Amhara Education Bureau
📈 Análisis del canal de Telegram Amhara Education Bureau
El canal Amhara Education Bureau (@anrse) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 39 400 suscriptores, ocupando la posición 4 645 en la categoría Educación y el puesto 876 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 39 400 suscriptores.
Según los últimos datos del 05 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 742, y en las últimas 24 horas de 3, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 37.24%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 14.77% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 14 672 visualizaciones. En el primer día suele acumular 5 820 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 26.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“Quality Education”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 06 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 05 septiembre | +4 | |||
| 04 septiembre | +2 | |||
| 03 septiembre | 0 | |||
| 02 septiembre | +7 | |||
| 01 septiembre | +42 |
| 2 | Sin texto... | 5 600 |
| 3 | ማስታወቂያ
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር | 8 440 |
| 4 | Sin texto... | 7 691 |
| 5 | "በክልሉ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምድ እያደገ ነው" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ የበለጸጉ እና በሥራ ላይ የሚገኙ ችግር ፈች የኾኑ ሲስተሞችን በአውደ ርዕይ ለጎብኝዎች ክፍት አድርጓል።
ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አውደ ርዕዩን አሥጀምረዋል። የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎችም ተገኝተዋል።
በአውደ ርዕዩ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ መልዕክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበትም የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ የተገኙት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ መንግሥት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ቴክኖሎጂን እንደ አካታች ሀገራዊ ብልጽግና፤ ዘላቂ ልማት እና ለብቁ ሀገራዊ ተወዳዳሪነት ቁልፍ መሠረት አድርጎ እየሠራበት ነው ብለዋል።
በኢኮኖሚ ዕድገት፤ ምርታማነትን በማሳደግ፤ በመንግሥት አገልግሎት ቅልጥፍናን በማሻሻል፤ የዜጎች ተሳትፎን በማሳደግ፤ የዲጂታል ክህሎትን በማጠናከር ግብ አድርጎ በትኩረት እየሠራ እንደኾነ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ለውጭ ኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አንስተዋል።
በአማራ ክልል "ዲጂታል አማራ" በሚል በ25 ዓመቱ የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ ላይ ቴክኖሎጅ እንደ ልማት መዳረሻ መፍጠሪያ ተደርጎ ተይዟል ነው ያሉት።
በ25 ዓመቱ ስትራቴጅክ ግብ ላይ በ2042 የአማራ ክልል ዋነኛ ሀብት፤ የአገልግሎት መስጫ እና የኢኮኖሚ የዕድገት ምንጭ ቴክኖሎጂ እንዲኾን ይሠራል ነው ያሉት።
በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት ቴክኖሎጂን የመጠቀም፤ የማላመድ እና የመሥራት ልምምዳቸውን እንዲያጠናክሩም እየተሠራ ነው ብለዋል።
በክልሉ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምድ ዕድገት እያሳየ መጥቷልም ነው ያሉት። የክልሉ መንግሥት ቴክኖሎጂን በስፋት ለመጠቀም በትኩረት እየሠራ ነውም ብለዋል።
