ እያሰብኩኝ እናቴ መጣራች ጀመረች አቤት እማ ስላት " ሰው ይፈልግሀል " አለችኝ ። ማያ መጣች ብዬ ባንዴ ፊቴ በርቶ ነበር !! ለማየት የናቴን ጀሳሳ ጎጆ አጎንብሼ ስወጣ ግን ከተበኩት በተቃራኒ ያልተጠበቀ እንግዳ ነበር ያየሁት !!ለምን እና እንዴት እንደሆነ ባላቅም ቀበጧ ሞልቃቃዋ የልጥጥ ልጅ ሰላምና አባቷ ሳሚ በር ላይ ቆመዋል !!!ልዕልና በሆነ አይነት አስተያየት ስታየኝ ነበረ ። እኔም ደንግጫለሁ !! በሆነ መንገድ ግን ትኩረቴ ማያ ጋር ስለሆነ ምን አገባኝ አይነት ስሜት አበረታኝና ጠጋ ብዬ ሰላም ሳሚ እንዴት ነህ ሰላም ደህና ናት ? አልኩት ። ከእሱ መልስ በፊት ግን ልዕልና  ቀደም ብላ ሚኪ እዚህ ምን ታደርጋለህ  ?? " ብላ አየችኝ ። ማለት ? አልኳት እንዳልገባሁ ሆኜ እዚህ ቦታ ላይ ምን ትሰራለህ በዛ ላይ አንተን ለማግኘት ስንት እንደለፋን ታውቃለህ ?? " አለችኝ ። በሰአቱ ለመመለስ ፍቃደኛ ባለመሆኔ በዝምታዬ ፀናሁ ሳሚም ጣልቃ ገባና ልጄ በሰላም ነው አይደል ሳትናገር የጠፋከው በዛ ላይ ፊትህ ልክ አይደለም አሞካል እንዴ ችግር አለ ? " አለኝ ። ልዕልና ከምጠይቃቸው ጥያቄዎች በተቃራኒው ነው የሱ ሀሳብ ለዛም ነው ምርጥ ሰው ነው የምለው !!!! እኔም እዛ ቤት መቆየታችንን ስላልወደድኩት በሰላም ነው ሳሚ እየሄድን እናውራ አልኳቸው ። ሰው ግቡና እናውራ ይላል እኔ...... ግን ውጪውን  አይታ እንደዛ ካለች መቼም ውስጥ ስትገባ ራሷን እንዳትስት ፈርቼ ነው !!!! ሳሚ ስለኔ በትንሹም ቢሆን ስለነገርኩት ቶሎ የተረዳኝ ይመስላል " አዎ ደስ ይለኛል እናወራለን በሉ ኑ " ብሎ ቀድሞን ወጣ ። ልዕልና ግን ጉዳዩን ለመረዳት የከበዳት ትመስላለች !! የኔ ቤት መሆኑን ለመቀበል የከበዳት ይመስል ሚኪ  ምን  ሆነህ ነው እ እዚህ ጊቢ ምን ታደርጋለህ ከቤተሰብ ተጣላህ እንዴ ደግሞ ለምንድነው እየራከኝ ያለከው ?? ብላ በጥያቄ አጣደፈችኝ ። እንደሁሌው መመለስ የማልፈልገው ጥያቄ ነውና በዝምታ አቀረቀርኩ ። " እኔና ሚኪ የምንወዳት ቤት አለች እዛ እንሂድና ቁጭ ብለን እናወራበታለን " አለ ሳሚ አይ እኔ ይቅርብኝ ወደቤት ልመለስ ትንሽ አሞኛል አልኩት ! ወደ ቤት ?" አለች ልዕልና ነገሩን ለመረዳት እየሞከረች ያለች ትመስላለች ። " ቆይ ቆይ ከእኛማ እንዲህ በአንዴ መራቅ አትችልም ሁሉ ንም ነገር እናውራው ይቀልሀል ካስፈለገም ሆስፒታል ደርሰን እንመጣለን በሉ ግቡ " ብሎ መኪናው ውስጥ ገባ ። እኔም ጋቢናውን ከፍቼ እስክትገባ ቆሜ ጠበኳትና ከዃላ ገብቼ ቁጭ አልኩኝ ። እንደነ ሳሚ አይነት የለጠጡ ሰዎች የኛ መንደር ብዙም ስላልተለመደ መንደርተኛው ብቅ ብቅ እያለ እያዩኝ ነበረ እንዲሁም ከኔ ችግር አለባቸው አሁንማ ስርቆት ጀመረ እንዳይሉ ፈራሁ ። በዝምታና በጨዋነት  ቢያምኑብኝም  ስኮሳተርና ስለምደባደብ እንደዛ እንዳያስቡ ፈራለሁ !! ብቻ ግን ከዚ በፊት ወደወሰደኝ ቦታ ይዞን  ሄደና መጀመሪያ ምግብ ጋበዘን ! ከዛም ለእኔና ለሷ ፋንታ አናናስ አዘዘና ማውራት ጀመርን ። ልዕልና ለመስማት ቸኩላለች ። " ድንገት ስጠፋ እኮ ተጨንቀን ነው በስንት ፍለጋ ነው ያገኘንክ ተጨንቀን አለኝ " ይቅራ አርጉልኝ ሰሞኑን ትንሽ ችግሮች ተደራርበውብኝ ነው አልኳቸው ። " እሺ እዛ ቦታ ምን ታረጋለህ ሚኪ " አለችኝ ልዕልና ፊቷን አጨማዳ ። ከዛ በላይ መታገስም መደበቅም ዝም ማለትም አልቻልኩኝም አየር በደንብ ሳብኩና ያ ቦታ የምትይውና የተፀየፍሽው ቦታ የእናቴ ቤት ነው የእኔም ቤት ማለት ነው !! እኔን እንድጠራልኝ የጠየቅሻት ሴት እናቴ ናት !! እኔ ማለት የአንዲት ምስኪን የደሀ ልጅ ነኝ እኔ ስለኔ ምንም ሳልላችሁ ራሳችሁ ናችሁ የካባችሁኝ !!! ሰውን በአለባበሱ ስለምትፈርጁ አይደለ !??? ብዬ ግንባሬን ቋጥሬ እንባ እየተናነቀኝ ተመለከትኳት ። ምክንያቱም ፊቷ በጣም ያስጠላ ነበር ስለዛ ቤት ስታወራ ያሳየችው ፊት ልክ አልነበረም !!!........ ....... . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣9⃣
223
4
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣7⃣ አልጋው ጫፍ  ላይ ቁጭ ብላ በራሷ እየተናደደች ነበር ። የኔ ምላሽ አለመስጠት አናዷታል !!እንደዛ ሳያት የምር ከፍቷትና ተደብራ ስላየዋት እግሯ ስር በርከክ ብዬ እኔን ቀደንብ ታውቂኛለሽ ብዬ አስባለሁኝ ለማንም ሴት ተሰምቶኝ የማያቀው ስሜት እየተሰማኝ ነው ያለው !!!ለሊቱን ሙሉ እንቅልፍ እንቢ ብሎኝ ሳለቅስ ነው ያደርኩት !?! ግን አሁን ከእጄ አምልጠሻል ምን አልባት በራሴ ጥፋት ቢሆንም አጣሁሽ !!!በቃ አሁን የሰው  ነሽ አለቀ !!!አልኳት ። በርግጥ ከልቤ አይደለም !!! እዚሁ አጠገቤ እንድትሆን ብፈልግም ግን እንድትሄድ እየነገርኳት ነበር ። አሁንም እኮ አንተ ጋ ነኝ እየለመንኩህ ነው እኮ አንዴ አጠፋህ እሺ አትድገመው " አለችኝ እያለቀሰች ። በቃ አይሆንም አልችልም ስላት ተነስታ አቀፈችኝ ። ሁለታችንም ከልብ ተቃቅፈን የራሳችን አለም ውስጥ እያለን በሩ ክፍት አለ ። ጥፋት እየሰራሁ እንደነበር ስለማውቅ መሠለኝ ክው ነው ያልኩት !!! እኔ ድርቅ ብዬ መዞርም ሲከብደኝ ማያ ዞር ብላ አየቻት ። ሰላም ዋልሽ ልጄ ምነው ችግር አለ እንዴ ?  " አለች ። ድምጿን ስሰማ ኡፍፍፍፍፍፍ ነው ያልኩት ምክንያቱም  የእናቴን ድምፅ በደንብ ነው የማቀው።እሷ ማየቷም ችግር ቢኖረውም ግን የተሻለ ነው ። እናቴ ወደ ውስጥ ገብታ በሩን ዘግታው በተደናገጠ ፊት ሁለታችንንም በየተራ ማየት ጀመረች ።ከድንጋጤያችን ብዛት ሁለታችንም ቃላት አጥሮን አፈጠጥንባት ።የበለጠ ግራ የተጋባችው የኔ የዋህ እናት " ልጆች ምን ሆናችዋል ማያ ስርካለም ምን ሆነች ባለቤትሽ ሊጎዳሽ ሞከረ እንዴ ...??" ብዙ ነገር እያለች ጭንቅላቷ ላይ የመጡትን ጥያቄዎች አወረደችብን ። ለትንሽ ደቂቃዎች ዝም ብለን የቆየን ቢሆንም ከደቂቃዎች ቡሀላ ግን  ማያ ራሷን ሰብስባም ቢሆን ተረጋጊ አረ ምንም አልተፈጠረም አለቻት ። እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ታዲያ ልጄ አስደነገጥሽኝ እኮ በዛ ላይ ሁለታችሁ ምን እያወራችሁ ነበር ?" ብላ ተመለከተችን ። ማውራታችንን ብቻ ከተመለከተችም ተመስገን ነው !!!!ምንም አረ  ሀብትሽን ፈልጌው ነው " ብላ ነገሩን አቡካካችው ። ደግሞ አመት ኮ ከላይ መለጣጥ ቡሀላ ቀና ብላ አይታኝ ማለቴ........" ብላ ታየኛለች ። ሁኔታዋ ትንሽ ፈገግ አስባለኝ ። " ለምን ልጄ በሰላም ነው ወይስ ?" አለቻት አይ አክስቴ በቃ ችግር የለውም በቃ አውርተናል ልሂድ " ብላ ተሸፍናበት የመጣችውን ሻርፕ አነሳች ። የኔ ልብ አሁንም ግራ እንደተጋባ ነው ! የሆነ ልቤ ቶሎ ከዚህ ቤት ወታ እንድትርቀኝ ይፈልጋል የሆነ ልቤ ደግሞ አጠገቤ ቁጭ እንድትል ይፈልጋል !!!! እዚህ ድረስ መተሽማ ዝም ብለሽ አቴጂም ተቀመጪ ልጄንን አሞብኝ እኮ መድሀኒት ላመጣለት ሄጄ መቶ ይመርመር አሉኝ እሱ ደግሞ ደረቀ ቡና ጠጥተሽ ትሄጃለሽ ቁጭ በይ "  ብላ ጎትታ ጠርዙ ላይ አስቀመጠቻትና " ለምን  ተነሳህ ልጄ " ብላ አጠገቧ አስተኛችኝና አልብሳኝ ከሰል ለማያያዝ ወደ ውጪ ወጣች ። ገና እሷ ከመውጣቷ ፀጉሬን እየደባበሰች እኔን እሺ አይዞክ አሁን ይሻልሀል " ብላ አይኔን ሳመችኝ ። ልቤ ደስ ሳይለው አይቀርም !!! ደስታውን በመውጋት እያሳየኝ ይመስላል የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው !!! እናቴ አስር ጊዜ ወጣ ገባ ተፍ ተፍ እያለች ነው ። ማያ ጭራሽ የማላቃት ሰው ሆናለች ያቺ ባየችኝ ቁጥር አንገቷን የምትደፋው ቀና  ብላ ለማየት የምትፈራው ማያ አሁን ላይ ጭራሽ የለችም ።ሳስበው ፍቅር ይቀይራል ሁሉንም ያስረሳል መሠለኝ ሴት እንድትነካኝ የማልፈልግ ልጅ ስትነካካኝ ፊቴን በየተራ ስትስመኝ ደስታ እንጂ ንዴት አልተፈጠረብኝም !!! ሳትናገር ይሄን ሁላ አመት ስሜቷን ይዛ መኖሯ ገራሚ ሆኖ ሳለ ያልተነገረ ፍቅሯን ምን አልባትም ቀደም ብላ ነግራኝ ቢሆን ነገሮች ይቀያየሩ ነበር !!!!! ለነገሩ ምንድነው የማወራው አንድም ቀን ቼክ አርጊያት የማላቃት ልጅ በምን ድፍረት መታ ትንገረኝ !!!ያልተነገረው ፍቅር ያመጣው ጣጣና ችግር ሁሉ በእኔ ጥፋት ነው !እናቴ..... ወጣገባ ማለቷን እንደቀጠለች ነው !! ቡና አቀራርባ ለእኔ ሰርታ አልበላም ያልኳትን በሌላት ብር የገዛቻትን አይነት ምግብ አሟሙቃ ስታቀራርብ ማያ ቶሎ ተነስታ የእጅ ውሀ ይዛ መጣች ። ምንም የመብላት ፍላጎት የሚባል የለኝም አልኳት ። ተው ልጄ እባክህ መብላት አለብህ " አለችኝ እማዬ ። ማያ ደግሞ በተቃራኒው በፊቷ እየተቆጣች ታጠብ ቶሎ በል እኔ እርቦኛል ብላ አስታጠበችኝ በግድ ። ከዛ እናቴ ምግቡን ስታቀርብ አንድ ላይ ሆነን እኔ መብላት ከብዶኝ ሳላውስ ማያ ቶሎ ቶሎ እያለች እያጎረሰችኝ እንድበላ አደረገችኝ !!! ዘለአለም እሷ እያጎረሰችኝ ብኖር ብዬ ተመኘው ። የምር የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው !! እናቴ ጉዷን አላወቀች እንዴት እንዲ ተቀራረቡ በሚል አስተያየት እያየችን ነበር ። እናቴ ስትለምነኝ ያልበላውትን በማያ ጉርሻ ጥንቅቅ አርጌ በላሁኝ ። እናቴ ማያ እንደወጣች የምታወርድብኝን የጥያቄ ናዳ ለመቀበል ራሴን በደንብ ማዘጋጀት ጀመርኩኝ !!! ቡና ጠጣን እማዬና ማያ ብዙ ነገር አወሩ በመሀል በመሀል ፈልጋ እንዳላገባችና ህይወቷን የምትሰጠው የምትወደው ሰው እንያለ ለእኔም ለእናቴም እያሳወቀችን ነበር ከልጅነቴ የምመኘውን ሰው ማግባት እፈልጋለሁ !!!ምናምን ብቻ በጣም ብዙ ነገር ነገረችን የዛኔ የምር ፀፀተኝ !!!! ምን አለ ቀድሜ ባወኩ ብዬ ቸመኘሁኝ !!እሷን የኔ ለማረግ መሞከርም ፈለኩኝ ። ግን ብዙ አልቆየችም ሰአቱ ፈጠነብኝ ጨርሳ ወደቤቷ ሄደች ማለቴ ወደዛ ሰውዬ!!!እና ተመልሳ ከሄደች ደግሜ እንደማላገኛት እያወኩ በአይኔ ሸኘዋት ። እናቴም እሷን ለመሸኘት ወታ ምን እያወሩ እንደሆነ አላውቅም ቆዩልኝ እኔም እድሌን ለመጠቀም ስለፈለኩኝ እንቅልፍ የወሰደኝ ለማስመሰል ሞከርኩኝ እናቴም እየሮጠየች እየመጣች ልጄ ልጅ " እያለች ነበር ። አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይሰማም " ነውና ነገሩ የምር እንቅልፍ እንደወሰደው ሰው ዝም አልኩኝ !የኔ የዋህ አምናኛለች !!! የኔ አባት አትላንት ጀምሮ ሳተኛ " እያለች ግንባሬን ስማ ብርድ ልብሱን አስተካክላ አልብሳኝ ወጣች ። ....... . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣8⃣
