uz
Feedback
📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

Kanalga Telegram’da o‘tish

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾 ➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና እንጊሊዘኛ ..... መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ። 📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️ B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር 100K ይደርስ ነበር ። For any comment @Meki3

Ko'proq ko'rsatish
2 254
Obunachilar
+624 soatlar
+227 kunlar
+8530 kunlar
Obunachilarni jalb qilish
Iyul '26
Iyul '26
+112
0 kanalda
Iyun '26
+109
1 kanalda
Get PRO
May '26
+67
0 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+48
0 kanalda
Get PRO
Mart '26
+60
0 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+45
1 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+65
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+92
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+83
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+56
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '25
+50
0 kanalda
Get PRO
Avgust '25
+70
0 kanalda
Get PRO
Iyul '25
+58
0 kanalda
Get PRO
Iyun '25
+66
0 kanalda
Get PRO
May '25
+92
0 kanalda
Get PRO
Aprel '25
+74
0 kanalda
Get PRO
Mart '25
+55
0 kanalda
Get PRO
Fevral '25
+38
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '25
+56
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '24
+68
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '24
+67
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+37
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+46
0 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+65
0 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+81
0 kanalda
Get PRO
Iyun '24
+35
0 kanalda
Get PRO
May '24
+36
1 kanalda
Get PRO
Aprel '24
+42
1 kanalda
Get PRO
Mart '24
+47
2 kanalda
Get PRO
Fevral '24
+46
1 kanalda
Get PRO
Yanvar '24
+32
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '23
+63
1 kanalda
Get PRO
Noyabr '23
+37
1 kanalda
Get PRO
Oktabr '23
+63
2 kanalda
Get PRO
Sentabr '23
+58
0 kanalda
Get PRO
Avgust '23
+77
0 kanalda
Get PRO
Iyul '23
+50
0 kanalda
Get PRO
Iyun '23
+63
0 kanalda
Get PRO
May '23
+46
0 kanalda
Get PRO
Aprel '23
+39
0 kanalda
Get PRO
Mart '23
+41
0 kanalda
Get PRO
Fevral '23
+54
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '23
+192
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '22
+125
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '22
+46
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '22
+57
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '22
+66
0 kanalda
Get PRO
Avgust '22
+64
0 kanalda
Get PRO
Iyul '22
+40
0 kanalda
Get PRO
Iyun '22
+43
0 kanalda
Get PRO
May '22
+64
0 kanalda
Get PRO
Aprel '22
+93
0 kanalda
Get PRO
Mart '22
+71
0 kanalda
Get PRO
Fevral '22
+36
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '22
+47
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '21
+54
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '21
+75
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '21
+135
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '21
+97
0 kanalda
Get PRO
Avgust '21
+132
0 kanalda
Get PRO
Iyul '21
+142
0 kanalda
Get PRO
Iyun '21
+114
0 kanalda
Get PRO
May '21
+71
0 kanalda
Get PRO
Aprel '21
+190
0 kanalda
Get PRO
Mart '21
+122
0 kanalda
Get PRO
Fevral '21
+172
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '21
+180
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '20
+1 524
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
23 Iyul0
22 Iyul+6
21 Iyul+4
20 Iyul+4
19 Iyul+5
18 Iyul+5
17 Iyul+5
16 Iyul+5
15 Iyul+5
14 Iyul+6
13 Iyul+5
12 Iyul+7
11 Iyul+6
10 Iyul+5
09 Iyul+6
08 Iyul+2
07 Iyul+7
06 Iyul+5
05 Iyul+8
04 Iyul+3
03 Iyul+3
02 Iyul+5
01 Iyul+5
Kanal postlari
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣7⃣ ......... በድጋሜ በእናቴ ስልክ ተደወለ ። በሰአቱ ስልክ ማውራት ቀርቶ  ወደ ጎን አርጎ ማንሳትም ከበደኝ ። እጄ መንቀጥቀጡት ያስተዋለው የቤኪ አባት ዞሮ መጥቶ ስልኬን ተቀብሎኝ አንስቶ ላውድ ላይ አደረገው ። " ሄሎ እናትዬ " አለች ። የእናቴን ድምፅ ስሰማው በአንዴ ተረጋጋሁኝና ስልኩን ተቀብዬው እማ ደህና ነሽ ??? አልኳት ። " አዎ አበባዬ ደህና ነኝ እሺ አታስቢ የኔ ቆንጆ " አለችኝ ። እማ ምን ተፈጥሮ ነው ንገሪኝ  እባክሽ ጎዳሽ እንዴ እ ምን አርጎሽ ነው ??? አልኳት መጥፎ ነገር ለመናገር ተዘጋጅቼ ። " አታስቢ የኔ ወርቅ ምንም አላረገኝም ሰክሮ መቶ ትንሽ ተናገረኝ ታቂ የለ በሆነ ባልሆነ እንደሚከፋኝ " አለችኝ ፈገግ ያለ ድምፅ እያሰማችኝ ። በሆዷ ብዙ ቁስልና ህመም የያዘች ይመስል በሆነ ባልሆነው ነው  እንባዋ የሚፈሰው ከዛ ለምን ታለቅሻለሽ ስላት ከት ብላ ትስቃለች !!!????። በዛች ቅፅበት በጣምምምም ብዙዙ ነገር አስቤ ስለነበር በረጅሙ ተንፍሼ እንዳስደነገጠችኝ ነገርኳት ። እሷ ደግሞ ድርቅ ብላ ደህና መሆኗን እንዳምን አድርጋ አወራችኝ !! እኔም በቀላሉ አመንኳትና ነገ እመጣለሁ ብዬ ቃል ገብቼላት ስልኩን ዘጋሁትና መኪናውን ተደግፌ በረጅሙ ተነፈስኩኝ ። ከእኔ ባልተናነሰ ሁኔታ ተጨንቆ የነበረው ሰለሞንም በአንድ እጁ ወገቡን ይዞ በአንድ እጁ  ደግሞ ከረቫቱን እያላላ ተነፈሰ ። ምን ያህል ሊረዳኝ ዝግጁ እንደነበረ በአይኔ ያየሁት ነገር ስለሆነ ከተደገፍኩበት ቀና ብዬ በጣም ነው የማመሰግነው እናም በጣም ይቅርታ አልኩት እጆቼን እያሻሸሁኝ ። "ምንም አይደል ልጄ ነይ ከብርድ ላይ ጊቢ ወደ ውስጥ " ብሎኝ ሊገባ ሲል የቤኪ አባት ብዬ ጠራሁት ። ለምን እንደሆነ አላቅም ሰለሞን ማለትም አንቱ ማለትም ይከብደኛል ። በጣም ወጣት ነዎ እኮ ቤኪን በስንት አመት እንደወለደውም አላውቅም ። እሱም ወደኔ ዞር ብሎ ምነው በሚል ፊት አየኝ ። ትንሽ ፈጣጣ ሆንኩኝ መሠለኝ ፈገግ ብዬ አንዴ እንደ አባት ልቀፍህ ?? ብዬ በአሳዛኝ ፊት አየሁት ። በነገራችን ላይ እንዲህ ያልኩት ያለ ምክንያት አይደለም !!! ከደቂቃዎች በፊት ልጄ ብሎ ጠርቶኝ ነበረ ። በምላሹ እሱም ፈገግ አለና  እጁን ዘረጋልኝ እኔም ቶሎ ብዬ በዛ ግርማ ሞገስ ባጀበው እቅፍ ውስጥ ገባሁኝ !!! የምር በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ !!!! በትክክለኛ አባቴ እንደታቀፍኩኝ ነው የተሰማኝ ሁላ  !!!!! ምናለ እኔም እንደሱ አይነት አባት በኖረኝ ብዬ እንድመኝ አደረገኝ !!!!!!! ከዛ እንባዬ መምጣት ሲጀምር አንዴ ከጀመረኝ ማቆሚያ የሌለኝ መሆኔን ስለማውቅ ቶሎ ከእቅፉ ወጥቼ በጣም አመሰግናለሁ ብዬ አሳጠርኩት ። " ነይ ወደ ውስጥ ግቢ " ብሎኝ እኔን አስቀድሞ ተከትሎኝ መጣ ። ከዛ ተመልሰን ቦታችን ጋር ተቀመጥን ። ወዲያው አስተናጋጁ መጣና እሱን አየው ። በአይኑ የአወንታ ምልክት እየሰጠ አንገቱን ሲነቀንቀው ወደኔ ዞር ብሎ " ምን ይምጣልሽ እመቤት " አለኝ በትህትና ጎንበስ ብሎ ። ምን እንደሚባል የማላቀው እኔ ዞር ብዬ ሰለሞንን አየሁት ። በአንድ እይታ ሰውን መረዳት የሚችል ሰው ነው !!!! ጎንበስ ብሎ ወደ ሜኑ አየና የሆነ የሆነ ነገር ብሎት አስተናጋጁ ሄደ ። ሰውዬው እስኪመለስ ልብ አንጠልጣይ ታሪኩን ለመስማት ጉጉት አደረብኝና አላስችል ቢለኝ ለወሬ ማስጀመሪያ እና ቤኪ ምኑን አሞት ነው ? ብዬ ወደ ወሬው መለስኩት ። ለትንሽ ደቂቃዎች በዝምታ ተውጦ አሰበ አሰበና ጥልቅ ሀዘን ውስጥ ገባ ። እኔ አይን አይኑን እያየሁኝ ምላሽ እየጠበኩ እንደሆነ አሳየሁት ። ያየኛል አየዋለሁ ያየኛል አየዋለሁ ።።!!! ከደቂቃዎች መፋጠጥ ቡሀላ  ግን ሰለሞን ጉሮሮውን እንደመጠራረግ አለና " ልጄ በጣም ታሞብኝ ነበር በጣም " አለኝ ። ምኑን ታሞ ነው ይሄን ያህል እ ምን ሆኖ ነበር ?? አልኩኝ ይበልጥ ለማወቅ እየጓጓሁ ። " እስኪ ከዛ በፊት አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ እውነታውን ትነግሪኛለሽ  ?" አለኝ ። እሺ ደስ ይለኛል ምንድነው አልኩት መልሼ " አያድርገውና ልጄ በረከት አይኖቹ ማየት ቢያቆሙ ምን ታደርጊያለሽ ??3" የሚል እጅግ ግራ የሚያጋባ ጥያቄ ጠየቀኝ ???......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣8⃣

