en
Feedback
Abu Imran Muhammed Mekonn

Abu Imran Muhammed Mekonn

Open in Telegram

ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ 👉 ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ◎ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Abu Imran Muhammed Mekonn

Channel Abu Imran Muhammed Mekonn (@abuimranaselefy) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 23 910 subscribers, ranking 3 135 in the Religion & Spirituality category and 1 439 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 23 910 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -252 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.05%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 4.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 798 views. Within the first day, a publication typically gains 1 048 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ 👉 ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ◎ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

23 910
Subscribers
-1224 hours
-1277 days
-25230 days
Posts Archive
አዲሰ ወሳኝ ሙሐደራ ርዕስ « የዒልም (እውቀት) መጀመሪያው ቁርኣን ነው» 🎙ሸይኽ ዐብዱልሐሚድ ያሲን አልለተሚይ ሐፊዘሁላህ 🕌 ጉንችሬ ከዕብ መስጂድ (ዳሩል ሂጅራ መርከዝ) 🗓 ቅዳሜ ነሐሴ /30/2018 ምሽት ከመግሪብ እስከ ዒሻእ የቴሌግራም ቻናል https://t.me/medresetulislah

አጠር ያለች ወሳኝ ምክር 👌ለምን ቅድሚያ ለተውሒድ እንላለን? ✅ ስለፊዮች ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ ስለሚሰጡ እንጅ ትምህርታቸው ረድ ብቻ አይደለም። ✅ ወደ ተውሒድ መጣራት ፣ ከሺርክ ማስጠንቀቅ የነቢያት፣ የሰሐቦችና የሰለፎች መንገድ ነው፡፡ 🚫 በዙሪያችን ያሉ ቤተሰቦቻችንና ዘመዶቻችን በሽርክና ቢድዓ ላይ ተዘፍቀው እያለ ተውሒድን አለማስተማርና ከሺርክ አለማስጠንቀቅ ከባድ ግፍ ነው:: 📆 ቅዳሜ ነሐሴ 30 2018 ከመግሪብ በኋላ ጉንችሬ ከዕብ መስጂድ ላይ የተደረገ ሙሐደራ 🎤 ኡስታዝ በሕሩ ተካ ሐፊዘሁላህ https://t.me/medresetulislah

አጠር ያለች ወሳኝ ምክር 👌ሰላምታ የአማኞች የውዴታ መገለጫ ✅ የሙስሊሞች ሰላምታ <<አስስላሙዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ >> ውስጥ ያሉ ከንዞች ✅ አማኞች ሲገናኙ እርስ በእርሳቸው ሰላምታን ማብዛት የመዋደድ ሰበብ ነው፡፡ 🚫 ሙብተዲዕን ሰላም ያለ ይወደዋል ማለት ነው:: ⏰ ቅዳሜ ነሐሴ 30 2018 ከመግሪብ በኋላ ጉንችሬ ከዕብ መስጂድ ላይ የተደረገ ሙሐደራ 🎤 ኡስታዝ አቡ ሐመዊያ ሸምሱ ጉልታ ሐፊዘሁላህ https://t.me/medresetulislah

👉 አዲስ pdf عنوان:- الفصل المبين في دحض شبهات وتلبيسات محمد حامي الدين. ርእስ:- ግልፅ የሆነ መለያ፣ የሙሀመድ ሃሚዲንን ብዥታና ማምታቻ በማጋለጥ ላይ… 📝 بقلم الشيخ الدكتور حسين بن محمد بن عبد الله الإثيوبي السلطي حفظه الله 📝 አዘጋጅ፦ ሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን ቢን ሙሀመድ ቢን ዐብደላህ አል-ኢትዮጲ አስ-ሲልጢይ (ሀፊዘሁላህ) (ዐረቢኛ የምትችሉ pdf  አውርዳችሁ አንብቡት) #join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://t.me/HussinAssilty https://t.me/HussinAssilty

ወሳኝ የጁሙዓህ ኹጥባ (ምክር)
ርዕስ :-"ጠንቋዮች (የሩቁን እናውቃለን ባዮች) እና አደጋወቻቸው "
🎙ሸይኽ አቡ ዘር ሐሰን ኮምቦልቻ    -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በ ኮምቦልቻ ከተማ ሰላም መስጂድ 🗓 ነሐሴ /𝟐𝟗/ 𝟐𝟎𝟏𝟖                                     ይደመጥ ! https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha

✅ታላቅ የምስራች ለሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ السلام عليكم ورحمة الله وبركاته በመጀመሪያ ለዐለማቱ ጌታ አላህ ምስጋና ይገባው! በመቀጠልም ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረሳዎች ሲቀሩ
ታላቅ የምስራች ለሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ السلام عليكم ورحمة الله وبركاته በመጀመሪያ ለዐለማቱ ጌታ አላህ ምስጋና ይገባው! በመቀጠልም ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረሳዎች ሲቀሩ የነበሩት ደርሶችና ተጨማሪ አዳዲስ ኪታቦች በአድስ መልኩ ቅዳሜ(ነሀሴ-30) ጀምሮ የሚሰጡ ይሆናል። ጊዜያችንን አመቻችተን በሚቀርበን ቦታ በመገኘት ድናችንን እንገንዘብ! የአላህ መልዕክተኛ ሲናገሩ፦ من يريد الله به خيرا يفقهه في الدين "አሏህ መልካም የሻለት ሰው ድኑን ያስገነዝበዋል" الجهل عار عار لا يرضى به إلا حمار ማሳሰቢያ ✅ደርሶቹ የሚሰጡበት ጊዜ👉 ከመጝሪብ-ዒሻ ✅ የሚሰጡበት ቦታ 👉 ዳቶ ፣ ቲቲሲና ተማሪዎች መድረሳ ✅ደርሱን የሚሰጡት፦ ↪️ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ደሴ ↪️ኡስታዝ ዐብዱልሀሚድ 👉👉👉ዝርዝር ፕሮግራሙን በፎቶው ላይ ተመልከቱ! ከሱብሂ በኋላ እንድሁም በቀኑ ክፍል የሚወጡ ፕሮግራሞችን የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ለሌሎች ሰዎች በማድረስ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!! 🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈 https://t.me/hutemariwochchannel

