en
Feedback
ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

Open in Telegram

''ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዛኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው'' contact : 0111 23 99 96 Facebook : @temromastemar YouTube : https://www.youtube.com/channel/UCZI9ztt_MA_dRnqGH6PTCvw

Show more
1 778
Subscribers
+324 hours
+67 days
+930 days
Posts Archive
ማሳሰቢያ! ለማኅበሩ አባላት በሙሉ! በቅድሚያ እንኳን ለምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ቅዳሴ ቤት ለሚከበርበት እና የመድኀኔ ዓለም ታቦት ለሚነግሥበት ብቸኛ ዓመታዊ በዓላችን አደረሳችኁ፡፡ ኹላችኁም እንደምታውቁት ይኽ በዓላችን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና ብፁዓን አባቶቻችን ሊቃነ ጳጳሳት ጭምር የሚገኙበት፤ ከተለያየ ስፍራ የሚመጡ ምእመናን ተገኝተው የሚባረኩበት፤ እኛም በጉጉት ነጭ ልብሳችንን ለብሰን በዝማሬ እና በእልልታ ከቤተሰቦቻችን ጋር  ውዳሴ የምናቀርብበት ብቸኛ እና ልዩ በዓላችን መኾኑ ይታወቃል፡፡ ስለ ኾነም በዓለ ንግሡ በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲካሄድ፤ ለተመደቡ አስተናባሪዎች ፍጽምት በኾነች ፍቅር በመታዘዝ፤ ከታቦቱ የሚገባውን ርቀታችንን በመጠበቅ፤ በመድረክ ላይ ለሚካሄዱ መርሐ ግብሮች፤ ለብፁዓን አባቶቻችን ሊቃነ ጳጳሳት እና እንግዶች ዋናውን መድረክ በመልቀቅ፤ ለሚመጡ እንግዶች ቅድሚያውን በመስጠት በዓለ ንግሡን እንድናከብር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ++++++++++++++++++++++++ አባታችንና አምላካችን ቸሩ መድኀኔ ዓለም በዓሉን የሰላም፤ የበረከት እና የፍቅር ያድርግልን፡፡ ++++++++++++++++++++++++

የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት የመዘምራን ዝግጅት https://vt.tiktok.com/ZS9x9tc4q/