ar
Feedback
ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

''ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዛኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው'' contact : 0111 23 99 96 Facebook : @temromastemar YouTube : https://www.youtube.com/channel/UCZI9ztt_MA_dRnqGH6PTCvw

إظهار المزيد
1 894
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+97 أيام
+4330 أيام
أرشيف المشاركات
አስቸኳይ የሥራ ማስታወቂያ (ዋና ጸሐፊ) ​ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ክፍት የሥራ መደብ ላይ ባለሙያ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ማመልከት ትችላላችኁ! ​📋 የሥራ መደብ ዝርዝርየሥራ መደብ: ዋና ጸሐፊ ​ብዛት: አንድ ​የቅጥር ኹኔታ: በኮንትራት ደሞዝ: በስምምነት ​የሥራ ቦታ: ተምሮ ማስተማር ​🎓 የትምህርት ዝግጅት ​የመጀመሪያ ዲግሪ በ​ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ​፣ ሰፕላይ/ማቴሪያል/ሎጅስቲክስ ማኔጅመንት ​ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት፣  የትምህርት መስክ የተመረቀ/ች። ​⏳ የሥራ ልምድ ​አራት ዓመታት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ላት። ​📝 የማመልከቻ መመሪያ ​መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች፡ ​ማመልከቻዎን፣ ​የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃ ዋናውን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር በመያዝ፣ ​በተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት የሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ በአካል በመቅረብ ወይም በወኪል መመዝገብ ትችላላችኁ። ​⚠️ ማስታወሻ፡ ፩.​መወዳደር የሚችለው የሰ/ት/ቤቱ አባል የኾነ ብቻ ነው። ፪· አመልካቾች ሙሉ ስም፣ የስልክ አድራሻ፣ የሚያመለክቱበትን የሥራ መደብና ደረጃ በተዘጋጀው የማመልከቻ ቅጽ ላይ መሙላትና መፈረም ይኖርባቸዋል። ​የፈተና ቀን በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል። ​(እባክዎ ይኽንን መልእክት ለሚያውቋቸው አባላት እንዲደርሳቸው ያድርጉ!)

ለአባላት በሙሉ በመርሐ ግብር መደራረብ ምክንያት እና ጸሎተ ፍትሐቱ እሑድ ጠዋት በአራት ሰዓት መኾን ስለ አለበት ወደ መስከረም ዐሥር ፳፻፲ወ፱ (2019) ዓ.ም. የተሸጋገረ መኾኑን እናሳስባለን።

ለአባላት በሙሉ "ያገለገለኽን ሰው ሞት ቸል አትበል፤ " መ.ሲራክ ፴፰÷፲፮ በየዓመቱ ማጠናቀቂያ በመደበኛ ጉባኤያችን ሰዓት በአጸደ ነፍስ ያሉ አባላትን የምናስብበት የጸሎተ ፍትሐት መርሐ ግብር እንደምናካሂድ ይታወቃል፤ በዚኹ መሠረት የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ ሠላሳ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ከስምንት ሰዓት እስከ ዐሥር ሰዓት ድረስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ (በቅኔ ማሕሌት) ጉባኤው እና ጸሎተ ፍትሐቱ በገዳማችን መምህር (አስተዳዳሪ) መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ፣ በአበው መነኮሳት እና አኀው ዲያቆናት መሪነት የሚካሄድ ስለ ኾነ አባላት በዕለቱ እና በሰዓቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንድትሰበሰቡ ይኹን፤ በተጨማሪም ያረፉ አባላትን አንድ አንድ ፎቶ ከዕለቱ በፊት እንድታመጡ ይኹን። "ይኄይስ: ስም: ሠናይ: እም: ቅብዐ፡ መዓዛ፤ ወዕለተ: ሞት: እም: ዕለተ: ልደት፤ ከመልካም ሽቱ መልካም ስም፤ ከመወለድ ቀንም የሞት ቀን ይበልጣል/ይሻላል።" መ.መክብብ  ፯÷፩ "ኦ: ክርስቶስ: ዘትፈትሖሙ: ለሙቁሐን፤ ፍትሓ: ወአግዕዛ: ለነፍሰ: ኲሎሙ: ክርስቶሳውያን: እም፡ ኩሉ፡ ሐዘን፡ ወአንብራ፡ ኀበ፡ ተጋብኡ፡ ቅዱሳን፤ በእንተ፡ ሚካኤል፡ ቃለ፡ አብ፡ ሰማኢ፤ ወገብርኤል፡ መዋዒ፤ ወሩፋኤል፡ እሳት፡ በላኢ፤ ወዑራኤል፡ ማኅፈድ ጽኑዕ፡ ቅድመ፡ ገጸ፡ ጸላኢ፤ ሥረይ፡ ላቲ፡ ኃጢአታ፡ ለነፍሰ፡ ክርስቲያን!" ግብረ ሕማማት ገጽ ፺፭~፺፮÷፵፮~፵፯ የታሰሩትን የምትፈታ ክርስቶስ ሆይ! የአብን ቃል ስለሚሰማ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ብለኽ፣ ድል ስለሚያደርገው ስለ ቅዱስ ገብርኤል ብለኽ፣ የሚባላ እሳት ስለ ኾነው ስለ ቅዱስ ሩፋኤል ብለኽ፣ ከጠላት ፊት የጸና መሸፈኛ ስለ ኾነው ስለ ቅዱስ ዑራኤል ብለኽ የኹሉንም ክርስቲያኖች ነፍስን ከሐዘን ኹሉ ፍታቸው፤ ቅዱሳን በተሰበሰቡበትም አስቀምጣቸው፤ የክርስቲያንንም ኹሉ ነፍስ ኃጢአቷን ደምስስላት!!!

https://vt.tiktok.com/ZSVYqXEwn/ "ወተወለጠ፡ ራእዩ፡ በቅድሜሆሙ፤ ወአብርሃ፡ ገጹ፡ ከመ፡ ፀሐይ፤ ወአልባሲሁኒ፡ ኮነ፡ ጸዐዳ፡ ከመ፡ በረድ።  መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ኾነ። " ማቴ.፲፯÷፪  እንኳን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር  በሰላም አደረሳችኁ!                                                በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አይቀርም!! ኹላችኹም ተጋብዛችኋል!!!

https://vt.tiktok.com/ZSVYV2LwE/ "ወተወለጠ፡ ራእዩ፡ በቅድሜሆሙ፤ ወአብርሃ፡ ገጹ፡ ከመ፡ ፀሐይ፤ ወአልባሲሁኒ፡ ኮነ፡ ጸዐዳ፡ ከመ፡ በረድ።  መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ኾነ። " ማቴ.፲፯÷፪  እንኳን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር  በሰላም አደረሳችኁ!                                                በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አይቀርም!! ኹላችኹም ተጋብዛችኋል!!!

photo content

photo content