👉 ሙሐመድ ሓሚዲን የሰይድ ቁጥብ ጠበቃ ! — የሶሓቦች ደረጃ በነብዩ ሙሐመድ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – ምስክርነት ! አላህ ከሰዎች ነብያቶችን መርጦ ወደ ሰው ልጆች በቃሉ ላካቸው ። በዚህም ነብያቶች በአላህና በሰው ልጆች መካከል አገናኝ ሆኑ ። ከተቀሩት ሰዎች መርጦ ደግሞ ለነብያቶች ሀዋሪያት አደረገ ። የነብዩ ሙሐመድ ባልደረቦች (ሶሓቦች) አላህ ለነብዩ ረዳትነት የመረጣቸው ምርጥ ትውልዶች ነበሩ ። የነብዩን መልእክት ባለበት ተጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ውድ ሕይወታቸውን ፣ ክብራቸውን ፣ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ቤዛ አድርገዋል ። ለዚህ ዲን ሲሉ አንገታቸው ተቀልቷል ፣ ገላቸው ተከታትፏል ። አጥታቸው ተሰብሯል ። በደማቸው የነብዩ ሸሪዓ ለምልሞ ለዓለም ደርሷል ። የአላህ መልእክተኛ ስለነዚህ ባልደረቦቻቸው ከተናገሯቸውና የሰደባቸውንና ክብራቸውን የነካን ምን እንዳሉ በሚቀጥሉት ሐዲሶች እንመልከት : – عن أبي سعيد رضي الله عنه قال : قال رسول الله – صلى الله عليه وآله وسلم –: «لَا تَسُبُّوا أَحَدًا مِنْ أَصْحَابِي، فَإِنَّ أَحَدَكُمْ لَوْ أَنْفَقَ مِثْلَ أُحُدٍ ذَهَبًا، مَا أَدْرَكَ مُدَّ أَحَدِهِمْ وَلَا نَصِيفَهُ» أخرجه البخاري ومسلم . " ከሶሓቦቼ አንዱንም አትሳደቡ ከናንተ ውስጥ አንዳችሁ የኡሑድ ተራራን የሚያክል ወርቅ በአላህ መንገድ ላይ ወጪ ቢያደርግ (የሶሓቦቼን) የአንዳቸውን እፍኝ ወይም ግማሹ አይደርስም " ። عن عائشة أم المؤمنين قالت: قال رسول الله – صلى الله عليه وآله وسلم –: «مَنْ سَبَّ أَصْحَابِي فَعَلَيْهِ لَعْنَةُ اللهِ وَالْمَلَائِكَةِ، وَالنَّاسِ أَجْمَعِينَ» . وقد رواه الإمام أحمد في "مسنده"، والإمام الترمذي وقال: حسن غريب، " ሶሓቦቼን የተሳደበ በሱ ላይ የአላህ የመላኢካዎችና የሰዎችም ባጠቃላይ እርግማን ይውረድ "። عن عبد الله بن مغفل – رضي الله عنه– قال : قال رسول الله – صلى الله عليه وآله وسلم–: «اللهَ اللهَ فِى أَصْحَابِي، اللهَ اللهَ فِى أَصْحَابِي، لَا تَتَّخِذُوهُمْ غَرَضًا بَعْدِي، فَمَنْ أَحَبَّهُمْ فَبِحُبِّي أَحَبَّهُمْ، وَمَنْ أَبْغَضَهُمْ فَبِبُغْضِي أَبْغَضَهُمْ، وَمَنْ آذَاهُمْ فَقَدْ آذَانِي، وَمَنْ آذَانِي فَقَدْ آذَى اللهَ، وَمَنْ آذَى اللهَ فَيُوشِكُ أَنْ يَأْخُذَهُ». " በሶሓቦቼ ጉዳይ አላህን ፍሩ, (እኔ ከሞትኩ በኋላ) ክብራቸውን በመንካትና በመስደብ አዛ በማድረግ ኢላማ አድርጋችሁ አትያዟቸው ( በመጥፎ ነገር ወደነርሱ አታነጣጥሩ) እነርሱን የወደደ እኔን ለመውደዱ ነው የወደዳቸው ። እነርሱን የጠላቸው እኔን ለመጥላቱ ነው የጠላቸው ። እነርሱን አዛ ያደረገ እኔን አዛ አደረገ ! እኔን አዛ ያደረገ አላህን አዛ አደረገ ! አላህን አዛ ያደረገ ሊዘው ይቀርባል " ። ጮሌ በምልክት ይገባዋል እንደሚሉት የነብዩና የሶሓቦች ወዳጆች ሶሓቦችን ለመውደድና ለማክበር አንድ የቁርኣን አንቀፅ ወይም የነብዩ ሐዲስ ይበቃቸዋል ። እነዚህ ስለሶሓቦች ክብርና እነርሱን መስደብ ወይም አዛ ማድረግ አደጋው ምን እንደሆነና ባለቤቱ ለአላህ እርግማንና ለሱ ቅጣት ራሱን የዳረገ መሆኑን የሚያሳዩ የነብዩ ንግግሮች ናቸው ። ሁሉንም እንዘርዝር ብንል መፅሐፍ ማሳተም ግድ ይለናል ። አላህ ካለ በሚቀጥለው ክፍል የሰለፍ ዑለሞች የሶሓቦችን ክብር የሚነካና የሚተች ሰውን አስመልክተው የሰጧቸውን ብይኖች እናያለን ። https://t.me/bahruteka

ልዩ አዲስ ሙሃዶራ ሱናን አጥብቆ መያዝ እና ግዜን በአግባቡ መጠቀም በሚል ሪእስ የተደረገ ነሓሴ 27/12/2018 🕌 በአል-ወሰጢያህ መድረሳ እና መርከዝ 🎤በዶ/ር ሸይኽ ሁሰይን ቢን ሙሀመድ አስ-ስልጢይ https://t.me/AbraribnAwal

📢 የአዲስ ሪሳላህ ማስታወቂያ ​📚 አዳቡል አውላድ ወነይሉል ሙራድ 📚 (آدَابُ الْأَوْلَادِ وَنَيْلُ الْمُرَادِ) 👉 ​ለልጆቻችን አደብ፣ ስነ-ምግባር እና ትምህርት እጅግ
+2
📢 የአዲስ ሪሳላህ ማስታወቂያ ​📚 አዳቡል አውላድ ወነይሉል ሙራድ 📚 (آدَابُ الْأَوْلَادِ وَنَيْلُ الْمُرَادِ) 👉 ​ለልጆቻችን አደብ፣ ስነ-ምግባር እና ትምህርት እጅግ አስፈላጊ የሆነ ጠቃሚ አዲስ ሪሳላህ ዝግጁ ሆኖ ቀርቧል። ​📝 ዝግጅት እና ስብስብ፦ ሸይኻችን አቡ መንሱር ሸይኽ ሙሐመድ ሀያት አል-ወሎውይ 📝 جَمْعُ وَتَرْتِيبُ أَبِي مَنْصُورٍ الشَّيْخ مُحَمَّد حَيَاةَ الْوَلَوِيِّ ​📖 ስለ ሪሳላው፦ ◈ ​የልጆችን የዕለት ተዕለት አደብ የሚያስተምር ◦ ​ለቤተሰብ እና ◦ ለኡስታዞች ◦ ለልጆች ማስተማሪያነት የሚረዳ ● ​በአጭሩ እና በግልጽ ሁኔታ የተዘጋጀ ✔️ ​ለበለጠ መረጃ እና ኪታቡን ለማግኘት ቻናላችንን ይከታተሉ! ​🔗 ቴሌግራም ቻናል: 👇👇 [https://t.me/kutub_of_pdf] ♻️ ሊንክ መቁረጥ ክልክል ነው።

