fa
Feedback
ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

رفتن به کانال در Telegram

''ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዛኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው'' contact : 0111 23 99 96 Facebook : @temromastemar YouTube : https://www.youtube.com/channel/UCZI9ztt_MA_dRnqGH6PTCvw

نمایش بیشتر
1 820
مشترکین
+524 ساعت
+117 روز
+5230 روز
آرشیو پست ها
📍 ሚኒሶታ፣ ሰሜን አሜሪካ 📣 የመንፈሳዊ ጥሪ ዜና፦ የተምሮ ማስተማር ማኅበር በሰሜን አሜሪካ በሚኒሶታ የገቢ ማሰባሰብ መርሐ-ግብር እያካሄደ ነው ⚽️ በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢት
+5
📍 ሚኒሶታ፣ ሰሜን አሜሪካ 📣 የመንፈሳዊ ጥሪ ዜና፦ የተምሮ ማስተማር ማኅበር በሰሜን አሜሪካ በሚኒሶታ የገቢ ማሰባሰብ መርሐ-ግብር እያካሄደ ነው ⚽️ በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ባገናኘው ዓመታዊው የስፖርት እና የኢትዮጵያውያን ቀን ፌስቲቫል ላይ፣ የተምሮ ማስተማር ማኅበር ልዩ የማስተዋወቂያ እና የዕርዳታ ማሰባሰቢያ ዳስ (Booth) በማዘጋጀት መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቱን በደመቀ ኹኔታ እያስተዋወቀ ይገኛል። ✝️ ማኅበሩ ለቀጣይ ዘላቂ የኾኑ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎቶች የሚውል የገቢ ማሰባሰብ እያከናወነ ሲኾን፣ ዋና ዋና ትኩረቶቹም፦ 📖 የወንጌል አገልግሎትን ማስፋፋት፦ መንፈሳዊ መጻሕፍትን እና የትምህርተ ወንጌል ግብዓቶችን ለዲያስፖራው ማኅበረሰብ በተለይም ለወጣቱ ትውልድ ተደራሽ ማድረግ። ⛪️ የአብነት ትምህርት ቤቶችን መደገፍ፦ በሀገር ቤት የቤተ ክርስቲያን ምሰሦ የኾኑትን የአብነት ተማሪዎችን እና መምህራንን ለመርዳት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ማጠናከር። 🤝 ትውልድን በሥነ-ምግባር መቅረጽ፦ በስደት የሚኖረው ወገን የሀገር ቤቱን መንፈሳዊ አገልግሎት በገንዘቡ እና በዕውቀቱ እንዲደግፍ ማነቃቃት። 📜 > "ይኽ ማኅበር በስደት ያለነውን ምእመናን ከሀገር ቤት መንፈሳዊ በረከት ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው"፤ — የበዓሉ ታዳሚዎች እና የዳሱ ጎብኝዎች በደመቁ መንፈሳዊ መዝሙራት እና መጻሕፍት የተሸለመው የማኅበሩ ዳስ በበርካታ ጎብኝዎች እየተጎበኘ ይገኛል። ይኽ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ማኅበሩ በቀጣይ የወንጌል አገልግሎቱን በስፋት ለማስቀጠል ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥርለት ታምኗል።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ለምእመናን በሙሉ  "ልጅኽን በሚሄድበት መንገድ ምራው፤ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።" መጽ.ምሳ ፳፪ ÷ ፮ በቅድሚያ መንፈሳዊ ሰላምታችንን እያቀረብን በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት የሕፃናት እና ማእከላውያን ጉዳይ ክፍል በየዓመቱ እንደሚያደርገው የ፳፻፲ወ፰ (2018) ዓ.ም.  ትምህርት መዘጋቱን ምክንያት በማድረግ  የክረምት መንፈሳዊ ትምህርቶችን አዘጋጅቷል፤ ስለ ኾነም ርስዎም ልጆችዎን እና በአቅራቢያዎ ያሉ ከአንደኛ እስከ ዐሥረኛ ክፍል ድረስ የሚገኙ ሕፃናትን ወደ ሰ/ት ቤታችን ልከው መንፈሳዊ ዕውቀትን እንዲገበዩ እግዚአብሔርንም እንዲያውቁ ያድርጉ። ትምህርቱ ሰኔ ፳፰ (28) ቀን ፳፻፲ወ፰ (2018) ዓ.ም. ይጀምራል፤ ትምህርቱ የሚሰጠው ዘወትር ከሰኞ እስከ ዐርብ ከ2:30 -6:00  ድረስ ነው። ዓመቱን ሙሉ የሚሰጠው ትምህርት ቅዳሜ  ከስምንት ሰዓት እስከ ዐሥራ አንድ ሰዓት እና እሑድ ከሦስት ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት መኾኑ ይታወቃል።                         ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ ቤት

