ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት
Open in Telegram
''ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዛኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው'' contact : 0111 23 99 96 Facebook : @temromastemar YouTube : https://www.youtube.com/channel/UCZI9ztt_MA_dRnqGH6PTCvw
Show more1 894
Subscribers
No data24 hours
+97 days
+4330 days
Posts Archive
1 894
አስቸኳይ የሥራ ማስታወቂያ (ዋና ጸሐፊ)
ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ክፍት የሥራ መደብ ላይ ባለሙያ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ማመልከት ትችላላችኁ!
📋 የሥራ መደብ ዝርዝር
የሥራ መደብ: ዋና ጸሐፊ
ብዛት: አንድ
የቅጥር ኹኔታ: በኮንትራት
ደሞዝ: በስምምነት
የሥራ ቦታ: ተምሮ ማስተማር
🎓 የትምህርት ዝግጅት
የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን
፣ ሰፕላይ/ማቴሪያል/ሎጅስቲክስ ማኔጅመንት
ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት፣ የትምህርት መስክ የተመረቀ/ች።
⏳ የሥራ ልምድ
አራት ዓመታት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ላት።
📝 የማመልከቻ መመሪያ
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች፡
ማመልከቻዎን፣
የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃ ዋናውን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር በመያዝ፣
በተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት የሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ በአካል በመቅረብ ወይም በወኪል መመዝገብ ትችላላችኁ።
⚠️ ማስታወሻ፡
፩.መወዳደር የሚችለው የሰ/ት/ቤቱ አባል የኾነ ብቻ ነው።
፪· አመልካቾች ሙሉ ስም፣ የስልክ አድራሻ፣ የሚያመለክቱበትን የሥራ መደብና ደረጃ በተዘጋጀው የማመልከቻ ቅጽ ላይ መሙላትና መፈረም ይኖርባቸዋል።
የፈተና ቀን በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል።
(እባክዎ ይኽንን መልእክት ለሚያውቋቸው አባላት እንዲደርሳቸው ያድርጉ!)
1 894
ለአባላት በሙሉ
በመርሐ ግብር መደራረብ ምክንያት እና ጸሎተ ፍትሐቱ እሑድ ጠዋት በአራት ሰዓት መኾን ስለ አለበት ወደ መስከረም ዐሥር ፳፻፲ወ፱ (2019) ዓ.ም. የተሸጋገረ መኾኑን እናሳስባለን።
1 894
ለአባላት በሙሉ
"ያገለገለኽን ሰው ሞት ቸል አትበል፤ " መ.ሲራክ ፴፰÷፲፮
በየዓመቱ ማጠናቀቂያ በመደበኛ ጉባኤያችን ሰዓት በአጸደ ነፍስ ያሉ አባላትን የምናስብበት የጸሎተ ፍትሐት መርሐ ግብር እንደምናካሂድ ይታወቃል፤ በዚኹ መሠረት የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ ሠላሳ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ከስምንት ሰዓት እስከ ዐሥር ሰዓት ድረስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ (በቅኔ ማሕሌት) ጉባኤው እና ጸሎተ ፍትሐቱ በገዳማችን መምህር (አስተዳዳሪ) መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ፣ በአበው መነኮሳት እና አኀው ዲያቆናት መሪነት የሚካሄድ ስለ ኾነ አባላት በዕለቱ እና በሰዓቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንድትሰበሰቡ ይኹን፤
በተጨማሪም ያረፉ አባላትን አንድ አንድ ፎቶ ከዕለቱ በፊት እንድታመጡ ይኹን።
"ይኄይስ: ስም: ሠናይ: እም: ቅብዐ፡ መዓዛ፤ ወዕለተ: ሞት: እም: ዕለተ: ልደት፤ ከመልካም ሽቱ መልካም ስም፤ ከመወለድ ቀንም የሞት ቀን ይበልጣል/ይሻላል።" መ.መክብብ ፯÷፩
"ኦ: ክርስቶስ: ዘትፈትሖሙ: ለሙቁሐን፤ ፍትሓ: ወአግዕዛ: ለነፍሰ: ኲሎሙ: ክርስቶሳውያን: እም፡ ኩሉ፡ ሐዘን፡ ወአንብራ፡ ኀበ፡ ተጋብኡ፡ ቅዱሳን፤ በእንተ፡ ሚካኤል፡ ቃለ፡ አብ፡ ሰማኢ፤ ወገብርኤል፡ መዋዒ፤ ወሩፋኤል፡ እሳት፡ በላኢ፤ ወዑራኤል፡ ማኅፈድ ጽኑዕ፡ ቅድመ፡ ገጸ፡ ጸላኢ፤ ሥረይ፡ ላቲ፡ ኃጢአታ፡ ለነፍሰ፡ ክርስቲያን!" ግብረ ሕማማት ገጽ ፺፭~፺፮÷፵፮~፵፯
የታሰሩትን የምትፈታ ክርስቶስ ሆይ! የአብን ቃል ስለሚሰማ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ብለኽ፣ ድል ስለሚያደርገው ስለ ቅዱስ ገብርኤል ብለኽ፣ የሚባላ እሳት ስለ ኾነው ስለ ቅዱስ ሩፋኤል ብለኽ፣ ከጠላት ፊት የጸና መሸፈኛ ስለ ኾነው ስለ ቅዱስ ዑራኤል ብለኽ የኹሉንም ክርስቲያኖች ነፍስን ከሐዘን ኹሉ ፍታቸው፤ ቅዱሳን በተሰበሰቡበትም አስቀምጣቸው፤ የክርስቲያንንም ኹሉ ነፍስ ኃጢአቷን ደምስስላት!!!
1 894
https://vt.tiktok.com/ZSVYqXEwn/
"ወተወለጠ፡ ራእዩ፡ በቅድሜሆሙ፤ ወአብርሃ፡ ገጹ፡ ከመ፡ ፀሐይ፤ ወአልባሲሁኒ፡ ኮነ፡ ጸዐዳ፡ ከመ፡ በረድ። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ኾነ። " ማቴ.፲፯÷፪ እንኳን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችኁ! በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አይቀርም!! ኹላችኹም ተጋብዛችኋል!!!
1 894
https://vt.tiktok.com/ZSVYV2LwE/
"ወተወለጠ፡ ራእዩ፡ በቅድሜሆሙ፤ ወአብርሃ፡ ገጹ፡ ከመ፡ ፀሐይ፤ ወአልባሲሁኒ፡ ኮነ፡ ጸዐዳ፡ ከመ፡ በረድ። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ኾነ። " ማቴ.፲፯÷፪ እንኳን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችኁ! በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አይቀርም!! ኹላችኹም ተጋብዛችኋል!!!