2
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣6⃣ .............. ቦታውን አላቀውም የት እንዳለን እዚህ ምን እንደምናደርግ እንኳን አላውቅም የቤኪ አባት ስለሆነ ብቻ ተከትዬዋለሁ ። የመኪናውን በር እንደከፈተ " ውረጂ !" ብሎ ዝም ብሎ ተመለከተኝ ። እዛ ድረስ ተከትዬው መጥቼ አልወርድም ብል ጥቅም አልባ ንግግር ነው ብዬ ስላመንኩ ቀጥ ብዬ ወርጄ ከመኪናው ጋር ተለጥፌ ቆምኩኝ ። የት እንዳለን አላውቅም ??? ከፊት ለፊቴ ሆቴል እንዳለ ብቻ ይታየኛል !!! ግን ጭር ያለ እና በዝምታ የተዋጠ ቤት ነው ። የመኪናውን በር ዘጋውና መሄድ ጀመረ ። እኔ እዛው ቆሜ ቀረሁኝ ። " ነይ ጊቢ " አለኝ ዞሮ ግን እዚህ ምን እናደርጋለን ? አልኩት እንደምንም ተዳፍሬ ። " ምን እንዳላደርግሽ ፈርተሽ ነው እኔ ሰለሞን እኮ ነኝ አፈየበለጠ አታናጂኝ ክብር እየሰጠውሽ ነው  የሌለኝን ትዕግስት አታስጨርሺኝ "አለኝ ጭምድድ ባለ ፊት ። በፈጣሪ ስም ቀይ ስለሆነ ትንሽ በተናደደ ቁጥር ፊቱ እንደ ቲማቲም ይቀላና ግንባሩ ይጨማደዳል !!!! ብቻ በጣም ነው የሚያስፈራው ምነው ባልተናገርኩ እንድል አደረገኝ !!!! ተጨማሪ ቃላትን ሳላባክን ተከትዬው ወደ ውስጥ ገባሁ ። የሚገርማችሁ ሌሎች ቦታ ካየሁት በላይ የሆነ ክብርን  ገና ከበር ማየት ጀመርኩኝ ። ገና ከበሩ ሞቅ ያለ ሰላምታ ጎንበስ ቀና የበዛበት መስተንግዶ ....... ብቻ ብዙ ነገር ። ...!!!!!! የዛኔ የምር አልቻልኩም !!! ሀብታሞች እንዲህ ነው የሚኖሩት ?? እንድል አደረገኝ ። በዛውም ደግሞ ከባለ ስልጣን ልጅ ጋ ማን ፍቅር ውስጥ ጊቢ አለሽ !!! እያልኩ ራሴን ወቀስኩኝ ። ወዲያው ደግሞ መልሼ በዚህ ልክ የሀብታም ልጅ ሆኖ እኛ ትምህርት ቤት ማን ግባ አለው ??? እያልኩኝ ጥፋቱን ወደ ቤኪ አዞረዋለሁ ። ጨዋታው ቀጠለ ለብቻችን ተቀመጥን ። አስተናጋጁን ቀና ብሎ አይቶት አንድ እጁን ከፍ አድርጎ መዳፎቹን ዘርግቶ አጠፋቸው ። ወዲያው አስተናጋጁ ጎንበስ ብሎ ተመልሶ ሄደ ። ሁሉም ነገር ለበጎ ነው ይባላል ምን አልባት ይሄን ህይወት ሊያሳየኝ ነው እንዴ ??!!ብዬ በሆዴ እያወራሁ ብቻዬን እስቃለሁ !!!! " እሺ እንቀጥል "አለኝ እ ምኑን ማለቴ እሺ አልኩኝ ከገባሁበት የልጅ ቀልድ ለመውጣት እየታገልኩኝ። " አውቃለሁ አንተዋወቅም ቁጭ ብሎ ለማውራትም ገና ነን ግን ስለ ቤኪ በደንብ እንድታቂልኝ እፈልጋለሁ !!! እኔ ክፉ ሆኜ አይደለም ግን ልጄን ይነጥቁኛል ብዬ እፈራለሁኝ   አንቺ ስለሱ ምን አታቂም  አምሮ ተውቦ ልዑል ሆኖ የምታይውን በረከትን ነው የምታውቂው ተሳሳትኩ ??" አለኝ ከላይ የለበሰውን ኮት አውልቆ ወንበሩ ላይ እያስቀመጠ ። ቃል ማውጣት አቃተኝ መሠለኝ በአወንታ ብቻ አንገቴን እየነቀነኩኝ  ። " እሺ ለማንኛውም እዚ ያመጣሁሽ እንድናወራ ስለፈለኩ ብቻ ነው ። አሁን ላይ አንቺ ፍቅር ውስጥ የከተሽው በረከት  ማለት እኔና ባለቤቴ ብዙ ያየንበት ብዙ ያጣንበት ብዙ ያገኘንበት ልጃችን ነው ። ከእኔ ጋ ብዙ ባንገናኝም አለምዬ ብዙ ነገር እንደምታቂ ነግራኛለች ። እና አሁን ያሉት ማንኛውም ነገር ድሮ ላይ አልነበረም ። እኔና እናቴ ( አለምዬን ማለቱ ነው  ) ከቤት ስንጠፋ  አንድ ነገር አልነበረንም !!. ገና ልጅ እያለን ነው በፍቅር የወደቅነው ። ቤተሰቦቻችን በከባዱ ሲያስፈራሩን ሁሉንም ለመቻል ወስነን ከቤት ጠፋን ። ሁለታችንም በየሆነ ቦታ ተበታትነን ስራ ለምስራት ሞከርን ። እናቴ አሁን እንደምታያት አልነበረችም ተሞላቃ ያደገች የሀብታም ልጅ ትመስላለች እንጂ በብዙ የተፈተነች ሴት ናት ። በሰአቱ እኔ ስራ ሳጣ እሷ እየሰራች በምታመጣው ብር ለመጀመሪያ ጊዜ በት ቸከራይተን ኬሻ አንጥፈን ለመተኛት እንድበቃ አደረገችኝ ። በሰአቱ በትምህርቴ በጣም ጎበዞ ተማሪ ነበርኩኝ ። የመማር እድሉን ሳላገኝ ቀርቼ ነበር ። ነገር ግን ሰው ቤት እየሰራች ትምህርቴን እንድጨርስ አደረገችኝ ። በጣም በትልቅ ነጥብ አለፍኩኝ ። ብታምኚም ባታምኚም ዩንቨርስቲ ገብቼ ትምህርት ጨርሼ እስክወጣ ድረስ በፅናት ብር እያጠራቀመች ጠበቀችኝ ። ያ ነገር ለኔ ብርታት ሆነኝ ። በተማርኩበት ስራ እስካገኝ ድረስ ጎን ለጎን መስራት ጀመርኩ ። አንድ ላይ ሆነን እየኖርን ልጅ መውለድ ተስኖን ነበር ። እኔ ደግሞ በጣም ወንድ ልጅ እመኝ ስለነበር ቅዱስ ሚካኤል ደጅ ሄጄ ወንድ ልጅ እንዲሰጠኝና ካሳካልኝ ብዬ መሳል የሌለብኝን ስለት ተሳልኩኝ ። ፈጣሪ ይመስገን  በዛው ወር አረገዘችና በመጀመሪያ ወንድ ልጅ ሰጠኝ ። የሱ መወለድ ያቺ ጠባብ ቤታችንን ስለሞላልን በረከት ብዬ ስም አወጣሁለት ። ከተወለድ አራት አመቱ አካባቢ ማታ በሰላም ተቃቅፈን ተኝተን ለሊት ላይ ድንገት ትንፋሹ ተቆራረጠች " ሁኔታው ትዝ ብሎት መሰለኝ እንባው መውረድ ጀመረ ። ለምን እንደሆነ አላውቅም ወንድ ልጅ  ሲያለቅስ ማየት በጣም ከባድ ነው !!! አባት የለኝ ይሆናል ግን አባትነትን በደንብ አነውበት !!!!! ልክ እንደ ከዚ ቀደሙ  ምን አለ አባት ቢኖረኝና የአባትነት ፍቅርን ባየው ብዬ ተመኘው !!!!!( ለካ አባት አለኝ 🧐🧐)...... አንዱ አባት ልጁን ይክዳል አንዱ ለልጁ እንባውን ያፈሳል ....... ህየወት ተቃራኒ ናት !!!! ምን ማለት እንዳለብኝም ሳላውቀው  አፌ ላይ የመጣልኝን ዋናው አሁን ላይ ከጎንክ ነው ለምን ታለቅሳለክ ብዬ ታሪኩን እንዲቀጥልልኝ ሰፍ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ ። ለመረጋጋት አየር እየሳበ እያለ እናቴ ደግማ ደወለች ። አሁንም ከጎን ነክቼ ዝም ልለው ስል የእናቴ መሆኑን አየና " አንሺው አንሺው እኔም ለመቀጠል ልዘጋጅ"  አለኝ ፈገግ ብሎ ። ውጩ እንደሆንኩ ካወቀች ጥያቄ ታበዛለች ብዬ ለመዋሸት ድምፄን ቀንሼ ሄሎ እማ ስላት ዝም አለችኝ ። ሄሎ ሄሎ እማ ስል የሚያለቅስ ድምፅ ሰማሁኝ ። ከደቂቃዎች በፊት ድምፄን መቀነሴን ረስቼው በድንጋጤ ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ እማ ሄሎ ሄሎ አልኩኝ በጩኸች ። ምንነቱንም ያላወቀው የቤኪ አባት ከኔ እኩል ከተቀመጠበት ተነስቶ ያየኛል ። " ሀ ሀ ሀ ሀ ...." የሚስቅ የወንድ  ድሞፅ ። የአባቴ ድምፅ ነበር እናቴ እያለቀሰች እሱ እየሳቀ ?????? ነገሮችን አሰብኩና እየሮጥኩ ከሆቴሉ ወጣሁ ። እሱ ደግሞ " ምንድነው ምን ተፈጠረ " እያለ ይከተለኛል ። እናቴ እናቴ ችግር ውስጥ ናት አልኩ እየተርበተበትኩኝ ። " እሺ መኪና ውስጥ ጊቤ እንሄዳለን ፍጠኚ " ብሎኝ ወደ መኪናው ስንገባ ድጋሜ በእናቴ ስልክ ተደወለ ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣7⃣
113
3
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣5⃣ ........ልጄን የወጋውና የስለት ልጄን ደም ያፈሰሰው ያንቺ አፍቃሪ ነው !!! የዛ ቀን ምሽት በዛ በምሽት ምን እንዳወራችሁ አላውቅም ልጄን እንዲጎዳ አደረግሽብኝ ለዛ ነው አሁን ገባሽ " አለኝ ። ኢዩኤል እንዲህ ያደርጋል ብዬ አልገምትም አላስብምም ነበረ !!! ቀና ብዬ ጄሪን ተመለከትኳት ከኔ በላይ ደንግጣለች እጆቿን አፏ ላይ ደራርባ በጥፋተኝነት ስሜት ተውጣ ፈዛ እያየችኝ ነበረ ። እውነት ለመናገር በሷ አልተናደድኩም ምክንያቱም  እሷ ምንም አታቅም በዛ እርግጠኛ ነኝ ። በሰአቱ ልመልስ የምችለው ነገር ስለሌለ በዝምታና በጥፋተኝነት ስሜት ሁሉንም አየዋቸው ። የውስጤን የተረዳችኝ አለምዬም አንዴ እኔን አንዴ ባለቤቷን ለማረጋጋት እየሞከረች ነው !! እኛ እዛ ቆመን ስንጨቃጨቅ ቤኪ በዝምታ ሲያዳምጥ ቆየና " አባ ራሴ ነኝ ነገር የፈለኩት ምንም ነገር ቢፈጠር እሷ ጥፋተኛ አይደለችም እሷን አትናገርብኝ " እያለው ነበር ። በሰአቱ ምን ያህል እንደሚወደኝና እንደሚያስብልኝ ለማወቅ ቀላል ነበር !!!!! መጥፎ ሁኔታ ውስጥ  ከትቼው ራሱ በዛ ሁኔታ ላይ ሆኖ ስለኔ እያሰበ ማየት ለኔ እንደ ጥንካሬ ነው !!!! እልና... ነገር ግን የቤኪን አባት ሁኔታ ሳይ የጥፋተኝነት ስሜቴ ያገረሽብኝና ሽምቅቅ እላለሁ!!!!! ቆመን እየተፋጠጥን እያለ ዶክተሩ ከነርሷ ጋር መጣ ። " መድሀኒት ሊወስድ ነው እና ትንሽ ረፍት ማድረግ አለበት ብቻውን ተውት ትንሽ ደቂቃ " አለ ። የሚገርማችሁ ዶክተሩ የቤኪን አባት ሲያወራ ያለው ክብርና እርጋታ በጣም የሚገርም ነው !!!!!!! ለነገሩ እንዴት አያከብረው ........ ለማንኛውም ግን ተያይዘን ከዛ ክፍል ወጣን በሩ እስኪዘጋ ድረስ ቤኪ የሆነ አስተያየት እያየኝ ነበር !!!! እንደወጣን ጄሪ ፊቴን እስካዞር ጠብቃ " አቡ በጣም ይቅርታ እሺ ለዚ ሁላ ጣጣ እኔ ነኝ ጥፋተኛ " አለችኝ ። እሷን ቀለል እንዲላት ብዬ በሰአቱ የሌለኝን ፈገግታ እያሳየዋት አንቺ ምን አደረግሽ ያምሻል እንዴ ቀውስ ደሞ ለበጎ ይሆናል  ብዬ ፈገግ አስባልኳት ። ወዲያው አለምዬ ወደኔ መታ አቀፈችኝና " እንዳትከፊ እሺ ብዙ የተፈተንበት ልጃችን ስለሆነ የሱ ደካማ ጎን ስለተነካበት ፈርቶ ነው እሺ " አለችኝ ። የዛኔ ከልቤ ስለ ቤኪ የማወቅ ጉጉቴ ጨመረ ። እስከዛሬ ስላለፈ ህይወቱ ስለቤተሰቡ ስለ ሀብታቸው ...... ስለምንም ነገር አስቤም ሆነ ጠይቄው  አላውቅም !!!!! አባቱንም ከልቤ ተረዳሁት !!!! አለምዬ ወደ ባለቤቷ ተመልሳ ከሱ ጋር ማውራት ጀመረች ። የዛኔ ያቤፅና ጄሪ መተው በየተራ እንደ እህትና ወንድም አቅፈው አባበሉኝ ። " ሰሌ በልጁ ቀልድ አያቅም !! በርግጠኝነት የምነግረሽ ነገር ቢኖር ቤኪ ምን ያህል እንደሚወድሽ ስለሚያውቅ ነው እንጂ ሌላ ሰው ቢሆን የነካው አንድ ደቂቃም አይገኝም !!!!! ኢዩኤል ደግሞ ከጊቢም ለቆ ጠፍቷል የት እንዳለ ማወቅ ስላልቻለ ነው ዝም ያለው " አለኝ ያቤፅ ቀስ ብሎ ። እስካሁን ካየዋቸውና በንግግሮች እንደተረዳሁት  ከሆነ ቤኪ በሆነ ችግር ላይ ያለፈ ሰው እንደሆነ ግልፅ ነው !!!! ለቤቱ ምን ያህል አስፈላጊና ውድ ልጅ እንደሆነ ገባኝ !!! ብዙም ሳይቆይ ከአለምዬ ጋር ምን እንዳወሩ ባላቅም የቤኪ አባት ወደኔ መጣ ። ገና አጠገቤ እንደደረሰ ሌላ ነገር ከማውራቱ በፊት ብዬ ምንም ነገር አላወኩም ነበር በጣም ይቅርታ አልኩኝ አይኔን መሬት ላይ ተክዬ ። ለትንሽ ደቂቃ በዝምታ ተመለከተኝና " ነይ ተከተይኝ " አለኝ ። ቀጣይ ምን እንደሚፈጠር ያላወኩት እኔ በድንጋጤ ቀና ብዬ በየተራ ተመለከትኳቸው ። የአለምዬን ፊት ሳየው ፍፁም የተረጋጋ ፊት ስለነበረ ትንሽ ተረጋጋሁ ። በሰአቱ ሌላ አማራጭ የለኝምና እሺ ብዬ መንገድ ስጀምር ጄሪም አብራኝ ለመምጣት ስትሞክር " አይ አይሆንም ሁለታችን የምንጨርሰው ነገር ነው " አላት " ግን እኮ ...." ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ያቤፅ ጎተት አድርጎ ወደ ራሱ ሳባትና ቀስ ብሎ አትጨነቂ አላት ። ከዛ ትልቅ ሆስፒታል ስንወጣ በእርግጠኝነት ከአራት ሰአት በላይ ሆኗል ። አለምዬ ለክፉ አትጥለኝም ብዬ እንጂ ማንን አምኜ በዛን ሰአት ከተናደደ ሰው ጋ እወጣለሁ !! ገና በሩን ጨርሰን ዞር እንዳልን ሹፌሩ እየሮጠ መቶ በሩን ሲከፍት የቤኪ አባት እጁን ዘረጋ ። የሚገርመው ሰውዬው ፈጥኖ በእጁ የያዘውን የመኪና ቁልፍ አውጥቶ ሰጠው ። ምን አይነት መግባባት እንደሆነ አላቅም ???? እጁን ሲዘረጋ ምንድነው ብዬ በግርምት እያየሁ እያለ እነሱ ተግባብተዋል !!! ከዛ እሱ መኪናውን ውስጥ እንድገባ አርጎኝ ወዴት  እንደሆነ ባላቅም መሄድ ጀመረ። እናቴ ጉዷን አልሰማች በዛ ሰአት ትደውላለች ። እኔ በዛ   ማንሳት ችግር ነው ብዬ ዝም አልኩኝ ከደቂቃዎች ጉዞ ቡሀላ ደረሰን ወረደና በሩን ከፍቶ ውረጂ አለኝ ። ቦታውን አላቀውም ...... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣6⃣
225
4
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣4⃣  ............ በረከት እየደከመ ነው አሉኝ ። በፈጣሪ ስም እንዴት እንደደነገጥኩ እኔ ነኝ የማቀው !!! ስልኩን ከአባቱ የበለጠ ወርውሬ የት እንደምሄድም ሳላውቅ በዛ ምሽት ዝም ብዬ ወጣሁኝ ። " ቆይ ተረጋጊ ተረጋጊ " ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረኝ ። የሀብታም ቅንጡ ስልኩን እየነካካ ከቢሮ ወተን እሱን እየተከተልኩ ስሄድ ጭራሽ ሹፌር ሳይቀር አለው ። በሰአቱ እንደዚ አይነት  ነገር አላስብም ነበር እንጂ ይሄ ቅብጠት ነው እል ነበር !!!! ብቻ ግን ሰሎሞን ቤኪን ምን ያህል እንደሚወደው እንደሚያሶብለትና እንደሚጨነቅለት ያወኩት የዛን ቀን ነው !!!!! ወንድ ልጅ በአደባባይ አያለቅስም የሚል ተራ ተረት ይዞት እንጂ እንባው አቅሮታል። እኔ ሴት በሁሉም ቦታ ማልቀስ ህብረተሰቡ ፈቅዶላታልና እንባዬን መቆጣጠርም አልቻልኩኝም !!!!! በሰአቱ የሰውዬው ንግግር ደከመ የሚለው ቃል ያጣሁት ያህል እንዲሰማኝ ነው ያደረገኝ !!!! " አፍጥነው ንዳው ፍጠን "" እያለ በተደጋጋሚ ይጮክበታል ሹፌሩ በሚያስፈራ ፍጥነት እየበረረ ነው ማለት ይቻላል !!! በሰአቱ ራሴን ላረጋጋ እሱን ላረጋጋ ግራ ገባኝ ። ለሰው ቅድሚያ መስጠት የህይወት መርሄ ስለነበረ  እንደምንም ራሴን አሳምኜና አረጋግቼ ቤኪ ለሚወዳቸው ሰዎች ሲል ይጠነክራል ምንም አይሆንም ብዬ ለማረጋጋት ስሞክር አመድ የለበሰውን ፍም ነካክቼ ቀሰቀስኩት " አንቺ እንደምታስቢውና በፊልም እንደምታይው ቀላል አይደለም የተወጉ ሰዎች ሁላ ይድናሉ ማለት አይደለም ገሀድ አለም ላይ እንዳለሽ አትርሺ !!!! ልጄ የሆነ ነገር ከሆነ ግን እመኛኝ በከባዱ ነው የምጎዳሽ !!!!"  አለኝ በሚያስፈራና በተናደደ ፊት !!! የተናገረው ንግግር ልክ እንደሆነ ገብቶኛል !!! ነገር ግን  ቤኪ የተጎዳው በኔ ምክንያት አይደለም እኮ ለምን እኔ ላይ ይሄን ያህል ተናደደ የሚለው ጭንቀት ሆኖብኛል !!!! ስንደርስ ግን ባለፉት ቀናቶች የነበረበት ቦታ ሳይሆን ትክክለኛ ሆስፒታል ነው የገባው ??? በቃ በጣም ታሞ ነው ብዬ በስንት ስቃይ የመለስኩትን እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩኝም !!!! የቤኪ አባት ሲሄድ በዝምታ እሱን እየተከተልኩ ገባሁኝ ። እንዴት እንዳወቀ ባላቅም ቀጥታ  ቤኪ ያለበት ክፍል ውስጥ ሄድን ። እጁ ላይ የተለያዩ ነገሮች ተሰካክተው አፉ ላይ መተንፈሻ ተደርጎ ምናምን ....በህይወቴ ላየው በማልፈልገው ሁኔታ ውስጥ  ሆኖ ተኝቶ አየሁት ። እሱን እያየሁ እንዳላጣው እየፈራሁ አለቅሳለሁ በዛው ሰአት እናቴ ደጋግማ ትደውላለች ???? በመሀል ላብድ ምንም አልቀረኝም ማለት ይቻላል !!!!!!!   የቤኪ አባትም በጣም ፈርቶ ምን እንደሚያደርግ ራሱ ግራ ገብቶት ሲንቆራጠጥ ቆይቶ ዶክተሩ ሲመጣ " ተናገር " አለ ቀጥታ ። " አሁን ደህና ነው ደም በብዛት እየፈሰሰው ስለነበር ለእርሶ መደወል ነበረብን እና በፍጥነት ደም የሚሰጠው ሰው ያስፈልጋል " ብሎ ሀሳቡን ሳይጨርስ እኔ እሰጣለሁ ከዚ በፊት አበረን ተመርምረናል የደም አይነታችን አንድ አይነት  የደም አይነት ነው ያለን እና በሽታም የለብኝም ምንም እ ቶሎ ስጠውና አድነው !!! አልኩት በአንዴ እጄን ሰብስቤ ደም  ለመስጠት  እየተዘጋጀሁ ። ዶክተሩ አንቱ እያለ እኔ አንተ ብዬ ጭራሽ በቁጣ ማውራቴ ትዝ ሲለኝ መቀራረባችን ይሆናል ብዬ ለራሴ ነግሬው ዝም አልኩኝ ። ወደ ውስጥ ገብቼ  ድጋሜ ቀለል ያለ ምርመራ አደረጉልኝና ደም ሰጥቼ እኔም እዛው ተኛሁ ። መዳፎቼኖ እጥፍ ዝርግት እያደረኩ እንደነበር አስታውሳለሁ ከዛ ግን ስነቃ ከቤኪ አጠገብ የተመቻቸ አልጋ ላይ ተኝቼ ሰለሞን አለምዬ ጄሪ ያቤፅ ቤኪና ዶክተሩ ጭምር ፍጥጥ ብለው እያዩኝ ነበር !??? ሁኔታው የመሠለኝ ሞቼ የተነሳሁ ያህል ነው የሆነብኝ !!!!! ተደናግጬ ሁሉንም በአይኔ እየማተርኩ ሳያቸው ቤኪ እዛው እንደተኛ በአሳዛኝ ፊት እያየኝ " ለምን እንደዛ አደረግሽ ለኔ መድሀኒቴ ነሽ ዝም ብለሽ አጠገቤ ብትቀመጪ እድን ነበረ እኮ " አለኝ ። " ብዙ ሰአት ስትቆይብን እኮ ፈራን አቡ " አለችኝ ጄሪ እጆቼን ደግፋ ይዛ ። የቤኪ አባት ትኩር ብሎ ተመለከተኝና " በአንቺ ምክንያት ያፈሰሰውን ደም መልሰሻል ጥሩ ነው ቢያንስ አሁን ንዴቴ አንቺ ላይ አይደለም " አለኝ ። የኔ ተቆርቋሪ ጓደኛ ጄሪ ቀደም ብላ " አብላካት ምን አደረገች እሷ እንዴት ለቤኪ መጎዳት መንስኤ ትሆናለች ?? " አለች ። በጣም ንዴት ላይ ነበር " ምክንያቱም  በሷ ምክንያት ነው ልጄን የጎዱብኝ " አለ በቁጣ ። " እኮ እንዴት እሷ ምን አደረገች ???" አለችው መለስ አርጋ "" ምክንያቱም ልጄን የወጋው ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣5⃣
361
5
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣3⃣ ....... እያየኝ ነበር ። ነገሮች የበለጠ እያናደዱኝ ነው !!! እስከማቀው ወንድ የሴት ዶርም መግባት ሳይሆን መቅረብ አይችልም !!! አልኩኝ በፌዜ አፌን አጣምሜ ። አንዳንዴ መቀራረብ ያናንቅ የለ !!! ለትንሽ ጊዜ ብንቀራረብ ይኸው አፍ ለአፍ መካፈት ጀመርኩ ። እንደ አለቃ እንደ ጊቢው አስተዳደርነት ከማክበር ይልቅ ሰው ፊት በንቀት ስላናገርኩት ክብሩን እንደወሰድኩ አሰበ መሠለኝ ቀይ ፊቱና ጆሮው ለብቻ ቲማቲም መሠሉ ። "" ወደ ቢሮ ሂጂ ነይ ውጪ ፍጠኚ !!" አለ በጣም በተቆጣ ድምፅ !! ከዛ በላይ እልህ ውስጥ መግባት ጥሩ መስሎ አልታየኝም ለሱ ብዬ ሳይሆን ለእራሴ ብዬ ተነስቼ ጃኬት ደረብኩኝና አልፌው ወጥቼ ወደ ቢሮ ሄድኩኝ ። ብዙም ሳይቆይ ተከትሎኝ መጣ እና በሩን ከውስጥ ቆለፈው ። የዛኔ የምር ፈራሁኝ !!! ለምን አፈቀርክ ብሎ ልጁን ትምህርት አቋርጦ ውጪ እስከመላክ የሚያደርስ ጭካኔ ያለው ኮስታራ ሰውዬ እና እኔ የእናቷ ብቸኛ ልጅ አንድ ክፍል ውስጥ ተቆልፎብናል ማለት ለኔ ከባድ ነገር ነው ። ላዬ ላይ ተከምሮ የነበረው ኮፍጣናነት ወኔና ደፋርነት በአንዴ ከኔ ራቁ !!!! ስሜቶች እንደዚ ናቸው!!!!! ማንኛውም ስሜት ቅፅበታዊ ነው !!!!! በስሜት መመራት በጣም መጥፎ ነገር ነው ለዛም ነው ስትናደድ አትናገር የሚባለው !!! ውጪ ላይ እያለው ገንፍለው የወጡ ብዙ ቃላትን ያስባከኑኝ እነዛ ሁላ ስሜቶች አሁን ላይ የሉም ከኔ ርቀዋል !!!!! " ተቀመጪ " ሲለኝ እንደ ከዚ ቀደሙ አላንገራገርኩኝም ቁጭ አልኩኝ !!! እጄን እያፋተኩኝ ጠረንጴዛው ላይ አይኔን ተክዬ ቀረሁ ። "  የገዛ ልጄን ራሱ እንደዚ ታግሼ አላቅም !!!!! ማንም ሰው እንዲህ በንቀት ተናግሮኝም አያውቅም !!! ነገር ግን ልጄ ላንቺ ያለውን ፍቅር ስላየሁ ነውዐየሌለኝን ማንነት እየታገስኩሽ ያለሁት ሰከን በይ!!" አለኝ ረጋና ቀስ ባለ ንግግር !!!! መረጋጋቱ ረበሸኝ !!! ቀስ ብሎ ሲያወራኝ ይበልጥ አስፈራኝ !!!! ምንም ማለት አልቻልኩኝም በዝምታ ቆየሁ ። " ሀሳብ ካልሰጠሽበት ነገሮችን በእራሴ መንገድ መረዳት ይኖርብኛል ማለት ነው  "  አለ ። የዛኔ በረጅሙ ተነፈስኩኝና ለማውራት ራሴን አነቃቃሁኝ !! እናንተም እንደኛ ሰው ናችሁ ። !!!! አዎ ምን አልባት ብዙ ነገሮች አንገናኝ አንቀራረብም ጭምር ይሆናል ግን እንደተረዳሁት ከእናንተ ይልቅ እኛ ጋር ጥሩና እውነተኛ ፍቅር አለ !!! በረከትንም በገንዘብ እየመረዝከው ነው !!! በእርግጠኝነት ከዚ ቡሀላ ሰው ሲቀርበው የሀብታም ልጅ ስለሆነና ገንዘብ ስላለው እንደሆነ ማሰቡ አይቀርም በእርግጠኝነት !!!! እኔ የተዋወኩት አንድ ትምህርት ቤት እየተማርን ነው ስለሱ የማቀው አንድም ነገር የለም ማለቴ አልነበረም እኔ የሀብታም ልጅ መሆኑን ሳላውቅ እሱ የደሀ ልጅ መሆኔን እያወቀ ነው ፍቅር ውስጥ የገባነው !!! እኔ እሱን ሳስብ አንድም ቀን አብሮ ሀብት ትዝ ብሎኝ አያውቅም ተምሬ የመቀጠር እና ሰርቼ የማግኘት ፍላጎት እንጂ ቁጭ ብዬ በሰው ገንዘብ የመቀለብ ፍላጎትም የለኝም !!!! አንተ እንደ አለምዬ አደለክም !!!እሷ ምርጥ ናት በገንዘብ አትመራም አትመካምም!!! አልኩት። " እባክሽ መሥመር አትሳቺ እኔ እንደዛ ለማለት ፈልጌ አንደለም በማታቂው ነገር በርግጠኝነት አታውሪ !!!!. በረከት ለኔ ብዙ ነገር ነው !!!! ለኔም ለአለምም ትልቅ ነገር ነው ! የልጅነት ልጃችን ነው በብዙ የተፈተንበት ነው !!!! እኛም ም ከእናንተ በላይ በድህነትና በችግር ውስጥ ሆነን ነው የተዋደድነው !!! ቢያንስ እናንተ ቤት አላችሁ እኛ እንኳን ቤት ይቅርና ከዝናብ የምንጠለልበት ሸራ እንኳን አልነበረንም !!!!! እንደመሸ አውቃለሁ !! ልታዳምጪኝ ከፈለግሽ ሁሉንም ነገር ልነግርሽ ዝግጁ ነኝ እንደምታስቢው አይደለም እዚ የደረስነው ....." እያለ እያስረዳኝ እያለ ስልኩ ጠራ ። አየውና ኮስተር ብሎ አነሳው !! " ምን ለምን ???" ብሎ ስልኩን ጠረንጴዛ ላይ አስቀመጠው ። ምንድነው ምን ተፈጠረ ምንድነው ....... እያልኩ ብጠይቅም የሚመልስለኝ አልነበረም !!!!!! ቶሎ ስልኩን አንስቼ ምንድነው ?? አልኩኝ ። " ቶሎ መምጣት ይኖርባችዃል በረከት እየደከመ ነው " አሉኝ ????? . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣4⃣
