Amhara Education Bureau
📈 Analytical overview of Telegram channel Amhara Education Bureau
Channel Amhara Education Bureau (@anrse) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 39 380 subscribers, ranking 4 644 in the Education category and 879 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 39 380 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 618 over the last 30 days and by -22 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 39.13%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 14.79% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 15 410 views. Within the first day, a publication typically gains 5 825 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 29.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“Quality Education”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 07 September | +2 | |||
| 06 September | +8 | |||
| 05 September | +4 | |||
| 04 September | +2 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | +7 | |||
| 01 September | +42 |
| 2 | No text... | 7 750 |
| 3 | ኢትዮ ቴሌኮም በደሴ ከተማ ለ3 ሺህ 640 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2018 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮ ቴሌኮም ሰሜን ምስራቅ ሪጅን በደሴ ከተማ ለሚገኙ 3 ሺህ 640 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
በኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ማስረሻ ገበየሁ በዚህ ወቅት÷ ለተደረገው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ 3 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ወጪ መደረጉን ተናግረዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ 113 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ ለ105 ሺህ 496 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን አመልክተዋል።
በትምህርት ዘርፉ ብቃትና እውቀት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት በዲጂታል ቤተ መጻሕፍት፣ በዲጂታል አጠቃቀምና ልህቀት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ይሰራል ነው ያሉት።
ኢትዮ ቴሌኮም ለተማሪዎች ምገባ፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የ1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የደብተር ድጋፍና በ45 ዩኒቨርሲቲዎች ለተመረጡ ተማሪዎች 97 ሚሊየን ብር የኪስ ገንዘብ በመስጠት ያልተቋረጠ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኩባንያው የ2028 ስትራቴጂን በሥራ ላይ በማዋል ባከናወነው ሥራ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው ተግባራት 492 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
የደሴ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ራቢአ ታረቀ በበኩላቸው÷ የመማሪያ ቁሳቁስ ግብዓት ድጋፍ ተማሪዎች ሳያቋርጡ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲገኙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
የደብተር ድጋፉ በደሴ ከተማ በቢለን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተጀመረ ሲሆን÷ በአጠቃላይ 7 ትምህርት ቤቶችን ተደራሽ እንደሚያደርግ ተመላክቷል። | 6 945 |
| 4 | "ነገን ለመገንባት ትምህርት ላይ ትኩረት ሰጥተን እየሰራን ነው።"
አቶ ሀያሉ ሰሎሞን (የኢትዮ ቴሌኮም ደ/ማርቆስ ዲስትሪክት ኦፕሬሽን ማናጀር)
*
ኢትዮ ቴሌኮም የደ/ማርቆስ ዲስትሪክት ለምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ለ1 ሽህ 200 ተማሪዎች የሚሆን 1 ሽህ 200 ደርዘን ደብተር አበርክቷል።
የዲስትሪክቱ ኦፕሬሽናል መናጀር አቶ ሀያሉ ሰሎሞን የደብተር ስጦታውን በአበረከቱበት ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮ ቴሌኮም ዘመናዊነትን ለመላበስ የ3 ዓመት አዲስ እቅድ አቅዶ እየሰራው ካለው በርካታና ዘርፈ ብዙ የዲጅታል ቴክኖሎጅ ተግባራት በተጨማሪ በበጎ አድራጎት ስራ እየተሳተፈ ይገኛል።
በዛሬው እለትም ነገን ለመገንባት ሲባል ለነገ ተስፋዎችና ሀገር ተረካቢዎች ህጻናት 1 ሽህ 200 ደርዘን ደብተር ለዞኑ ትምህርት መምሪያ አስረክበናል ብለዋል።