👉 ሙሐመድ ሓሚዲን የሰይድ ቁጥብ ጠበቃ ! ክፍል አንድ ሶሞኑን ሙሐመድ ሓሚዲን የእውቀት ቅርስ በሚል ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ስለ ሰይድ ቁጥብ የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርቦለት በጣም አሳፋሪ በሆነ ሁኔታ የነብያቶችን ክብር የሚያጎድፈውን የነብዩ ባልደረቦችን የሚያዋርደውንና የሙስሊሙን አለም ማህበረሰብ በግልፅ የሚያከፍረውን የሰይድ ቁጥብን ጥመቶች እንደ ተራ ጥፋት በመቁጠር ስሌት ሰርቶ ሙዋዘና በሚባለው ሸውራራ ሚዛን እየለካ ያ ጥፋት በዚህ ይጣፋል በሚል አይነት አንድምታ ያለው ዑዝር እየሰጠ ሲያልፍ ሰምተናል ። ከዚህ ጎን ለጎን የሰይድ ቁጥብን ስህተቶች በመረጃ በማጋለጥ ለነብያቶችና ለነብዩ ባልደረቦች ክብር ዘብ የቆሙትን ዑለሞች ወሰን አላፊዮች በሚል የንግግር ቃና ወርፏል ። በዚህ ሳያበቃ ለሸውራራ ፍርዱ ይረዳው ዘንድ ከዘመናችን ዑለሞች ውስጥ ስለግለሰቡ ሳያውቁ በፊት የተናገሯቸውን ንግግሮች በማምጣት ባጢልን ሐቅ ለማስመሰል ሞክሯል ። እዚህ ጋር አንባቢያን ሊያውቁት የምፈልገው የሰይድ ቁጥብ ስህተቶች ተራ ስህተቶች ሳይሆኑ አንዱ እንኳን ከእስልምና የሚያወጣ አይነት ለተራራ የከበዱ ቅጥፈት የተሞላባቸው ከባባድ ወንጀሎች መሆናቸውን ነው ። ከእነዚህ ውስጥ እንደማሳያ የነብያትን ክብር መንካት ፣ ሶሓቦችን በኒፋቅ መወረፍ የኢስላሙን አለም ማህበረሰብ በግልፅ ማክፈር የሚሉት ይገኙበታል ። እንደነዚህ አይነት ስህተቶች የኢስላም ሊቃውንቶች ዘንድ ያላቸው ብይን ባለቤቱ ይከፍራል ወይስ አይከፍርም የሚል ነው ። በሱና ዑለሞች ዘንድ ፋሲቅና ሙብተዲዕ ለመሆኑ ኺላፍ የለም ። አላህ ካለ ወደፊት በሚመጡ ክፍሎች በዝርዝር በመረጃ የምናያቸው ይሆናል ። ለዛሬ ለመግቢያ ይሆን ዘንድ ስለነብያትና ሰለሶሓቦች ክብር የተወሰነ እንይ :– — ነብያቶች በአላህና በፉጡራኖቹ መካከል አገናኝ እንዲሆኑ ፉጡራኖችን ከኩፍር ጨለማ ወደ ኢማን ብርሀን እንዲያሸጋግሩ አላህ መርጦ የላካቸው ምርጥ ባሮቹ ናቸው ። ይህን አስመልክቶ አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል : – { وَإِذَا جَاءَتْهُمْ آيَةٌ قَالُوا لَن نُّؤْمِنَ حَتَّىٰ نُؤْتَىٰ مِثْلَ مَا أُوتِيَ رُسُلُ اللَّهِ ۘ اللَّهُ أَعْلَمُ حَيْثُ يَجْعَلُ رِسَالَتَهُ ۗ سَيُصِيبُ الَّذِينَ أَجْرَمُوا صَغَارٌ عِندَ اللَّهِ وَعَذَابٌ شَدِيدٌ بِمَا كَانُوا يَمْكُرُونَ} الأنعام (124) " ተዓምርም በመጣቻቸው ጊዜ ፡- «የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ እስክንሰጥ ድረስ በፍጹም አናምንም» አሉ ፡፡ አላህ መልክቱን የሚያደርግበትን ስፍራ ዐዋቂ ነው ፡፡ እነዚያን ያመጹትን ሰዎች ይዶልቱ በነበሩት ነገር አላህ ዘንድ ውርደትና ብርቱ ቅጣት ያገኛቸዋል "፡፡ በዚህ አንቀፅ ላይ እንደምናየው አላህ ለከሀዲያኖች መልስ ሲሰጥ " አላህ መልእክቱን የሚያደርግበትን ስፍራ ዐዋቂ ነው " ይላቸዋል ። መልእክቱንም ከሰዎች ውስጥ ነብያቶችን መርጦ ልባቸውን ለመልእክቱ ማስቀመጫ ስፍራ አደረገው ። እነዚህን አላህ መልእክቱን ሊያስቀምጥባቸው የመረጣቸውን ነብያቶች ክብር መንካት ያከፍራል ። ይህ ሲባል የአንድ ነብይ ክብር መንካት ያጠቃላይ ነብያቶች ክብር መንካት ማለት አይደለም የሚል የሸረሪት ድር አይነት ሹብሀ የሚያነሱ ስለማይጠፉ አላህ ይህን በር በሚቀጥለው አንቀፅ ዘግቶታል : – { قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ} آل عمران (84) «በአላህ አመንን ፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም (በቁርኣን) ፣ በኢብራሂምና በኢስማዒልም፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው ፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው (አመንን) ፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም ፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» በል ፡፡ በዚህ አንቀፅ ላይ እንደምናየው አላህ ከመልእክተኞች መካከል መለየት እንደማይቻል እንዲህ ብሎ ነገረን " ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም " ። እኛ ለነርሱ ታዛዦች ነን በል " ። ብሎ በሁሉም ነብያቶች ማመን ግዴታ መሆኑ ነግሮናል ። ከዚህ በመነሳት የኢስላም ሊቃውንቶች አላህ ከላካቸው መልእክተኛች ውስጥ የአንዱንም ክብር መንካት የሁሉንም ክብር መንካት እንደሆነ በተለይም ደግሞ ዑሉል ዐዝም የተባሉትን ክብር መንካት የወንጀሉን ክብደት እንዲጨምር እንደሚያደርገው ይስማማሉ ። ለዚህ ነው ከእስልምና መሰረታዊ የኢማን ክፍሎች ( አርካኑል ኢማን) አንዱ በነብያት ማመን የሆነው ። የነብያትን ክብር መንካት በነብያት ማመንን ይፃረራል ። ሰይድ ቁጥብ የሚያቋሽሻቸው ነብዩላሂ ሙሳ ከዚህ ለየት ባለ መልኩ አላህ ለኔ መርጨሃለሁ ያላቸው መሆኑን በሚቀጥለው አንቀፅ እንመልከት : – { وَاصْطَنَعْتُكَ لِنَفْسِي} طه (41) «ለነፍሴም (በመልእክቴ) መረጥኩህ ፡፡ ይህ ስለነብያቶች ከመጡ መረጃዎች ከባሕር እንደ ጠብታ ሲሆን ለጮሌ ማመላከት ይበቃዋልና ልብ ያለው ልብ ይበል ። እኝህን አላህ መርጦ ያከበራቸውና መልእክተኛው አድርጎ ወደ ሰው ልጆች የላካቸውን የአላህ መልእክተኛን ነው ሰይድ ቁጥብ ክብራቸውን በመንካት የሚያዋርዳቸው ። አላህ ካለ በሚቀጥለው ክፍል ስለ ሶሓቦች ደረጃና ክብር እንዲሁም እነርሱን የመሳደብና ክብራቸውን የመንካት ብይን እናያለን ። https://t.me/bahruteka