196
5
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣6⃣ ..........ፊት ለፊቴ ቆማለች ። ሳያት ደነገጥኩ ። በሰአቱ እሷ ልትመጣ ትችላለች የሚል ሀሳብ ቀርቶ እሷንም ላለማሰብ እየታገልኩ ነበር ። በመምጣቷ ከመደሰት ይልቅ ምክንያቱን ባላቅም ፊቴን ነው ያዞርኩባት ። ከእጄ የወጣ ነገር ስለሆነ ለራሴ ድጋሜ ተስፋ መስጠት አልፈለኩኝም በዛ ላይ ጭንቅላቴ ውስጥ የሰርጓን ምሽት ከዛ ሀብት ጭንቅላቱን ከደፈነው ሰውዬ ጋ አሳልፋለች የሚለው ሀሳብ ጭንቅላቴን ሞልቶታል ። ከእኔ ነው የምትሸሸው ?? " አለችኝ ። በንዴት ነው እያወራች የነበረው ። በርግጥ እውነቷን ነው ። እኔ ነኝ ተስፋ ሰጥቼ መልሼ የነጠቋት !! ሙሉ በሙሉ የኔ ጥፋት ነው ግን የሰው ባህሪ ነውና ጥፋቴን እሷ ላይ ለማላከክ ስለፈለኩ ብቻ በሰአቱ እኔ ባልኖርም እንቢ ማለት ትችይ ነበር አልኳት ። ንግግሬ የበለጠ አናደዳት መሠለኝበአንዴ ፊቷ ተቀየረ እና " ከዛስ አንተ ስለኔ ምን እንደምታስብም ሳላቅ ምን ልሆን ?? ሰርጉን እንቢ አልኩ ከእናቴ ጋ እንጣላለን አንተ ጭራሽ አፈልገኝም ከዛ እኔ ሜዳ ላይ ቀረሁ !!......" ብላ በንዴት ብዙ ነገር አወራችኝ ። እኔም የሷን ንግግር ተንተርሼ ራሴን ነፃ ለማረግ ብዬ ብቻ እኔስ ያንቺን ስሜት በምን ላውቅ እችላለሁ እኔስ ሰውዬውን ወደሽው ቢሆነስ በምን አውቃለሁኝ ? ብዬ ራሴን ነፃ ለማረግ ሞከርኩ ። ስህተቴን ለመሸፋፈን በሞከርኩ ቁጥር በጣም እያናደድኳት ነው ያለሁት ግን በራሴ እጅ እንዳጣዋት ስለተሰማኝ ላለመቀበል እየሞከርኩ ይመስለኛል !! ከእራሴ ጋር ከበድ ያለ ትግል ላይ ነኝ !!! እንዳሰብኩትም በጣም ተናዳ ወደዃላ እየሸሸች " አንተ እውር ስለሆንክ ነዋ እኔ ምን ላርግ " አለችኝ ። ምን ማለት ነው አልኳት ከተኛውበት ቀና እያልኩ በጣም በብዙ መንገድ ማወቅ ትችል ነበር በብዙ መንገድ ላሳይክ ሞክሪያለሁ ክፍል ውስጥ ሳላይክ ውዬ አላቅም አንተ ግን ቀና ብለህ አይተከኝም አታቅም ከልጅነታችን ጀምሮ እመኝክ ነበር አዎ አልዋሽም ግን አንተ ማየት አትችልም ። ከሴክሽን አንደኛ ወጥቼ ሲጨበጨብለኝ ትኩረት ክጠከኝ ብዬ ስንቴ ተመኝቻለሁ ...." እያለች ብዙ ያላስቸዋልኳቸውን ነገሮች ነገረችኝ ። በዝምታ ሳዳምጣጥ ከቆየሁ ቡሀላ ለምንድነዉ አሁን የምትነግሪኝ ታዲያ ካለፈ ቡሀላ ምን ለመሆን ነው የምትነግሪኝ ቆይ እ እንዲቆጨኝ ከሆነ ተሳክቶልሻል በቃ ተይኝ አልኳት ። ከልቤ እንድትተወኝ ፈልጌ ባይሆንም ራሴን ለመሸወድ እየሞከርኩ ነበር ። !! " አንተ ምልክት እንኳን መች አሳየከኝ እና ነው ቆይ እ የሆነ ሳምንት ልታስቆመኝ ልትቀርበኝ ሞከርክ ከዛ መልሼ ልቀርብ ስሞክር ባላየ ማለፍ ጀመርክ ምንድነው የኔ ጥፋት " አለችኝ ። ቀና ስል ከየት እንደመጣ አላውቅም እንባዋ እንደ ጉድ እየወረደ ነበር ። ደንግጬ እያመመኝም ቢሆን ከተኛውበት ተነስቼ እንባዋን እየጠራረኩ አቀፍኳት ። ምን ያህል እንደተናደደችብኝ  የሚያስታውቀው በዛ ልክ መናገሯ ነበር ። ሰው ቀና ብላ አታይም የምላት ልጅ በጣም ነበር የተናገረችኝ ። ለትንሽ ደቂቃዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ተነካክተን ተቃቀፍን ። ልክ እቅፏ ውስጥ ስገባ ከላይ ላይ የተጫነ ድንጋይ ቀስ በቀስ የተነሳልኝ እስኪመስለኝ ድረስ እየቀለለኝ ነበር ። እቅፏ የሆነ ሰላም አለው !!! የሆነ ፀጥ ያለ ነፋሻማ ቦታ የገባሁ ይምስል ራሴ ሰላም እየተሰማው ቀስ ያለ ንፋስ እየፈሰብኝ መስሎ ተሰማኝ ። ከሷ እቅፍ ላለመውጣት ምንም ላደርግ እንደምችል ይሰማኛል !!!እሷም ከየት እንደለመደች ባላውቅም ፍቅር  መስጠት ችላበታለች ቀስ እያለች ለስላሳ ፀጉሬ ውስጥ እጇቿን እያርመሰመሰች እቅፏን እንደወደው አደረገችኝ ። ከረጅም ደቂቃ ዝምታ ከሰፈነበት ሰላምታ ቡሀላ ሀብትሽ ? " አለችኝ ። በቃ ተነስ ልትለኝ ስለመሰለኝ በእናትሽ ትንሽ እንቆይ አልኳት ። " ለምን ትንሽ እ እድሜዬን ሙሉ እንዲህ ብናሳልፍም አይከፋኝም " አለችኝ ። በንግግሯ የተደሰትኩት እኔ ሳላስበው አንገቷ ስር እንደተወሸኩ ሳምኳት ። የሚገርመው ምንም አላለችኝ በአፀፋው መልሳ ሀብትሽ "" አለችኝ ። ወዬ አልኳት እኔም ደግሜ " አንድ ነገር ልንገርህ አትናደድም " አለችኝ ። አትናደድም ተብለው የሚነገሩ ነገሮች እንደሚያናድዱ ግልፅ ነው ግን እሷ ሆናብኝ አልናደድም ኝገሪኝ አልኳት ። " እንዴት እንደምነግርህ አላቅም ቀሌላ አትረዳኝ ላንተ ካለኝ ፍቅር ነው ግን........ " ብላ ዝም አለች ። ግን ምን ንገሪኝ አልናደድብሽም አልኳት ። በቃ አልችልም !!" አለችኝ ። ምንድነው የማትችይው አልኳት ግራ ገብቶኝ በቃ ለሱ ክብሬን መስጠት አልችም !!!! "  አለችኝ በሀፍረት ፊቷን ደረቴ ላይ ለጥፋ ። እኔ ግን ደንግጬ አሁንም ወደ ዃላ ገፍትሪያት ከእቅፏ ወጣሁ .......ደንግጣለች !!! ሴት የሚለውን ክብሯን ትታ ሴትነቷን ለመስጠት ጠየቀችኝ ለሷ ምን ያህል ከባድ አመት ንደሆነ ግልፅ ነው !!! እኔ ግን ጭራሽ አስቤውም የማላቀው በጣም የምፈራው ነገር ነው ። በጭራሽ ደግሞ እንደዛ ትላለች ብዬ አስቤውም አላውቅም !!! ከሷ በላይ እኔ ደንግጫለሁኝ !! አፌን እንደከፈትኩ ዝም ብዬ ስመለከታት " አትየኝ እኔ ባለጌ ሆኜ አይደለም ወይም ክብር ሳይኖረኝ ቀርቶ አይደለም በደንብ ታቀኛለህ ሰው ቀና ብዬ ሳላይ ነው ያደኩት !!ግን አንተን ከቁጥጥሬ በላይ እወድሀለሁ ለፍታ ካሳደገችኝ እናቴ እኩል ወይም በላይ ኡፍፍፍ በቃ አላቅም ብቻ አልችልም !!የሆነ ቀን አይተከኝ ወይ በሆነ ተአምር ወደከኝ ተጋብተን ካንተ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደምወልድ እያለምኩ ነው ያደኩት !!!ያኔ እኛ ቤት በከመጣህበት ከአስር አመቴ ጀምሮ ምኞቴ ነበርክ !!እድሉን ባታበላሽ እኮ እናቴ እንደምታዝን እያወኩም ሰርጉን ልተወው ነበር ????..... ለምን ግራ ታጋባኛለህ ቆይ የማትወደኝ ከሆነ ለምን አትነግረኝም ??" ብላ ተመለከተችኝ ። ስሜቱን ከዚህ በፊት ስለማላቀው ለመረዳት ቢከብደኝም ግን ደግሞ ሁኔታዎች ለሷ ያለኝን ፍቅር ግልፅ ያደርጉታል !!!ለሴት ትኩረት የሚባል የማልሰጥ ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሌላ ሰው ጋ ሳያት ልቤ እንደተሰበረ የተሰማኝ በሷ ነው !! ስትረቀኝ የተከፋሁት የታመምኩትም በሷ ነው !!.ከእናቴ ቀጥሎ እቅፏን የወደድኩት ዪጀመሪያ ሴት ናት ። ልዕልና ስታቅፈኝ የሚሰማኝ ድንጋጤ ለካስ የፍቅር አልነበረም ከሴት ጋር ያለኝ ርቀት እንጂ ....ከህመሜ በእቅፏ የፈወሰችኝ ሴት እሷ ናት !!!ለሊቱን ሙሉ ሳስባት ስጨነቅ ነው ያደርኩት !!ስለዚህ አልወድሽም ብል ውሸት ነው የሚሆንብኝ !!!አቅፊያት ለሊቱ እንዲነጋ አብራኝ እንድትሆን ብፈልግም ግን አስተዳደጌና ራሴን ያሳመንኩበት ማንነት ከለከለኝ !!!.ፍላጎቴን እንድደብቅ አስገደደኝ !!! ....... . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣7⃣
222
6
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣5⃣ ..........እጇን ያዘኳት ። በሰአቱ የአንዳንድ ሰዎች አይኔ እኛ ላይ መሆኑን ባስተውልም እንድታዳምጠኝ እየጠየኳት ነበር ። አርፍጄ ሁሉንም አበላሽቼ ስጨርስ ኤፈደም አሁንም አዳምጪኝ አልኳት ። የመጨረሻችን ነው በሚል አይነት ፊት እያየችኝ እኔ ጋ ያለው ስሜት አንተ ጋ አለ እ ታፈቅረኛለሁ ትወደኛለህ ከዚህ አውተህ ታገባኛለህ ???" ብላ የጥያቄ ናዳ አወረደችብኝና ፍጥጥ ብላ አየችኝ ። ህይወት በጭራሽ ሁለተኛ እድል አትሰጥም !!! ለእኔ ግን ሰታኝ ነበር ለዛውም እንደ ጥፋቴ ያልሆነ በቂ እድል ነገር ግን ደግሜ ፎረሽኩ!!???እድሌን መጠቀም አልቻልኩም !!! እሷ እንደመልስላት ስትጠብቀኝ እኔ እዛ ጋ ቆሜ በሌለ ደቂቃና ሰአት ቆሜ ገና ሁለቱን ማወዳደር ጀመርኩ ። የሰጠችኝን ደቂቃ ከመጠቀም ይልቅ ቆሜ የሚሰማኝ ስሜት የትኛው ትክክል እንደሆነ ሳሰላስል ነበረ !! ባይገባኝም በጣም ለረጅም ደቂቃ ቆማ ምላሼን ጠበቀች !እኔ ግን መወሰን አቅቶኝ እጄን እያንቋቋሁ ቆሜ አሰላስላለሁኝ ። ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት " ትላለች እናቴ ። ልቤ መወሰን ባለመቻሌ ሁለቱንም እድሌን አባከንኩት !! ይቅር ብላ ደግማ የያዘችኝን እጅ ደግሜ ከዳዋት !!! ደግሜ ልታመንላት ባለመቻሌ ባሁን እስከመጨረሻው በሚመስል ሁኔታ እጇን አላቃ ጥላኝ ሄደች ። አጠገቤ ሆና ስትለምነኝ ከሷ ጎን መቆም ያልቻልኩኝ ልጅ  ልክ ከኔ ስትርቅ ልቤን የሆነ ነገር የወጋኝ ይመስል አይነት ስሜት ተሰማኝ !! ከዛ በላይ ከእራሴ ጋር መጣላቴን መቋቋም ስለከበደኝ ከዛ ቦታ በፍጥነት ወጥቼ ወደ ቤት ገብቼ ለጥ አልኩኝ ። ራሴን በእንቅልፍ ለመሸወድ አስቤ ነበር !! ነገር ግን ሀሳቦች ጭንቅላቴን ሞልተውት መተኛት ራሱ ከበደኝ ። የተናደድኩት በልዕልና ቢመስለኝም ዋና ፀብ ከእራሴ ጋር ነበረ ። ከእራስ ጋር መጣላት ደግሞ ምን ያህል እንደሚከብድና ራስን እስከመጥላት እንደሚያደርስ ልነግራችሁ አልችልም !!!! በዛ ላይ እናት በጣም አመሸች ። ጭንቅላቴ " እሄኔ እኮ ተጋብተው ጨርሰዋል ... አቅፏት ይሆናል ....እየጨፈሩ ይሆናል .....  " ይለኛል ልቤ ደግሞ በተራው " አዎ ብለህ ወስደሀት ቢሆን ኖሮ እሄኔ ለሷ ጀግና ወንድ ሆነክ ፍቅርህን አምነህ ተቀብለህ ከሷ ጋር አንድ ላይ ነበርክ ....ልብህ በደስታ እየመታ ነበር .....ከሀዘን ይልቅ ደስታ ላይ ነበርክ ..." እያለ ይሟገተኛል ። በጭንቅላቴና ልቤ የተለያየ ሀሳብ እኔ ልፈነዳ ምንም አልቀረኝም !!! ሳስበው እናቶቻችን " የፈሰሰ ውሀ አይታፈስም " ያሉት ለእንደኔ አይነቱ ልበ ቡኩን ሰው ይመስለኛል !!!!! ጭንቅላቴ ከመፈንዳቱ ትንሽ ቀደም ብላ እናቴ ወደቤት መጣች ። ብቸኝነቱ ስለተነሳልኝ ትንሽ ቀለል ብሎኝ ነበረ ነገር ግን ውስጤ ሰላም ሊሆንልኝ አልቻለም !!እናቴም እንደመጣች ፊቴን አይታ ልጄ ምን ሆንክብኝ እ ከሰርጉ ቡሀላ ደህና አደለህም " አለችኝ ። የኔ እናት ጉዷን አላወቀች !!! ደህና እንደሆንኩ አሳምኛት በሯን ዘጋግታ አጠገቤ መታ ተኛች ። እኔ ግን እንቅልፍ ሊወስደኝ አልቻለም ይልቁንም በጣም አመመኝ ። ውስጤ ጭንቀቱ ሰውነቴ ግሏል ያንዘፈዝፈኛል ብርድ ብርድ ይለኛል ራስ ምታት .... አንድ ላይ ተደማምረው በህይወቴ አሞኝ የማያቅ ልጅ ልሞት እስኪመስለኝ ድረስ  ታመምኩኝ !! ለሊት ላይ እናቴ ግለትክ ቀሰቀሰኝ ብላ ብድግ አለች ። የኔ እናት  ማታ ላይ እንደደከማት እየነገችኝ ነበር ግን እኔን ስታይ ሁሉንም ረስታ ብድግ ብላ የቻለችውን ሁሉ አጀረገችልኝ ። ኀለሊቱን ሙሉ ጉልበቷ ላይ አስተኝታኝ ስትጨነቅ አደረች ። ጠዋት ሲነጋጋ ደማከሴው ምናምን በቡና አጠጣችኝ ጭንቅላቴን አሻሸችኝ  ትንሽ ራስ ምታቱ ቀነሰ እንጂ ጤንነት ሊሰማኝ አልቻለም ። ሆስፒታል እንድሄድ ስትለኝ እንቢ ስላት መጣሁ ብላኝ ከብር ማጠራቀሚያዋ ውስጥ አውጥታ ከቤት ወጣች ። ምን ሆኜ እንደሆነ አላቅም ከህየወቴ ከባዶቹ ህመሞች ውስጥ አንዱ ነው !!! እናቴ ጥላኝ ስትወጣ ደግሞ የበለጠ አመመኝ ። እንቅልፌን ለማምጣት ለረጅም ሰአት ስገላበጥ ቆየሁ ግን ወፍ የለም !!!??? ፊቴን አዙሬ ተኝቼ ሳለ በሩ ሲከፈት ሰማሁና እናቴ መጣች ብዬ በደስታ ዞር ስል ማያ ፊት ለፊቴ ቆማለች ???...... . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣6⃣