ትምህርት ላይ መስራት ነገን መገንባት ነው የሚሉት አቶ ሀያሉ በጤናና በትምህርት ተቋማት በተለይም በሞዴል ክላስና በዲጂታል ላይበራሪ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ እንደሆነ አብራርተው ለደ/ማርቆስ ከተማ 576 ደርዘን እንዲሁም ለምዕራብ ጎጃም 924 ደርዘን ደብተር መስጠታቸው እና በስጦታውም ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ስጦታውን የተረከቡት የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሓላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ የተደረገውን በጎ አስተዋፆ በዞኑና በተማሩዎች ስም አመስግነው ዞኑ ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት በግጭት ውስጥ በመቆየቱና በትምህርት ስራው ላይ ሳንካ ፈጥሮ እንደነበርና አሁን በተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም በተያዘው በጀት ዓመት በዞኑ ከ820 ሽህ በላይ ተማሪዎችን መዝግቦ የትምህርት ስራውን ለመጀመር በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ የበርካታ ዜግችን ህይወት የሚያሻሽል እና ለሌሎች ተቋማትና ግለሰቦችም ምሳሌ የሚሆን በመሆኑ እናመሰግናለን ብለዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ በዲጅታል ላይበራሪ፣ በሞዴል ትምህርት ቤት፣ በተማሪዎች ዲጂታል መታወቂና በመሰል ዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ከእኛ ጋር አብሮ እሰራ በመሆኑ ተግባሩን የበለጠ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።
ጳጉሜ 1/2028
መረጃው ምስራቅ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ነው
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 4 836 |
| 5 | No text... | 4 991 |
| 6 | ከ326 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባው ትምህርት ቤት ተመረቀ።
።።።።።።።።
ጳጉሜ 1/2018(ትምህርት ቢሮ) የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ326 ሚሊየን ብር በላይ ያስገነባውን የማህበረሰብ ትምህርት ቤት ዛሬ አስመርቋል።
ለምረቃ የበቃው ትምህርትም ከቅድመ አንደኛ እስከ 8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንዲችል ተደርጎ የተገነባ ሲሆን በ2019 የትምህርት ዘመን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ተማሪዎችን መዝግቦ እንደሚያስተምር ተገልጿል።
የትምህርት ቤቱ መገንባት ዩኒቨርሲቲው ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያለውን ትስስር እንደሚያጠናክር በምረቃ ስነስርዓቱ ወቅት ተገልጿል።
በምረቃ ስነስርዓቱም የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሣይህ ካሳው (ዶ/ር) ፣ከምስ/ጎጃም ዞንና ደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ ከሀይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከታዋቂ ሰዎችና ከንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።
መረጃው የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ነው
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 5 162 |
| 7 | No text... | 5 423 |
| 8 | የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በሊቦከምከም ወረዳ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በኾነ በጀት የትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመረ።
።።።።።
የፌዴራል ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦከምከም ወረዳ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
በሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የፌደራል ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ.ር) ፣ ምክትል ዳይሬክተሩ ተፈራ ፈይሳ እና ምክትል ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወንድማገኝ ጨምሮ የአገልግሎቱ ከፍተኛ ሥራ አሥፈጻሚዎች፣ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኀላፊዎች እና የደቡብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የፌዴራል ተቋማት ወደ ክልሎች ወርደው በዜጎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማኅበረሰቡ ድጋፍ እንዲያደርጉ ባወረዱት አቅጣጫ መሠረት የሚገነባ መኾኑ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ(ዶ/ር)ገልፀዋል።
የሚገነባው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በኾነ በጀት እንደሚገነባ ዶ/ር እሸቱ ገልፀዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በወረዳው ለአላቦ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ500 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው አንድ ደርዘን ደብተር፣ ፖርሳ፣ እስክርቢቶ እና ሌሎች የትምህርት ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል።
በተጨማሪም የሥራ ኀላፊዎቹ በወረዳው ችግኝ ተክለዋል።
ለትምህርት ቁሳቁስ ድጋፉ ከ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ማድረጉን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ.ር) ተናግረዋል።