👉 ቢዳዓ ከመጠጥ በላይ ያሰክራል ! ኢኽዋኖች መርሐቸው እንደ አየሩ ፀባይ ይቀያየራል ። ወጥ የሆነ መርህ የላቸውም ። መለኮታዊው የህይወት መመሪያ የአላህና የነብዩ ንግግሮችና መመሪያዎች ለእነርሱ መርህ የሚሆኑት ከስሜታቸው ጋር ከገጠሙ ብቻ ነው ። ካልሆነ ቦታ የላቸውም ! እነርሱ የሚጋልቡበት የስሜት ፈረስ ወደ ሚፈልጉት የስልጣን እርከን ካደረሳቸው ሁሉ ነገር ሀላል ነው ። ሁሉ ነገር መስላሓ ነው ። ሁሉ ነገር ለእስልምና ሲባል ነው ። ምናልባት ያ ተግባር የእስልምናን መሰረት የሚንድ ቢሆንም እንኳን ! ለዚህ ነው በተለያየ ጊዜ በሸሪዓ ሚዛን ያልተመዘነ ንግግር የምንሰማውና ሸሪዓን የሚንዱ ተግባራቶችን የምናየው ። ሶሞኑን ጉዞውን ወደ ባሌ ያደረገው የሀገራችን የኢኽዋን መሪዮች ቡድን ትላልቅ ካላቸው መሪዮቹ ውስጥ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ይገኙበታል ። ይኸው ቡድን አብዛኛ ማህበረሰብ የሽርክ መናኻሪያ ያደረገውንና በአሁኑ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ እየተገነባ ያለውን የሶፍ ዑመርን ዋሻን ፕሮጀክት ከጎበኘ በኋላ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ባደረጉት ንግግር ከነብዩ በኋላ ነብይ ስለማይመጣ ዶ/ር አብይን ወልይ ብንለው ምን ትላላችሁ ሲል የተሰበሰበው ህዝብ በተክቢራ አጅቦ ወልይነቱን አፅድቋል ! ። ንግግሩን በሚቀጥለው ሊንክ ገብታችሁ አዳምጡ : – https://drive.google.com/file/d/17fzkqAYx5JvC-V4XvqAi2a70bKEiCGg4/view?usp=drivesdk ኦሮምኛ የማትችሉ አስተርጉማችሁ ስሙት ። ገርሞ ገርሞ ይገርማል ። የትኛው ደስታ በዚህ ልክ እንዳሰከራቸው አናውቅም ። መጀመሪያ አካባቢ የማህበረ ቅዱሳን አክቲቪስቶች ዶ/ር አብይ ነብይ ነው ሲሉ ነበር ። እነዚያ አካላት ዛሬ እየተራገሙ ይገኛሉ ። ከእነርሱ ውስጥ የኢኽዋን አክቲቪስቶችም ነበሩበት ። አሁን ደግሞ ኢኽዋኖቹ ደረጃውን ወደ ወልይነት አወረዱት ። ያም ሆነ ይህ ወልይነት ለፈለጉት የሚያለብሱት ካባ ሳይሆን በአላህ ብቸኛ ተመላኪነት በማመንና እሱን በመፍራት የሚገኝ ሲሆን ነብይነት ደግሞ የሚሰጠው በአላህ ምርጫ ነው ። ለማን እንደሚገባና ለማን መሰጠት እንዳለበት የሚያውቀው እሱ ነውና ። ለማንኛውም መርህ አልባ የሆነ አካል መርሁ ስሜቱ ነውና ብዙም አይገርመንም ። ነገር ግን ሁሉም ማወቅ ያለበት ዱንያ ላይ የሚሰጡ ምስክርነቶች አላህ ፊት የሚያስጠይቁ መሆናቸውን ነው ። ለዚህ ማረጋገጫው የሚከተለው የአላህ ቃል ነው : – {وَقِفُوهُمْ ۖ إِنَّهُم مَّسْئُولُونَ} الصافات (24) «አቁሟቸውም ፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል) ፡፡ አላህ ሐቅን አውቀን የምንከተለውና ባጢልን አውቀን የምንርቀው ያድርገን ። https://t.me/bahruteka