287
7
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣4⃣ ........  የሚያናደው ደግሞ ስደርስ ቀላል ነገር ነበር ! እንደውም ከጠበኩት በተቃራኒው አንድ ላይ ውጪ ቁጭ ብለው አየር እየተቀበሉ ነበር ።ሰላም ደህና ነሽ ? አልኩኝ እየተመለከትኳት አዎ የኔ ልጅ በጣም ደህና እየሆንኩ ነው ከፈጣሪ ቀጥሎ እድሜ ለአንተ " አለችኝ ። ከዛም ልዕልናን በመጥፎ አይን እየተመለከትኩኝ ታዲያ ለምን እንደዛ አልሽኝ አልኳት ንዴቴን ለመቆጣጠር እየሞከርኩኝ ። ልቤ እዛው መሆን ቢፈልግም እግሬ ጭንቅላቴን እያዳመጠ በሱ ተመርቶ ባዶ እግሬ ሲሮጥ ወደሷ መጣ ??? ገና እዛው ቆሜ እየፀፀተኝ ነበረ ። ልዕልና ግን ምንም እንዳልተፈጠረ " እንድትመጣ ስለፈለኩ ነዋ ግን ሙሉ በሙሉ ውሸት አይደለም ቅድም ትንሽ አሟት ነበር " አለችኝ ነገሩኖ ቀለል አድርጋ??? አስታውሰዋለሁ በሰአቱ በጣም ተናድጄ በህይወቴ ሴት ልጅ ለመንካትም አስቤ የማላውቅ ልጅ ልመታት አቃቶኝም ነበር ። በሰአቱ በራሴ ላይ ችግሮችን ላለመደራረብ ብዬ ፊቴን አዙሬ ሳሚ ይቅርታ አሁን መሄድ አለብኝ በጣም ከአስፈላጊ ነገር ላይ ነው አሟታል ሰጡት ትለኝ አቋርጬ የመጣውት ደህና ዋሉ ! ብዬ ምላሽም ሴልጠብቅ እየሮጥኩ ከዛ ጊቢ ወጣሁ ። እስከዛሬ ከወጣሁ ብዙም ሳልቆይ ሳላስበው ቤቴ የምደርስ ልጅ ከነሱ ቤት ጀምሮ ብሮጥም መንገዱ እንደ መንግስተ ሰማያት ነበር የራቀኝ !!! በጣም ከመጨነቄ የተነሳ ሀምሳ ኪሎ ባነሳ የማያልበኝን የላብ ውሀ ሳዘንብ ነበረ !!!መንገዱን ጠላሁት ከዛ ቀን ቡሀላ በዛ መንገድ ላላፍ ቃል መግባት እያማረኝ ልቤን እስክተፋት ድረስ እየሮጥኩ ወደ ሰርጉ ቤት ሄድኩኝ ። አረፈድኩ !!!!! ማርፈድ ዋጋ ያስከፍላል ሲሉ አላምንበትም ነበር ነገር ግን ለኔ የህይወቴን ትልቁን ዋጋ አስከፈለኝ !!!. ሰርጉ ተደርጎ ጋብቻው ፀድቆ ሰው መብላት መጠጣት ሲጀምሩ ኘበር የደረስኩት ። በሰአቱ ባገኘውት ነገር ራሴን ብደበድበው ደስታዬ ነበር ። ከሰዎቹ መሀል ሹልክ ሹልክ እያልኩኝ ወደ ማያ ደረስኩኝ ። ፊት ለፊቷ ሆኜ አንዴ ነይ እያልኩ በሚስጥር ለመንኳት !!ነገር ግን እኔ ጊዚያዊ ስሜቴን አዳምጬ እየሮጥኩ ስሄድ የሷን ልብ ሰብሬ ነው የሄድኩት ለካ !!!!. ብቻዬን ሄጄ ባናግራት ችግር ነው ብዬ ስለፈራሁኝ  ቆሜ ሳስብ እናቴ ወደነ ማያ ስጦታዋን ይዛ ስትሄድ ቸመለከትኩኝ ! የእኔ እናት ጉዷን አላወቀች ለልጇ ሀዘን ሰርግ አዘጋጅታለች ። በሰአቱ በርካታ ጥያቄዎች ጭንቅላቴ ላይ እየተመላለሱ ነበሮ ግን ቅድሚያ እሷን ማውራት ስለነበረብኞዥዠኝ ሹልክ ብዬ ከእናቴ ጋር ወደሷ ቀረብኩኝ። እንደምንም ጠጋ ብዬ  አንዴ  ላወራሽ እፈልጋለሁ  አልኳት ። ግንባሯን እየነቀነቀች አይሆንም አለችኝ ። እኔም ቶሎ ብዬ ቃል እገባለሁ ምንም ችግር አይፈጠርም አንዴ እናውራ አልኳት ። አጎንብሳበት የነበረው አይኗ  ቀና ስትል በእንባ ተሞልቶ ልውጣ አልውጣ እየታገሉ ይመስል ነበረ !! እሷም ላለማልቀስ እየሞከረች በፍጥነት " አረፈድክ የአንተንም የእኔንም እድል አባከንክ ለአንድ ደቂቃ ጠብቀከኝ ቢሆን ኖሮ እኔም እንቢ የማለት ድፍረት አገኝ ነበር !!! አንተን እያየሁ መብቴን ለማስከበር እደፍር ነበር ምን አልባትም ሮጬ መጥቼ እቅፍህ ውስጥ እደበቅ ነበር !!! ከልጅነቴ ጀምሮ እኔ አንተን ሳይ አንድም ቀን ትኩረት ሰተከኝ አታቅም !!ህይወቴን በሙሉ አንተ የሆነ ቀን አይተክ ወደከኝ እንደምታጠባኝ እያሰብኩ ነው የኖርኩት ። ታችኛውን መንደር ትምህርት ቤቱንና ክፍላችንን አንድ ላይ አስታውስ እስኪ ምን አልባት ያኔ ምን ያህል እመኝክ እንደነበር ይገባህ ይሆናል !!!! ልታድነኝ አልቻልክም መቃብር ውስጥ እንደወረወርከኝ ቆጥረዋለሁ ምክንያቱም ምሽቱን ሙሉ የኔ ጀግና መልከአክ አድርጌህ እንደምታድነኝ ተማምኜ ነበረ !! "  አለችኝ እንባዋ እየወረደ ግን ፊቷን ቶሎ ቶሎ እየጠረገች ። አታርፍድ !! ለሚለው ቃል ትኩረት ሰጥቼው ባላውቅም የዛኔ ገና ትርጉሙ ገባኝ !!!.ማርፈድ የኔ የሆነውን ሰው ነጠቀኝ !!!ማርፈድ አንድን ሰው ወደስቃይ ከተተብኝ ......በሰአቱ ቃላት ማውጣት እስኪከብደኝ ነው የተረበሽኩት ዝምታዬ የበለጠ መልስ የሆነ መስሏት እሷም " መልካም ህይወት እመኝልሀለሁ !! ላንተ ምርጧ ነው የምትገባህ ! ዪጀመሪያዬም የመጨረሻዬም ነህ እወድሀለሁ !!!" ብላኝ ፊቷን አዙራ ወደነማዬ ልትቀላቀል ስትል ቶሎ ብዬ እጇን ያዝኳት ........ . . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣5⃣
248
8
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣3⃣         ..........ጊዜ የለኝም አንድ ሚስጥር ነግሬህ እሄዳለሁ አለችኝ ለኔ ምን ልትነግረኝ እንደምትችል አልገባኝም ?? በዛ ሰአት ተሸፋፍና ወደኔ  ስትመጣ ደንግጫለሁኝ ። ምክንያቱም እኔ እዛ የሞት ድግስ ላይም የታደምኩት እናቴን ላለማስከፋትና ከሰው ላለማጋጨት አስቤ ነው ። ምንድነው ?? አልኳት አይን አይኗን እየተመለከትኩኝ ። እኔና እሷ በዛ ልክ ተቀራርበን ስናወራ የመጀመሪያችን ነበር ።ማያ ቀና ብላ አይኔን አይታኝ አታውቅም ነበር የዛን ቀን ግን ወደላይ አንጋጣ እያየችኝ ነበር ።አይኖቿን ሳይ ምንም ነገር መናገር አልቻልኩኝም ነበረ ምላሼ በዝምታ ማየት ነበር ። የዛ ቀን ገና አስተውዬ ውበቷን መመልከት ቻልኩኝ!!! አይኖቿ ቡኒ ሆነው ከረጅም ሽፋሽፍቷና ከብዙ ቅንድቧ ጋር ተደምሮ በጣም ውብ እይታ አላት ። በሰአቱ እሷን እያየው አይምሮዬ ውስጥ ልዕልና እያለች ሁለቱን እያነፃፀርኩ ይሁን ምን ይሁን በማላቀው ሁኔታ በየተራ እያሰብኳቸው ነበር ?? ግራ ተጋብቼ ሁሉንም ነገር እያደበላለኩት ነው !!!ግራ ቢገባኝ አይኔን ጨፍኜ መግለጥ ስጀምር አሁን በምነግርክ ነገር እንዳትጠላኝ ለኔ ያለክ አመለካከት እንዳይቀየር " አለችኝ እንደዛ ስትል የበለጠ ጉዳዩን ለማወቅ እንድጓጓ አደረገኝ ። እሺ ምንድነው ችግር አለ ?? አልኳት ለመናገር ቃላት ያጠሯት ይመስላል እ እ እያለች መርበትበት ጀመረች ። እሷ ለመናገር ድፍረት እስክታገኝ ብዬ አስቤ በእናትሽ አታድርጊው እሱን አታግቢው እንዳታረጊው አሁንም ጊዜ አለሽ !! አልኳት በልመና ንግግር ። " አልችልማ !!! " አለችኝ ። እሺ ለምን ??? በምን ምክንያት ነው ንገሪኝ መቼም ሰውዬውን እወደዋለሁ ልትይኝ አትችይማ !! አልኳት ምክንያቱም እንኳን እሷ በወንድምነትም ለመውደድ የሚከብድ በጣም ክፉና ተንኮለኛ ሰውዬ ነው ። አልችልማ ለእናቴ ስል አደርገዋለሁ በቃ አለቀ ያለ አባት ለፍታ ነው ያሳደገችኝ እሱን ታውቃለህ እኮ " አለችኝ ። እሱን አውቃለሁ ግን  ሰርካለምን ለማውራት እንሞክር እሺ እኔ ልጠይቃት አልኳት አይይ አይሆንም መልሷን እያወክ ምንድነው የምትለኝ አሁን አዳምጠኝ በዚህ ሰአትና በዚህ ድፍረት ብቻ ነው እውነታውን ልነግርህ የምችለው " አለችኝ ። እሺ ንገሪኝ ብያት እስክታወራ መጠበቅ ጀመርኩኝ ። ነገሮችን አይተህ ባላየ አልፈህ ይሆን ባላውቅም ግን ከልጅነታችን ጀምሮ ግልፅ ነገር ነበር " አለችኝ ምኑ አልኳት ግራ ገብቶኝ ሀብትሽ እኔ ..." ብላ ንግግሩን ሳትጨርስ እናቴ እየተጣራች ወደኔ መጣች ። " ሀብቴ  ሀብትሽ    ሀብትዬ "  ትላለች ምንድነው እማ አልኳት ቀስ ብዬ " ስልክ ይፈልግሀል በጣም ብዙ ጊዜ ተደውሎልካል " አለችኝ ። ከልዕልና ውጪ ሌላ የሚደውልልኝ ሰው የለም ስለዚህ እሷ ፊት ቆሜ ስልክ ማውራት አልፈለኩኝም ግን የምትነግረኝ እንዳይጠፋባት ብዬ ፈርቼ ትንሺ ፊቴን አዙሬ አቤት ? አልኩኝ " ሚኪ እባክህ ታስፈልገናለህ " አለችኝ ። እያለቀሰች ነበር ክው ነው ያልኩት ምንድነው ?? ችግር አለ ምን ሆነሽ ነው ??  አልኩ እየተንተባተብኩ " እማ አሟታል ዶክተር ብንጠራም ምንም ጥቅም የለውም ከማደንዘዣ ውጪ አንተ ለኛ መልአክ ነክ አሁኑኑ ና እባክህ ሚኪ ፍጠን " አለችኝ ። ልዕልና ስትመጣ ደግሞ ሁሉንም ረስቼ በሷ ቁጥጥር ስር እሆናለሁ ። እሷን እንቢ ማለትም ሆነ እያለቀሰች መስማት ስላላስቻለኝ ለእናቴ ስልኳን ሰጥቻት ለመሄድ ሩጫ ስጀምር " ሀብታሙ !" አለች ማያ በጩኸች ። እንደዛ ስታወራ ሰምቻት ስለማላቅ ደንግጫለሁኝ !!! በሰአቱ  ሌላ አማራጭ ስላልነበረኝ ተመልሼ እመጣለሁ ብያት መሄድ ስጀምር ከዛሬ ውጭ ልነግርክ አልችልም እባክህ " አለችኝ ። እኔ ግን ምን እንደሆንኩ ባላውቅ ሀሳቤ ሁሉ ልዕልና ጋር ሆኖ ምን አልባትም የህይወቴን ትልቁ ስህተት እንደሰራሁ የሰማኛል  !!!! አሁን እመለሳለሁ እሺ አልኳትና ዞር ብዬ እየሮጥኩ ወደ ልዕልና ቤት ሄድኩኝ ! የሚያስከፋው  ደግሞ እዛ ስደርስ .......... . . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣4⃣
273
9