ቴክኖሎጂን በመጠቀም ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ እና ዜጎች በአገልግሎት ደስተኛ እንዲኾኑ እየተሠራ እንደኾነም ጠቁመዋል።
የአማራ ክልል የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ ምክትል ኀላፊ የቻለ ይግዛው የመርሐ ግብሩ ዓላማ በአማራ ክልል የለሙ የዲጂታል መፍትሔዎችን በጋራ ለመመረቅ እና ወደ ሥራ ለማስገባት ነው ብለዋል።
በርካታ የለሙ ሲስተሞች ወደ ሥራ መግባታቸውንም ገልጸዋል። ሌሎች የለሙ ሲስተሞችም ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተናግረዋል።
አውደ ርዕዩ የመንግሥት የአሠራር ሥርዓት ዲጂታላይዝድ እንዲኾን ለማፋጠን እና ዲጂታል 2030ን እውን ለማድረግ ያለመ ነውም ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ከ35 በላይ ዲጂታል መፍትሔዎች ለምተው ለተቋማት እና ለኅብረተሰቡ ክፍት መኾናቸውንም ገልጸዋል።
አውደ ርዕዩ አገልግሎት ሰጭው እና አገልግሎት ተጠቃሚው ስለ ዲጂታል መፍትሔዎች አውቆ እንዲጠቀም ለማድረግ እንደሚያስችልም ነው ያነሱት።
የለሙ ሲስተሞች ለአገልግሎት ክፍት መኾናቸውንም ገልጸዋል።
Amhara Communications
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 6 976 |
| 6 | Sin texto... | 6 623 |
| 7 | "በእጃችሁ የያዛችሁት ስማርት ስልክ የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት ነው" በለጠ ሞላ (ዶ.ር)
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ መልዕክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት የፓናል ውይይት አካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር) ኢትዮጵያ ዲጂታል 2025 ስትራቴጅን ተግባራዊ በማድረግ የሕዝብ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ያደረገችው ርብርብ ተጨባጭ ፍሬን አፍርቷል ብለዋል።
የመንግሥት ተቋማት ከወረቀት አሠራር ወጥተው ወደ ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር እየተሸጋገሩ መኾኑንም ተናግረዋል። ከ49 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት በመኾን፤ ዜጎች በቴሌ ብር እና በባንኮች በዲጂታል መድረኮች በመገበያየት እና በመሶብ አገልግሎት ፈጣን ተጠቃሚ ኾነዋል ነው ያሉት።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን እውን ለማድረግ ወደ ሥራ ተገብቷልም ብለዋል። ተደራሽነትን ማስፋት፤ ለሁሉም ዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፤ በዜጎች እና በተቋማት መካከል እምነትን ማጠናከር የዲጂታል 2030 የትኩረት አካል መኾናቸውን ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ ያዘጋጀው አውደ ርዕይ የተቋማትን የዲጂታል ግንዛቤ ለማሳደግ፤ የፈጠራ ሥራዎችን ለሕዝብ ለማስተዋወቅ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የሚያግዝ ነው ብለዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የመንግሥት አጀንዳ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ ሕዝብ እና መንግሥት የሚገናኙበት እውነተኛ መንገድ መኾኑን ተናግረዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማትን ማግኘት ቅንጦት አይደለምም ብለዋል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለሁሉም ተጠቃሚዎች በእኩልነት የሚያገለግል አድሎ አልባ ድልድይ መኾኑንም አንስተዋል።
ወጣቶች በእጃችሁ የያዛችሁት ስማርት ስልክ መዝናኛ ብቻ ሳይኾን የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት በመኾኑ በአግባቡ ልትጠቀሙበት ይገባል ነው ያሉት። የሚመጣው የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዘመን የሚፈልገው ወጣቶችን በመኾኑ ራሳችሁን ከአዲሱ ቴክኖሎጂ ጋር ልታላምዱ ይገባል ብለዋል።