428
6
20 like or emoji I will send at next part 43 🫠
416
7
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣2⃣ ...........ተመልሼ ስገባ ተከትሎኝ መጣ ። " አስቢበት የምትፈልጊውን ያህል ነው ለቁጥሩ አልጨነቅም " አለኝ ። በሰአቱ በጣም ብከፋና ባዝንም ግን ለቤኪ ብዬ ታግሼ ዝም አልኩኝ !!! ፊቴን ከስክሼ ክፉ ቃል ላለማውጣት ጥርሴን ነክሼ ቦርሳዬን ለማንሳት ስዞር ጄሪ ኮራ ብላ ቆማለች ። ቤኪና ያቤፅ የታፈነ ሳቅ የያዙ በሚመስል ፊት ያዩኛል???? የተፈጠረውን አላወቁ ብዬ ንዴቴን ተቆጣጥሬ እግዚአብሔር ይማርክ !! ብዬ ከቤቱ ልወጣ ስል የቤኪ አባት ያጨበጭባል ሌሎቹ ይስቃሉ ???? ነገሮች ሊያሳብዱኝ ነበረ !!!! " ለፈተና እንደማትወድቂ እርግጠኛ ነበርኩ " አለች ፈገግ ብላ ። ቤኪ ቀበል አደረገና " ካንቺ ጋ አምስት አመት ብቻ ሳይሆን ህይወቴን እንደኖርኩ ነው የሚሰማኝ በደንብ አቅሻለሁኝ እርግጠኛ ነበርኩ " አለ ። አያልቅባቸው ያቤፅም ቀጠለና " ረጅም ጊዜ ባላቅሽም ከሚስቴ ጎን ነበርኩ " ይላል  ይባስ ብሎ የቤኪ አባት ለጥቆ "  እኔ እንኳን እንደማንኛውም አባት ትንሽ ተጠራጥሬሽ ነበረ ግን ልጄን ስላላሳፈርሽው አመሰግናለሁ ...!" አለ ። የሚያወሩት ነገር በማላቀው ቋንቋ ተረት እንደመስማት የሆነብኝ እኔ ፈጥጬ አያቸዋለሁ ????!!!!! ብቻ የበለጠ ተናደድኩኝና በሩን ወርውሬው ትቻቸው ወጣሁኝ ። የምር በጣም ከፍቶኝም ተናድጄም ነበር !!!!! መቼም እኛ ሰዎች ስንባል ስንከፋ እንጂ ስንደሰት የማናስታውሳት መሸሸጊያ የሀይማኖት ቦታ አለችንና እኔም ቀጥታ ወደ ቤተክርስቲያን ሄጄ እስኪበቃኝ ንዴቴን ተወጣሁኝ!!!! ሳለቅስ ለቀቀኝ እና ቀለል ብሎኝ ወደ ዶርም ተመለስኩኝ ። ራሴን በነገሮች ለመወጠርና ችግሬን ለመርሳት ብዬ ላይብረሪ ገብቼ ማንበብ ጀመርኩኝ!!! ስልኬ ላይ ማንም እንዳይደውል ስለፈለኩኝ ዘግቼ ቁጭ አደረኩት !!! ለሰአታት ራሴን ደብቄ ሳጠና ቆየሁኝ ። ስንት ሰአት የገባሁ ልጅ መሽቶ ነው የወጣሁትም ስልኬንም የከፈትኩትም። በጣምምም ብዙ የማላቃቸው ስልኮች ሁላ ሳይቀር የአሳውቁኝ መልእክት ገባልኝ ። መርጬ እናቴ ጋ ደወልኩ ። " አበባዬ እናቴ ምን ሆንሽብኝ እ ሳታወሪኝ ውለሽ ስልክሽን አጠፋሽብኝ እኮ ችግር  አለ እንዴ " አለችኝ ። በጣም አስጨንቂያት እንደነበር ድምጿና ንግግሯ ግልፅ ነው !!!!! እማ ይቅርታ እሺ መብራት ጠፍቶ ስልኬ ዘግቶብኝ ስለነበረ ነው ብዬ ላረጋጋት ሞከርኩኝ ። ብዙ ልታወራኝ እንዳሰበች ሲገባኝ እማ ነገ ፈተና ነኝ ልተኛ ነው  ብዬ ዋሸዋትና ስልኩን ዘጋሁት ። ዶርም ባልገባ በጣም ደስስስ ይለኝ ነበር !!!ሌላ የምሄድበት ቦታ ቢኖርና በሄድኩ ደስ ባለኝ ። አማራጭ ስላልነበረኝ ቀጥታ ወደ ዶርም ሄድኩኝ ። እንደፈራሁትም ጄሪ  በር ላይ ቁጭ ብላ ጠበቀችኝ ። " የት የበርሽ ያምሻል እንዴ ያልፈለግንሽ ቦታ የለም እኮ አስጨነቅሽን ...." እያለች ትለፈልፍ ጀመር ። ይቅርታ ማውራት አልፈልግም ደህና እደሩ ብዬ አልጋዬ ውስጥ ገብቼ ለጥጥ አልኩኝ ። እሷ ግን ያለማቋረጥ እየተከተለችኝ ታወራለች ትለፈልፋለች !!! " እኔ አይሆንም ብዬ ነበር ደግሞ እንደማታደርጊው እርግጠኛ ነበርኩ ለዛ ነው እንጂ ክፋት አስቤ አደለም " እያለች ልታስረዳኝ ሞከረች ። አሁንም የኔ መልስ ዝምታ ነበር ። " ቀልድ አይገባሽም እንዴ ተይ እንጂ "አለቾኝ። ቀና ብዬ ከቻልሽ ዝም በይ ብያት ተመልሼ ተኛሁኝኝ ። " እሺ በቤኪ ሞት ተነሺና አውሪኝ " አለችኝ ። በውስጤ ጠላቱ ይሙት ብዬ ለጥ አልኩኝ ። " እሺ በመስኪ ሞት " ስትል መታገስ አልቻልኩም ብድግ ብዬ የእናቴን ስም ከአሁን ቡሀላ ብጠሪ እንጣላለን ገባሽ የኔ እናት በእንዳንቺ አይነት ውሸታም ሰው አፍ አትጠራም እወቂ ። እንዳንቺ አይነት ጓደኛም ሆነ እህትም አልፈልግም  እኔ !!!! ብዬ ጮኩባት። " አቡ ጠላሽኝ እንዴ " አለችኝ በአሳዛኝ ድምፅ ። እኔም ድንገት ግንፍል አለብኝና አዎ  ሁላችሁም አስጠላችሁኝ ስወድም ስጠላምእንዲ ነኝ ..... እያልኩ እያወራሁ ሀሳቤንም ሳልጨርሰሰ  በሩ ክፍት አለ ። የበረከት አባት ፊቱን ጭጋጎት አድርጎ ፊቴ ተገት ሮ እያየኝ ነበር ............????? . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣3⃣
419
8
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣1⃣ ........ክው ብየ ደርቄ ቀረሁ ። በሰአቱ ራሴን የትም ሆነ እንዴትም ልደብቅም ሆነ ከአቶ ሰለሞን ልደብቀውም ሆነ እንዳያየኝ ላደርግ አልችልም!!! በሰአቱ ያለኝ አማራጭ ቆሞ መጠበቅ ነበር !! ልክ አባቷን በጉጉት እንደምጠብቅ ህፃን ልጅ በር በሩን እያየሁ ቆሞ መጠበቅ ነበር !!! የልጁን ጤንነት ለማየት ተቻኩሎ የመጣው አባት ከዶክተሩ ጋር እያወራ በሩን ክፍት አድርጎ ገባ ። ያቤፅ ደግሞ ከዃላ በድንጋጤ ቆሞ ምን ላርግ??? በሚል ፊት ይመለከተኛል !!!! እኔ ከደነገጥኩት ባልተናነሰ ሁኔታ እሱም ደንግጧል ። ለምን እንደዛ ሊለየን እንደፈለገ ባላውቅም የአመታት ጠላቱን እንዳየ ደመኛ ቀጥ ብሎ ቆሞ ፊቱን አጨማዶ ያየኛል !!???? ምን እንደማረግ ምን እንደምል የማላቀው እኔ አሁንም ግራ በመጋባት ስሜት ተሞልቼ ቆሜ እያየዃቸው ነው !!!!! መፍትሄው እንደሆነ ሳናወቅ በመፋጠጥ ብቻ ደቂቃዎችን አባከንን !!! ከዛም በቀስታና ግርማ ሞገስ በተላበሰ አረማመድ ወደኛ መምጣት ጀመረ። ለዛ ቀን ሲባል የቤት ግድግዳ በአንድ በኩል ክፍት ቤሆን ኖሮ ብዬ ተመኘው !!!!! እሱም አልበቃ ብሎ ምን አለ መሬት መደበቂያ ቦታ ቢኖራትም ብዬ ተመኝቻለሁ !!!! ፊቱ ቀለል ያለ እና መልከ መልካም ቢሆንም ከዚ በፊት የተለያየንበት ሁኔታ ጥሩ ስላልነበረ እፈራዋለሁ !!! አጠገቤ እንደደረሰ በጥፊ የሚያጋጨኝ መስሎ ተሰማኝ !!!! ያቺ ትንሽ ቤት ራቀችብኝ ። !!!!!! ከበሩ እኔ ጋር እስከሚደርስ ያለው ርምጃ ረዘመብኝ !!!!!! ከስንት የልብ ምትና ፍራቻ ቡሀላ አጠገቤ ደረሰ ። በቤኪ በግራ በኩል ቆመ ። እኔ በቤኪ በቀኝ በኩል ቆሜ እያጎረስኩት ነበረ !!!! በስተመጨረሻም ፊት ለፊት ተፋጠጥን !! " እዚህ ምን ታደርጊያለሽ ??""  ብሎ ዝምታውን ሰበረው ። እ አይ እ ... እያልኩ የ አ ቤት ፊደላትን ጥሪ የተባልኩ ይመስል እ አይ እ እያልኩ እቀባጥራለሁ !!!! " ባለፈው ቀን አላደመጥሽኝም መሠለኝ !!" አለኝ ።   አሁንም የኔ መልስ ዝምታ ነው በኩራት ከጁ ላይ ሰአት እየተመለከት " ብዙ ሰአት የለኝም ግን እባክሽ ብቻሽን ላናግርሽ " አለኝ ????? አሁን የበለጠ ፈራሁኝ ። !!!!!ግን አሁንም ቃል አላወጣሁም ዝም ብዬ አየዋለሁ ። " እባክሽ " አለ እጁን ወደ በሩ እየዘረጋ ። ምን ያርገኝ ምን ይበለኝም ሳላውቅ ቀጥጥጥ ብዬ ወጣሁ ። ከዛ እጆቼን አጣምሬ አይኔን መሬቱ ላይ ተክዬ ቀረሁኝ ። ከዃላይ ቀስ ብሎ መጣና ፊት ለፊቴ ግትር አለ ። "  የምትፈልጊውን ያሆል ገንዘብ እሰጥሻለሁ ስንትም ይሁን የአንቺንም የእናትሽንም ህይወት የምትቀይሪበት ገንዘብ ልስጥሽ ብቻ ከልጄ ራቂ "" አለኝ ???!!!! ጭራሽ ያልጠበኩት ንግግር ነው ። ሰው ሲያከብረኝ ነው የማከብረው ። የነበረውን ሞገስ በአንዴ አጣ !!!! ለሱ የነበረኝ ክብር ዝቅ ሲል ቀና ብዬ ተመለከትኩት !!!!! ምን ማለት ነው ፍቅር በገንዘብ አይገዛም እሺ ?!!!!!!! አለምዬን በገንዘብ ነው የገዛሀት እንዴ እ !!!!! ሌላ ሰው እንዳይሰማ !!! እኔ ማንነቱን እንጂ ያለበት ደረጃን ወይ ሌላ ነገሮች አደለም የወደድኩት !!! ብዬ ተመልሼ ስገባ ........... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣2⃣
399
9
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 4⃣0⃣ .......እጄን መጎተት ሲጀምር ከዛ በላይ ዝምታን ያልቻለው ቤኪ አባዬ !!! ብሎ ጭክ አለ። የቤኪ አባት ኮስተር ሲል በጣም አስፈሪ ግዙፍ ነው !!! ግንባሩን አጨማዶና ቅንድቡን ሰቅሎ ወደ ቤኪ ዞረ ። እንዳይመታው ፈርቼ ነበር ግን በአባት እና በልጅ መሀል መግባት ስላልፈለኩኝ ግራ እየተጋባሁ እያለ ያቤፅ መቶ በአንድ እጁ እኔኔ በአንዱ እጅ ጄሪን ይዞ እየጎተተ አስወጣንና በር ላይ "ገና ወደዚ ከመመለሱ ድጋሜ እንዲሄድ አታድርጊው በእናትሽ !!!!! " አለኝ ። ምን አድርጌ ያቤፅ እ አልኩት መደበቅ የማይችለው አፉ ሁሉንም ነገር  ነገረኝ ። ቤኪ ወደ ውጪ የመሄዱና ትምህርት አቋረጥ የመቅረቱ ምክንያት እኔው መሆኔን ተናገረ!!! ለካስ  አባቱ ከእኔ ጋር አይቶት ነው ከአባቱ ጋር ተጣልቶ ጥሎኝ ለመሄድ የሞከረው ።!!!! እናም ያቤፅ በቀስታ አረጋግቶ ነገረኝ !! " ድጋሜ ችግር ውስጥ ከገባ ላይመለስ እንደሚልከው ተናግራል እሱ ደግሞ ካወራ አወራ ነው ።!!!" አለኝ ከዛ በላይ ችግር መፍጠሩንም ሆነ ቤኪ እንደዛ ሆኖ ማየት አልችልም !!!!!! ስለዛ ከጄሪ ጋር ተያይዘን ቀጥ ብይ ከዛ ቦታ ወጣሁኝ ። ሁሉም ነገር አስከፍቶኛል በጣም ከባድና አሳዛኝ ቀን ነው ያሳለፍኩት !! ከዛ ቀን ቡሀላ ቤኪን እንኳን በስርአት ማውራት አልቻልኩኝም !!! ልክ አባትየውና ዶክተሩ ከዛ ክፍል ሲወጡ ያቤፅ ይደውልልኛል ገብቼ ስሜው ናፌቆቴን ተወጥቼ ቁስሉን ዳብሼ ነካክቼ አውርቼው ለማስታወሻ እያልኩ ፎቶ  እያነሳሁት ......ብቻ በተመሣሣይ መንገድ እስስከ ሳምንት ድረስ በአንድ አይነት ሁኔታ ቀጠልን ። ቀስ በቀስ ቤኪ እያገገመ መጣ ። የኔ አካልም ልቤም ቀልቤም ሁሉ ነገሬ ቤኪ ጋር ሆኖ ትምህርቱን እየተውኩት መጣሁኝ ። ተደብቄ ገብቼ ስንጫወች ሰንስቅ እየቆየን ስለነበር መማርን ረሳሁት !!!! ፈተና እንደደረሰ ሰሰማ ብቻ የገረፍታ ንባብ እያነበብኩ ባለችኝ ጭንቅላት ፈተናውን ሰራሁት ። በቀጣዩ ቀን ሌሌት የቀሰቀሰኝ የእናቴ ስልክ ነበር ። ስለ ቤኪ ነግሪያት ስለነበረ ስለሱ አጥብቃ ጠየቀችኝ እኔም ደህና መሆንኑን  ነገርኳት ። እንደለመድኩት ሀገር አማን ብዬ ከጊቢ ወጥቼ የምገዛውን ገዛዝቼ ምግብ ቴክአዌ አድርጌ ወደ  ቤኪ ጋር ደረስኩ ። ሳየው የሚያሳዝን አስተያየት ተኝቷል ። ትንሽ ቆይቼ እቀሰቅሰዋለሁ ብዬ ምግቦቹን መብያ ወንበሮቹ ላይ እየደረደርኩ እያለ ስልኬ ጠራ  ቀጥታ አነሳሁት ። ሄሎ .... " አባትሽ ነኝ !!" አለ ። እባክህ ዛሬ ደስ የሚል ጅማሮ ላይ ነኝ እና ማዘኔ አልፈልግም!!!!!! አልኩት ። " ልጄ ተይ አረ ልቀርብሽ ስሞክር እንኳን ተረጂኝ !!!!!"አላኝ እሺ ቡሀላ ደውላለሁ ዘጋሁት ። በቀስታ  ቤኪን ቀስቅሼ  የተደተደረውን ምግብ አስተካክዬ ሰጠሁትና ሊበላ ተዘጋጅቶ ገና እጁን ሲሰበስበበሪ ክፍት አለ ???? በዛ ላይ ሰለሞን ነበር የበረከት አባት !!! ክው ብዬ ደርቄ ቀረሁ ........ . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣1⃣