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣2⃣ ......... በጣም ፈርቼና ደንግጬ ነበር ። ለምን እንደደነገጥኩም አላውቅም እኔ ብቻ ግን የሆ በህይወቴ ውስጥ የቆየ እና የኔ የሆነ ነገር እንደተነጠኩኝ አይነት ስሜት ተሰማኝ በሰአቱ ሳላስበውም ቢሆን ምን ምን ማለት ነው አይሆንም ብዬ ጮኩኝ ምክንያቱም ፊቷን በደንብ አይቼዋለሁኝ !! ማያ አይኗ ውስጥ የሆነ ከባድ ህመም ነገር ይታያል !!.ያለመፈለጓን ከፍራቻ ጋር ተደምሮ በደንብ ያስታውቅባታል !! ሰርካለም ትንሽ ከበድ ያለች እናት ናት እኔ ብቻ ልደመጦ እና ልከበር አይነት ነገር ያጠቃታል በዛ ሰአትም ያለ ፍላጎቷ ልትድራት አስባ እንደሆነ እርግጠኛ መሆን ችዬ ነበር !!! ማለት ልጄ ለምነሰ አይሆንም ?" አለችኝ መስከረም የሆነ አይነት አስተያየት እያየችኝ ። በሰአቱ ተናድጄ ስለነበር እየጮኩኝ ስለማይሆን ነዋ አይሆንም ! አልኩኝ ። የሆነ ታላቅ ወንድሟ ወይም የረጅም አመት ፍቅረኛዋ ነበር የምመስለው ! እናቴ ጮኬ በማውራቴ ተናዳ እየገላመጠችኝ ነበር !ግን ነገሩ ልክ እንዳልሆነ ስለማውቅ ነበር እንደዛ የተናገርኩት " ቆይ እሺ ማንን ነው የምታገባው ? " አለች እናቴ በተረጋጋ አነጋገር ! በላይሁንን አለች ወ/ሮ"  መስከረም ፈገግ እያለች በላይሁን ? " አለች እናቴ ሰውዬውን ለማወቅ ስሙን እየደጋገመች ።በላይሁን ነዋ የጋሽ ጥበበ ልጅ " አለች እማዬ ክው ብላ " አታረጊውም " አለቻት ። እናቴ ቀስ በቀስ እኔን መደገፍ መቻሏ ቢያስደስተኝም መደንገጧ የበለጠ አስገረመኝ ምክንያቱም እኔ ሰውዬውን ማስታወስ ከብዶኝ ነበረ ከዛ ግን በድንገት ጋሽ ጥበበ የሚባሉት የወዳኛው ሰፈር ታዋቂ ባለሀብት ሰውዬ እና ወፍራሙና ግዙፉ አስፈሪው ሰውዬ በላይሁንን አስታወስኩት !!! እሱ ማለት እንኳንስ ለቆንጅዬዋና ትንሿ የዋህና ዝምተኛዋ ማያ ቀርቶ ለማንም ሴት ማይመጥን ክፉና የማይረባ በገንዘብ ልግዛ የሚል ባለሀብት ሰው ነው !! ከዛ የበለጠ ባሰብኝና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ በጭራሽ እሱን ማግባት አትችልም ያንን አልፈቅድም አይሆንም ለገንዘብ ብለሽ ልጅሽን ልትሸጪ ነው ? ብዬ ጮኩባት ።  ከዛ ግን ሰርካለምም ከተቀመጠችበት ተነስታ ያንተን ፍቃድ ማን ጠየቀህ ጎረምሳው እኔኮ ምንም ቢሆን ክፉ ደግ አሳልፈናል ብዬ ለልጄ የደስታ ቀን እንድትገኙ ልነግራችሁ ነበር ። ወዲያው ቀለበት አርገው እዛው ሊጋቡ ነው ብዬ ጭራሽ አድገህ እኔን ማዘዝ አማረክ እንዴ ሆ ጉድ እኮ ነው ....." እያለች እያጉረመረመች  የማያን እጅ እየጎተተች ይዛት ሄደች ። በሰአቱ የሆነ ስልጣን ቢኖረኝና እጇን ይዜ ከምትገባበት ፈተና ባወጣት ደስ ባለኝ ግን ምንም እንደማላመጣ ስለማውቅ አፌን ዘግቼ ዝም አልኩኝ ።ነገር ግን ፊቷ ላይ ያየሁትን ሀዘንና መከፋት ልረሳው አልቻልኩኝም የዛ ቀን ምሽቱንም ለሊቱን ሙሉም ሳስብና ስጨነቅ አደርኩኝ !!!! በቀጣዩ ቀን ከመቸው እንደተስፋፋ አላቅም ከዛኛው መንደር ያለው ድግስና ወከባ እዚህ ድረስ ይሰማ ነበር !!! በሰአቱ ጭንቅላቴ ማሰብ አቁሞ ነበር ምን ማረግ እንዳለብኝም ማወቅ አቃተኝ !!! ምንም ነገር ሳላደርግ የሰርግ ጥሪ ????.... " አቶ በላይነህ ጥበበ ወ/ሪት ማያ ደረጄ 💍💍 " የሚል በፎቶዎች የደመቀ የሚያስጠላ ወረቀት ተበተነ ። ለሷ ያለኝን ነገር ባላውቅም ያንን ነገር ማየት ሰላም ነስቶኝ ነበረ ። የማይደርስ የለም የተባለው ሰአት ሲደርስ ቁጭ ብዬ ሳይ ነበረ ። ድንገት እናቴ ስልክ ሲጠራ ደንግጬ ባነን አልኩኝ ። እናቴ ማውራት ጀመረች " ሄሎ ...አቤት ..... እግዚሀር ይመስገነሰ ....አይደለም ልጄ ተሳስተሻል ... አረ ምን እስዋሸሽ ሙች ስልሽ ተሳስተሻል ...እሺ " የእናቴ በየዋህነት የምታወራው ንግግሯ ። ስልኩ ሲዘጋ ማነው ? አልኳት ግራ ገብቶኝ ። " ተሳስታ ነው ልጄ ሚኪ የለም ወይ ትለኛለች " አለች ። የኔ እናት ስሜን ማስቀየሬን ረስታው ይመስላል !! እማ አንዴ ስልኩን ስጭኝ አልኳትና ወደ ውጪ ወጥቼ ስልክ ደወልኩ ። ልዕልና እንደሆነች ስላወኩ ነው እንደዛ ያረኩት ። ሄሎ አልኩ " ሄሎ ሚኪ እንዴት ነህ ናፈከኝ እኮ  ጠፋክ ዛሬ ና በእናትህ እናቴም ትፈልግሀለች " አለችኝ ። ይቅርታ ልዕልና ዛሬ መምጣት አልችልም ነገ ጠዋት መጣለሁ ብዬ አውርቻት ዘጋውት ። ከዛ  እናቴ ለባብሳ ስትወጣ ወዳጁን እንደሚቀብር ሰው ፊቴን ጥዬ ሄድኩ ። ፈተናውስ የልጅነት ውበቷስ አርግዛ እዚህ የማንም መጫወቻ ልትሆን ነው ??  እያልኩ መብሰልሰል ጀመርኩኝ ። ልክ ወደ ሰርጉ ቦታ እንደጀረስኩ ከእናቴ ተለይቼ ወደዃላ ቀረሁ ። ከዃላዬ የሆነ ሰው ሲነካኝ ደንገጥ ብዬ ዞርኩኝ ። ተሸፋፍናለች ማያ ነበረች ። " ጊዜ የለኝም አንድ ሚስጢር ነግሬህ እሄዳለሁ " አለችኝ ...... . . . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣3⃣
261
10
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣1⃣ ...........ወደ ውስጥ ገባ ። አባቴን እወደዋለሁ አከብረዋለሁኝም ጭምር ግን አንዳንዴ ሌሎች አባቶችን አይቼ እሱን ሳይ የምር ከልቤ እከፋለሁ ምንም እንኳን የተደላቀቀ ህይወት ካልሰጠኝ ብዬ ባላማርርም ድህነታችንን እንኳን አጣጥመን እንድንኖራት አልፈቀደልንም ። ማለት ስሜን ሀብታሙ ብሎ አውጥጦ ሀብታም እስክሆን ከመጠበቅ ውጪ ምንም እያደረገልን አይደለም !! ቢያንስ እንኳን ለፍቶ በቀን ስራ ምናምን የሚያገኛትን ብር ለኛ የሆነ ነገር ማረግ ባይችል እንኳን እናቴ ልብስ አጥባ የምታመጣውን ብር ለመውሰድ መድፈር አልነበረበትም !! ቢያንስ እንኳ ሁሉም ቢቀር ሰክሮ እየመጣ በየቦታው እያደረ ክብሯን ባይሰርቅብኝ ደስ ይለኝ ነበር ። አንዳንዴ እናቴ የተሸከመቻቸውን ችግሮችና በሆዷ የያዘቻቸውን ህመሞችና ሚስጥሮችን ሳስብ  በጣም ታሳዝነኛለች !!! ከድሮ ጀምሮ በሆዷ በርካታ ሀዘንና ሚስጢር አለ ግን ደስተኛ ሰው ይመስል ሁሌ ስትስቅና በእልልታ ስታደምቅ ትታያለች !! የን ቀንም ቢሆን ምንም እንዳልተፈጠረ ሰው ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ሲመጣ እሱ እየተንገዳገደ ባደፉ ልብሶቹ ተሸፍኖ ወደ ቤት  መጣ !! ቀን በቀን አባቴ እየተቀየረ ነው የመጣው !! እየባሰበት እንደ ልብሱ ልቡም እያደፈ የመጣ ይመስል ክፉ መናገር አዘውትሯል የዛን ቀንም ሲገባና በዛ ሁኔታ ውስጥ ሲያየን ምንም በማያስቀው ከት ብሎ እየሳቀ እናትና ልጅ ተስማምታችዃል አይደል  እኔ ስወጣ ደስተኛ ሆናችዃል ድሮም እኮ ያራራኳችሁ እኔ ነበርኩ አይደል  ሀ ሀ ሀ  ሀ ሀ ሀ ( ረዘም ያለ የፌዝ ሳቅ ሳቀና) ሳስበው የድህነት ኑሮ የተስማማችሁ ይመስላል !!" አለን ወደ ውስጥ እየገባ ። በሰአቱ ከማንም በላይ የእናቴ ቅስም እንደሚሰበር ግልፅ ነው በጣም ከፍቷት እንባዋ እስከማቅረር ቢደርስም ስሜቷን ዋጥ አድርጋ የኔን መከፋት እንዳስተዋለች " ዛሬ ደግሞ ከነ ጋኑ ነው መሠለኝ የተጋተው " ብላ ያልመጣባትን ከትት ብላ ሳቀች ። እኔም የሷን ደስታ ለማርዘም ስል ፈገግ ብዬ በይ አሁን ስጦታዬን ተቀበይኝ ብዬ ግንባሯን ስሜ የገዛውላትን በብልጭልጭ የተሸፈኑ ጌጣጌጦች አደረኩላት የኔ እናት አርቴ ሆነ የብር ሆነ ምንም አያሳስባትም ። በህይወቷ የታደለች አይደለችም ስጦታ ምናምን ተሰቷት ስለማያቅ ይሄ ለሷ ትልቅ ነገር ነው !!እንደውም ልጄ ደረሰልኝ ብላ በደስታ ነው የምትኩራራው ። በነገራችን ላይ እኔ ሀብታም መሆኑን የምፈልገው ለእኔ አይደለም እኔ እንደ አብዛኞቹ እኩዮቼ ጥሩ ልብስ እለብሳለሁ ግን ለእናትና አባቴ ስል ማድረግ አለብኝ በተለይ ለእናቴ  !!!! እኔና እናቴ በዛቾ ትንሽ ነገር ስንላቀስና ምን ያል እንደምትወደኝ እየነገረችኝ በሩ ተንኳኳ ።እንባዋን ከአይኗ እያበሰች ሄዳ በሩን ከፈተችው ። ወደ ውጪ ስመለከት ሰርካለምና ማያ ነበር በወጣሁ ቁጥር መንገድ ለመንገድ የምንገናኘው አልበቃ ብሎ ጭሳሽ ቤቴ ?? ብዬ በጣም ተናደድኩኝ! በነገራችን ላይ ይሄ የአይምሮዬ ንግግር ነው ልቤ በተቃራኒው ግራ እየተጋባም ቢሆን እንድትቆይ ይፈልጋል ። ማያ እኔ በሌለው ቀን ካልሆነ በቀር እዛ ቤት ድርሽ ብላ አታውቅም ነበር ግን ቤታችንንም ድህነታችንንም  ስለምታውቀው ያን ያህል አልጨነቀኝም ። የነሱ ቤት በጣም ከኛ የተሻለ ነው እንደኛ አካባቢ ሀብታም የሆነ ቤተሰብ ነው በተለይ ደስተኛ መሆናቸው ያስቀናኛል ። እንደሚጠበቀው እናቴ ገና በሩ ከመከፈቱ " እልልልልል እይማ አየሽ ልጄ ምን እንደሰጠኝ ኑ ግቡ ቆይ ብላ ቶሎ ቶሎ ቡና ማፍላት ጀመረች ።እዛ ቤት ውስጥ የኔና የማያ የአይን ግጥጥሞሽ ሊያሳብደኝ ደርሷል !!!ግን አሁን ላይ የህነ ነገር እርግጠኛ እየሆንኩ ነው!!! በሁለታችንም መሀል የሆነ ቅርበትና መሣሣብ አለ!!! በስርአት ላወራት ራሴ አስቤ ስጨርስ በመሀል ሠርካለም ዛሬ እኔም ምነግራችሁ ትልቅ ነገር አለ ። ማያ ቀለበት ልታስር ነው " ስትል ፊቴ ላይ ያለውን ፈገግታ እና የሆነ የስሜት እሳት  ውሀ ደፍታ አጠፋችው.... ላይኩ 100 ከሞላ አንድ ክፍል ይለቀቃል . . . . ይቀጥላል ክፍል 2⃣2⃣
251
11
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣0⃣ .......ከፊቷ ሄጄ ቆምኩኝ ። ልጅቷዐበድንጋጤ ወደዃላ ልትወድቅ ምንም አልቀራትም !!! " እ አቤት ምነው ምን አረኩ " አለችኝ በፍራቻ ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠ ። የፈራችበት ምክንያት አልገባኝም ነበር ማለት ሰፈር ውስጥ ፀበኛ ተደባዳቢ ነው ስለሚባል ነው ወይስ ለምን ቀና ብላ ለማየት ትፈራኛለች ??? ምክንያቷን ባላውቅ ብቻ ዝም ብዬ ሳያት ነበር ። ከእኔ አንፃር አጭር የምትባል ልጅ ናት እና እኔን ለማየት የግድ ቀና ማለት አለባት ። በእጇ የፀሀዩን ግለት ከአይኗ እየጠበቀች " አቤት ችግር አለ ምን ሆነክ ነው " አለችኝ ። ምን አስቤ እንደሆነ አላውቅም ስታወራኝ ማውራት አቃተኝ !!! ከእራሴ ጋር የገባውበት ግራ የገባ ስሜት ልረዳው ስላልቻልኩ ከራሴ ጋ መታገል ከብዶኝ ከፊቷ በቆምኩበት ቦታ ቁጢጥ ነገር ብዬ ጭንቅላቴን ይዤ ራሴን ለመረዳት ስሞክር ምንድነው ምን ሆነክ ነው አሞክ ነው እንዴ በአማኑኤል ና ተነስ ....." ብቻ በድንጋጤ ዝምታዋና ፍርሀቷ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ እግሬ ስር ያለሀሳብ ተንበርክክ በስስት አይን እያየችኝ ነበር ስታወራ የነበረው ??በዝምታ እየተመለከቷት ነበረ እና ፊቷን ሳየው ለረጅሞ አመት ተዋውቀን ተግባብተን ተዋደን የቆየን ያህል እየተሰማኝ ነው ??? የሆነ አለ አይደል ብዙ አመት አብሮኝ የቆየ አይነት ሰው በቃ ለእኔ እንደዛ ነው የሚሰማኝ ። ለረጅም ሰአት በሰስት ሳያት ግራ የተጋባችው ልጅ ፊቴን እንደ ጥፊ ነገር ነካ ነካ እያደረገችኝ " ግን ደህና ነህ ?" አለችኝ ። አዎ ደህና ነኝ ብዬ ቆምኩኝና አንድ እርምጃ ከሷ ሸሸሁኝ ። እሷም ከተንበረከከችበት ጉልበቷን እየጠረገች ተነሳችና ፊቷን ጨምደድ አድርጋ ለትንሽ ደቂቃዎች ተመለከተችኝና ያንን ወደፊት የመጣ ፀጉሯን ወደዃላ እየወረወረች ጥላኝ ሄደች ። ስትሄድ ቅሪ አትሂጂ ብላትና አቅፊያት ብቆይ ደስ እንደሚለኝ አይነት ስሜት እየተሰማኝ ነው !!!