ቴክኖሎጂ መንግሥት ሠራተኛኞችን ለፈጠራ እና ለውሳኔ ሰጭነት የሚያበቃ በመኾኑ ቴክኖሎጂን መታጠቅ እና መላመድ ይገባል ብለዋል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ከዳር ለማድረስ በተቋማት መካከል ያሉ የዲጂታል መረጃ ቋቶች እርስ በዕርስ የሚናበቡበት እና በሕግ መሠረት መረጃ የሚለዋወጡበት ሀገራዊ ማዕቀፍ ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ትኩረታችንን በፈጠራ እና በግንባታ ላይ በማድረግ ልጆቻችን የሚኮሩባት ሀገር እንገነባለን ብለዋል።
#አሚኮ #ቴክኖሎጂ #ኢትዮጵያ
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 6 773 |
| 8 | "የአንድ ተማሪ ህይወት የሙሉ ቤተሰብ ህይወት ነው"
ዶ/ር መሉነሽ ደሴ
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ | 8 934 |
| 9 | Sin texto... | 9 031 |
| 10 | Sin texto... | 8 076 |
| 11 | "ጠንካራ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት በማበረታታት ክፍተት ያለባቸውን በመደገፍ ወደ ተቀራራቢ አፈጻጸም እንዲመጡ እየተሰራ ነው።" ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ።
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እየገመገመ ነው።
በግምገማ መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በክልሉ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ጉልህ ተግባራት መከወናቸውን ተናግረዋል።
የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እየተከናወኑ ያሉ ቅንጅታዊ ተግባራት በሱፐርቪዥን ቡድን የድጋፍ እና ክትትል ስራዎች መከናወኑን ገልጸዋል።
ድጋፍና ክትትሉ በትምህርት፣ በጤና ፣ በሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ በሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መካሄዱ ተገልጿል።
በተደረገው ድጋፍ እና ክትትል በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እና በመንግስት የታቀዱ ኢኒሸቲቮች በመልካም አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ አመላክተዋል።
የክላስተሩ ተቋማት በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ቤት የሚደርሱ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊዋ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል እየሰሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ ተቋማት እርስ በእርስ ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡ እንዲማማሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን እንዲያሳድጉ ተከታታይ ድጋፎች ይደረጋሉ ብለዋል።
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
| 9 139 |
| 12 | የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች‼️
=========
ነሐሴ 24/2018(ትምህርት ቢሮ)በአማራ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 15.56%ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸው ይታወቃል። ከተመዘገበው ውጤት በተጨማሪ የባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሁለት መንትዮች ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸው አስደናቂ ክስተት ሆኗል። ተማሪ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ የሚባሉ መንትዮች በባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ሁለቱም ተመሳሳይ 413 ከ600 ውጤት ማስመዝገባቸው ብዙዎችን አስገርሟል።
በዚህ ዙሪያ የዘርፉ የስነልቦና ባለሙያዎች አስተያየት ስጡበት‼️
#AmharaEducation
#ትምህርትለትውልድ
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau
📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau | 13 317 |
| 13 | Sin texto... | 12 026 |
| 14 | Sin texto... | 16 557 |
| 15 | ከ88 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቆ ርክክብ ተካሄደ ።
በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ በከተማና መሰረተ መሰረተልማት ሚኒስቴር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ኘሮጀክት ከ88 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቆ የዞኑ የስራ ኀላፊዎች በተገኙበት ርክክብ ተካሂዷል።
የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ሰጠ ታደሰ እንዳሉት፣
ትምህርት ቤቱ ሁለት መማሪያ ክፍሎችን ጨምሮ ዘጠኝ ብሎኮች አሉት ። በሁለት ፈረቃ እስከ አንድ ሺህ ተማሪዎችን ለማስተማር እንደሚያስችልም ገልፀዋል። ትምህርት ቤቱ በጃራ የስደተኞች ካምኘ ላሉ ታዳጊዎች መጋቢ ሆኖ ያገለግላልም ብለዋል።
በርክክብ ሂደቱ ላይ የተገኙት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ፣ የሰሜን ወሎ ዞንን የትምህርት ሽፋን ከፍ ለማድረግና የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ቀደም ሲል ከተማ አስተዳደሩ በጉባላፍቶ ወረዳ ሁለት ትምህርት ቤቶችን ገንብቶ ለዞኑ አስተዳደር ማስረከቡን አስታውሰዋል።
የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተፈናቃይ ወገኖች መጋቢ በመሆኑ ከተማ አስተዳደሩ በግንባታው ሂደት የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷልም ነው ያሉት። ህብረተሰቡ ትምህርት ቤቱን እንዲጠብቅና እንዲንከባከብም አሳስበዋል።
የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ ታምራት ንጋቱ በበኩላቸው፣ ትምህርት ቤቱ ደረጃውን ጠብቆ ተገንብቶ መረከባቸውን አውስተዋል። ለ2019 የትምህርት ዘመን ማስጀመሪያ በቂ ግበዓት መኖሩን ጠቅሰው፣ ተጨማሪ የትምህርት ቁሳቁስ ለማሟላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ዞን አስተዳደሩ መክሮ የመማሪያ ወንበር፣ ጥቁር ሰሌዳ፣ የቤተሙከራ፣ የቤተመጻህፍትና የአይሲቲ ማዕከሉን ሙሉ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል።
የአካባቢው ሀገር ሽማግሌ ሸህ ሀሰን ከረሙ የትምህርት ቤቱ መገንባት የአካባቢው ወጣቶች አመለካከት በመለወጥ የህገወጥ ስደት ሰለባ ከመሆን ይታደጋል ሲሉ አስተያየታቸውን ለአሚኮ ተሰጥተዋል።
አሚኮ
#ደሴ #አሚኮ #ዜና #ሰሜን_ወሎ #ትምህርት #ወልድያ | 13 572 |
| 16 | Sin texto... | 14 552 |
| 17 | Sin texto... | 11 564 |
| 18 | ዓባይ ባንክ በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት መማር ለሚቸገሩ ተማሪዎች 50 ሺህ የመማሪያ ደብተሮችን ድጋፍ አደረገ።
ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ ዓባይ ባንክ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እና የትምህርት ዘርፉን ከማሳደግ አኳያ በኢኮኖሚ ጫና ምክንያት ለልጆቻቸው የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ለማይችሉ ወላጆች እና ልጆች ከትምሕርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የሚያግዝ የ50,000 ባለ50 ገጽ ደብተሮችን ለአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስረክቧል፡፡
ድጋፉ በክልሉ በተለያየ ምክንያት ትምህርታቸውን መከታተል እየፈለጉ በቁሳቁስ ዕጥረት ለተቸገሩ ተማሪዎች በፍትሐዊነት ለሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የሚሰራጭ ነው።
የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፉ በአማራ ክልል መማር እየፈለጉ በአቅም ማነስ እና በሌሎች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ምክንያት እገዛ ማግኘት ላልቻሉ ተማሪዋች በባንኩ መለያ በልዩ ህትመት የተዘጋጁ ደብተሮች ናቸው።
ርክክቡ ዛሬ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በባሕርዳር ከተማ ሲካሄድ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት አደመ ባደረጉት ንግግር፣ “የክልሉን የትምሕርት ስትራቴጂ ከማሳካት አኳያ እንደ ዓባይ ባንክ ያሉ አጋሮች የተቀናጀ ኢንቨስትመንት ከማካሄድ ባሻገር የማኅበራዊ ልማት ላይ በንቃት መሳተፍ ድርሻው ከፍ ያለ ነው” ብለዋል።