637
10
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣9⃣  ........አለ ቤኪ ክው ብሎ ። ዩንቨርሲቲ ውስጥ ከአንዴም አራቴ ያየሁት ሰው ነው ። ወፈር ብሎ ረዘም ያለ ኩል የሆነ አለባበስ ያለው የሚያምር ቀይ ሰው  ነው ግን ግንባሩ ጭምድድ ያለ ሰው ነው  ። የዚህ ሁሉ ልጅ አባትም አይመስልም !!! በሁለት እጄ  አጣምሬ የያስኩት እጁን ለቅቄ ወደ ዃላ እየደበኩኝ ፍጥጥ ብዬ አየሁት ያቤፅና ጄሪም በድንጋጤ አንዴ እኔን አንዴ የቤኪን አባት እየተመለከቱ ደርቀው ቀሩ ። " ምንድነው እዚህ ምን ታደርጋላችሁ ያቤፅ " አለው ግርማ ሞገስ ያለው ወፍራም የተረጋጋ ድምፁን እያሰማ። " አይ ቤኪ እኮ  ....." ብሎ ዝም አለ ። " ቀጥል በረከት  ምን ??? " አለው ወደኛ እየቀረበ ። " አረ ሶል ቤኪ ትንሽ አሞት እኮ አስደነገጠን እና ወደዚ ይዘነው መጣን አለ ወደ ቤኪ እየቀረበ ። ዞር ብዬ ሳይ ቤኪ ብርድ ልብሱን ጭምቅ አድርጎ ይዞታል ??? የቤኪ አባት በዝግታ እየተራመደ ወደኛ ሲመጣ ያቤፅ ከፊት ቀድሞ ቆመና " ሰሌ ደህና ነው አሁን ተረጋጋ እሺ እዚህ ጋ ቁጭ በል " አለው ወደ ወንበሩ እየጠቆመ ። " ያቤፅ አትልፋ ታቀኛለህ እኮ " ሲለው በአንዴ ተግባቡ ። መንገዱን ለቆ ጥጉን ይዞ ቆመ ። ከያቤፅ ጥሪ እንደተረዳሁት ከሆነ ስሙ ሰለሞን ነው መሠለኝ።  ሁላችንንም አልፎ ወደ ቤኪ ተጠጋና በእጁ ጨምቆ የያዘውን ብርድ ልብስ ገፈፈው ። ክው ነው ያልኩት የቤኪ ሆድ ከጎን ላይ ታሽጓል ። ምን ያህል ስሜቱን መደበቅ እንደቻለ አላውቅም እኔ  ሙሉ ቀኑን አብሬው ስውል ሆዱ ላይ ስተኛ ስነካካው ......... እንዴህ እንደተቆጣጠረው አላውቅም እኔ !!!!!! ምንድነው ምን ተፈጥሮ ነው ??? አልኩኝ አምልጦኝ ነው !!!!የቤኪ አባት ዞር ብሎ በሆነ በሚያስፈራ አስተያየት ተመለከተኝ ። " በዚች ልጅ ምክንያት ነው አይደለ !!! " ብሎ በሚያስፈራ አስተያየት አየኝ ። " አራ አባ እሷ ምንም የምታቀው ነገር የለም ስትሰማ ደንግጣ እየሮጠች መጣች አለቀ ብሎ ለኔ ለመሸፋፈን ሞከረ ። " ዶክተርክ ሁሉንም ነገር ነግሮኛል ከማን  ጋር ተጣልተህ ነው በል ተናገር ቶሎ ። "ፐብሎ ተናገረው ። " እንደዛ አይደለም አባ እሷ ምንም አታቅም !!!!!!!!" አለው ። " በሞትና ህይወት መሀል እያለህ ለሷ ትሟገታለህ ደደብ " አለው የአስተማሪ ነገር ። ወዲያው ዶክተሩ መጣ ። "እሺ አሁን ምን እናድርግ????" አለው  የቤኪ አባት ወደ ዶክተሩ እየቀረበ !!! እሱ ዞር ሲልልኝ ጠብቄ እጆቹን ይዤ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ እየጠየኩት እያለ  አባሁ ዞረ ። ቶሎ ለመልቀቅ ሞከርኩኝ ። ነገር ግን ከእይታው ማምለት የማይታሰብ ነው ። " ልጄን ልታስገድይብኝ ነዋ????....ብሎ አፈጠጠብኝ ። ምንም የማላቀው እኔ ቤኪና ያቤፅን በየተራ እያየሁ ጉዳዩን እንዲያስረዱኝ ጠብቃለሁ !!! ያቤፅ በሚያሳዝን ፊት አየኝና " ሶል እሷ ምንም የምታቀው ነገር የለም ዛሬ ገና ነው እንደታመም የሰማችው " ብሎ ለመሸፋፈን ሞከረ ። አሁንም ከኔ ጋ ምን እንደሚያገናኘው ግልፅ አልሆነልኝም ?????? ወደ ቤኪ ተጠግቶ እንደ ህፃን ልጅ ፀጉሩን አሻሸና ቀና ብሎ " ትሰሚኛለሽ የስለት ልጄ ነው በልጅነት የተፈተንኩበት ልጄ ነው እዚጋ አምሮበት ደምቆ ተውቦ ስላገኘሽው ብቻ አይደለም ብዙ ዋጋና ፈተና ተከፍሎበታል!!!! ትሰሚኛለሽ የብዙ ነገር ማስታወሻዬ ነው እንኳን እንደዚህ ሆኖ ላየው ይቅርና እንቅፋት ሲመታው ራሱ ያመኛል ገባሽ  " አለኝ ። ሳላስበው እንባዬ አመለጠኝ ። በተናገረው ንግግር ብቻ ሳይሆን የማላቀውን የአባትነት ፍቅር በሱ ላይ አየሁት !!!! የማላቀውን አሳየኝ አባት ለልጁ ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ ሳይ ...... ሁለት ልጄ ብለው ጠርተውኝ የማያቁ ድብደባ ጥላቻ ቁጣን አንዴም አባትነትን መካድን ቆይቶ መመለስን .....ብቻ የማይረቡ ነገሮችን እያሳዩኝ የነበሩት ሁለት አባት ከተባሉ!!! እሱን አሰብኩኝና የምር ከፋኝ !!!!! ሳላስበው እንደ ህፃን ልጅ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩኝ !!!!!!! አንዳንዴ የኔ ስጋ የምትለው ሲከዳህ በዙሪያክ መልካም ሰዎችን በመላክ ይክሳልና ጄሪና ያቤፅ ወደኔ መተው  አባበሉኝ ። ጄሪ እንባዬን ከፊቴ ላይ እየጠረገች " እረፊ እነሱ ፊት አታልቅሺ " አለችኝ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ ። ራሴን እንደምንም አሳምኜ እንባዬን ወደ ውስጥ መልሼ ተነፈስኩና ለእርሶ ልጆ ነው እኔ ደግሞ ልጆን እወደዋለሁ ከእርሶ እኩል አስብለታለሁ እጨነቅለታለሁ ከችግሮች ልመልሰው እንጂ መቼም ችግር ውስጥ እንዲገባ አላረግም አልኩኝ አፌን ሞልቼ !!! ሰው ቀና ብዬ ለማየት የምፈራ ልጅ ያንን ድፍረት ማን እንደሰጠኝም ላውቅም !!!??? ስገምት ግን አፌን ብዘጋ የተሻለ ነበር መሠለኝ የበለጠ ተናደደ ። አንገቱ ላይ የተቋጠረውን ከረቫት እያላላ " አንቺ የልጄን ጠባሳ የፈሰሰውን ደም ትመልሻለሽ " ብሎ በጩኸት ቤኪ የለበሰውን ብርድ ልብስ ገፈፈው። በፈጣሪ ስም ከድንጋጤዬ ብዛት እዛው ቀጥ ልል ነበረ!!!!! ቤኪ ለመሸፈን ቢሞክርም አየሁት ሆዱ ጋር በስለት እንደተወጋ ሰው አራት መአዘን ቅርፅ ታሽጋ በብዙ ነገር ተሸፋፍናለች !!!! መጀመሪያ ላይ እኔ ዝም ብሎ ህመም ያመመው እንጂ እንደዚ አይነት ነገር አልጠበኩኝም !!! ከድንጋጤዬ ብዛት እጄ እየተንቀጠቀጠ አፌ ተያያዘ ። " እስካሁን ብዙ ነገር ስታወሪ አልነበር ምነው  ድንገት ዝም አልሽ ጥፋትሽ ገባሽ "......እያለ ያወራል ??? እኔ እሱን ረስቼዋለሁ ንግግሩ አይሰማኝም ቤኪ ምን ሆነክ ነው ማነው እንዲህ ያደረገህ  ማነው ምንድነው ........ምን እንደማወራም አላቅም ብቻ ድንገተኛ መርዶ እንደተነገራት እናት እጄን አንዴ  ጭንቅላቴ ላይ አንዴ እሱ ላይ እያደረኩኝ እርበተበታለሁ ። " ምን እንዳላወቀ ትሆኛለሽ ባንቺ ምክንያት እኮ ነው ከዚህ ቡሀላ ልጄ አጠገብ ባይሽ መጥፎ ችግሮች ይፈጠራሉ እወቂ!!!!!! ልጄ አጠገብ እንዳላይሽ አሁን ቀጥ ብለሽ ከነ ጓደኛሽ ከዚህ ሂጂ ላትመለሽ .....ገባሽ !!!!" ብሎ እየጮከ እጄን መጎተት ሲጀምር ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_4⃣0⃣
672
11
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣8⃣ ..........አይኑን ክድን አደረገው !!! በፈጣሪ ስም ለአራት ሰከንድ አይኑን ጨፍኖ ቢቆይ በዛች ሰከንድ አይኑን ጨፍኖ የሚቀር መስሎኝ ምን ላደርግ እንደነበረ ራሱ አላውቅም ???!!!!! ብዙ ነገር ከማሰቤና ከመናገሬ ቀድሞ መሎሶ በዝግታ አይኑን ገለጠነ " አቡ " አለኝ ። ሞቼ ተነስቼ ቃላትን እየሰማሁ ነው የመሰለኝ ማለት እችላለሁ !!!! ሁለት ፊደላት አረጋጉኝ !!! ከድንጋጤዬ ብዛት ግን መናገርም መንቀሳቀስም ከብዶኝ ነበር !!! የሰማያዊት እናቴን  ስም እየጠራሁ ደጋግሜ አማትቤ ራሴን አረጋጋሁኝ ። ወደራሴ ስመለስ ቀረብ አልኩኝና እጆቹን አጥብቄ ይዤ ቤኪ የኔ አባት እኔ አንተን አጥቼ መኖር አልችልም የኔ አባት እንዴትስ እችላለሁ " ፀጉሩን እየነካካሁ .እጆቹን እነሳምኩ ) አንተ ለኔ ፍቅርን ያስተማርከኝ ሰው ወዳድ ያደረከኝ ያበረታከኝ ፅኑ ሴት ያረከኝ ነገሮችን በተግባር ያሳየከኝ ሁሉ ነገሬ ነህ የድሮዬ የአሁኔ የወደፊቴም ...........በስሜታዊነት ሳላስበው   በጣም ብዙ ከኔ ይወጣሉ የማልላቸውን ከየት እንዳመጣዋቸውም የማላቃቸው የፍቅር ቃላት ለፈለፍኩበት ። እውነት ለመናገር ብዙ እንዳወራሁ የገባኝ ራሱ ንግግሬን ጨርሼ ሳያቸው ሶስቱም ከንፈራቸው ለጠጥ አድርገው በፈገግታ እየተመለከቱኝ እንደነበር ሳውቅ ነው !!! " የኔ እናት  እንደዚህ ያማሩ ንግግሮች ካንቺ መስማት ለኔ ፈውስ ነው እኮ " ብሎ አጥብቀው የያዙት እጆቼን ስሞ አንገቱን አስደገፈበት !!! የቤኪ የግል  ዶክተር የተባለው ሰውዬ " ብዙ አታስወሩት ለቁስሉ ጥሩ አይደለም" ብሎን በነፃነት እንድናወራ ጥሎን ወጣ። አራት እብድና የፍቅር ሰዎች አንድ የተዘጋ ከፍል ውስጥ ተገጣጠምን ። ለወሬ እንዲመቸን አድርገን ወንበሩን አስቀምጠን መፋጠጥ ጀመርን ። ለወሬ ማስጀመሪያ ብዬ የቤኪ የዚህን ያህል ቅርብ ሰው ከሆንክ እንዴት አላቅህም ቆይ ???? አንድም ቀን አይቼክ አላቅም የት ነበር የምትማረው ?? አልኩት ያቤፅን አንን አይኑን በጥያቄ ፊት እያየሁኝ !! " እኔ ግን በደንብ ነው የማውቅሽ ካንቺ ቀድሜ ነው መፈቀርሽንም ያወኩት ( ፈገግ እያለ ) እኔ የተማርኩት እዚህ አይደለም የምኖረውም እዚህ አካባቢ አልነበረም "" ብሎ በስሥም ብቻ የማቀውን የሀብታም ትምህርት ቤት ስም ጠራልኝ ። ጄሪም እንደመንቃት ብላ ቆይ ግን ለምንድነው እነ አቡ ትምህርት ቤት የገባከው አለችው ። ቤኪ ብዙ እንዳያወራ ነፈለገው ያቤፅ ከእራሱ በላይ እንደሚያቀው ሰው በኮንፊደንስ ተሞልቶ ነገረን " ከአስተማራ ጋር እየተጣላ ትምህርት እያስደገሙት  በጣም ሲቸገር ዘጠነኛ ክፍልን ብቻ እዛ ተምሮ ይመለስ ብለውየመንግስት  ቢያስገቡት  የበለጠ ረብሾ አንድ አመት ደገመ በሰከንድ ግን ቅይር አለ እድሜ ለአንቺ !!" " ማለት " አለች ጄሪ ቀደም ብላ ። " ትምህርት በገባ በሳምንቱ ጠብ አደረገችው ተቃራኒ ባህሪ ስላላቸው አብረው እሱ ግንፍል ሲል አቡ እያበረደች ። እሱ ሊጣላ ሲል ፍቅር እየሰጠች ተንከባክባ በዛው እንዳቀጥል አደረገችዋ እንደዛ ተማሪ ያረገውን ጫማ አላደርግም የሚል በሽተኛ ልጅ ጠብ አደረገችው !!!!*" ብሎ ትንሽ ማጋነን የበዛባት ክሽን ያለች ቆንጆ ንግግር አደረገ !!! አንዳችን አንዳችንን እየተጠያየቅን ስንስቅ ስንስቅ እዛው አመሸን ። ሁላችንም ወደ ጊቢ የመመለስ እቅድ የለንም ደግነቱ ቁጭ ብለን ስናወራ ነበር ። በመሀል እናቴ ደወለች ። ብትሰማ ለአለምዬ እንደምትነግራትና እንደምትጨነቅ ስላወኩኝ ዝም እንዲሉ ተናግሬ ስልኩን አነሳሁት ። " አብዬ ሳጀውይልኝ ዋልሽ እኮ እናቴ ጨነቀኝ እና ነው የደወልኩልሽ " አለችኝ ። የኔ ኘዋህ እናት !!!!!!!❤❤❤ ድምፄን እያንሾካሸኩኝ ቀስ ብዬ እናቴ ጠዋት እደውልልሻለሁ አሁን እያጠናሁ ነው እሺ ደህና ነኝ እወድሻለሁ አልኳት ። እኔን ለማመን አታመነታም !!! እሺ እሺ እማ ብላ ስምኩን ዘጋችው ። ወዲያው ስልኩን ከመዝጋቴ " አንድ ጥያቄ አለኝ እኔ "  አለች ጄሪ ምንድነዎ ተረጋጊ እንጂ ቀስ ብለሽ አውሪ አልኳት መልሼ "  በመጀመሪያ  አራታችንም በአንድ ቀን ነው የምንጋባው !!!! ጥያቄው ግን መች ነው የምንጋባው ሁላችሁም ተናገሩ ። እኔ ከአራት አመት ቡሀላ ጥር ሀያ አንድ ላይ " አለች ፍልቅልቅ እያለች ። ደስታዋ ፊቷ ላይ ይነበባል ። እስካሁን በዝምላ ነቆየው ቤኪ "" እኔ የምመኘው ግን ....." ሲል በሩ ብርግድ አለ ። ያቤፅ የጄሪን እጅ ለቆ ብድግ አለ " አባ "  አለ ቤኪ ክው ብሎ ......... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣9⃣