ግን እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ ፊቴንም ሳላዞር ቀጥ ብዬ ወደ እናቴ ቤት ሄድኩኝ ። የኔ እናት ፊቷ ላይ የሆነ የደበራት ትመስል ነበር ደህና ነሽ እናቴ ? አልኳት አልጋ ላይ እየተጋደምኩ ልጄ እኔ ማንም እንደሌለኝ እያወክ እንዴት እንዲህ ትተወኛለህ ቆይ እ ከሆነ ጊዜ ጀምሮ እኮ ከኔ ርቀሀል ጠዋት ወተህ ማታ ነው የምትመጣው ምን ነካብኝ ልጄ??  "አለችኝ ሳላስበው ድንጋጤ ውስጤን ወረረው  ምን ያህል እንደተቀየርኩ ብዙ ማሳያዎች አሉ ግን ይሄን ያህል ያስታወቀብኝ አልመሠለኝም ። ወዲያው ከባድ ንዴት ጭንቀት ፍራቻ የተደበላለቀበት ስሜት ተሰማኝ ። ከነ ሳሚ ቤተሰብ ጋ በመተዋወቄም ሆነ ሰላምን ጥሩ  ሙድ ላይ ማየቴ ለነሱ ደስታ መፍጠሬ ቢያስደስተኝም ግን በእራሴ እንድናደድ የሚያረግ ሀሳብ በአይምሮዬ እየተመላለሰ አስቸገረኝ !!! በህይወቴ አንድም ቀን ለእናቴ እንደዛ አይነት ነገር አርጌ አላውቅም ማለቴ ስጦታ ገዝቼላትም አላውቅም !! ምን አልባትም ያንን ነገር የገዛሁት ለእናቴ ቢሆን ኖሮ ሰፈሩን በእልልታ አድምቃ እየዞረች ልጄ ደረሰልኝ ልጄ የገዛልኝ እያለች እንደምታሳይ እርጥጠኛ ነኝ ማንም ቢሆን ምስክሬ ነው !!! ለሰላም በማረጌ ባልፀፀትም ለእናቴ ባለማረጌ አበሳጨኝ !!! ቀኑ እየመሸ ስለነበር ምንም ሌላ እርምጃ ሳልወስድ በዝምታ አዳመጥኳትና ዝም ብዬ ተኛሁ ። ልክ የቀጣዩ እሁድ ቀን በጠዋት ተነስቼ ቤተክርስቲያን ተሳልሜ ስፖርት ሰርቼ እንጀጨረስኩ ቀጥታ ወደቤት መጣሁኔ እናቴን ጠራዋት ። ገላዬን ታጥቤ ወጥቼ እስክመጣ ጠጅ ነው የምትይው ቡና ናፍቆኛል እያፈላሽ ጠብቂኝ ብያት ኪሴ ውስጥ ያለችቅንና የደበኳትንም ይዤ ወጣሁኝ ። ወጥቼ ብሩን ሳይ ሳላስበው ለካ አንድ አንድ እያልኩኝ ጨርሻታለሁ አምስት መቶ ሰባ ብር ናት የቀረች ። የስፖርት ክፍያ ጌጡን የምገዛበት ሲነሳ አርባ ብር ብቻ እንደሚቀር አሰላሰልኩኝ ። ገበያ ን አደርገዋለሁ እያልኩ ራሴን እያሳመንኩ ቀጥ ብዬ ስሄድ አሁንም በድጋሜ አየዋት ። ነፍስ ካወቅን ቡሀላ ምን ተፈጥሮ ሳንተያይ ይሄንን ያህል አመት አስቆጥረን አሁን ቀን በቀን ምክንያቱ ባይገባኝም እንኳን የዛኔ ራሴን ገታ አንርጌ ምንም እንዳልተፈጠረ ቀጥ ብዬ አልፊያት  ሄድኩኝ ። ቀጥታ እዛው ቦታ ላይ ነበረ የሄድኩት ። የሚያማምሩ ጌጣጌጦቼ አሉ ከሰላም በሰጠዋት አይነት ሌላ የሚያምር የአንገጠፈት ጌጥና የእጅ አንባር አየሁኝ ። እዛ ቆሜ ሳስበው መልስ እንዳለኝ የገመትኩትን ብር አንድ ብርም ሳይመለስ ያኛውም ሳልከፍል ያለችኝን  ሙሉ አጠፋው ። ግን ለእናቴ ስለሆነ ምንም ይሁን ብዬ ሄድኩኝ ። ቤት ስደርስ እንደምፈልጠው የምላ ቀጤማዋን ተጠቅማ ቤቱን የሌለ አሳምራ ጠበቀችኝ ። እኔም ቸኩዬ እናቴ ነይማ ብዬ ከውጪ ወደ ውስጥ እንድትገባ አረኳትና ከልጅሽ የሚሰጥሽ ስጦታ አለ ትቀበይኛለሻ አልኳት ፈገግ ብዬ " ለእኔ ልጅ ?? ምን አስቸገረክ ብር እንዳገኘክ ለራስክ ወይ ልብስም ብትሆን አገዛም ነበር " አለችኝ ። ከእሳሷ በላይ ለኔ ሟች ናት !!! ከዛም አሳምራ አስቀምጣ የሰጠችኝና የእጅና የአንገት ጌጥ አውጥቼ ፊት ለፊቷ ያስኩት በጣም ደንግጣለች ገና እንዳየችው ለእኔ ነው ግን ?? ብላ አነሳችውና ማየት   ስትጀምር በደስታ ተሞልተን እያለ ሰካራሙ አባቴ ከአራት ቀን ቡሀላ በእለተ እሁድ ለዛውም በሰንበት ረፋዱ ገድ ገድ እያለ ወደ ውስጥ ገባ ....... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣1⃣
274
12
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣9⃣ ......... ማነው አልኳት ። ምክንያቱን ባላቅም በትንሹ ፈገግ አለች ። ለምን እንደሳቀች ባላቅም በእራሴ ፍቅረኛዋን ስላስታወስኳት  በደስታ ነው የምትስቀው ብዬ ደምድሜ ተበሳጭቼ ዝም አልኩኝ ። " እ እንግዲህ የኔ ፍቅረኛ .......( ረዘም ያለ ዝምታ ) ... ፍቅረኛ ማለቴ ስተት ከሆነ ባላቅም የኔ አማካሪም የምወደውም ወንድሜ ሚስጢረኛዬ ጓደኛዬ ፍቅረኛዬ ሁሉ ነገሬ አባቴ ነው እኔ ያንተን ፍቅረኛ ለማየት ፈልጌ እንጂ ፍቅረኛ የሚባል የለኝም  " ብላኝ አረፈች ። ሌላጨፍቅረኛ ስለሌላት እና ሁሉ ነገሯ አባቷዐመሆኑ ደስ ቢለኝም መዋሸቷ አያደደኝ ። ምክንያቱም እኔ በሷ እልህ ማያን ባላስባት እዚህ ግራ የገባው ስሜት ውስጥ ባልገባሁ ነበረ !!!! ለነገሩ ማን ያቃል ምን አልባት በምክንያት ሊያግባባን ፈልጎ ይሆናል ፈጣሪ ??? ወይስ የቆየ ነገር አሁን ተገልጦልኝ ነው !?? እና ማያን ሳያት ለምንድነው የምደነግጠው ??? ....... በጣም ብዙ ነገሮችን እያሰብኩኝ ከእራሴ ጋር ሀይለኛ የራስ መጋባት ጦርነት ውስጥ ገብቼ አረፍኩት ። ደስ የሚለው ከሀሳቤ ያነቃኝ ከረጅም ሰአታት ቡሀላም ቢሆን ውብ ሆና የመጣችውን ሰላምን ተመለከትኳት ። በጣም ታሳዝናለች የሆነ የማታውቀው ፍራቻ ሰላም ነስቷታል !!! በዛ ላይ ቤቱን ልክ እንደ እንግዳ ነው እየዞረች የምትመለከተው !! ምን ያህል የብቸኝነት ህይወትና የተዘጋ ክፍል እንደከበዳት ፊቷ ማሳያ ይመስለኛል !!! ሳሚም ከዃላዋ መቶ እጇን ይዞ ወንበር ላይ አስቀመጣት ። የቤት አጋዧ እንዳየቻት  በደስታ አቀፈቻት ስገምት ከድሮ ጀምሮ የቆየች ሰው ናት መሠለኝ !!! ከዛም ቶሎ ምግብ አቀራረበችና መብላት ልንጀምር ስንል በስመአብ ብዬ ቀና ስል ሶስቱም እያለቀሱ ነው ። ደነገጥኩ  ሳሚ ልዕልና ምንድነው ምን ተፈጠረ አልኳየው ግራ እየተጋባው ። ልዕልና ከተቀመጠችበት ጠረንጴዛ ብድግ ብላ መጣችና ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ ። በፈጣሪ ስም ሙሉ ሰውነቴ የሆነ ነገር ሲነዝረኝ ተሰማኝ !!! ወዲያው ለቀቀችኝና እየተቀመጠች " ማርያምን አንተ ለኛ ባለውለታ ነክ ከላይ የተላክ መልእክተኛ ነክ ብታምንም ባታምንም እንዲ ተቀምጠን ከበላን ከሶስት አመት በላይ ሆኖናል እኮ !!!!!" ብላ መልሳ ማልቀስ ጀመረች ። ሳሚም ቀበል አድርጎ " ላንተ ቃል የለኝም  ልጅ ፈጣሪ ይስጥክ " ብሎ ንግግሩን በአጭሩ ገታው ። ይባስ ብሎ ሰላምም ቀበል አድርጋ  " ከላይ የተላክ መልአክ ነክ ይሄ ጅማሮ ነው ለእኔ ታስፈልገኛለክ  " ብላኝ አረፈች ። ሲጀመር ወደዚህ ቤተሰብ የተቀላቀልኩበት መንገድም ግራ የሚያጋባኝ እኔ በዚህ ልክ ሲሄድ በቃ ፈጣሪ በእኔ ላይ አድሮ ስራውን እየሰራ ነው ብዬ አሰብኩ !!! ግን በምን ስራዬ እንደሆነም አላውቅም !!!! ብቻ ግን በሁኔታዎቹ በጣም ደስተኛ ነኝ!!!በእራሴ እየኮራሁ ነው ሁላ ! ከዛ እንባቸውን ጠራርገው ወደ ምግቡ ተመለስን ። እዛ ቤት ስሄድ የምበላየው ምግቦች በስመአብ እስከ ሁለት ቀን ያቆዩኛል ማለት እችላለሁ !!! ሀገር አማን ብዬ ምግቡን እያጣጣምኩ እየበላሁ ልጨርስ ስል ያላሰብኩትን ዱብዳ የሆነ ጥያቄ ጠየቁኝ ። የሳሚ ሚስት ትንሽ እንደበላች ነበር የተነሳችው እናም ቁጭ ብላ ስታፈጥብን ነበር ። ልዕልናም ስትጨርስ " እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ " አለች ፍልቅልቅ እያለች ። መጀመሪያ ላይ ጉዴን ሳላውቅ የሚያምረው ፈገግታዋን በመመልከት ብቻ አብሪያት ስስቅ ነበር " ምንድነው ልጄ እሺ ተናገሪ " አላት ። " እማዬ ከቤት ወታ ስለማታቅ አንድ ቀን ሰብሰብ ብለን የነ  ሚኪ ቤት ሄደን ቤተሰቦቹን እንተዋወቃቸው ደስ አይልም " አለች ምን ደስ የሚል ነገር እንዳወራች ባላውቅም ;መጀመሪያ ሚኪ ስትል እኔን አልመሠለኝም መሠለኝ ዝም ብዬ ነበር " ደስ አይልም ሚኪ " ስትል ነበር ክው ብዬ አፌ ውስጥ ያለው ምግብ ትን ብሎኝ ልሞት እስክደርስ አስደንብሮን ሁላችንም እስክንጨነቅ ድረስ አሰቃይቶኝ በስንት መከራ ለቀቀኝ !! በሂወቴ ትልቅ መርዶ ብሰማ ራሱ እንደዛ የምደነግጥ አይመስለኝም በስመአብ !!! በስንት ስቃይ ከተረጋጋሁ ቡሀላ ሰላምና እሷ ምነው ምንድነው ምን ተፈጠረ ... እያሉ በጥያቄ ቢያስጨንቁኝም ምርጡ ሳሚ ግን ስሜቴን ተረድቶት በዝምታ ተቀምጦ ቆየና በስተመጨረሻም " ምን ችግር አለ እሁድ ይጋብዘናል ግን እኔ ከቤት ይልቅ መጀመሪያ ካፌ ነገር ብትጋብዘን ባይ ነኝ  " አለና በአይኑ ምልክት ሰጠኝ ። እ እሺ አረ ችግር የለውም ብቻ ሰላም ይሻላት እንጂ አልኩኝ እየተንተባተብኩኝ ። ከዛም በቻልኩት ፍጥነትና ምክንያት ደራርቤ ቶሎ ከዛ ቤት ወጣሁ ። ለእኔ በጣም አስደንጋጭ ጥያቄ ነው ። ራሴን ካወኩ ጀምሮ በስተት እንኳን የሰው ቤት ገብቼ አላውቅም አድጌ የክላስ ጓደኞቼንም ቢሆን ቤት ላለመውሰድ ነው የነሱ ቤት የማልሄደው !!! የልዕልናን ዘግናኝ ጥያቄ እያሰላሰልኩ ወደቤት ስሄድ  ከፊቴ ማያ ስትመጣ ተመለከትኳት ። በአጋጣሚ ብዙ ጊዜ እያገኘዋት እንደሆነ ይታወቀኛል !!! ልክ እሷን ሳያት ልዕልናንም ችግሬንም ድንጋጤዬንም ሁሉንም እንድረሳ አድርጋ ትኩረቴን ተቆጣጠረችው!!! በልቤ ላይ እየተካሄደ ያለው የስሜት  ጨዋታና ከሆነ ጊዜ ጀምሮ እሷን ማግኘቴ ሲገጣጠምብኝ ላናግራት ወሰንኩ ። ልክ በአጠገቤ ስታልፍ ምን እንደምላት ሳላስብ እንኳን ማያ ቁሚ ብዬ ከፊቷ ሄጄ ግትር አልኩ???? . . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣0⃣
308
13