ሀገራዊ የትምህርት ዘርፋን ለማሳደግ እና የተማሪዎችን ውጤታማነት ከፍ ለማድረግ ከሚደረገው እንቅስቃሴ ጎን ለጎን እንደ ዓባይ ባንክ ያሉ ቀዳሚ የልማት እና የፋይናንስ አጋሮች የሚያደርጉት ድጋፍ ለሌሎችም ምሣሌ የሚሆን ነው ተብሏል።
ኃላፊው በክልሉ የትምህርት ዘርፍ የመሠረተ-ልማት እና የግብዓት እጥረቶችን ለመፍታት በሚያደርገው ጥረት የፋይናንስ ተቋማት እገዛ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፣ የዓባይ ባንክ የመማሪያ ደብተር ድጋፍም በከልሉ የተማሪዎችን የማቋረጥ ምጣኔን ለመቀነስ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ ዐቅም ይኖረዋል ብለዋል። ድጋፋ በትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ወደ ትምህርት ገበታ መሄድ ያልቻሉ የክልሉ ተማሪዋችን ችግር ለመቅረፍ እና “በዚህ ችግር ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልመጡ ተማሪዋችን ተስፋ የሚያለመልም ነው” በማለት ምስጋናቸውን ለባንኩ አቅርበዋል፡፡
የዓባይ ባንክ ስትራቴጂ ዋና መኮንን አቶ ወንድይፍራው ታደሰ ባንኩ የማኅበራዊ ልማት ዘርፉን ከማሳደግ አኳያ እያከናወነ ያለውን ድጋፍ አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል። ዓባይ ባንክ “በእያንዳንዱ የማኅበረሰብ ጎጆ ገብቶ ቀዳሚ የፋይናንስ አጋር የመሆን ፍኖት እና በቀጣዩ ትውልድ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ዕውቀት-መር የኢንቨስትመንት አስተሳሰብ መገንባት” እየተተገበረ ያለ አቅጣጫ መሆኑን አሳውቀዋል። ባንኩ በተለያዩ ዘርፍች ማኅበረሰቡን የሚጠቅሙ እና የማህበራዊ ኃለፊነት የመወጣት ዕቅዱ አካል የሆኑ ድጋፎችን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለሚገኙ ተቋማት እና ዜጎች ሲያደርግ መቆየቱንም አውስተዋል።
ዓባይ ባንክ በፋይናንሱ ዘርፍ ለብዙዎች የታላቅነት ምንጭ ከመሆን ባሻገር የኮርፖሬት ማኅበራዊ ኃላፊነትን እንደ ቁልፍ ስትራቴጂያዊ የማኅበረሰብ አጋርነት እና ተቋማዊ ትሥሥር ዓላማ የሚያውል መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ዓባይ ባንክ አሁን ላይ ካደረገው የትምህርት ግብዓት ድጋፍ ባሻገር በጥቅል የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ከ4.8 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ደንበኞቹ ሰፊ የዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች በማቅረብ ግንባር ቀደም የፋይናንስ አጋር በመሆን እየሠራ መሆኑ ተጠቅሷል።
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
| 12 160 |
| 19 | Sin texto... | 17 255 |
| 20 | ከ54 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት የመለሰው የበጎ ፈቃድ ሥራ።
በደቡብ ጎንደር ዞን በተካሄደው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ51 ሺህ በላይ ዜጎች በማዕድ ማጋራት ተጠቃሚ ኾነዋል። "ለአንድ ተማሪ አንድ ደርዘን ደብተር" በሚል መሪ መልዕክትም ከ54 ሺህ በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል።
የደቡብ ጎንደር ዞን ሴቶች፣ ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ አንጓች ፋሲካው እንደገለጹት ይህ ስኬት በዞኑ በሚገኙ መምሪያዎች እና ተጠሪ ጽሕፈት ቤቶች የጋራ ርብርብ የተገኘ ነው። የበጎ ፈቃድ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ መንበር ክፈተው ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች ቀድሞ መድረስ ለትውልድ የሚተርፍ ተግባር መኾኑን ጠቅሰዋል።
የማኅበራዊ አገልግሎት ሥራዎችም በደም ልገሳ እና በቤት እድሳት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው የጠቆሙት።
በተደረገው ድጋፍ ከተጠቀሙ ወገኖች መካከል የሦሥት ልጆች እናት ወይዘሮ ደማም ተሾመ የተደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ልጆቻቸውን ከጎዳና ሕይወት ታድጎ በነጻነት እንዲማሩ ማድረጉን ገልጸዋል።
የ7ኛ ክፍል ተማሪዋ ዳሳሽ ምሥጋናው የተደረገላት ድጋፍ ከጓደኞቿ ጋር እኩል እንድትሰለፍ የሞራል ስንቅ እንደኾናት እና ጠንክራ በመማር ዶክተር የመኾን ራዕይ እንድትሰንቅ እንዳስቻላት ተናግራለች።
ነሐሴ 18/2018
አሚኮ | 14 555 |