🎤 ታላቅ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ጥሪ↩️ ⚙ የፕሮግራሙ አዘጋጆች፦ ✅ የኢሎስ ሰለፍያ ጀምዓ 🪑የእለቱ ተጋባዥ እንግዳዎቻችን ፦↩️ 🎙ሸይኽ አብዱልሀሚድ አል-ለተሚይ -ሐ
🎤 ታላቅ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ጥሪ↩️         ⚙ የፕሮግራሙ አዘጋጆች፦           ✅ የኢሎስ ሰለፍያ ጀምዓ 🪑የእለቱ ተጋባዥ እንግዳዎቻችን ፦↩️ 🎙ሸይኽ አብዱልሀሚድ አል-ለተሚይ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ሸይኽ መህቡብ ከሳንኩራ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ሸሰይፉላህ ከምስራቅ ስልጢ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ኡስታዝ ኢዙዲን ከሁልባራግ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ኡስታዝ ነስሩዲን ከሳንኩራ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ኡስታዝ ኢብራሂም ከወራቤ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ኡስታዝ ስራጅ ከወራቤ -ሐፊዘሁሏህ- 🎙ኡስታዝ በህሩ ከስልጢ ወረዳ -ሐፊዘሁሏህ- ☞ የፕሮግራሙ መሪ :- ↳ አቡ ዒምራን ↳ አቡ ዐማር ↳ አቡ ሑዘይፋህ ↳ አቡ ኑዐይም ⇾ኢንሻአላህ ሌላም ተጋባዥ እንግዳ ይኖራል !! 🗓ፕሮግራሙ የፊታችን ቅዳሜ ቀን /23/12/2018 በኢትዮ 3:00 በሳኡድ=9:00 ይጀመራል ቀደምብላቹ በመገኘት የፕሮግራሙ ተካፋይ ይሁኑ!!! ✅ፕሮግራሙን ለመከታተል ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ። ✍በቻናል እና በግሩፓች ሼር በማድረግ ሀላፍትናችንን እንወጣ ➷➷➷➷➷➷➷➷➷ https://imo.onelink.me/RAdY?af_dp=imo%3A%2F%2Fuser.voiceroom.join%2Fmy.0s168dngpwesn5dx%3Fentry_type%3Dshare⁡_web_dp=https%3A%2F%2Fimo.im&from=copy_link

🔹ወሳኝ የጁሙዓህ ኹጥባ (ምክር)
ርዕስ :-" አንደበትን (ምላስን) መጠበቅ "
🎙ሸይኽ አቡ ዘር ሐሰን ኮምቦልቻ    -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በ ኮምቦልቻ ከተማ ሰላም መስጂድ 🗓 ነሐሴ / 𝟐𝟐 / 𝟐𝟎𝟏𝟖                                     ይደመጥ ! ✈️https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha

🟢በማያውቁት ጉዳይ መግባት …🟢 አላህ በጥብቅ የከለከለው ጉዳይ: قال الله سبحانه 《وَلَا تَقْفُ مَا لَيْسَ لَكَ بِهِ عِلْمٌ ۚ إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا》  الإسراء:(36) "እውቀት በሌለህ በሆነ ነገር አትከተል።መስሚያ ፣ መመልከቻም ፣ ልብም በእነዚህ ሁሉ (ተግባር) ባለቤታቸው እኮ ተጠያቂ ነው።" ሰለፎች እውቀት በሌለ ነገር ከመከተል ውስጥ የሚከተሉትን ጠቅሰዋል። لا تتبع ما لا تعلم وما لا يعنيك 1⃣የማታውቀውንና የማይመለከትህን ጉዳይ አትከተል። لا تقل ما ليس لك به علم 2⃣ እውቀት በሌለህ ጉዳይ አትናገር። لا تقل: رأيت ولم تر، وسمعت ولم تسمع 3⃣ ሳታይ አይቻለሁ ፣ ሳትሰማ ሰምቻለሁ አትበል። قول الزور، وشهادة الزور 4⃣ ከቅጥፈት ንግግርና ከቅጥፈት ምስክርነት ተጠንቀቅ። التحلم بحُلمٍ كاذب 5⃣ ያላዩትን ህልም እንዳዩ አስመስሎ ወይም አቀነባብሮ ከማውራት ተጠንቀቅ። الحكم  بالظن 6⃣ በግምት ብይን ከመስጠት ተጠንቀቅ። التقليد الأعمى 7⃣ ከጭፍን ተከታይነት ተጠንቀቅ። البدعة في الدين 8⃣ በዲን ላይ የአምልኮ ፈጠራን ተጠንቀቅ። الجرح والتعديل 9⃣በውል ስለማታውቀው አካል ትችትም ሆነ ውዳሴ ተጠንቀቅ። እነዚህ ባህሪያትና ተግባራት አላህ ዘንድ በጥብቅ ያስጠይቃሉ። 👉ጭራሽ በማያውቁት ጉዳይ ይቅርና በጥርጣሬ (الظن) ላይ ሆኖ መናገር እንኳን ከባድ ስለመሆኑ የቁርኣንና የሀዲስ ጥቅሶች በርካታ ናቸው። ( وَقُلْ رَبِّ زِدْنِي عِلْمًا ) ✍ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ) http://t.me/Abuhemewiya

🌸🍃 ‏"كلمتُكَ الطيبةُ لها أَثَر؛ اعتذارُكَ له قيمَةٌ؛ تفهمُكَ للآخرينَ أدَبٌ؛ التغاضي عن الأخطاءِ وعيٌ ؛ مراعاةُ المشاعرِ نُبْلٌ ؛ صَوْنُ الوُدِّ وُدٌّ ؛ ما تُقدِّمه لغيركَ عائدٌ إليكَ ؛ لا تبخلْ بالجَمَالِ فتصبح خاليًا منه" 💡መልካም ተግባራቶች ​"መልካም ቃላትህ ትልቅ ተፅዕኖ አላቸው ይቅርታህ ዋጋ አለው ሌሎችን መረዳትህ ስነ-ምግባር ነው ስህተቶችን ማለፍና ችላ ማለት ብስለት ነው የሌሎችን ስሜት መጠበቅ ልግስና/ክብር ነው ፍቅርን መጠበቅ ራሱ ፍቅር ነው ለሌሎች የምትሰጠው ነገር ሁሉ ወደ አንተ ተመልሶ ይመጣል ስለዚህ ውበትን አትስሰት (አትቁጠብ) አሊያ ከእሱ ባዶ ትሆናለህና። ↪️↪️ 💬 የፍቅር ቤት ❨ @YeFkrBet_1 💬 ለተጨማሪ ነጥቦች ↙️ 🌐 https://t.me/YeFkrBet_1 💡 ሀሳብ ካለዎ 👇 ያናግሩን https://t.me/YeFkrBet_1bot

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ ሰለፊዮች እንኳን ደስ ኣላችሁ ይህቺ አፕ በተሳካ ሁኔታ በplay store ተጭናለች ከዚህም ቦሀላ የምንሰራቸው አፖችን በፕሌይስቶር ስለምንጭን ሰርች ሲደ
+1
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ ሰለፊዮች እንኳን ደስ ኣላችሁ ይህቺ አፕ በተሳካ ሁኔታ በplay store ተጭናለች  ከዚህም ቦሀላ የምንሰራቸው አፖችን በፕሌይስቶር ስለምንጭን ሰርች ሲደረጉ ከፊት እንዲመጡ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ገብታችሁ  አምስት ኮከብ እንድትሰጡ በታለቅ አክብሮት እና ትህትና እያጠየቅን መላው ሰለፊይ የቻናል በልተቤቶች ለሌሎች እንዲደርስ ሼር መድረግን አትርሱ! Play Store👇 https://play.google.com/store/apps/details?id=com.abdulrezak.tuhfetulatfal&utm_source=chatgpt.com 📲 አሁኑኑ አፑን ያውርዱ እና ለሌሎችም ያጋሩ☝☝ 🛠 የአፕ ማሰሪያ አገልግሎት ለማግኘት 👉 @JJ_selfy_app_developer 📢 ከ100 በላይ እስላማዊ አፕልኬሽኖችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/jj_app_developer https://t.me/jj_app_developer https://t.me/jj_app_developer

🔊#አዋጅ! #አዋጅ! #አዋጅ! 🔊 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 🔵እነሆ የፊታችን ጁሙዓ ማለትም ነሀሴ 22/2018 አ. ል. {ረቢዓል አወል ١٥/١٤٤٨. هـ } በዓይነቱ ል
🔊#አዋጅ! #አዋጅ! #አዋጅ! 🔊   السلام عليكم ورحمة الله وبركاته  🔵እነሆ የፊታችን ጁሙዓ ማለትም ነሀሴ 22/2018 አ. ል. {ረቢዓል አወል ١٥/١٤٤٨. هـ } በዓይነቱ ልዮ የሆነ ታላላቅ የሰለፍያ #መሻይኾች የሚሳተፉበት ሀገር አቀፍ #የonline የዳዕዋ ፕሮግራም ተሰናድቶ አርሂቡ ይላቹሀል።    💺ተጋባዥ መሻይኾች  1,ሸይኽ ሀሰን ገላዉ {ከባህር ዳር}  2,ሸይኽ ዐብዱል ሐሚድ አል'ለተሚይ{ከስልጤ}   3,ሸይኽ ዩሱፍ አሕመድ(ከባህርዳር)  4,ዶ/ር ሸይኽ ሑሰይን  አስ'ስልጢ (ከአዲስ አበበ) 5,ሸይኽ ጦሀ ኸድር (ከአዲስ አበባ)  6,ሸይኽ አቡ ዘር ሐሰን (ከኮምቦልቻ)  7,ሸይኽ ሙሐመድ ጀማል(ከኮምቦልቻ)  8,ሸይኽ ሙሀመድ ሀያት {ከሀራ}  9,ሸይኽ ሑሰይን ከረም (ከሀራ)  10,ሸይኽ ሙባረክ (ከወልቅጤ)  ✪ሌሎችም እንግዶች ይኖሩናል    🌍የፕሮግራሙ ቦታ  በሀራ ሰለፍዮች የቴሌግራም ግሩፕ  💻የፕሮግራሙ አዘጋጆች የሀራ ሰለፍያ ጀመዓዋች   🕰የፕሮግራሙ ሰዓት  🇪🇹በኢትዮ. 3:00  pm 🇸🇦በሳዉድ. 9:00 pm 🇦🇪በዱባይ. 4:00 pm   📡ፕሮግራሙን ለመከታተል 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/haraselefi  https://t.me/haraselefi https://t.me/haraselefi https://t.me/haraselefi 👆👆👆👆👆👆👆👆 Join ይበሉ!   ✅የፕሮግራሙ ቀን እስከሚደርስ #ሸር ባማድረግ ለብዙ እህት ወንድሞች ተደራሽ እንድሆን የበኩላችንን እንወጣ። 🔵ባረከሏሁ ፊኩም!!!! 💻 ሌሎች መሻይኾቻችንና ዱዓቶቻችን ኢንሻ አሏህ በሌላ ፕሮግራም የምንገናኝ ይሆናል  