645
12
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣7⃣ .......ስናይ ቤኪ በእጁ ላይ ብዙ ነገር ተደርድሮ ግሉኮስ ተደርጎለት ምናምን ...... የሚያስጠላ የሆስፒታል ድባብ ባለው መልኩ ተኝቷል ። ሙሉ ቤቱን በአይኔ እያማተርኩ ከተመለከትኩ ቡሀላ  ልወድቅ ስንገዳገድ ከቤኪ ጋር የነበረው አንድ ሰውዬና ጄሪ አተረፉኝ ። ደጋግፈው ወንበሩ ላይ አስቀመጡኝ ። ያቤፅ ምንም ማለት ፈርቶ መሠለኝ ጥጉን ይዞ ያየናል ። እኔም ሆንኩ እናቴ ሆስፒታል የሚባል ደርሰን ስለማናውቅ እንደዛ አይነት ሁኔታዎችን የማውቃቸው ፊልም ላይ ብቻ ስለሆነ በጣም ደንግጫለሁ በድን ሆኜ ነበር ለደቂቃዎች " አብላካት ማለት አንቺ ነሽ ?" ብሎ በትኩረት ተመለከተኝ ። በሰአቱ  ቃላት ለኔ በጣም ውድ ሆኑብኝና ማውራት ሲከብደኝ ጄሪ ቀደም ብላ " አዎ እሷ ናት " አለችው ። " ያንቺን ስም በተደጋጋሚ ሲጠራ ነበር ያቤፅ መታመሙን ለመደበቅ ሲሞክር ነበር ግን አንቺ በጣም ታስፈልጊዋለሽ ለዛ ነው ያስጠራሁሽ " አለኝ ። ምን ሆኖ ነው ምንድነው የተፈጠረው ?? አልኳቸው ድምፄን ኩሽሽ አድርጌ ። ለኔ ሳይመልሱልኝ ሶስቱም በየተራ እርስ በርስ ይተያያሉ ። እኔ ደግሞ እንደዚ አይነት ነገር እፈራለሁ !!!! ሰው ጥያቄ ጠይቄው ከኔ ይልቅ እይታውን ሌላ ሰው ላይ ካደረገ ወይ የሆነ ችግር ተፈጥሯል ወይም ደግሞ ለመዋሸት እያቀደ ነው ብዬ ነው የማምነው !!!! ለመጠየቅ ደግሜም አላሰብኩም ወዲያውኑ ለምንድነው የምትተያዩት ምንድነው የተፈጠረው ንገሩኝ !!!! ብዬ ጮኩኝ ። "" ቀላል ነገር ነው የሚያስጨንቅ ነገር የለም " አለኝ ሰውዬው ቀደም ብሎ ታዲያ ደህና ከሆነ ለምን አያወራኝም እ ለምን ዝም አለ አልኩት ከጭንቀቴ ብዛት " እባክሽ ተረጋጊ የእንቅልፍ መድሀኒት ስለወሰደ ነው ትንሽ ሰአታት ቆይቶ  ይነቃል " ብሎ ሊያረጋጋኝ ሲጠጋኝ ወደ ዃላ እየሸሸሁ ያቤፅ ሲጀመር ይሄ ሰውዬ ማነው ከዚ በፊት አይተነው የማናቀው ሰው ቤኪ ጋር ምን ያደርጋል ??? ብዬ ተኮሳተርኩበት!!! " አብላካት እረፊ እንጂ ( ወደ ሰውዬው እየዞረ ) ይቅርታ ዶክተር ስለተጨነቀች ነው " ብሎ ጥፋቴን ለመሸፈን ሞከረ ። ዶክተር  ነው እሱ ታዲያ ለምን አክሞ አያስነሳውም የዶክተር ማቴሪያል ለመን አልያዘም ......... እያልኩኝ የህፃን ጥያቄዎች እየጠኩኝ ነበር ። " የግል ዶክተሩ ነው ተረጋጊ አብላካት " አለኝ ። አይ ሀብታም !!!!😂😂😂 እኛ የግል ሽንት ቤት የለን !!....... በሰአቱ ጭንቀት ላይ ስለነበርኩኝ  ይሄን ነገር አላሰብኩትም ነበር ካለፈ ቡሀላ ነው ትዝ እያለኝ እስቅበት የነበረው ።!!!! በሰአቱ እንደምንም አረጋግተውኝ ተቀመጬ እስኪነቃ መጠበቅ ጀመርኩኝ ። ዶክተሩ እይዳለው በትንሽ ሰአት ውስጥ አልነቃም ። በዛ ለሊት እየሮጥን የመጣን እስከ ቀትር ሰባት ሰአት የቤኪን ድምፅ መስማት አልቻልኩኝም !!! አንዴ ሳለቅስ አንዴ ስነሳ አንዴ ስቀመጥ ....... ብቻ ሰከንድ ደቂቃን ደቂቃ ሰአትን ሰአት ሰአታትን እያፈራረቁ ዘጠኝ ሰአት አካባቢ ሆነ ። አስር ጊዜ አፍንጫው ስር እየተለጠፍኩኜ የትንፋሹን ድምፅ ስሰማ ቆየሁኝ ። ሲጨንቀኝ የምፀልያትን ፀሎት ደጋግሜ እየፀለይኩ ነበረ !!! በስተመጨረሻም የአይኑ ሽፋሽፍት መርገብገብ ጀመሩ ። ቤኪ ቤኪ ብዬ እላዩ ላይ ልጥፍ አልኩኝ ። ሙሉ ሰውነቱን እየዳበስኩኝ በህይወት መኖሩን አረጋገጥኩኝ ። ላለማመን እንጂ ያጣሁት ሁላ መስሎኝ ነበረ !!!!! ".....( ያቃስታል )...አቡ .....አ....አቡ....." የተቆራረጡ ጥሪዎች አሰምቶኝ መልሶ ".... ያ...ያማል ....." እያለኝ ፊደሉን በቅጡ ሳይጨርሱ አይኑ ክድን አደረገው ?????........... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣8⃣
681
13
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣5⃣ .........ጭምቅ አድርጌ አቅፌዋለሁኝ ። እንዳትስሚኝ የሚለውን የቤኪን ንግግር ረስቼዋለሁ !! ለነገሩ በዛ በምሽት ማንም አይመጣም በሚል መተማመን   ከእቅፉ ተደበኩኝ ። እንዳልቀርበው ነግሮኝ ነበር ሳቅፈው ግን ራሱ ፀጉሬን እያሻሸ  "  ተከፍተሽ ማየት አልፈልግም እናቴ ተከፍተሽ ሳይሆን በሳቅ ብዛት ከሆነ ብቻ ነው እንባሽ ሲወርድ የማየው !!" አለኝ ከለስላሳ  ፀጉሮቼ ጋር ሸርታቴ እየተጫወተ ። ደቂቃዎች ለኔ በዝተውብኝ ያ ሁላ እናባ ያ ሁላ መከፋት ያ ሁላ ተስፋ መቁረጥ በአንድ ለመለመ!!! ቤኪ የጭንቀቴ መራቂያ ነው !!!ከሱ ጋር ስሆን ሁሉም ነገር መልካምና ውብ እንደሆነ ይሰማኛል !!! ብዙ የተደበላለቁ ነገሮች ቢኖሩ እንኳን ሁሉም ነገር ልክ እንደሆነ ይሰማኛል !!!!!! ከተቃቀፍንበት ሳንላቀቅ እንደዛው አግዳሚ ወንበሮቹ ላይ ቁጭ አልን ። ተቃቅፈን የራሳችንን አለም እየቀዘፍን ባለንበት ሰአት " በዚህ ሰአት እዚ ምን ታደርጋላችሁ ?" የሚል የተቆጣ ሰው ድምፅ ሰማንና በድንጋጤ ቤኪን ሸሽቼ አፌን ይዤ ዞርኩኝ ። ወይ አባቱ ወይ አንዱ አስተማሪ ያዘን በቃ ብዬ በፍርሀት ቀጥ ልል ነበር !!!! ችግሩ ግን እኔ እንደፈራሁት ሳይሆን ባልጠበኩት ሁኔታ ኢዪኤል ነበር !" ሳላስበው ከድንጋጤዬ መንቃት እየከበደኝ ያምሀል እንዴ አንተ ራስክ እዚህ ምን ታደርጋለህ?? አልኩት ኮስተር ብዬ ። " ማነህ አንተ ምን ፈልገህ ነው የተከተልካት??   " አለ ቤኪ ከተቀመጠበት እየተነሳ ። በሁለቱ መሀል ደግሞ የበለጠ የጋለ ነገር ሊፈጠር እንደሆነ የገባኝ እኔ ቀድሜ መሀል ገብቼ ቆምኩኝ ። " አንተ ራስህ ማነህ ??? በዚህ ሰአት እዚህ ይዘካት የምትመጣው " ብሎ ኢዩኤል ነገሩን አባባሰው " ጠዋት ላይ ነግሬክ ነበር እኮ ልድገምልክ የአሁን ፍቅረኛዋ የወደፊት ባሏ ነኝ !!!!" አለ አንድ እርምጃ እየተጠጋ .......... አንድ አንድ እየተባባሉ የጋለ የቃላት ምልልሱ ወደ ድብድብ ሊያስገባቸው ልክ ቤኪ አንዴ እንደሰነዘረ " ምንድነው ምንድነው " ብሎ ዘበኛችን መብራቱን ቀጥታ አይናችን ላይ አበራብን !!!! ወደ ቢሮ ከተወሰድንና የቤኪ አባት ካየን ነገሩ ሙሉ ይበለሻሻል ማለት ነው !!!!! ቀርቦ እንዳየን በረከትን ሲመለከት ትንሽ ተረጋጋና " በረከት አንተ እዚህ ምን ታደርጋለህ ?" አለው እንደሚጠበቀው  ከኛ በላይ የሱ እዚ መገኘት አስገርሞታል ። ቤኪ ቀና ብሎ በየተራ ተመለከተንና እጁን ኢዩኤል ፊት ላይ አድርጎ " እያስቸገራት ስለነበር ነው የመጣሁት " ብሎ ኢዩኤልን ለመበቀል  ሞከረ ። ዘበኛችን መብራቱን ወደሱ እያዞረ " ና አንተ ልክስክስ " ብሎ ትከሻውን ሲይዘው አረ እንደዛ አይደለም ከፍቶኝ እያለቀስኩ ነበረ ከዛ እሱ ሊያባብለኝ እየሞከረ ሳለ በረከት መጣ እና ቅርበታችንና ማለቀሴ ሲደባለቅበት እያስቸገረኝ መስሎኝ ነው ብዬ ነገሩን ሀማስተካከል ሞከርኩኝ ። ከጠበኩት በተቃራኒ ግን  በረከት በፌዝ ተመለከተኝና " ነው እኔዴ ይቅርታ አላወኩኝም ነበር " ብሎ  የሆነ አይነት አስተያየት አየኝና ጥሎን ሄደ ። በሰአቱ እሱን ልከተል ለዘበኛው ላሳምን ግራ ተጋባው ። " እንደዛ አደለም አረ " ሲል ኢዩኤል ችግሩን መፍታት ነበረብኝና ቤኪን ቡሀላ አወራዋለሁ ብዬ ዘበኛውን አሳምኜ ወደ ዶርም ተመለስኩኝ ። ስልኬን አውጥቼ ቤኪ ጋር ደወልኩኝ ። ያለማጋነን ከአስር ጊዜ በላይ ደወልኩኝ አይነሳም ። አኩርፎ ነው ብዬ እናቴ ጋር ደውዬ አውርቻት  ተኛሁ ። ሌሊቱን ሙሉ ሲያቃዠኝ መጥፎ ህልም ሳይ አድሬ ሊነጋጋ ሲል እንቅልፍ ወሰደኝ ። " አቡ አቡ በረከት ....." የሚል የጄሪ ያለከለከ ድምፅ ካሸለበኝ እንቅልፍ አነቃኝ ........... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣6⃣
592
14
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣6⃣ .......ከእንቅልፍ አነቃኝ ። ቀረከት የሚለው ስም በጆርዬ ጥልቅ ብሏል ። በረከት ምን ሆነ አልኳት ከተኛውበት ብርግግ ብዬ እየተነሳሁ ። " ተረጋጊ አቡ ተረጋጊ መጀመሪያ "  እያለች አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጠች ። እኔ ግን ያለማቋረጥ ቤኪ ምንድነው የሆነው ንገሪኝ ቶሎ......!!!!???እያልኩ መለፍለፍ አላቆምኩኝም ። ምን ያህል እንደምወደውና እንደማስብለት ለማረጋገጥ በሰአቱ ያየኝ ሰው የሚያቀው ነገር ነው !!! ምንነቱን እንኳን ሳላውቅ ህልሜን የማታ ጥላችንንና ስልክ አለማንሳቱን አገጣጥሜ የሆነ ነገር ሆነ ብዬ ደምድሚያለሁ !!! እጄ ይንቀጠቀጣል እንባዬ መጣ  የሆነ ነገር ሆነ ብዬ ፈራሁ ........በዛ ሁላ ግራ መጋባት ስሜት ተውጬ የጄሪ ዝም ማለት ደግሞ የበለጠ አስደነገጠኝ ። ለምንድነው የማትናገሪው ብዬ በሀይል ጮኩባት ። " ሳትረጋጊ እንዴት ልንገርሽ አዳምጪኝ እንጂ መጀመሪያ " አለችኝ ከኔ ቀላይ እሷ ተናዳ ። አየችኝና አሳዘንኳት መሠለኝ መልሳ አጠገቤ ቁጭ አለችና " ተረጋጊ ታሞ ሀኪም ቤት እንደሆነ ብቻ ነው የሰማሁት ሌላ ነገር አላቅም " አለችኝ ። ሙሉ ቀሙሉ የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ ። ማታ እሱን ስላልተከተልኩ እንደከፋው አውቃለሁ !!!! ችግሩን ለማቅለል ብዬ ነበር እንደዛ ያደረኩት!!!!! ምን ተፈጥሮ ምን ሆኖ ምኑን አሞት የት ሆስፒታል !?????? የሚሉ የመአት ጥያቄዎች በአንዴ ሳዘንብባት የበለጠ ተጨናንቃ " ኡፍ አላቅም " ብላ ሳታስበው ጮከች ። " ተረጋጊ አብላካት እንዴ ያቢ ነው ደውሎ የነገረኝ ሁሉንም ጥያቄ እሱን እንጠይቀዋለን ተረጋጊና ልብስ ቀይረሽ ነይ " ብላኝ ተነስታ ወጣች ። ያለማካበድ በጣም ፈርቼ ነበር!!!! ከቁጥጥር ውጪ ሆኜ የበለጠ ጄሪንም እንዳናደኳት ይገባኛል !!!! ግን በቃ ደካማ ጎኔ ነው !!!!! ስለሱ ስሰማ ፈራለሁ !!! የሆነ ቀን ድንገት የማጣው እየመሠለኝ ፈራለሁ !!!!! የህይወቴ ግማሹ ክፍል አርጌዋለሁ ። ከዛም ቀጥታ ለባበሼ ፊቴን ታጥቤ ወጣሁ ። " አሁን ተረጋጋሽ አቡ " አለችኝ እያቀፈችኝ ። " እሺ እሺ አንቺ ተረጋጊ መጀመሪያ ከዛ ያቤ ጋር ደውለን ሁሉንም እንጠይቃለን ቅርብ ከሆነ እንሄዳለን " ብላ ትልቅ ተሴፋ ሰጠችኝ ። ከዛም ደውይልት ቶሎ ፍጠኚ ብላ አጣደፈችኝ ። ከዛ በላይ መቆየት አልቻልኩም ለያቤፅ ደወልኩ ። ችግሩ ስልክ አያነሳም???? በጣም ደጋግሜ ደወልኩ አይነሳም ???? በቤኪ ስልክ ደወልኩ አይነሳም ????? ከአብላካት ባስከኝ ?? በስንት ሀሳብ ውስጥ እየታገልኩ እያለ ስልኬ ጠራ አነሳሁት ያቤፅ ቶሎ ቶሎ አወራና ስልኩን ዘጋው ???? አቡን ይዘን እየሮጥን ከጊቢም ወተን ወደ ተባልኩት ቦታ ቀሩጫ መሄድ ጀመርን ። የማይደረስ የለ እንደምንም ደርሰን ስናይ ቤኪ ....... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣7⃣