#ትምህርት #አማራክልል_ኢትዮጵያ
#ባሕር_ዳር #ነሐሴ_29_2018_ዓ_ም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ | 8 129 |
| 9 | No text... | 7 834 |
| 10 | ማስታወቂያ
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር | 9 957 |
| 11 | No text... | 9 735 |
| 12 | "በክልሉ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምድ እያደገ ነው" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ የበለጸጉ እና በሥራ ላይ የሚገኙ ችግር ፈች የኾኑ ሲስተሞችን በአውደ ርዕይ ለጎብኝዎች ክፍት አድርጓል።
ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አውደ ርዕዩን አሥጀምረዋል። የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎችም ተገኝተዋል።
በአውደ ርዕዩ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ መልዕክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበትም የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ የተገኙት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ መንግሥት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ቴክኖሎጂን እንደ አካታች ሀገራዊ ብልጽግና፤ ዘላቂ ልማት እና ለብቁ ሀገራዊ ተወዳዳሪነት ቁልፍ መሠረት አድርጎ እየሠራበት ነው ብለዋል።
በኢኮኖሚ ዕድገት፤ ምርታማነትን በማሳደግ፤ በመንግሥት አገልግሎት ቅልጥፍናን በማሻሻል፤ የዜጎች ተሳትፎን በማሳደግ፤ የዲጂታል ክህሎትን በማጠናከር ግብ አድርጎ በትኩረት እየሠራ እንደኾነ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ለውጭ ኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አንስተዋል።
በአማራ ክልል "ዲጂታል አማራ" በሚል በ25 ዓመቱ የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ ላይ ቴክኖሎጅ እንደ ልማት መዳረሻ መፍጠሪያ ተደርጎ ተይዟል ነው ያሉት።
በ25 ዓመቱ ስትራቴጅክ ግብ ላይ በ2042 የአማራ ክልል ዋነኛ ሀብት፤ የአገልግሎት መስጫ እና የኢኮኖሚ የዕድገት ምንጭ ቴክኖሎጂ እንዲኾን ይሠራል ነው ያሉት።
በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት ቴክኖሎጂን የመጠቀም፤ የማላመድ እና የመሥራት ልምምዳቸውን እንዲያጠናክሩም እየተሠራ ነው ብለዋል።
በክልሉ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምድ ዕድገት እያሳየ መጥቷልም ነው ያሉት። የክልሉ መንግሥት ቴክኖሎጂን በስፋት ለመጠቀም በትኩረት እየሠራ ነውም ብለዋል።
ቴክኖሎጂን በመጠቀም ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ እና ዜጎች በአገልግሎት ደስተኛ እንዲኾኑ እየተሠራ እንደኾነም ጠቁመዋል።
የአማራ ክልል የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ ምክትል ኀላፊ የቻለ ይግዛው የመርሐ ግብሩ ዓላማ በአማራ ክልል የለሙ የዲጂታል መፍትሔዎችን በጋራ ለመመረቅ እና ወደ ሥራ ለማስገባት ነው ብለዋል።
በርካታ የለሙ ሲስተሞች ወደ ሥራ መግባታቸውንም ገልጸዋል። ሌሎች የለሙ ሲስተሞችም ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተናግረዋል።
አውደ ርዕዩ የመንግሥት የአሠራር ሥርዓት ዲጂታላይዝድ እንዲኾን ለማፋጠን እና ዲጂታል 2030ን እውን ለማድረግ ያለመ ነውም ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ከ35 በላይ ዲጂታል መፍትሔዎች ለምተው ለተቋማት እና ለኅብረተሰቡ ክፍት መኾናቸውንም ገልጸዋል።
አውደ ርዕዩ አገልግሎት ሰጭው እና አገልግሎት ተጠቃሚው ስለ ዲጂታል መፍትሔዎች አውቆ እንዲጠቀም ለማድረግ እንደሚያስችልም ነው ያነሱት።
የለሙ ሲስተሞች ለአገልግሎት ክፍት መኾናቸውንም ገልጸዋል።
Amhara Communications
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 8 069 |
| 13 | No text... | 7 760 |
| 14 | "በእጃችሁ የያዛችሁት ስማርት ስልክ የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት ነው" በለጠ ሞላ (ዶ.ር)
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ መልዕክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት የፓናል ውይይት አካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር) ኢትዮጵያ ዲጂታል 2025 ስትራቴጅን ተግባራዊ በማድረግ የሕዝብ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ያደረገችው ርብርብ ተጨባጭ ፍሬን አፍርቷል ብለዋል።