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣8⃣ .........ወደ መታጠቢያ ቤት ሮጥን ። በር ላይ ስንደርስ እኔ እዛው ቆምኩ ልዕልና በሩን ከፍታ ልትገባ ስትል ከትት ብለው ሲስቁ ሰማን ። ነገሮች ግራ አጋብተውኝ ልዕልናን ስመለከታት በሩን ኳ ኳ እያደረገች "  ማ ማ ደህና ነሽ ምንድነው ሰላም ናችሁ " አለቻት። በጭንቀት ልባችን ልትወጣ ደርሳ ነበር ሳሚ ግን ፈገግ ብሎ በሩን ከፍቶ ብቅ አለና ደህና ነን አታስቡ አረ የድሮውን አስታውሰን ነው እኮ " አለ ። እሱ ላይ ያንን ፈገግታ ማየት ደስ የሚል ነገር ነው ። በባለቤቱ ጉዳይ በጣም እንደተጎዳ ግልፅ ነገር ነው!! በምላሹ ተደስተን ሁለታችንም ተመልሰን ወደ ሳሎን ሄደን ፊት ለፊት ለፊት ለፊት ተቀመጥን እውነት ለመናገር ረብሾኛል እኔ ከእራሴ ጋ እየተጋጨሁ ነው ደ እኔ ስለ ፍቅር ምንም የማላውቅ ልጅ አሁን ከራሴም ጋ አልተግባባሁም ። ሰሞኑን እየተፈጠሩ ባሉት የእንግዳ ስሜቶች ጥርቅም በጣም እየተጎዳሁ ያለሁ ይመስለኛል !!!! ምክንያቱም ተሰምተውኝ የማላቃቸው ስሜቶች ሁለት በተለያየ አለም በሚኖሩ ሴቶች ላይ እየተሰማኝ ነው ??? የትኛው ስሜት ምን እንደሆነ ራሱ አላውቅም እኔ ስሜቶቹ ምን እንደሆኑ ራሱ አላውቅም !!! ብቻ  ማያን ሳያት የሚከሰቱት እነዛ የማላቃቸው ስሜቶች አሉ ራሴን አለመቆጣጠር መደንገጥ መወዛገቦች አሉ ??? አሁን ላይ ደግሞ ልዕልናን ሳያት የሆነ ስሜት አለ ደስ ይለኛል እንድትነካኝ አልፈልግም ምክንያቱም የሚፈጠረውን የልብ ንዝረት አልችለውም !!! ስትቀርበኝ እፈራለሁ !! ሳያት የሆነ የሚያሳሳት ነገር አለ .......እና  ብቻ ግን እኔ ግራ ገብቶኛል እነዚ ቀይ ቆንጆና ጠይም ቆንጆ ሴቶች ግራ አጋቢ ስሜቶችን እያበዙብኝ ነው ያ ደግሞ ለእኔ ጥሩ አይደለም !!! እኔ ታች ቁጭ ብዬ ልዕልናን ላለማየት አይኔን ሳማትርና ስታገል ነበር ። ለደቂቃዎች በዝምታ የቆየች ቢሆንም ጭንቀቱ ለቀቅ ሲያደርጋት ነው መሠለኝ " ደህና ነክ ግን አንተ ?" አለችኝ ጠረንጴዛ ላይ ያስቀመጠውን ኩትን እጅ ነካ እያደረገች ። እኔ ከአይኗ ለመራቅ ስሞክር እሷ ጭራሽ ያንን ቀይይይይ እና ለስላሳ የሚያንፀባርቅ እጇን ትልክብኛለች ወይ ጉዴ !!! ደግነቱ ቶሎ እጇን አነሳችለኝ እንጂ ውሀ ሆኜ ነበር !!!ራሴን አረጋግቼ ደህና ነኝ አረ ምነው ? አልኳት " እኔንጃ ፊትክ የተረበሽክ ይመስላል " አለችኝ እጆቿን ከአገጯ ጋር እያወዳጀች ። ስትነካኝ ብደንግጥም እንድትነካኝ ባልፈልገም ሳያት ምናለ እጆቿን አቅፌ በተቀመጥኩ  ከጉንጮቼ ጋር አጣምሬ በቆየሁ ብዬ እመኛለሁኝ !!! በነገራችን ላይ ስለሁሉም ቁንጅና ተናግሬ ራሴን ዘነጋሁት መሠለኝ ☺️☺️ እና እናቴና ሌሎች በርካታ ሰዎች እንደሚሉት ከሆነ የሚያምር የቆዳ ቀለም ከሚያምር አይን ጋር ሰልካካ አፍንጫ ከተደረደሩና ነጭ ከሆኑ ውብ ጥርሶች ጋር ለስላሳና በመጠኑ ያደገ ፀጉር ስፖርት የጀመርኩት ከብቸኝነት ለመሸሽ እና ጊዜዬን ለማሳለፍ ቢሆንም የሚያምርና የተስተካከለ አቋም ዘመኑን ከዋጀ አለባበስ ጋር ብዙ ነገር ሰቶኛል !!! ብቻ ምን አደከማቹ ልቅም ያልኩ ቆንጆ ነኝ !!!😂አልፎ አልፎ እነሱን ብጠራጠራቸውም የእናቴ ክብ መስታወት ፊት ስቆም ራሴን እንደ ቆንጆ መቁጠር እጀምራለሁ !!! ከገባሁበት ራስን የመቆለል ሰመመን ውስጥ ያነቃችኝ " ደግሞ ፍቅረኛክን ሳታስተዋውቀኝ አ " ስትል ነበረ ። እንደዛ ስትል ማያ ትዝ አለችኝ ግን ከውሸቶቼ መሀል አንድ ልቀንስ ብዬ አስቤ ያንቺን ባል አስተዋውቂኝ እንጂ እኔ ፍቅረኛ የለኝም አልኳት ። የሆነ ፈገግታ አየሁባት የምን እንደሆነ አላውቅም ግን ደስ ብሏታል ። ፍቅረኛ እያላት ምንድነው እንዲ የሚያስደስታት ሆይ ። ውይ የሀብታም ልጆች ግን ከመቼው ነው ይቺ ልጅ ፍቅረኛ የያዘችው ምናለ ቢያስ ትንሽ ብትቆይ ወይ ቢያንስ ደግሞ ከኔ ጋ ባትተዋወቅ ለነገሩ ከመሠሎቿ ጋ መሆን አለባት ያመኛል እንዴ ........ በጣም ቦዙ ነገሮች እየቀባጠርኩ ብቻዬን ሳወራ ነበረ ። " የኔን ፍቅረኛ እኮ ታቀዋለህ " አለችኝ ። ክው ነው ያልኩት ። ማ እኔ አልኳት ግራ ገብቶኝ ። " አዎ ታቀዋለህ እኮ " አለችኝ ምላሹን የመስማት ፍላጎት ባይኖረኝም ማነው ?? አልኳት . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣9⃣
222
14
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣7⃣   .........,እዛው ቁሜ ቀረሁ ; ከዛ ልዕልናን ዞሬ ሳያት እንዴት እንደተረዳችኝ ባላውቅም ከተቀመጠችበት እየተነሳች " እማ እሱኮ ሚኪ ነው አስተዋውቅሻለሁ ያልኩሽ ልጅ እሱ ነው ጥሩ ልጅ ነው በዛ ላይ  የአባዬ ጓደኛ ነው እኮ " አለቻት ልክ እኔ በያት ልላት አመት እዳሰብኩት ለዛውም የተሻለ አርጋ አሳመነችልኝ ። ቀስ ብላ ተረጋጋች አየር እየሳበችና እየተነፈሰች ራሷን አረጋጋች ። ይቺ ሴት እብድ አይደለችም !!!! ምን ማረግ እንዳለባትም ሆነ ምን እያረገች እንደሆነ ጠንቅቃ ታውቃለች ራሷን እንዴት እንደምታረጋጋ ሳየቀር ታውቃለች ። ሰው  ስለበደላት የሰው ጥላቻ ብቻ ነው እሷን የጎዳት  !!!! እና እሷን ለማረጋጋት በጣም ቀላል ነገር ነው !!! እኔም እድሌን ተጠቀምኩኝ እግሯ ስር በርከክ ብዬ እያረጋጋዋት ላንቺ ባይመጥንሽም ስለ አንቺ ስለነገሩኝ ትንሽዬ ስጦታ አምጥቼልሻለሁ ማየት አፈልጊም ?? አልኳት ። ተመቻችታ እየተቀመጠች ቁጥብ ፈገግታ አሳየችኝ ።ከዛም ብልጭልጭ ቢሆንም በምርጫ ጎበዝ ነኝ መሠለኝ ስጦታውን ሳወጣሁ ሁሉም ተገርመው አዩኝ ሳስበው አልጠበቁም መሠለኝ !! እሷም በጣም እንደወደደችው እንድገምት የሚያደርግ ፊት አሳየችኝ ። ከዛም ከማስቀመጫው ላይ አውጥታ እየወሰደች " በጣም ያምራል " አለችኝ በለሆሳስ ። ድምጿ በጣም ደስ ይላል !!! በዛ ላይ በጣም ቆንጅዬ ናት !!! በርግጠኝነት ሳሚ ራሱን ጥፋተኛ አደረገ እንጂ  በቁንጅናዋና በእድለኝነቷ የተነሳ በቅናት ተገፋፍታ እንዲ ያደረገቻት ይመስለኛል !!! ግን ምን አይነት ጭካኔ ነው በፈጣሪ የፈለገ ቢሆን እንዴት አብሮ አደግ ጓደኛዋን እንዲ ታደርጋታለች ሴትዮዋን ባቃትና የኔ እናት ብትሆን የምገላት ሁላ መስሎ ተሰማኝ !!! ብቻ ግን ቃሉ አትፍረድ !! ነውና ፈርጄ ከጨረስኩም ቢሆን አስታውሼ ዝም አልኩኝ ። እኔ ሀብታም ሰዎች አርቴፊሻል ነገር የሚጠቀሙም አይመስለኝም ነበር ፊቴ ላይ ትወረውረው ይሆን እንዴ እያልኩ እየፈራሁ ነበር የሰጠዋት ። ከጠበኩት በተቃራኒው ግን በጣም እንደወደደችው እየነገረችኝ በፍቅር አይን  እያየችኝ " አመሠግናለሁ በጣም " አለችኝ ። ኡፍፍፍ የኔ እናት እርጋታዋ ደርባባነቷ በጣም ነው ደስ የሚለው ። ረጅምና ለስላሳ ፀጉሯ ሁለት ቦታ እንደተሰራ የቆየ ይመስላል ። ያ ቀይ ፊቷ በቁስል እና በተቧጨረ ነገር ተሞልቷል ሲመስለኝ ሲያማት ራሷን ለማጥቃት ትሞክራለች መሠለኝ !!! ግን የተፈጥሮ ውበቷ ያስታውቃል በዛ ላይ ያን ያህል ትልቅ አይደለችም ወጣት የምትባል ሰው ናት !!! እኔ በሷ ተፈጥሮ እየተመራመርኩ ለካ ሳሚ እያወራ ምን እንዳለ ሳልሰማው " እናመሠግናለን  " ሲል ብቻ ሰማሁት ። ምን ይበል ምን ባላውቅም አረ አይባል ሳሚ ብዬ ፈገግ አልኩኝ ። ከዛ እዛ ሀብሉን ልታረገው ስትል አይ አይ እንደዚ አይደለም መጀመሪያ አንዱን ልዕልና አንዱን ሳሚ ፀጉርሽን ይፈቱታል ከዛ ረጅም ሰአት የሚፈጅ ሻውር ከባለቤትሽ ጋ ትወስጃለሽ ቀስ ብሎ ያጥብሻል ከዛ ልብስ ትቀይሪና ጌጥሽን አድርገሽ ዛሬ ከእኔ ጋር ነው ምሳ የምንበላዎ እንጠብቅሻለን አልኳት መልሷ ምንም ቢሆነን ለመጋፈጥ እየተዘጋጀሁ ። እንዳሰብኩትም ማልቀስ ጀመረች ስቅስቅ ብላ ካለቀሰች ቡሀላ ወደኔ ተጠግታ ጭምቅ አድርጋ አቀፈችኝና " የምር እንዳልከው ማረግ እችላለሁ እ ??" ብላ በጥያቄ ፊት አየችኝ ። እኔም በደስታ ተሞልቼ  አዎ አዎ በደንብ ትችያለሽ በጣም ቀላል ነገር ነው እኮ ትችያለሽ !!!! ብዬ ለማነቃቃት ሞከርኩኝ ተመቻችታ ተቀምጣ  ዞር ብላ ሳሚን አየችው ። እሱም እሺ የምትል ስላልመሠለው ችላ ብሎ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም  ስታየው በደስታ ተነስተው ሁለቱም እንደ እንቁላል እየተንከባከቡ በቀስታ ፈቷት ። በጣም ተጎድቶ ራሱ የሚያምር ፀጉር አላት ከዛም ወደ ሳሎን ተመልሰን እኔና ልዕልና ቁጭ ብለን ሁሉም ሰላም እንዲሆን እየፀለይን ቆየን ። ከዛም ቀራርቦ  የነበረው ምግብ አንዳንዶቹን እያነሳች ማሞቅ እና ሰላም በፊት ላይ ትወዳቸው የነበሩ ምግቦችና ጁስ መጨመር ጀመረች ። ልዕልና በጣም ጨንቋት ስትቆም ስትቀመጥ ስትነሳ ስትጨነቅ ነበር እውነት ለመናገር እኔም በጣም ፈርቻለሁ !!! የሆነ ነገር እንደሚቀየር እያሰብኩ ተጨንቄ ነበር ። እዛው ተቀምጠን ከ አንድ ሰአት ከሀምሳ ደቂቃ በላይ ቆየን !! አዲስ ነገር ብንጠብቅም ቆዩብን።እስከዛ ሰአት ሰላም መሆናቸው ትንሽ አረጋግቶኝ ልክ ቁጭ ስል የሚረብሽ ጩኸት  ሰማንና ሁለታችንም ለሩጫ እንደተዘጋጀ አትሌት በሩጫ ወደመታጠቢያ ቤት ሮጥን ......... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣8⃣
348
15
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣6⃣  ........ ከማያ ጋ ተገጣጠምኩ ። በፊት ላይ አግኝቻትም የማላቃት ልጅ አሁን በዚህ ልክ መገጣጠማችን በጣም እያስገረመኝ ነው ። አሁን አልተሳሳትኩም ራሴን እንደምንም ተቆጣጥሬ አለፍኳት ። የሆነ አካሌ ግን ያዛት ያዛት ይለኛል ?? ከዛም ምን እንደሚያያዝ ባላውቅም ሀብታም ቤት  ሙዝ ይዤ አልሄድም ብዬ ገበያ ውስጥ ስዟዟር የሆነ የሚያምር ጌጣጌጥ ቤት ተመለከትኩኝ ። አርቴፊሻል ቢሆንም የሚያማምር ሀብልና የእጅ ጌጥ አየሁኝ ። እና ሚኪ በጣም አስተዋይና አሳቢ ሰው ስለሆነ የሷን መንፈስ የሚያድሱና እሷን የሚያስደስቱ ነገሮች መግዛት ይሻላል ብዬ አሰብኩኝና በሌለኝ ብር መከራከር እንኳን አልችል የሚያምር ሀብልና የእጅ ጌጥ ገዝቼ በእቃ ላይ አስደርጌ ወደነ ሳሚ ቤት ሄድኩኝ ። ልክ እኔ ስደርስ የሳሚ  መኪና ስትገባ ተገጣጠምን ። ስራ ጨርሶ ምሳ ለመብላት መምጣቱ ነበር ። እኔም እግር ጥሎኝ እያልኩኝ በአይነት የቀረበው ምግብ ላይ ደረስኩኝ ። ሚኪ ከባድ የራስ መተማመን ተጭኖታል ። መኝታ ቤቷን ቆልፋ የምትኖረውን የልዕልናን እናት ሰላምን ጤነኛ ሰው ለማረግ ሀላፊነት ወስዷል ። ልዕልናም እጇን ተጣጥባ ስትመጣ ከኔ ጋ አይን ለአይን ተገጣጠምን ። እየሮጠች መታ ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ ። ደነገጥኩኝ ክው ብዬ እስክትለቀኝ መጠበቅ ጀመርኩኝ ። " ትላንት እኮ እናቴን አወራዋት ከስንት ጊዜ ቡሀላ አወራችኝ ስታለቅስ አየዋት በጣም  ነው የምናመሠግነው እሺ ደግሞ ስለ አንተ ነግሪያታለሁ እኮ አስተዋውቅሻለሁ ብያታለሁ  " ብላ ጉንጬን ሳመችኝ ። ክው ነው ያልኩት !!! ደንግጬ ፍዝዝ ብዬ ሳያት ምንም ሳትል ዞራ ምግቡ ጋ ቁጭ አለች ። ወዲያው አንድ የሚገርም ሀሳብ መጣልኝ ቀጥታ ወደ ሳሚ ዞርኩኝና አንድ ሀሳብ አለኝ !! አልኩ ፈገግ ብዬ " ምንድነው እሺ  " አለኝ ሳሚ ወንበሩ ላይ እየተቀመጠ ። ወደ ምግብ ከመግባታችን በፊት አንዴ ሰላምን እንያት አልኳቸው ። ቤቱ በአበቦች ነፈካ ስለሆነ ከማስቀመጫው ላይ አበባ ሳብ ሳብ አርጌ ሁለት አወጣሁ እና ይሄን ይዘን አልኳቸው ። " አሁን ምሳ ሊቀርብላት ነው ትብላና እናወራለን ከፈለክ " አለኝ ሳሚ በተጨናነቀ ፊት ። አይ አይ አይሆንም ምግብም አብረን ልንበላ እንችላለን