627
15
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣4⃣ ........." አባትሽ እዚህ ነው " አለችኝ ። ክው ነው ያልኩት ። እንደበፊቱ ሊጎዳት የሄደ ስለመሰለኝ ከተኛውበት እየተነሳ እማ ተረጋጊ አሁኑኑ አለምዬ ጋር ደውላለሁ እንዲጎዳሽ እንዳትፈቅጂለት እሺ ተረጋጊ ወይም ስልኩን ስጪው ላናግረው ........ ሳላዳምጣጥ በጣም ብዙ ነገር ለፈለፍኩባት ። የኔ የዋህ ምንም ሳትል እስክጨርስ አዳመጠችኝ ። " ተረጋጊ የኔ ፍልቅልቅ በሰላም አወርተናል እስካሁን የት እንደነበር አላቅም ካላወራዋት ሞቼ ኝገኛለሁ ሲልብኝ ቢጨንቀኝ ደወልኩልሽ " አለችኝ ። የበለጠ ነው ግራ የገባኝ ። ??? ማለት ድንገት መቶ ይሄን ያህል ማሽቃበጥ ምን የሚሉት ነው ????? ብቻ ግን በሰአቱ የኔ ፍራቻ እናቴን እንዳይጎዳት ስለነበረ ስጪው ላውራት ብዬ በረጅሙ ተነፈስኩኝ "  ሄሎ ልጄ " አለኝ ። ልክ ስለሱ ሳስብ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ውስጥ እገባለሁኝ !!!!!! ልጄ ተብዬ ስለማላቅጰደስ ሊለኝ እፈልግና አፍ አውጥቼ አባቴ ማለት እንደማልችል ሳስበው ክፍት ይለኛል ። !!!! እኔ ቂመኛ ሆኜ ይሆን የገሩ ከባድ ሆኖ ራሱ አላውቅም !!????? ብቻ ግን ቃላት አጥሮኝ እየተንተባተብኩ አ...አቤ....ት አልኩኝ እንደምንም ታግዬ ። " ደህና ነሽ ለምን ስትሄጂ አላሳወቅሽኝም ?" አለኝ እሱ ገና ሳልወለድ ጥሎኝ ሲሄድ ያማከረኝ ይመስል ?!!!!! ዝምታዬ መልስ አልሆነለትም መሠለኝ " ደግሞ አደግሽና ዩንቨርስቲ ገባሽ አሉ ግን የት እንዳለሽም አላወኩም አልነግርም አለችኝ መጥቼም እንዳላገኝሽ ?" አለኝ ። አባት ስላልሆንክ ይሆናላ !! ቆይ ከኔ ምን ፈልገህ ነው ለምንድነው ድንገት በዚህ ልክ የፈለከኝ ? አልኩት እንደምንም ራሴን አደፋፍሬ ። ሰው ጥፋቱ ሲነገረው እንዲህ ነው የሚሆነው !!!! ጥፋቱ ገብቶት ዝም አለ ብዬ ሳልጨርስ " ካንቺ ምን ልፈልግ እችላለሁ አባቴ ብለሽ እንድጠሪኝና ልጅ አለኝ ብዬ ማውራት ብቻ ነው የፈለኩት " አለኝ ። አነጋገሩ ላይ ትንሽ አለመብሰል ይታይበታል!!! ከአንቺ ምን እፈልጋለው ማለት አልነበረበትም !!!! በሱ ተናድጄ ሳልጨርስ ግን ንግግሩ ሆዴን በላው ። ምክንያቱም ደግሞ እኔ አንዴ እንኳን አባቴ ብዬ መጥራትና አባት አለኝ ብዬ ማውራት የምመኘው ነገር ነው !!!!!! ከዛ በላይ ስሜቴን ማፈን አልቻልኩኝም እንባዬ አመለጠኝ !!!! ብርድ ልብሴ ውስጥ ተደብቄ እስኪወጣልኝ አለቀስኩኝ !!!! በጣም ከፋኝ !!! ከሆነ ጊዜ ጀምሮ ቶሎ መከፋት ጀምሪያለሁኝ !!!???? እንባዬን ማውጣት ራሱ እንዳልችል ጄሪ መታ " አቡ ምነው ምን ሆንሽብኝ ምን ሆነሽ ነው ምንድነው ????" የሚሉ በርካታ ጥያቄዎች ደረደረችልኝ ። ሳያት ደግሞ ስለ አባቷ የምታወራው የምትነግረኝ በቀን ስንቴ እንደሚደውልላት ...... ብዙ ነገሮች አሰብኩኝና የበለጠ ማልቀስ ጀመርኩኝ ። ደስ የሚለው በአንዴ ተረዳችኝና በዝምታ አቅፋ ጀርባዬን ማሻሸት ጀመረች ። ከዛ ስልኳን ከኪሶ አውጥታ የሆነ ነገር ነካ ነካ አደረገችና አስቀምጣው አልቅሼ እስኪወጣልኝ በትዕግስት አቀፈችኝ ። በዘመድ ቢበድለኝ በባዳ ሰው ክሶኛል ። አለምዬ ቤኪ ጄሪ .... ብቻ ቸማላቃቸው አውቀውኝ ተገኝተዋል ብዙ ህመሜን የሚካፈሉ ሰዎች ሰቶኛል !!!! " ነይ አየር እንቀበል ተነሺ ጃኬት ደርቢ ፍጠኚ " ብላኝ ከዶርም ወጣች ። እንቢ ብልም ተመልሳ መጥታ እንደምታብድብኝና እይደምታስወጣኝ ስላወኩኝ ቀድሜ ራሴን ችዬ ጃኬቴን አድርጌ በኮፍያ ተሸፍኜ ወጣሁ ። ስልክ እያወራች ነበረ እሺ እሺ ብላ ዘጋችው ። " ነይ ትንሽ ወክ እናድርግ ይለቅሻል " ብላ እንደሰሠቀ ተማሪ በአትክልቶቹ ውስጥ ለውስጥ ወሰደችኝ ። ወዴት ነው የምንሄደው ያምሻል እንዴ አልኳት " እህ ደስ የሚል ቦታ አለ ኢዩ አሳይቶኛል " ብላ ቀጥታ ወሰደችኝ ። እዛ ስንደርስ ቤኪ እኔን ለማቀፍ ተዘጋጅቶ እየጠበቀኝ ነበር ። የጄሪ ስራ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ ። እኔም እሱን ሳይ ሊከፋኝ ሲል ወደኔ ቀርቦ እዛ ደረት ላይ ለጥፎ ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ ። ጄሪ ደግሞ  " እህቴን አደራ ቤኪ " ብላ እየሮጠች ሄደች ። እኔ ከእቅፉ ባልወጣሁ እያልኩኝ ጭምቅ አርጌ አቅፌዋለሁ ....... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣5⃣
765
16
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣3⃣ .............አራታችንም እኩል ዞርን ። እኔ አይቼው የማላቀው ሰው ነው ። ዞሬ ሳያቸው ግን ቤኪና ያቤፅ ት ደንግጠዋል ? ፈገግታቸው ከፊታቸው  ርቆ በአንዴ አኩርፈዋል ??? ቤኪ ምንድነው አልኩት ግራ ገብቶኝ ። ሊነግረኝ የፈለገ አይመስልም " መጣን እሺ ካፌ ጠብቁን " ብሎኝ ሳይስመኝ እንኳን ከቦታው ሰውዬውን ተከትለው ሄዱ ። ማነው አልኳት ጄሪን ከኔ በላይ በረከትን የምታቀው ይመስል ። " አብሬሽ አ ያለሁት እኔ በምን አውቃለሁ ?" አለችኝ ። ልክ ስለነበረች ሌላ ነገር አላወራሁም ተያይዘን ወደ ካፌ ሄድንና እሷ ሻይ እኔ ማኪያቶ አዘን ቁጭ አልን ። " የአንቺና የባልሽ ውለታ አለብኝ " አለችኝ ። እንዴት አልኳት ፈገግ እያልኩ " እህ በቃ ያቢን የበለጠ እንድወደው አደረጋችሁኝ " አለች ። ያቢ ያቤፅ ማለቷ ነው እንግዲ ስም ማቆላመጥ ላይ ጎበዝ ናት🙄 እኛ ምን አረግን እና አንቺ ነሽ ወደሽ አጣርተሽ ጠይቀሽ አፍቅረሽ ነገሩን የጨረሽው እኮ  አልኳት ። " አረ ቤኪ ስንት ለፍቶ ለምኖ ነው ያስታረቀን ሁሉንም ነገርዐነግሮኛል " አለች ፈገግ እያለች ። ቁጭ ብለን የናፍቆታችንን የባጥ የቆጡን እያወራን ቆየን ። ንድ ከቆይታዎች በሀላ ቤኪና ያቤፅ ተመልሰው መጡ ። ምን ተፈጠረ የት የት ነበራችሁ አልኳቸው ። " ሴቶች ቆይተው ሲገናኙ ወሪያቸው አያልቅም ይባላል " ብለው ወሪዬን ለመቀየስ ሞከሩ ። ከዛ  ምሳ በላንና በዛው ተጫወትን አወራን ።...... ከቤኪ  ጋር ስሆን ሳላሰሰሰበው ሰአቱ ይሮጣል ቀኑ የፈጥናል በጣም ነው የሚገርመኝ???? ቤኪ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቤኪ ጋር ረጅም መንገድ ብቻችንን ተራመድን ። ጄሪና ያቤፅ አኔድ ላይ ሆነው ያማረ ወክ አደረግን ። " ታቂያለሽ እናቴ በጣም ደስ የሚል ቀን ነው !!!!!! ሶስመቶ ስልሳው ቀን እንደዚህ ቢያልፍ ብዬ ተመኘው !!!! " አለኝ ። ፈገግ ብሎ። እኔም ደስ ይለኝ ነበር የኔ አባት ብዬ ጉንጩን ነካ አደረኩት ። " እዚ መቆየቴ አይቀርም እና እንገናኛለን ግይ አደራ መንገድ ላይ እንዳትስሚኝ " አለኝ ። ነገሩን ቀሌላ መንገድ ነው የተረዳሁል ለምን ማለቴ ወጣልክ ወይሴ ሌላ ሴት አየክ አሌኩት በአንዴ ፊቴ እየተሸየረና እንባ እያቀረረኝ ። " እንደዛ አትበይ አረ የኔ ፍቅር " አለኝ ። ነው እንጂ ለምን ከመሬት ተነስተክ እንዲ አልክ ??? አልኩት ። " ምክንያቱም  አባቴ እዚህ ነው !!!!"ፐብሎ ቆሌዬን ገፈፈው ??? ............ገፈፈው ። አባቱን አላቃውም ብቻ ግን ወደ ውጪ ስለላከው እና ስለ አባቱ አውርቶኝም ስለማያቅ በጣም እፈራዋለሁ ። የማቀው ከስንት አንዴ ብቻ ቤት ደርሶ እንደሚመለስ ብቻ ነው የማቀው ። የአለምዬን እድለኛ ባልና የልዑሉን አባት ባውቀው ደስ ይለኝ ነበር እያልኩ እያሰብኩ አባትህ እዚህ ምን ያደርጋል ?? አልኩት ግራ ገብቶኝ ። ለመመለስ ትንሽ አንገራገረ  የዛኔ የበለጠ ለማወቅ ጓጓሁ ። እ አልኩት ፍጥጥ ብዬ እያየሁ ። " የዩንቨርስቲው ዋና አስተዳደር ነው "  አለኝ ። ክው ነው ያልኩት ። ምክንያቱም ከዚህ በፊት ከጄሪ ጋር ሄደን ያናገርነው ገዘፍ ያለ ሰውዬ መጣልኝ ። ጨምዳዳ ግንባር ግን የሚያምር ፈገግታ ያለው ሰው ። !!! በዛ ላይ በጭራሽ እንደዛ አይነት ስራ አልጠበኩኝም ። ቀአራት አመት ፍቅራችን ውስጥ ፈጣሪ በሚያቀው ስለ ሀብት ምንጭ የእናት አባቱ ስራ ..... ብቻ ከገንዘብ ጋር የተያያዙ ነገሮች ለደቂቃ አሳስበውንም ሆነ አውርተን አናቅም። አላውቅም ነበር ቤኪ አልኩት ። ከዛ ለምን ዘበኛችን ያን ያህል ክብርና ፍቅር እንደሰጠው ግልፅ ሆነልኝ !!!!! ያው ምድራዊ ነገር ናት ሲኖርክ ትከበራለህ !!! የዚች ምድር ህግ ነው !!!! ያው እኔ ባላምንበት እድሜዬን ሙሉ ገንዘብ ላለው ሰው ቅድሚያ እና አክብሮት  ሲሰጥ  እያየው ነው ያደኩት!!! እናቴ ያን ያህል  ገንዘብና በዋናነት ግን አለሁልሽ የሚላት ባልም ሆነ ዘመድ  ስላልነበራት እንደማንኛው ሰው የሚገባትን ክብር ስታጣና ፊት ስትነሳ አይቻለሁ!!!!! በርግጥ ይህ ነገር በትምህርቴ ምርጥ አድርጎኛል ። በሰአቱ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም !!!! ተምሬ ስራ ይዤ እናቴን ሀብታም አርጌ ........ናቸው የኔ ህልሞች ። በነገራችን ላይ አለምዬን የምወዳት በምክንያት ነው !!! እናቴ ስራ ፈልጋ ቤቷ ብትሄድ ንፁህ ጓደኝነት እህትነት አልፎም ደግሞ የመጀመሪያ ልዑሏን ለኮርማታዋ ሴት ልጅ ያለማንገራገር ሰታታለች ።!!!!! እንደ ሌላው አልተፀየፈችንም የእማን የልብ ንፁህነት እንጂ ያጣ እጇን አላየችም !!!! ያን ያህል ባይቸግረንም ያን ያህልም የለንም የሚባል ደረጃ ላይ እንዳለን እያወቀች ከዛ የተንጣለለ ቤት ወታ እኛ ቤት ደስ እያላት ትበላለች ትጠጣለች !!!!! ያው አብዛኞቹ ደረጃው ከፍ ያለ ቤት ውስጠሰ  ሲኖር ታላቅ የሆነ ይመስለውና ከስር ያለነውን ለመናቄ  ያስባሎ ።!!! አለምዬ ግን እንደዛ አደለችም!!!!! " የኔ ልዕልት አኩርፈሽኝ ነው እናቴ እኔ እኮ አምትጠቆሪ ብዬ ነው " የሚል የቤኪ አሳዛኝ ድምፅ ከተዋጥኩበት ሀሳብ አነቃኝ !! እ አልኩት ፈዝዤ ። ይሄን ሀላ ነገር እያሰብኩኝ በሀሳብ ሄጄ ነበር !!! ከዛ ያወራውን ትንሽ አስቤ እሺ የኔ አባት አልኩትና ። ቀጥታ መጓዝ ጀመርኩኝ ። እስካሁን ሳስባቸው የነበሩትን ለምን ሆኑ ልኩኝ እያሰላሰልኩ ዱካኩን ጨመረብኝ። ከዛም ከጄሪ ጋር ተያይዘን ወደ ዶርም ሄድን ። እንደገባን እቃዬን አስገባብቼ ለጥ ብዬ ድካሙን ለማካካስ ሞከርኩኝ ። ከዛም እናቴ ጋር ደውዬ በሰላም መግባቴን እየነገርኳት እያለ "  ልጄ ስልኩን እንዳዘጊው ግን የምነግርሽ አለኝ "አለችኝ ። ምነው እናቴ አልኳት እየደነገጥኩ " አባትሽ ..." . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣4⃣