#ስለ_መውሊድ_በኡለሞቻችን ➪➩➪➩➪➩➪➩➩➩ ✅ በአለም ላይ ታዋቂ የሆኑና በአላህ ፍቃድ ባላቸው እውቀት ከጥመት ባለቤቶች ውጭ ትንሽ ትልቁ፤ ሴት ወንዱ የሚያከብራቸው ውድና የተከበሩ የሱና መሻይኾች በአሁኑ ሰዓት እየተደገሰ ስለሚገኘው መውሊድ የሰጡት የተለያዩ ትምህርት ሲሆን ከታች በሊንክ ቀርቦላችኋልታላላቅ ኡለሞች ስለ መውሊድ ምን አሉ? ╭─••─═••═─•••─╮ ✅ ክፍል ❶ እስከ ⓯ ╰─••─═••═─•••─╯ ❶ኛ ➦ በታላቁ ዓሊም አንደበት ስለ #መውሊድ 🎙 سماحة الشيخ عبدالعزيز بن باز رحمه الله 🎙 በሸይኽ አብዱል አዚዝ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3911 ➋ኛ መውሊድ ቢድዓ ስለመሆኑ ስለ አጀማመሩም ↩️ هل الإحتفال بالمولد بدعةٌ أو سُنّةٌ؟ومتىٰ عُرف هذا الإحتفال، ومتىٰ بدأ؟ 🎙 فضيلة الشيخ العلامة محمدأمان بن علي الجامي رحمه الله تعالى 🎙 በሸይኽ ሙሐመድ አማን ቢን አልይ አልጃሚ ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3920 ➌ኛ ለነብዩ መውሊድ መሰባሰብ ይቻላልን? ↩️ هل يجوز أن نحتفل بالمولد النبوي؟ 🎙 فضيلة الشيخ  سليمان الرحيلي حفظه الله 🎙 በሸይኽ ሱለይማን አሩሃይሊ ሀፊዘሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3924 ➍ኛ  ነብዩ ﷺ ረቢዕ 12 ቀን ተወልደዋልን? ↩️ هل ولد النبي ﷺ يوم ١٢ ربيع الأول؟ 🎙  فضيلة الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله 🎙 በሸይኽ ሱለይማን አሩሃይሊይ ሀፊዘሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3938 ❺ኛ አጠር መጠን ባል ገለፃ የቀረብ ወሳኝ ነጥብ መውሊድ ቢድዓ ለመሆኑ 🎙الشيخ الدكتور عبد العزيز الريس حفظه الله 🎙 በሸይኽ አብዱልአዚዝ አረይስ ሀፊዘሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3943 ❻ኛ በዲናችን ላይ የፈለሰፈ በሚለው ሀዲስ ላይ ተዕሊቅ በዛውም ለመውሊድ ምላሽ ተሰጥቶበታል። ↩️ تعليق مهم على حديث "من أحدث في أمرنا" وفيه الرد على بدعة المولد 🎙 الشيخ محمد بن علي بن آدم الإتيوبي الولوي 🎙 በታላቁ ኢትዮጵያዊ ዓሊም ሙሐዲስ አሽ‐ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ ብን አደም ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3946 ❼ኛ መውሊድ ቢድዓ ሊሆን እንዴት ቻለ? ➺ መውሊድን የጀመሩት እነማን ነበሩ? ➺ ሶሃቦችስ መውሊድን አክብረዋልን? 🎙 الإمام الفقيه العلامة محمد بن آمان بن علي الجامي رحمه الله تعالى 🎙 በታላቁ ኢማም ሙሀመድ ቢን አማን አልጃሚ ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3951 ➑ኛ በመውሊድ ዙሪያ ጥሩ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ወሳኝ ሙሐደራ ነው። ➽ በምርጥ አገላለፅ አቅርበውልናል። 🎙 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى 🎙 በሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3953 ❾ኛ ለመውሊድ የአቡ ለሃብን መናም መረጃ ለሚያደርጉ ምላሽ ↩️ الرد على من يستدل بمنام أبي لهب في جواز الاحتفال بالمولد 🎙 الشيخ محمد بن علي بن آدم الإتيوبي الولوي 🎙 በታላቁ ኢትዮጵያዊ ዓሊም ሙሐዲስ አሽ‐ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ ብን አደም ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3955 ❿ኛ ጥሩ ቢድዓ አለን? ለመውሊድ መሰባሰብስ ፍርዱ ምንድን ነው? ↩️ هل هناك بدعة حسنة؟ وحكم الإحتفال بالمولد؟ 🎙 الشيخ العلامة الإمام عبد العزيز بن عبد الله بن باز رحمه الله تعالى በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3958 ⓫ኛ ስለ መውሊድ ሁክም በተለያዩ ታላላቅ ዓሊሞች ↩️ حكم الإحتفال بالمولد النبوي ✅ لمجموعة من العلماء الأكابر: 🎙 الإمام مقبل الوادعي 🎙 الإمام ابن عثيمين 🎙 الإمام الألباني 🎙 الإمام ابن باز رحمهم الله جميعًا በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3960 ⓬ኛ እጅግ በጣም #ማራኪ አገላለፅ በመውሊድ ዙሪያ 🎙 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى 🎙 በሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን ረሂመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3966 ⓭ኛ የነብዩ ﷺ መውሊድ በሚከበርበት ቦታ መገኝት ፍርዱ ምን ይሁን? 🎙 العلامة الإمام : مقبل بن هادي الوادعي ـ رحمه الله تعالى 🎙️ በሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አል-ዋዲዒ ረሒመሁሏህ በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3970 ⓮ኛ ነብያችን ከመውሊድና መውሊድ ላይ ከሚፈፀመው ጥፋት የጠሩ ናቸው። ➡️ ሰኢድ አልኩመልይ ለተባለው ሱፍይ የተሰጠ መልስ 🎙 العلامة الإمام : صالح بن فوزان الفوزن  حفظه الله 🎙️ ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን ሐፊዘሁሏህ። በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3973 ⓯ኛ መውሊድ ሲደርስ ስለ ረሱላችን ﷺ የሕይወት ታሪክ፣ ባህሪያት ማውራት ይቻላል? 🎙 العلامة الإمام : صالح بن فوزان الفوزن  حفظه الله 🎙️ ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን ሐፊዘሁሏህ። በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/AbuImranAselefy/3977