ማን ያውቃል አልኳቸው ። በጣም ደስ እያለኝ ነው ሀሳቤን የነገርኳቸው !!! ሳስበው ሚኪ ጥሩ የስነ ልቦና ሀኪም መሆን የሚችል ይመስላል !!! በጣም አስተዋይ ሆኛለሁ ሲጀመር እዚህ ቤት ስመጣ ሌላ የማላቀውን ሰው ነው የምሆነው ። ብቻ ግን  መልሳቸውን ስጠብቅ ልዕልና ቀደም ብላ " ጥሩ ሀሳብ አይመስለኝም " አለች ሳሚም እሷን ተከትሎ " አዎ አትልፋ አይሆንም እሺ አትልም " አለኝ ከየት እንዳመጣሁት ባላቅም ይሆናል !!! ባይሆንም እንሞክረዋ ከሆነ ይሆናል ካልሆነ ቀጣይ ይሆናል ባለፈው ቀን እኮ አምንሀለሁ ብለከኛል እንደምታምነኝ አሳየኛ !!! አልኩት ። ሳሚም አላሳፈረኝም እሺታውን ለመግለፅ ከተቀመጠበት ተነሳ ። ልዕልና ሀሳቡን እንዳታስቀይረው ፈርቼ በእጄ ግትቼ ላነሳት ስሞክር ገና እንደያስኳት የሆነ የንዝረት ስሜት ስለተሰማኝ ደንግጬ ቶሎ ለቀኳት  ። ከዛም አበባውን ለሁለቱም  ሰጠዋቸውና እናንተ ግቡና እመጣለሁ ብያቸው ወደዃላ ቀረሁ ። ከዛም ወደ ልዕልና ጠጋ ብዬ ገብተሽ በደንብ አውሪያትና ከዛ እንግዳ ላስተዋውቅሽ ብለሽ ጥሪኝ አልኳት ቀስ ብዬ እሷም እሺ ብላኝ ወደ ክፍሏ ሄድን ። ሁለቱም ከመፍራታቸው የተነሳ በሩ ላይ ሲደርሱ ሁለቱም በረጅሙ ተንፍሰው አማትበው ወደ ውስጥ ገቡ ። ውጪ እያለች ልዕልና በጣም ፈርታ የነበረ ቢሆንም ቀበጥ መሆኗ ጠቀማት መሠለኝ ፍልቅልቅ እያለች " ማማ አየሽ ምን እንዳመጣንልሽ አበባ ላንቺ ነው እኮ ናፍቀሽን ነበር " አለቻት እቅፏ ውስጥ እየገባች። ሳሚ ቃላት ማውጣት ስለከበደው በፀጥታ ተውጦ ግንባሯን ሳማትና ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ ። ከዛም ልዕልና ቶሎ ብላ " እማ የማስተዋውቅሽ ሰው አለ " ብላ በምልክት  ጠራችኝ ። እስካሁን እነሱን ሲመክርና ሲያበረታታ የነበርኩ  ልጅ  ለመግባት ራሱ ፈራሁ ከዛ ግን ሳማትብ ለቀቀኝና ፈገግ ብዬ ገና እግሬን ሳስገባ ወደዃላ እየሸሸች መፍራትና መንቀጥቀጥ ጀመረች የሆነ መንፈስ እንዳየ ሰው አረጋት ። " ከነገርኩህ ጊዜ ጀምሮ ሰው ትፈራለች የማታቀውን ሰው አትወድም ትሸሻለች ነግሬህ ነበር እኮ እንደማይሆን " አለኝ ሳሚ ከተቀመጠበት ተነስቶ በቀስታ ። የነበረኝ ትልቅ በራስ መተማመን ይጥቀመኝ ይጉዳኝ ባላውቅም በራሴ ተማምኜ ሊሆን ይችላል ብዬ ወደሷ ቀርቤ ከአልጋው ስር በርከክ ብዬ ስቀመጥ በትልቅ ፍራቻ ታየኝ ጀመር ። እኔ በሌለኝ ብር አውጥቼ የገዛውት ስጦታ ልሰጣት ከሁዴዬ ውስጥ ፌስታሉን ሳወጣ እሪሪሪ ብላ ጮኸች መረበሽ ጀመረች ትራሶቹን ወረወረችብኝ ማልቀስ ጀመረች ......... በጣም ደነገጥኩ ሳሚ እጄን እየጎተተ እንደወጣ ቢነግረኝም እዛው ቆሜ ቀረሁ ....... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣7⃣
250
16
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የፍቅር የሰላም የጤና ያርግልን ❤️ @ethioleboled
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የፍቅር የሰላም የጤና ያርግልን ❤️ @ethioleboled
315
17
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣5⃣  ......... እጇን ጭምቅ አድርጌ ያስኩት ። ልጅቷ ስርአት ያላት ፈሪና ጭምት  ሰው ናት ። ስይዛት ከመደንገጧ የተነሳ እጆቿ እየተንቀጠቀጡ ነበር ። ግራ ቢገባት ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ " ምንድነው ችግር አለ ?" አለችኝ በታፈነና ቀስ ባለ ድምፅ ። ምን እያሰብኩ እንደነበር አላውቅም እንደመባነን ብዬ እጇን ለቀኳትና በጣም መርበትበት ጀመርኩኝ ። እ.... እ .... እያልኩኝ ወደፊት ወደዃላ መርበትበት ጀመርኩኝ ። ምን እንደሆንኩና ምን እየተሰማኝ እንዳለ ማወቅ አለመቻሌ የበለጠ ግራ አጋባኝና እረበሸኝ !!! ከዛ በላይ ከፊት ለፊቷ ቆሜ መጋፈጥ ስላልቻልኩኝ የሌለብኝን ከአንገቴ ጎንበስ ብዬ   ይቅርታ ብያት ፖሊስ እንዳባረረው ሌባ በሩጫ ከቦታው ራኩኝ ። ቀጥታ ወደቤት ሄድኩ ። ስገባ እናቴ ቡና እያፈላች ነበር ። " ምሳ ስጠብቅህ ቆየህብኝ እኮ ልጄ በሰላም ነው ሰሞኑን ከቤት መራቅ አበዛክብኝ " አለችኝ ። እውነት ለመናገር ልክ ናት ወይ ቤት አይደለሁም ወይ ደግሞ ቁጭ ብዬ ስለ ልዕልናና ስለ ቤተሰቧ እያሰብኩ አመሻለሁ በቃ !!! የዛሬው ለየት የሚያረገው ግን የእናቴን ስፔሻል ምግብ ድንይ በሽሮ ከበላሁና ድካም የሚያጠፋው ቡናዋን ከጠጣሁ ቡሀላ ገብቼ ስለ ማያ ማሰብ ጀመርኩኝ ። በርግጥ ስሟንም የማውቀው አንድ ትምህርት ቤትና አንድ ክፍል በመሆናችን ነው ። የክላሱ ቀለሜ እና ዝምተኛ የፊት ወንበር ወዳጅ እንደሆነች ባውቅም ትኩረት ሰጥቻትም ሆነ በስህተት እንኳን አውርቻት የማላቃት ልጅ አንድ ቀን በራሴ የፈጠርኳት ካራክተር ከመሆኗ ብሶ እንዴት ሆኖ አሁን ላይ የሚሰማኝ ስሜት እንደተፈጠረ አልገባ ብሎኛል ። ምሽቱን ሙሉ ከአይምሮዬ ማውጣት ከብዶኝ ተጨነኩ !!! ጠዋት በጠዋት ተነስቼ እንደተለመደው ተሳልሜ ኸደ ስፖርት ሄድኩኝ ። ሀሳቤን የሚያስረሳኝ ይመስል በጣም ለረጅም ሰአት ስሰራ ቆየሁ ። ረጅምም ሰአት ከመስራቴ የተነሳ በጣም ደክሜ ትንፋሼ መቆራረጥ ጀምሮ ነበር ቆይቼ አስተዋልኩት እንጂ  !! አሰልጣኙ መቶ እንዳቆሚ ስነግረኝ ነበር ትዝ ያስተዋልኩትም !!!! ከዛ ወጥቼ ቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩኝ ። መንገዱን ሙሉ ፊት ለፊት እንዳላገኛት እየፈራሁ እንደሰረቀ ሰው ዙሪያዬን እያማተርኩ በሰቀቀን ስጓዝ ከፈራሁት በበለጠ እናቴ መስከረም እና ማያ አንድ ላይ ፊት ለፊቴ ሲመጡ አየዋቸው ። ወደ ግራሞ ወደቀኝም ብመለከት መታጠፊያ የሚባል የለም መሀል ግድግዳዎች ናቸው ። ወደዃላ ተመልሼ ልሄድ እያሰብኩ እያለ ከሩቅ እናቴ ፈገግ ስትል አየዋት ደ ያ ማለት ደግሞ አይታኛለች ማለት ነው  ብዬ ስላሰብኩ ቀጥ ብዬ ቆምኩኝ ። የሚያናደው ደግሞ አጠገቤ እየቀረቡ ሲመጡ ነበር ያስተዋሉኝና የዛኔ ነበር የእናቴንና የመስከረምን ተገርሞ እኔን ማየትና የማያን ቀድንጋጤ ቀጥ ብሎ መቆም ያስተዋልኩት ። ምናለ ቀጥ ብዬ ብመለስ ያልኩት !!! ምክንያቱም ገና ሲቀርቡኝ ሌቤ መረበሹና እንግዳ ስሜቶችን ማስተናገድ የጀመርኩት ። አጠገቤ እንደደረሱ እንደሁሌው እናቴ አገላብጣ ሳመችኝና " ልጄ ስጠብቅህ ስትቆይብኝ እኮ ነው የወጣሁት " አለችኝ  ቀበል አድርጋም መስከረም እንደናቴ ከሰማችኝ ቡሀላ " ጎረምሳው አሁንማ እየጠገብክ ነው እንደልጅነትህም አይደለህ " አለችኝ ። እሷ ስታወራ ሲያስጨንቀኝ የነበረው ግን ሰላም ልበላት አልበላት እያልኩ ግራ ስጋባ ነበር !!! እጇን መንካት ፈራሁ ሁላ ብቻ አረ እንዴት እናንተ ላይ ይጠገባል አንድ ላይ አሳድጋችሁኝ ... ምናምን ብዬ ነገሩን ለመደባበስ ሞከርኩኝ ። "" የመስኪዬ ልጅ ናት እኩ ሰላም በላት እንጂ " የሚለው የእናቴ ንግግር ነበር ቆሌዬን የገፈፈው ። ምን እንደማረግ ግራ ገብቶኝ እናቴን ስመለከታት ቆየሁኝ ። በአይኗ ቁጣዋን ስታሳየኝ ደንግጬ እጄን ዘረጋሁላት እሷ ፈርታለች ቶሎ እጄን ነካ አድርጋ ሰበሰበችው ። ምንም ባላመጣው እኔን መንካት ደብሯት ነው ! በዬ ተናደድኩኝ ። ሳስበው ስናደድ ነው መሠለኝ ወደ እራሴ የምመለሰው ኮስተር ብዬ ሰላም ዋሉ ብዬ ማያን ገፍተር አድርጊያት አልፌ ሄድኩኝ ። ቤት ገብቼ ሻውር ወስጄ ጨርሼ ራሱ መናደዴን ማስቆም አልቻልኩኝም የሆነ ያለመከበር ያለመፈለግ አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ !!! በእራሴና በሁኔታዎች እየተናደድኩኝ  ነበር ። ከዛ ቁርሴን በልቼ ጨርሼ ለጥ አልኩኝ ። ደክሜ ስለነበር ቶሎ እንቅልፍ ወሰደኝ ለረጅም ሰአት ተኝቼ ተነሳሁኝ ። ከዛ ስነቃ ሳሚ ትዝ አለኝ ። ብር ማስቀመጫዬ ላይ ሳይ ትንሽ ብር ነበረችኝና ህመምተኛ ለመጠየቅ በሚል ሰበብ ለመሄድ አሰብኩ ከዛ ለባብሼ ከቤት ወጣሁ ልክ ስወጣ ከማያ ጋ ተገጣጠምኩ  ...... . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣6⃣
302
18
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣4⃣ ......... ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ ። እሷም ክው ብሓ እርምጃዋን ገታችው ??? እየተፈጠረ ያለው ነገር ከኔ አልፎ ያስጨነቀው ሳሚ " ምነው ልጄ ችግር አለ ?" ብሎ እጄን ሲይዘኝ ከገባሁበት ሰመመን ባነን ብዬ ይቅርታ ሳሚ የሆነ ነገር ትዝ ብሎኝ ነው !! ብዬ ንግግሬን ገታ አደረኩት ። እሷም የበለጠ ነጠላውን እየተሸፋፈነች አንገቷን ደፍታ ቄሱን  ተከትላ ሄደች ። ምን እንደተፈጠረና ምን እንደሆንኩ ያልገባኝ እኔ በሀሳብ ተውጬ እያለ ነበር ሳሚ " ልትነግረኝ ካልፈለክ ተወው በቃ " ያለኝ ። ለካስ ስለ እራሴ እንድነግረው ሲጠይቀኝ ስለነበር ይሄ ድንጋጤ የተፈጠረው ማውራት ያልፈለኩ መስሎት ነበር ። እኔም አረ በጭራሽ እንደዛ አይደለምዐበምነግርህ ህይወት ለመገረም ተዘጋጅ እንጂ ነግርሀለሁ አልኩት ። በመጀመሪያ ትክክለኛ ስሜ ሚኪያስ አይደለም ሀብታሙ ነው ብዬ መናዘዝ ጀመርኩ ። ገና ሳልነግረው የተገረመ ፊት አሳየኝ ። እኔም ፈገግ ብዬ እኔ የደሀ ልጅ ሆኜ ስሜ ሀብታሙ መሆኑን ስለማልወደው ነው ያስቀየርኩት ። እና ደግሞ እናቴም አባቴም በጣም ደሀ ከተባለ ቤተሰብ ወተው ደሀ ቤተሰብ መስርተው ይኖራሉ ። የቤቱ ብቸኛ ልጅ ነኝ ። አባቴ የመጠጥ ሱሰኛ ነው አንድ ካቲካላ ጎንጨት ካላለ የሎብ ምት እንደቆመ ሰው ያረገዋል ። ሲጠጣ ደግሞ ታርዳ እንደተጣለች ዶሮ ያንፈራግጠዋል !!! ከልጅነቴ ጀምሮ በድህነት ህይወት ውስጥ ነው ያደኩት ። እናቴ ጉልት ሰርታ ነው ያሳደገችኝ አባቴ አልፎ አልፎ ይሰራል ችግሩ እዛው በካቲካላ ይጨርሳታል ። እናቴን ያን ያህል ጠባየ ግዛትም እንደገቢያችን ወጪም የለንም እኔ ከጠገብኩ አለም ሁሉ ሰላም ውሎ ያደረ የሚመስላት ምስኪን እናት ናት ያለችኝ ። " አልጠራጠርም " አለ ሳሚ ጣልቃ ገብቶ ። በቃ አሁን ላይ የምታነው ሀብታሙን የገነባችው እናቴ ናት ሚኪን ለመገንባት ደግሞ በትንሹ የራሴ ጥረትም አለበት ። እና አጋጣሚ ከእናንተ ጋር አስተዋወቀኝ እኔ መኖር አለመኖሩንም የማላቀውን አይነት ህይወት ነው የምትኖሩት ። ደግሞ በፈጣሪ ስም የምምልልክ እኔ በገንዘብ የምገዛ ሰውም አይደለሁም እና ለገንዘብ ብዬ የቀረብኳችሁ ምናምን እንዲመስላችሁ አልፈልግም እኔ በትምህርቴም ደካማ አይደለሁም በጉልበትም ጠንካራ ነኝ በራሴ ሰርቼ ማግኘት የምችል ሰው ነኝ ነገሮች አልመቻች ብለውኝ ነው አልኩት ። ከሱ ጋ ሳወራ  ከልቤ ነው የማወራው እና ለረጅም ደቂቃ በጣም ብዙ ነገር አወራን ከሱ የምደብቅበት ምክንያት የለኝም ለልዕልና ይንገራት አይንገራትም  አላሳሰበኝም ሁሉንም ነገር  ነገርኩት ። በጣም ለብዙ ሰአት ነው ያወራነው ደስ የሚለው እሱም በእኔ ላይ ሙሉ እምነት እንዳለው እስከመጨረሻው አብረን እንደምንዘልቅ እኔን እንደ ልጅም እንደ ጓደኛም እንደተቀበለኝ ሙሉ በሙሉ እንደሚያምነኝ ስለ ድህነት ስለ ሀብት እሱም በፊት ላይ ምን አምነት ህይወት እንደነበረው ብቻ በጣም ብዙ ነገር አወራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በዚህ ልክ የውጪ ሰው ሳወራ ። ከሰው ብጣላም ከአስተማሪ ብጣላም በድህነት ብከፋም ብቻ ምንም አይነት ነገር ቢኖር እናቴ እቅፍ ውስጥ ገብቼ ነው የማለቅሰው ሌላ የማወራውም የለኝም ። ከረጅም የግል ንግግር ስንነቃ ነበር ቤተክርስቲያን ውስጥ መሆናችንም የታወቀኝ ። ከዛ ተሳልመን ከዛ ወጣን ። እኔ ተመልሼ ወደነሱ ቤት መሄድ አልፈለኩኝም ። ሳሚ ደግሞ አብረን እንድንሄድ አስቦ ነበር ግን ስራ አለኝ ብዬ ግግም አልኩበት ። በስተመጨረሻም ቅዳሜ መጥቼ ጠይቃታለሁ ብዬ ቃል ገብቼ እኔም ወደቤቴ በእግሬ መሄድ ጀመርኩ ሳሚም በመኪናው ተመለሰ ። መንገድ ላይ ሆኜ በርካታ ሀሳቦች ሲመላለሱብኝ ነበር !!!!! ማያን ሳያት ለምን እንደደነገጥኩ ራሴን ጠየኩት   ። አይ ለልዕልና ያወራሁትንና እሷን ስላሰብኩ ስህተት ስለሆነ ነው ብዬ አሰብኩኝና ቀጥ ብዬ መንገዴን ቀጠልኩኝ ። ከሳሚ ጋር ስላወራሁ የሆነ ነገር ቅልል ብሎኛል ። ስለድህነቴ ለልዕልና ነገራት አልነገራት ብዬ አለመጨነቄ ግን ትንሽ አስጨንቆኛል !!! ዙሪያ ጥምጥም አድርጌ በሩቅ መንገድ አርጌ ብቻዬን እያወራሁ ነበር እየሄድኩ የነበርው ። የመጨረሻው የኛ ቤት መታጠፊያ ቀጭኗ መንገድ ጋር ስደርስ ግን ከየት መጣች ሳልላት ከፊት ለፊቴ ማያ ስትመጣ አየዋት ። ሳላስበው ቀጥ ብዬ ቆምኩኝ ። ለምን እንደሆነ አላቅም ሳያት ሰውነቴ መታዘዝ ያቆም ይመስል የማስበውን ማረግ ከብዶኛል ። ቅድም ለምን እንደቆምኩም ሆነ አሁን መራመድ ለምን እንደከበደኝ አላቅም !!! ስታየኝ እሷም መደንገጧ ደግሞ የኔን ሀሳብና ጭንቀት አጋጋለብኝ ። ከሩቅ ስትመጣ ጀምሮ እያየዋት ነበር !!! ያን ያህል ቆንጆ መሆኗን ያየሁት የዛኔ ነበር ቁመት አቋም ቀሚስ ለባሽ ከእርጋታ ጋር አነውባት ። ቀስ በቀስ ረጠገቤ ደረሰች እሷ አውርቻትም ሆነ ቼክ አድርጊያት ስለማላቅ እንደሁሌው አንገቷን ደፍታ እያለፈች ነበር ። ያቺ ቀጭን መንገድ ግን አቀራርባናለች እና እጄ አልታዘዝ ብሎኝ በሰላም እየሄደች የነበረችውን ልጅ ሳላስበው  ቀሚሶቿን ሰብስባ የያዘችበት እጇን ጭምቅ አድርጌ ያስኩት . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣5⃣
302
19
https://t.me/stars_oneklic_bot?start=_tgr_4t0oaJ40NDU0 Join us
288
20
❤️ያልተነገረ ፍቅር ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣3⃣  .......... ጭምድድ አርጎ አቀፋት ። አምልጦኝ እንደተቆጣጣሪ አባት  ማነው ምንሽ ነው ?? ብዬ ልሟገታት ምንም አልቀረኝ ማለት ይቻላል ግን እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ በዝምታ ከበሩ ገለል አልኩኝ ። መን ፈልጋ እንደሆነ አላቅም ዲቦራ ተብዬዋ ተከተለችኝ ። " አንዴ ስልክህን ስጠኝ " አለችኝ ። ደፋር እንኳን ቁጥሬን በዘዴ ልትቀበል ስልክም እንደሌለኝ ማን በነገረልኝ እያልኩ በውስጤ የለኝም ብዬ ንግግሩን በአጭሩ ለመቋጨት ሞከርኩኝ ። " ልደውል እኮ ነው ""አለች ላለማስነቃት ፊቷን አኮሳትራ ። በቅርቡ ሰረቁኝ የለኝም አልኩሽ እኮ አልኳትና ፊቴን ዘፈዘፍኩት ። ትንሽ ደቂቃ በሩ ላይ ቆመው ምን እንዳወሩ ባላቅም ቆየት ብለው ወደኛ መጡ ። ዲቦራንም አቅፎ ሰላም ካላት ቡሀላ " ሄይ ሚኪያስ እባላለሁ " ብሎ የራሴን ሁለተኛ ስም ደግሞ ነገረኝ ። ገና ሳየው አልወደድኩትም ከሱ ጋ ብዙ ላለማውራት እኔም ብዬ ሰላምታውን መልሼ ዝም አልኩኝ ። " ኑ ግቡ "" ብላ ልዕልና ከፊት ቀደመች እሱም ተከትሏት ሶፋው ላይ ተቃቅፈው ልበል ተዛዝለው ብቻ ተሸካክመው ተቀመጡ ። ምንም ያህል የምትወደው ፍቅረኛዋ ቢሆን እኛ ፊት የተጋነነ ሁኔታ ማሳየታቸው የምር አናዶኛል ከልቤ !!! ከዛ ግን ምንም እንዳልመሠለው ለመሆን የማረገው ሳጣ በጥሩ ሰአት ሳሚ ከክፍሉ ሲወጣ አየውት ። ኀለእኔ በጣም አሪፍ ነገር ነው ። ሳየው ከተቀመጥኩበት ብድግ አልኩኝ አመጣጡ ያስፈራል ነገር !!!! እኔ ምንም አይነት ጩኸት ስላልሰማሁ ነገሩ ሁሉ ሰላም መስሎኝ ነበር !!! ፈራሁ በማያገባኝ ገብቼ ነገር ያበላሸው መስሎኝ በጭንቀት ድፍት ልል ስል ቀጥታ መቶ ላዬ ላይ ተጠመጠመብኝ ። ይሄን እቅፍ አላውቀውም !!!!! bcha gn des mil neger alewu !!! ሲያቅፈኝ ተረጋጋሁም ተጨነኩም ግራ ገብቶኝ ነበር !!!! ለደቂቃዎች ካቀፈኝ ቡሀላ ለቀቀኝና በእጆቹ እጄን አጥብቆ ይዞ " የኔ ልጅ አንተ ማለት ከፈጣሪ  የተላክ ስጦታ ነክ ና እንውጣ ላወራክ እፈልጋለሁ ና " ብሎ እጄን እየጎተተ ሊወስደኝ ሲል ያ ሴታሴት " እንዴ ሳም " አለ ። የሚገርመው ያንን ያህል ሰአት ልጁን አላስተዋለውም ነበር ደንገጥ እያለ " እንዴ ናቲ " ብሎ ጨበጠውና  ሰላምታ ከተቀያየሩ ቡሀላ " ና በቃ ልጅ ሚኪ  " ብሎ ወደ ውጪ ገሰገሰ ። እናውራ ሲል ጊቢ ውስጥ መስሎኝ የነበረ ቢሆንም የውጪውን በር ከፍቶ መኪናውን አመጣና ውስጥ እንድገባ ነግሮኝ ይዞኝ ሄደ ። ቤት ውስጥ ምን እንደተፈጠረ አለመስማቴ እየረበሸኝ ነው ። ደግነቱ በጣም ቅርብ ቦታ ነው የሄድነው የሰፈራችን ድምቀት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ነበር የወሰደኝ ። የኔ ከጫጫታ ማምለጫዬ መደገፊያዬ መጠለያዬ የልብ ጓደኛዬ... ብቻእዛ መሄዳችን አስደስቶኛል !!! ሳሚ ተንበርክኮ ያለማቋረጥ ምስጋናን ያቀርባል !!!! ፀሎቱን እስኪጨርስ ሸሸች ብዬ የራሴን ፀሎት አደረስኩኝ ። ከዛም ከረጅም ደቂቃዎች ቡሀላ ወደኔ መቶ ከአጠገቤ ተቀመጠ ። ሰአቱ ቀትር አካባቢ ስለነበር ብዙም ሰው የለም እና ጥጋችንን ይዘን ተቀመጥን ። እስከሚያወራ እየጠበኩት ነበር !! " ታውቃለህ ልጄ አንተን ለምን እንደቀረብኩህ ከዚ በፊት ነግሬካለሁ !!! ታማኝነትህን ስለወደድኩትና ወንድ ልጅ እንዲኖረኝ ብመኝም ስላላገኘው አንተን ሳይህ ስለወደድኩህ ብቻ ነው !!!! በጊዜው ሌላ ሀሳብም አልነበረኝም ግን ታውቃለህ ሳስበው ፈጣሪ ነው ወደኔ የላከህም ሆነ ከኔ ጋ ያገናኘህ !!!!" አለኝ ደስታውጰፊቱ ላይ እየታየ ። ምን እንዳገኘና  ለምን በዚህ ልክ ደስተኛ እንደሆነ የማቀው ነገር ባይኖርም ፈገግ ሲል አብሬው ፈገግ እያልኩ ነበር ። ከዛም ተሳካልን እንዴ ?? አልኩት ምን እንደምል ግራ ገብቶኝ ። " በደንብብብ ከስንት ጊዚያት ቡሀላ እኮ አወራችኝ የሚስቴን ድምፅ ሰማሁት " አለኝ ። ተመስገን አልኩ በልቤ ። ከዛ ወዲያው መለስ አርጎ " ልጄ አንተ ልክ ነበርክ የሚያወራትና አዳማጭ ነበር ያጣችው ።!!! ገና ስታየን እሪ ስለምትል ስለምትጮኽ ስለምታለቅስ እፈራለሁኝ  ለዛ ነበር የማላወራት " አለኝ ። እኔ እንደማስበው መታ ካላየቻችሁና ካላወራቻችሁ በር ከፍታ ካልወጣች ገብታችሁ አታወሯትም አይደል ? አልኩኝ ። ከሳሚ ጋ ስሆን የሚመጣው አሳቢ አስተዋይና ቁም ነገረኛ ልጅ ማን እንደሆነ ባላቅም በንግግር የበሰለ ሰው እያረገኝ ነው ። ሳሚም ለጠቅ አድርጎ " እሷ ብዙ ጊዜ የእንቅልፍ ና ሌሎች መድሀኒቶች ትወስዳለች እና ስንገባ የምትታመም ስለሚመስለን ስለምንፈራ ፈልጋን ካልመጣች ዝም ነው የምንለው " አለኝ ። አየክ አይደል እንጀዛ ስትርቋት ደግሞ እሷዐስለታመመች የተዋችዋትና የጠላቹዋት መስሎ ይሰማታል እና ፈልገሀት ክፍሏን ከፍተህ ስገባ ያለመጠላትና የተፈላጊነት ስሜት ተሰምቷት ነው !! አልኩት ። " በጣም የሚገርም እይታ ነው ጎበዝ ልጅ ነህ " አለኝ ። የምርም ግን በእራሴ ንግግር ራሴ እየኮራሁ ነበር ። ለካ አዳማጭ ካለ ጥሩ ተናጋሪ ይወጣል ማለት ጀመርኩኝ !!! ከአምላኬና ከእናቴ ውጪ የማወራው አንድም ሰው ስለሌለ ማውራት እንደምችል ራሱ ራሴን እንድጠራጠረው ያደርገኛል !!! " ታውቃለህ ገና ስገባ እንደናፈቅት ነገረችኝ ብቸኝነት እንደጎዳትና ራሷን እንድጠላ እንዳደረጋት ነገረችኝ ( እንባውን ከአይኑ እየጠራረገ ) ታውቃለህ እኔ እንደማስበው እኔን ሳይሆን ራሷን ጥፋተኛ ነው የምታደርገው ቤተሰባችሁን ደስታችሁን ወጣትነትህን ስለነጠኳችሁ ይቅርታ አለችኝ እኮ ( ያለቅሳል ) የመጨረሻ ቃሏ ደግሞ እርዳኝ አለችኝ እኮ !!! ከፈጣሪ ቀጥሎ የአንተ እርዳታ ያስፈልገኛል እባክህ "  አለኝ ። እኔ በምን ልረዳህ እችላለሁ ሳሚ ?? አልኩት ግራ ገብቶኝ ። " አሁን እንደረዳከኝ እርዳኝ በቃ ፈጣሪ መርቆ ጥበበኛ ልጅ አርጎሀል እሲ ጥበቡን ይገልጥልሀል ብቻ የቤተሰቤን ጤና እና ደስታ እንድመልስ አግዘኝ " አለኝ በድጋሜ ፊቱ ላይ የሚያንዣብበውን እንባ እየጠረገ ። ወዲያው ማሰብ ጀመርኩኝ ። " ከዛ በፊት ግን ....." ብሎ ዝም አለ ። ግን ምን ሳሚ አልኩት እኔም " ስለ አንተ ሁሉንም ነገር ማወቅ እፈልጋለሁ እውነታውን !!" አለኝ ። ስለኔ አልኩት ደንግጬ እንኳን የሚወራ የሚነገር ታሪክ ሊኖረኝ በህይወት መኖሬም የአምላክ ስራ ነው !!!! እንዲህ ነው የምለው ታሪክ የለኝም ብዬው ቀና ስለ ከፊት ለፊቴ ከደብሩ አንድ አባት ጋር ረጅም ቀሚስ ሻሽና ነጠላ እንደለበሰች ወደኛ መስመር ሲመጡ አየዋቸው ። ሳላስበው ደነገጥኩ ልቤ ላይ የሆነ እንግዳ ስሜት ሲሰማኝ ነበር ። እንደዛ ሆና ሳያት ለካ እንደዚ ቆንጆ ናት እንድል አደረገችኝ ። የሚገርመው የልዕልናና የኔ የፍቅረኛ ማሳየት ውድድር ባይኖር እኮ ጭራሽ ልብ ብዬም አይቻት የማላቀው ልጅ ናት !!! ምን እንዳሏት ባላውቅም በነጠላው አፏን አፈን እያደረገች ስትስቅ አየዋት ። ልቤ ላይ ያለውን አላስፈላጊ የልብ ምትና ያልታወቀ ስሜት ግራ አጋባኝ ድንገት ቀና ስትል አይን ለአይን ግጥምጥም አልን !!! ክው ብዬ ሳላስበው ከተቀመጥኩት ተነሳሁ ???? . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣4⃣
375