ለአባላት በሙሉ ከባሌ ሃገረ ስብከት  ለ፲፭ (15) ቀናት  ሃያ አራት (፳፬)  ደቀ መዛሙርት ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሰባቱ ምስጢራት፣ ሥርዐተ ቤ/ክ፣ ዕቅበተ እምነት እና የመሳሰሉትን ትምህርቶች በትምህርት እና ሥልጠና ሥራ ሥራ አስፈጻሚ እና  በበጎ አድራጎት ሥራ አስፈጻሚ  በኩል ከሰኔ ፳፩ (21) ቀን  እሰከ ሐምሌ ፭ (5) ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም.  ሥልጠና ስለሚሰጥ አባላት ደቀ መዛሙርቱ  የሚለብሱት አንሶላ እና ብርድ ልብስ  እንድታመጡልን ጥሪያችንን እያስተላለፍን፤ በተጨማሪም ለደቀ መዛርቱ  ምግብ ለማዘጋጀት  እና ለማስተናገድ የሚመቻችኁ  አባላት  ለትምህርት ሥልጠና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ለበጎ አድራጎት ሥራ አስፈጻሚ ስማችኁን እንድትሰጡልን አደራ እንላለን፡፡

የአገለገለኽን ሰው ሞት ቸል አትበል ሲራክ ፴፰:፲፮ የሐዘን መግለጫ የገዳማችን እና የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት አባል የነበረው ወንድማችን ሙሉጌታ አርአያ (ብርሃነ መስቀል) ከዚኽ ዓለም ድካም በማረፉ በረከታችንን በማጣታችን የተሰማንን ሐዘን እንገልጻለን። ሙሌ በገዳማችን እና በሰንበት ትምህርት ቤታችን ውስጥ ለረጅም ጊዜ በቅንነት፣ በትጋት እና በፍቅር በማገልገል ለብዙዎች መልካም አርአያ ኾኖ ኖሯል። የሰጠው አገልግሎት እና ያሳየው መልካም ምግባር ኹል ጊዜ በክብር ይታወሳል። ሙሌ አባላት ሲጠፉ የሚፈልግ፣ ሕፃናትን ከልቡ የሚወድና ዘወትር ቅዳሜ እና እሑድ በሕፃናት ጉባኤ እየተገኘ የሚያስተባብር ትጉኅ አገልጋይ የነበረ ከቤተ መቅደስም አንድም ቀን ሳይለይ በቅዱስ ቁርባን ጸንቶ የኖረ በረከታችን ነበር። ኾኖም ከአምላክ ጋር ለመገናኘት ድልድይ የኾነው መንገድ የሥጋ ዕረፍት ነውና በዛሬዋ ዕለት ዐርፎ ሥርዓተ ቀብሩ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የገዳማችን የበላይ ሐላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ የገዳማችን አበምኔት መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ ፣ የገዳማችን ማኅበረ መነኰሳት እና ዲያቆናት ፣ የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፣ ቤተሰቦቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት በደብረ ሰላም ቀጨኔ መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል። በመኾኑም ለቤተሰቦቹ ፣ ለገዳማችን ማኅበረ መነኰሳት፣ ለተምሮ ማስተማር አባላት  ለወዳጆቹ እና ለኹሉም የአገልግሎት ባልደረቦቹ ከልብ የመነጨ መጽናናትን እንመኛለን። ልዑል እግዚአብሔርም ነፍሱን በክብር እንደሚቀበለው ብናምንም ነፍሱን በአብርሃም፣ በይስሐቅ እና በያዕቆብ አጠገብ ያሳርፍልን እንላለን!!! የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ቀን: ፲፬/፲/፳፻፲፰ ዓ.ም.

ሰላም! የማኅበራችን አባል የኾነው እና በገዳማችን ውስጥ የሚኖረው ወንድማችን ሙሉ ጌታ አርአያ በዛሬው ዕለት ዐርፏል። የወንድማችንን ነፍስ ይማርልን! መላው ቤተ ሰብንም መንፈስ ቅዱስ ያጽናናልን! የ
ሰላም! የማኅበራችን አባል የኾነው እና በገዳማችን ውስጥ የሚኖረው ወንድማችን ሙሉ ጌታ አርአያ በዛሬው ዕለት ዐርፏል።  የወንድማችንን ነፍስ ይማርልን! መላው ቤተ ሰብንም መንፈስ ቅዱስ ያጽናናልን! የቀብር ሰዓት፦ ነገ እሑድ ሰኔ ዐሥራ አራት ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ከሦስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት (ከቅዳሴ እንደ ተወጣ) በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ነው።