fa
Feedback
ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

رفتن به کانال در Telegram

''ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዛኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው'' contact : 0111 23 99 96 Facebook : @temromastemar YouTube : https://www.youtube.com/channel/UCZI9ztt_MA_dRnqGH6PTCvw

نمایش بیشتر
1 849
مشترکین
-324 ساعت
+87 روز
+4230 روز
آرشیو پست ها
የሕፃናት መንፈሳዊ ጉዞ ተካሄደ፤ በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ሕፃናት እና ማእከላውያን ጉባኤያት መኻከል ከቅዱስ ጳውሎስ (ዐምስተኛ) ክፍል እስከ ቅዱስ ዮሐንስ
የሕፃናት መንፈሳዊ ጉዞ ተካሄደ፤ በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ሕፃናት እና ማእከላውያን ጉባኤያት መኻከል ከቅዱስ ጳውሎስ (ዐምስተኛ) ክፍል እስከ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (ዐሥረኛ) ክፍል ድረስ ያሉት ስድስት ክፍሎች ብቻ በሐምሌ ፲፱ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ወደ ርእሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ጉዞ አካሂደዋል። በዚኽ ጉዞ ሕፃናቱ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ በመግባት በመሳለም እና ጸሎት በማድረግ ቅኔ ማሕሌቱን በማየት፣ ወደ ቤተ መዘክሩ በመግባት በአስጎብኚው በኩል በመጎብኘት፣ የዐፄ ምኒልክን ቤተ መንግሥት በመጎብኘት፣ በተዘጋጀላቸው አዳራሽም ጉባኤ በማካሄድ የቅዱስ ገብርኤልን በዓል እና የጉዞ ዓላማ እንዲኹም የቤተ ክርስቲያኗን ታሪክ በዝርዝር ተምረዋል። ከሩሲያ የመጡ ጎብኚዎች ጋርም የሐሳብ ልውውጥ ተደርጓል።

በተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት የጥናትና ምርምር ማበልጸጊያ አገልግሎት አዘጋጅነት የተካሄደው ፪ኛው ዓመታዊ የጥናትና ምርምር መድረክ በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ በቋንቋ፣ በክህነት አገልግሎትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዙሪያ ያተኮሩ ሶስት ዋና ዋና ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።  መርሐ ግብሩ በተሳታፊዎች ምዝገባ እና በዲ/ን ኢ/ርመስፍን ተክለዮሐንስ የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ሥራ አመራር ጉባኤ ሰብሳቢ የእንኳን ደኅና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸውም የጥናትና ምርምር ሥራዎች ለቤተክርስቲያንና ለሰንበት ትምህርት ቤቱ እሴቶች እድገት ያላቸውን ከፍተኛ ሚና አብራርተዋል።  በመርሐ ግብሩ ላይም በርከት ያሉ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን :- ፩. የግእዝ ቋንቋ መደበኛ ተነባቢ ፊደላት ድምጽና የሴም ቋንቋዎች ንፅፅር  አቅራቢ፡ መምህር ዮሴፍ ሙሉጌታ  ይዘት፡ ጥናቱ የግእዝ ቋንቋ መደበኛ ተነባቢ ፊደላት ድምጽን ከሴም ቋንቋዎች ፊደላት ድምጽ ጋር በተመረጡ ቃላት በማነጻጸር ያለውን የድምጽ አገባብ ችግር የመረመረና የመፍትሔ ሀሳቦችን ያመላከተ ነው።  ፪. የዘመናዊነት ተፅዕኖ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ክህነት ላይ (Exploring contemporary impacts of Modernization on the Priesthood of EOTC)  አቅራቢ፡ ቀሲስ በርተሎሜዎስ ክንፈ ገብርኤል ያቀረቡ ሲሆን ይዘት፡ በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ክፍለ ከተሞች ላይ ትኩረት በማድረግ ዘመናዊነት በካህናት አገልግሎትና አኗኗር ላይ የሚያሳድረውን በጎና ተፎካካሪ ተፅዕኖዎች ተንትኗል።  ፬. የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተፅዕኖ በሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ላይ (Assessment of the Impact of Digital Technology on Religious Practices)  አቅራቢ፡ መምህር ብሩክ ተክሉ ይዘት :በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚገኙ የተመረጡ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ጥናት በማድረግ ዲጂታል ቴክኖሎጂ በምዕመናን ሃይማኖታዊ ክንውኖች ላይ ያመጣቸውን አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖዎች አቅርቧል።  ከጥናት ጽሑፎቹ ማቅረቢያ በኋላ በተካሄዱት የውይይት ሰዓታት ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በአቅራቢዎችና በአወያዮች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በዕለቱ ማጠቃለያም ላይ ለጥናት አቅራቢዎችና አስተባባሪዎች የተሳትፎ ሰርተፊኬት ከተበረከተ በኋላ፣ በመዝጊያ ንግግርና ጸሎት መርሐ ግብሩ በስኬት ተጠናቋል።  ሐምሌ ፤ ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም

የስራ ማስታወቂያ ተምሮ ሚዲያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ትውፊት እና ሥርዐት ጠብቆ፣ የቤተ ክርስቲያን ምእመናን ወንጌልን፣ እምነት እና ሥርዐትን እንዲማሩበት እና እንዲያውቁ እየሠራ ያለ መገናኛ ብዙኃን ነው።   Job Title   Social Media Director Location   Addis Ababa, Ethiopian (6 kilo in front of Miskaye Hizunan Medehanialem) Job Type - Full Time Salary Negotiable Job Description The Social Media Director is responsible for developing and leading the organization’s social media strategy to grow brand awareness, engagement, and audience reach. The role oversees content planning, creation, publishing, performance analysis, and coordination with creative and marketing teams.   Key Responsibilities ·         Develop and implement social media strategies and campaigns ·         Plan monthly and weekly content calendars for all platforms ·         Oversee creation of videos, graphics, and written content ·         Manage and supervise social media team (editors, designers, creators) ·         Publish, schedule, and monitor posts across platforms ·         Engage with followers, respond to messages and comments ·         Analyze performance using insights and analytics tools ·         Prepare reports on growth, reach, and engagement ·         Manage paid social media ads (if required) ·         Ensure brand consistency across all platforms ·         Stay updated with social media trends and platform changes Qualifications & Experience ·         Bachelor’s Degree or Diploma in Communication, Media, Film, Photography, or related field (preferred) ·         Minimum 2 year experience ·         Proven experience managing multiple social media platforms ·         Strong understanding of content strategy and audience engagement ·         Experience with analytics tools (Meta Insights, Google Analytics, etc.) ·         Leadership and team management skills ·         Excellent communication and writing skills ·         Creative thinking and problem-solving ability     Note   In addition to the work experience we mentioned, it would be good if he was a deacon (ዲያቆን).   How to Apply Applicant Deadline, July 28, 2026 Interested and Qualified applicants shall apply via the following email address temromastemar27@gmail.com

የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤትን የመጀመሪያ የዲጂታል መጽሔት ሚያዚያ ፳፯/፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. በዕለተ መድኀኔ ዓለም ዓመታዊ በዓላችን እንዳስመረቅን ይታወቃል፤ ቀጣይ በሚወጣው እትም ላይ በጽሑፍ እንድትሳተ
የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤትን የመጀመሪያ የዲጂታል መጽሔት ሚያዚያ ፳፯/፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. በዕለተ መድኀኔ ዓለም ዓመታዊ በዓላችን እንዳስመረቅን ይታወቃል፤ ቀጣይ በሚወጣው እትም ላይ በጽሑፍ እንድትሳተፉ እየጋበዝን፣ መሳተፍ የምትፈልጉ አባላት እስከ ሐምሌ ሠላሳ (፴) ድረስ ጽሑፋችኹን በሰንበት ት/ቤቱ ቤተ መጻሕፍት ወይም ከታች ባለው link  እንድታስቀምጡ እንጠይቃለን። በዚኽ ሊንክ ማስቀመጥም ይቻላል https://forms.gle/C35b1H2jociGkxXe7

የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤትን የመጀመሪያ የዲጂታል መጽሔት ሚያዚያ ፳፯/፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. በዕለተ መድኀኔ ዓለም ዓመታዊ በዓላችን እንዳስመረቅን ይታወቃል፤ ቀጣይ በሚወጣው እትም ላይ በጽሑፍ እንድትሳተ
የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤትን የመጀመሪያ የዲጂታል መጽሔት ሚያዚያ ፳፯/፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. በዕለተ መድኀኔ ዓለም ዓመታዊ በዓላችን እንዳስመረቅን ይታወቃል፤ ቀጣይ በሚወጣው እትም ላይ በጽሑፍ እንድትሳተፉ እየጋበዝን፣ መሳተፍ የምትፈልጉ አባላት እስከ ሐምሌ ሠላሳ (፴) ድረስ ጽሑፋችኹን በሰንበት ት/ቤቱ ቤተ መጻሕፍት ወይም ከታች ባለው link  እንድታስቀምጡ እንጠይቃለን።

የተደረገለት ነገ ሐሙስ 1:00 ሰዓት ይጠብቁን
የተደረገለት ነገ ሐሙስ 1:00 ሰዓት ይጠብቁን