738
17
20 like or emoji I will send at next part 33 🫠
632
18
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣2⃣ ........ አለኝ ። አዎ በጣም ዝግጁ ነኝ አልኩት ለማየት መጓጓቴን ፊቴ ላይ እያንፀባረኩኝ ። ጎንበስ ብሎ እጁ ላይ ሰአት አየና " ሁለት ደቂቃ አለን ገምቺ እስኪ " አለኝ ። መቼም አግቢኝ ብለክ ልጠይቀኝ  አይሆንም አይደለ ? አልኩት ፈገግ ብዬ ። በእኔ ቤት ጥሩ ቀልድ መቀለዴ ነበረ !!! ቤኪ ግን በአንዴ ቅይር አለና " ባደርገው ትቀበይኛለሽ እ ሁሉንም ትተን ፍቅራችንን እንድናስቀድም ታደርጊያለሽ ?? ከማንም በላይ ልዕልት አድርጌ እንደማኖርሽ ታቂያለሽ አደለ " አለኝ እጆቼን እየያዘ ። በአንድ ቅስሜ ፍስስ ነው ያለው ማለት ይቻላል ። እኔ በጭራሽ ማንም ቢሆን በሰው ገንዘብ መኖር አልፈልግም ። ቤኪ ሌላ ነገር እንደማያስብ አንቀባሮ እንደሚያኖረኝ አውቃለሁ !!! ነገር ግን እኔ  ምንም ያህል ባፈቅረውና ምንም ቢፈጠር የራሴን ነገር ሳልይዝ ትዳር አላስብም !!!!! ከሱ እኩል ካልሆነ ልል አልችልም አውቃለሁ ቢያንስ ትምህርቴን ጨርሼ ስራ ሳልይዝ አላደርገውም !! " ምነው አቡ በአንዴ ቅይር አልሽብኝ እኔ እኮ ስቀልድ ነው አሁን እሱን የምታስቢበት ጊዜ እንዳልሆነ በደንብ አቃለሁኝ "ብሎ ሊያረጋጋኝ ይሞክራል ። ለካስ ይሄ ሁላ ነገር ሳስብ የነበረው ጠላቷ ፊቷ እንደቆመ በቀለኛ ግንባሬን ጨሜድጄና ቅንድቤን ጠምዝዤ ነበር ። እንደመባነን ስል ሌላ ነገር እንዳያስብ ፈርቼ ወደፊት ስንጋባ  ..... ስንወልድ የሚኖረንን ህይወት እያሰብኩ እኮ ነው አልኩት ነገሩን ለማብረድ እየሞከርኩኝ ። ሀሳቤን የተረዳው ቤኪም በጣቶቹ ጉንጬን ነካ እያደረገ " አታስቢ የኔ ስስት እረዳሻለሁ " ብሎ ቀለል አደረገልኝ ። እሺ አሁን ምን ልታሳየኝ ነው እዚህ ድረስ ያመጣከኝ አልኩት መገመት ስላልቻልኩኝ " እኔ እንድታዝኛም ሆነ የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማሽ አልፈልግም " ብሎ ወደ ቀኝ ተመለከተ ??? አይኖቹን ተከትዬ እኔም ስዞር የኔ እብድ ጓደኛ ጄሪ በበረከት ማለቴ ያቤፅ እጆች ተይዛ ወደኔ መጣችና አጠገቤ ስትደርስ  ተጣልተን እንደሄድን እስክረሳው ድረስ ተጠምጥማ አቀፈችኝ !!! እብደቷ የልቧ ንፁህነት ሳቋ .....ብቻ የናፈቀችኝን ያህል አቅፌ ተወጣሁ ። የገረመኝ ደግሞ እኔ እስኪበቃት አገላብጣ ከሳመችኝ ቡሀላ ቤኪንም ጥምጥም ብላ አቀፈችው ??? ይባስ ብላ ወደ ያቤፅ ተመልሳ እጁን እየጎተተች አመጣችውና እንደማይተዋወቅ ሰው አድርጋን "  እሷ አብላካት ትባላለች እሱ ደግሞ ያቤፅ ይባላል ..... እ የአሁን ፍቅረኛዬ የወደፊት ባሌ ነው ከአባቴ ቀጥሎ የምድርም የልቤም ንጉስ አድርጌዋለሁ " አለችኝ ፍልቅልቅ እያለች ። እኔ እንዴት አድርጌ ነው የምነግራት እያልኩ በጭንቀት ላብድ ደርቼ እሷ በፈገግታ ተሞልታ እያስተዋወቀችኝ ተገኘች !!! " የወንድሜ ሚስት ይቅርታ እሺ ለሱ ላደርግለት ከምችለው ነገር አንዱ ስለሆነ ነው የቤኪ ትዕዛዝ ነው የኔ እጅ የለበትም " ብሎ እጁን ዘረጋልኝ ። አሁን ላይ እሱን የምሸሽበት ምክንያት የለኝም በደንብ ሰላም አልኩት ። እኔና ጄሪ አጠገብ ለአጠገብ ቤኪና ያቤፅ አጠገብ ለአጠገብ ቆመን ተፋጠጥን ። ሰው እንዴት ቁመት እንኳን አይበላለጥም !!!!! መንታ ራሱ እንደነሱ አይመሳሰልም ሲስቁ , ዲምፕላቸው , ጥርሳቸው , ቡኒ አይናቸው , አቋማቸው እርጋታን ጨምሮ አንድድድድ ናቸው!!!!!! እኔና ጄሪ ተመካክረን ይመስል በአንድ ድምፅ መንታ ናችሁ ? የሚል ጥያቄ አቀረብንላቸው ። እኔና እሷ እኩል በማለታችን እየሳቅን እነሱ በጥያቂያችን ሲስቁ አራታችንም ከትት ብለን እየሳቅን እያለ ነበረ " በረከት" የሚል የተቆጣ ድምፅ የሰማነው ። አራታችንም እኩል ዞርን ....... . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣3⃣
695
19
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 3⃣1⃣ ........አንድ  ላይ ከቤት ወጣን ። ቅርብ ስለነበር ቶሎ ነው የደረስነው ። ሸኝቶኝ ሊመለስ ስለመሰለኝ ልሰናበተው ስዘጋጅ " አብረን ነው የምንገባው አረ " ብሎኝ ከመኪናው ወረደ ። ማለት  ቤኪ የት ልትሄድ ?? አልኩት ። " አንድ ሰርፕራይዝ አለችኝ ዝም ብለሽ ጊቢ " አለኝ ። ያምሀል እንዴ በመታወቂያ ነው የምንገባው እኛ አልኩት አናዶኝ ። ንግግሬ አሳቀው መሠለኝ ፈገግ ብሎ አየኝና " ኦ የማላቀውን ነገር ስለነገርሽኝ አመሠግናለሁ የኔ ቆንጆ " ብሎ ጉንጮቼን ነካ አደረጋቸውና መንገዱን ቀጠለ ። ከፊት ከፊቱ እየቀደምኩ አሁን ከአሁን ዘበኛው መቶ በያዘው ዱላ ፈነከተው እያልኩኝ ልቤ ስትንቀጠቀጥ የዘበኞቹ በር ጋር ደረስን ። መታወቂያዬን አሳይቼ የያስኩትን ሙሉ ተፈትሼ ስጨርስ ቤኪ ወደኔ መጣ ። ሴቷ የጊቢ ጠባቂ ፈትሻኝ ጨርሳ ቀና ስል ቤኪ ወደኔ እየመጣ ነው ተቀምጦ የነበረው ዘበኛችን ከመቀመጫው ፈንጠር ብሎ ተነሳ ። ወይኔ ጉዴ ብዬ ከቤኪ ፊት ቀድሜ ቆምኩኝ ። የዛኔ ቋጥሮት የቆየ ሳቁን ለቀቀውና " ይሄን ያህል ነው የምትወጂኝ ለካ !!" ብሎ እየሳቀ ወደ ሰውዬው ቀረበ ። ጭራሽ ይባስ ብለው ሁለቱም በትህትና ጎንበስ ብለውና በፈገግታ ተሞልተው እየሳቁ በከባዱ ሰላም ተባብለው ተቃቀፉ እኔን የፈተሸችኝንም ሰላም አላት???? በመሀል ግራ በመጋባት ስሜት በየተራ ሁለቱም ላይ አይኔን አማትራለሁ ??? ጭራሽ " ጋሼ ደህና ናቸው አለምስ ሁላችሁም ቤተሰብ ጠፋችሁ ....... ብቻ በርካታ ነገር እየተባባሉ እንደ ረጅም አመት ጓደኛ በሰፊዊ ተጠያየቁ ። በዛ ሁላ መሀል ግራ የገባኝ እኔ ትክ ብዬ ቤኪን እያየሁ የነሱን ጨርሶ ለኔ እስኪመልስልኝ እየጠበኩ ነበረ !!! ይበልጥ ያስገረመኝ ደግሞ " ይቺ ቆንጆ ልጅ አዲሷ የጊቢያችን ሰቃይ ተማሪ ናት ስለሷ ብዙ ሰምተናል " አለው የኔው ጉድ መሆኑን አላወቀ ። ቤኪ ሁሌ እንደኮራብኝ ነው ወደ ራሱ ጎተት አድርጎ አቀፈኝና " አዎ የጊቢው ሰቃይ ብቻ ሳትሆን የጊቢው ቆንጆም ሚስት ነው ያለችኝ "አለ አይን አይኔን እየተመለከተ። ምንም ብወደው በሰው ፊት እንደዛ ሲል በጣም ነው የማፍረው እኔ አንገቴን መሬት ተክዬ ዝም አልኩኝ ። እሱ ግን የተገረመ ይመስላል " ሚስት ?" አለው ። ደንገጥ ብሎ እያፈጠጠ " አዎ የአምስት አመት ፍቅረኛዬ የወደፊት ሚስቴ ናት ተዋወቃት " አለ እጁን ወደኔ እየጠቆመ ። ትንሽ አንደበቴ ተያይዞም ቢሆን አብላካት ብዬ ዝም አልኩኝ ። " በለፈው ወር ጋሼ መተው ነበረ እኮ እኔ ጋር ስለዚህ ዜና ሳያበስሩን "አለው ። " አባባን ለማሳመን ትንሽ ሰአት ይፈጅብኛል ለዛ ነው " ሲለው በአንዴ ተግባቡ ። " ምን እግር ጣለክ ታዲያ " አለው ቤኪን " አንድ አስፈላጊ ሰው ማግኘት አለብኝ መጀመሪያ እዛ ልሂድና ከዛ ዞር ዞር  እልና ሰው አግኝቼ እመለሳለሁ " አለው ቤኪ በትህትና ተሞልቶ ። "እሺ የምትፈልገው ነገር ካለ ጥራኝ ግን አሁን ወተዋል እሳቸው.... " ብሎ ወሬውን ሊቀጥል ሲል ቤኪ ንግግሩን በአጭሩ እሺ እሺ በማለት አሳጠረውና ወደ ውስጥ ገባን ። አላደርስ ብሎኝ ስለነበር ገና እዛው ዞር ስንል ቤኪ ምንድነው ??? እንዴት በዚህ ልክ ልትግባቡ ቻላችሁ ??? ቶሎ ንገረኝ አልኩት ከፊት ከፊቱ እየቀደምኩኝ ። " አሁን ሰርፕራይዙን ለማየት ተዘጋጂ እሱን ተይው " አለኝ ። እየተናደድኩ ነው ለምን እተወዋለሁ ???? ንገረኝ እባክህ ብዬው ቀና ስል የጄሪ ጓደኛ ኢዩኤልን ከፊት ለፊት ሲመጣ አየሁት ። ክው ነው ያልኩት ባላየ ባለፈኝ እያልኩ ግንባሬን እየፈተኩ ለመደበቅ ብጀምርም እየፈጠነ መቶ ጥምጥም ብሎ አቀፈኝና " አቡታ የት ጠፍተሽ ነው ቆየሽ እኮ ናፍቀሽኝ ነበር " ሲል ቀጥታ ቤኪን ተመለከትኩት !!! በአንድ ጊዜ ፊቱ ቅይር ነው ያለው ያ በእስፖርት የለመደ ደምስሩ በአንድ መስመር እየሰሩ መተላለፍ ጀመሩ ። እንደነገርኳችሁ በንዴቱ ጊዜ የማብረድ ሀይል አለኝና እሱን  ተጠቅሜ እጁን ያስኩትና ወደ እቅፉ ተጠግቼ ደህና ነኝ አመሠግናለሁ አለሁኝ ብዬ ወደ ቤኪ እየዞርኩኝ አባቴ ተዋወቀው የጊቢ ወንድሜ ነው ብዬ ልቡን ሰከን አደረኩት ። " በረከት እባላለሁ "አለና መንገዱን ቀጠለ ። ዞር ብዬ ሳየው ኢዩኤል  በግርምትና በድብርት ድብልቅ ስሜት እያየኝ ነበረ ። ግን እንዳይጣሉ ሌላ ምርጫ አልነበረኝም !!!!! ከዛ በመሀል እየሄድን ሰዎች እንዳለ ቤኪ ላይ እያፈጠጡ ነበረ ።??? በዛ ውበት በዛ ኩሩነት በዛ አለባበስ ...ብቻ ሁሉም ተደምሮ ከፍሬሽ ተማሪ እስከ ሲኒየሮች ያዩት ሁላ ፍዝዝ ብለው እየተመለከቱት ነበረ !! ትንሽ ረብሾኛል ??!!! ግን ቀንቼ አይደለም !!!! ጊቢውን ከኔ በላይ የሚያቀው ይመስላል ሹልክ ሹልክ እያለ ውስጥ ለውስጥ ወሰደኝና ብዙ ዛፍ ያለበት ቦታ ስንደርስ " እ ዝግጁ ነሽ የኔ ስስት " አለኝ ። . . ይቀጥላል #ክፍል_3⃣2⃣
648
20
https://t.me/wallet/start?startapp=ref-3-vbAk0KlNDOk 👋 Hey! I'm using Wallet in Telegram to buy crypto — it's right inside the app, no extra setup. Join with my link and you can get up to $50 back on your first trade.
709