የመንግሥት ተቋማት ከወረቀት አሠራር ወጥተው ወደ ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር እየተሸጋገሩ መኾኑንም ተናግረዋል። ከ49 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት በመኾን፤ ዜጎች በቴሌ ብር እና በባንኮች በዲጂታል መድረኮች በመገበያየት እና በመሶብ አገልግሎት ፈጣን ተጠቃሚ ኾነዋል ነው ያሉት።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን እውን ለማድረግ ወደ ሥራ ተገብቷልም ብለዋል። ተደራሽነትን ማስፋት፤ ለሁሉም ዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፤ በዜጎች እና በተቋማት መካከል እምነትን ማጠናከር የዲጂታል 2030 የትኩረት አካል መኾናቸውን ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ ያዘጋጀው አውደ ርዕይ የተቋማትን የዲጂታል ግንዛቤ ለማሳደግ፤ የፈጠራ ሥራዎችን ለሕዝብ ለማስተዋወቅ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የሚያግዝ ነው ብለዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የመንግሥት አጀንዳ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ ሕዝብ እና መንግሥት የሚገናኙበት እውነተኛ መንገድ መኾኑን ተናግረዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማትን ማግኘት ቅንጦት አይደለምም ብለዋል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለሁሉም ተጠቃሚዎች በእኩልነት የሚያገለግል አድሎ አልባ ድልድይ መኾኑንም አንስተዋል።
ወጣቶች በእጃችሁ የያዛችሁት ስማርት ስልክ መዝናኛ ብቻ ሳይኾን የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት በመኾኑ በአግባቡ ልትጠቀሙበት ይገባል ነው ያሉት። የሚመጣው የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዘመን የሚፈልገው ወጣቶችን በመኾኑ ራሳችሁን ከአዲሱ ቴክኖሎጂ ጋር ልታላምዱ ይገባል ብለዋል።
ቴክኖሎጂ መንግሥት ሠራተኛኞችን ለፈጠራ እና ለውሳኔ ሰጭነት የሚያበቃ በመኾኑ ቴክኖሎጂን መታጠቅ እና መላመድ ይገባል ብለዋል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ከዳር ለማድረስ በተቋማት መካከል ያሉ የዲጂታል መረጃ ቋቶች እርስ በዕርስ የሚናበቡበት እና በሕግ መሠረት መረጃ የሚለዋወጡበት ሀገራዊ ማዕቀፍ ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ትኩረታችንን በፈጠራ እና በግንባታ ላይ በማድረግ ልጆቻችን የሚኮሩባት ሀገር እንገነባለን ብለዋል።
#አሚኮ #ቴክኖሎጂ #ኢትዮጵያ
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 7 742 |
| 15 | "የአንድ ተማሪ ህይወት የሙሉ ቤተሰብ ህይወት ነው"
ዶ/ር መሉነሽ ደሴ
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ | 9 928 |
| 16 | No text... | 9 938 |
| 17 | No text... | 8 976 |
| 18 | "ጠንካራ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት በማበረታታት ክፍተት ያለባቸውን በመደገፍ ወደ ተቀራራቢ አፈጻጸም እንዲመጡ እየተሰራ ነው።" ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ።
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እየገመገመ ነው።
በግምገማ መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በክልሉ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ጉልህ ተግባራት መከወናቸውን ተናግረዋል።
የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እየተከናወኑ ያሉ ቅንጅታዊ ተግባራት በሱፐርቪዥን ቡድን የድጋፍ እና ክትትል ስራዎች መከናወኑን ገልጸዋል።
ድጋፍና ክትትሉ በትምህርት፣ በጤና ፣ በሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ በሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መካሄዱ ተገልጿል።
በተደረገው ድጋፍ እና ክትትል በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እና በመንግስት የታቀዱ ኢኒሸቲቮች በመልካም አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ አመላክተዋል።
የክላስተሩ ተቋማት በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ቤት የሚደርሱ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊዋ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል እየሰሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ ተቋማት እርስ በእርስ ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡ እንዲማማሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን እንዲያሳድጉ ተከታታይ ድጋፎች ይደረጋሉ ብለዋል።
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
| 10 257 |
| 19 | የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች‼️
=========
ነሐሴ 24/2018(ትምህርት ቢሮ)በአማራ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 15.56%ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸው ይታወቃል። ከተመዘገበው ውጤት በተጨማሪ የባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሁለት መንትዮች ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸው አስደናቂ ክስተት ሆኗል። ተማሪ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ የሚባሉ መንትዮች በባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ሁለቱም ተመሳሳይ 413 ከ600 ውጤት ማስመዝገባቸው ብዙዎችን አስገርሟል።
በዚህ ዙሪያ የዘርፉ የስነልቦና ባለሙያዎች አስተያየት ስጡበት‼️
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 14 093 |
| 20 | No text... | 12 552 |