🚫 የሰለፍዮች የዳዕዋ ነፃነት በመጅሊስ አመራሮች መልካም ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ አይደለም ! ኢትዮዽያዊያን የፈለጉትን አስተሳሰብም ሆነ እምነት የማራመድ መብታቸው በማያሻማ ሁኔታ እንደ ጠዋት ፀሀይ ፍንትው ብሎ በሚታይ መልኩ ህገ – መንግስቱ ያስቀምጣል ። በመሆኑም እኛ ኢትዮዽያዊያን ሰለፍዮች ህገ – መንግስቱ ለዜጎች የሰጠውን መብታችን በመጠቀም በሀገራችን ላይ የመረጥነውን የሰለፍያ መዝሀብ የመከተልና ሌሎችንም ወደዚሁ የመጥራት መብት አለን ። ህገ – መንግስቱ ለዜጎች እምነታቸውን በነፃነት የማራመድ መብታቸው ካረጋገጠባቸው አንቀፆች ውስጥ የሚከተለውን እንይ : –      በኢፊድሪ ህገ – መንግስት አንቀፅ 27(1) እንዲህ ይላል : – " ማንኛውም ሰው የመረጠውን እምነት የመያዝ ፣ የማክበር ፣ የማራመድ ሙሉ ነፃነት አለው " ። ይህ ሀገራችን የምትመራበት ህገመንግስት ለሁሉም ዜጎች በእኩልነት የሰጠው መብት ነው ። የትኛውም አካል ማንንም ከኔ ስር ካልሆንክ ብሎ የማስገደድም ሆነ የማዘዝ መብት እንደሌለው ያረጋግጣል ። በሌላ በኩል ይኸው ህገመንግስት ለዜጎት ያልተገደበ የእምነት ነፃነት የሰጠና ማንም ይህን ነፃነት የመገደብና የማስገደድ መብት እንደሌለው ያስቀምጣል ። ይህም በሚከተለው የህገመንግስት አንቀፅ እናገኘዋለን : – – በኢፊድሪ ህገ– መንግስት አንቀፅ 27(3) እንዲህ ይላል : – " ማንኛውም ሰው የሚፈልገውን እምነት ለመያዝ ያለውን ነፃነት በሀይል ወይም በሌላ ሁኔታ በማስገደድ መገደብ ወይም መከልከል አይችልም "። ህገመንግስቱ በዚህ መልኩ ለዜጎች ያልተገደበ የፈለጉት እምነት በነፃነት የማራመድ መብት መጅሊሱ አላይም አልሰማም ብሎ ከኔ ስር ካልሆንክ ብሎ ዜጎችን እያሳሰረና ከመስጂድና ከመድረሳ እያስባረረ ይገኛል ። ይህ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮዽያ የምትከተለው የብዝሀነት ፖሊሲ እንዲሁም በእነዚህ አንቀፆች ስር የተቀመጠውን ህገመንግስታዊ መመሪያ የጣሰ ነው ። በተጨማሪም መጅሊሱ የሚያራምደው በኔ ስር ካልሆንክ የሚለው የረጋጭነት አካሄድ ከብዝሀነት መርሁ ጋር ፍፁም ተቃራኒ ከመሆኑም በላይ የዜጎችን ህገመንግስታዊ መብት ነጥቆ ረግጬ ልግዛህ ባይነት ነው ። እኛ ኢትዮዽያዊያን ሰለፍዮች ሀገራችን የምትመራው በህገመንግስቱና ረጋጭነትን በሚዋጋ ብዝሀነትን መሰረት ባደረገ መርህ መሆኑን ጠንቅቀን እናውቃለን ። በመሆኑም ሀገራችንን እያስተዳደረ ያለው ብልፅግና ፓርቲ የህገመንግስቱን የበላይነት አስጠብቆ የብዝሀነትን መርሁን እውን አድርጎ መብታችንን ሳይቆራረስ እንዲያስከብርልን እንጠይቃለን ። ከዚህ ጎን ለጎን የብልፅግና ፓርቲ እንዲያውቅልን የምንፈልገው የሀገሪቱን ህገመንግስታዊ መመሪያ ተከትለው ህዝብን በእኩልነት እንዲያገለግሉ የህዝብ አደራ ተጥሎባቸው በመንግስት የስልጣን ወንበር ላይ የተቀመጡ አንዳንድ ባለስልጣናትና እንዲሁም አንዳንድ የፖሊስና የሰላምና ፀጥታ አካላት ያስቀመጣቸው የገዢው ፓርቲ ሳይሆን መጅሊሱ ረግጬ ልግዛህ የሚለውን አላማው ሊያስፈፅሙለት ደሞዝ የሚከፍላቸው የሚመስሉ መሆኑን ነው ። ይህ በኢፊድሪ ህገ – መንግስት አንቀፅ 11 መሰረት መንግስት በሀይማኖት ጣልቃ እንደማይገባና ሀይማኖትም በመንግስት ጣልቃ እንደማይገባ የተቀመጠውን መርህ የሚጥስ ነው ። እነዚህ አካላት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዮች በእምነት ጣልቃ ገብተው አንተ እገሌን ተከተል ከእገሌ ስር ሁን እያሉ የፈለጉትን እያሰሩ የሰለፍዮችን ተቋማት ( መድረሳና መስጂዶችን እያሸጉና አስለቅቀው ለመጅሊስ እያስረከቡ ይገኛሉ ። በመሆኑም እኛ ኢትዮዽያዊ ሰለፍዮች የዚህ አይነቱ ፀረ ህገመንግስታዊና ፀረ የፓርቲው መርህ አካሄድና ጭቆና በአስቸኳይ እንዲቆምልን እንጠይቃለን ። በጣም የሚገርመው የዚህ አይነቱ ግፍና ጭቆና አሁን አብዛኛው ኢትዮዽያዊ በጉጉት የሚጠብቀው ሀገራዊ ምክክር እየተካሄደ ባለበት ወቅትም ጭምር እየተፈፀመ መሆኑ ነው ። ሌላው ሁሉም ሰለፍይ ሊያውቀው የሚገባው መጅሊሱ ሰኔ 28/2012 በአዋጅ ሲቋቋም አንቀፅ 6 ንኡስ አንቀፅ 3 ላይ " የዚህ ምክር ቤት መቋቋም የሀገሪቷ ሙስሊሞች በክልልም ሆነ በፌዴራል ደረጃ የመሰረትዋቸውን በሀይማኖት የተደራጁ ተቋማት መብትም ሆነ ለወደፊት የመደራጀትና የመመዝገብ መብታቸውን አይከለክልም " በማለት በግልፅ ማስቀመጡን ነው ። ይህ ማለት በተቋም ለመደራጀትና ለመመዝገብ ከፈለጉ ይችላሉ ማለት እንጂ ካልተደራጁ እምነታቸውን በነፃነት ማራመድ አይችሉም ማለት አለመሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ከላይ በአንቀፅ 27(3) ያየነውን መብት የሚያጠናክር ነው ። ውድ ሰለፍዮች ሆይ ዐቂዳችሁን በግል ቤታችሁም ይሁን ቤት ተከራይታችሁ ወይም ገዝታችሁ የማስተማርና በነፃነት ዳዕዋ የማድረግ መብታችሁ ህገ – መንግስቱ ያረጋገጠላችሁ የዜግነት መብት እንጂ ማንም በምፅዋትነት የለገሳችሁ ስላልሆነ መብትና ግዴታችሁን አውቃችሁ ወደፊት ቀጥሉ ። አንዳንድ የመንግስትና ህዝብን አደራ ወደ ጎን በማድረግ የግል አመለካከታቸውን በስልጣን ለማስፈፀም የሚሄዱና እንዲሁም የተጣለባቸውን ህዝባዊ አደራ በጥቅም የሸጡ አካላት የሚያደርሱባችሁን ግፍ ተጋፍጣችሁ ለአላማችሁ ፅኑ ። እንደነዚህ አይነት አካላትን እስከመጨረሻ በመታገል ማንነታቸው ለፍትሕ የቆሙ የመንግስት አካላት እንዲያውቁዋቸው ለማድረግ ጥረት አድርጉ ። ምክንያቱም በሁሉም አካባቢ የተሰጣቸውን የህዝብ አደራ ለመወጣት ቆርጠው የቆሙ አሉና መፍትሄ ታገኛላችሁ ። አላህ ቁርኣንና ሐዲስን በሰለፎች ግንዛቤ የበላይ ያድርግልን ።    http://t.me/bahruteka

Repost from N/a
ቂርአቱ የሚጀመረው ነሃሴ 20//2018 ነው። አሰላሙአለይኩም ወራህመቱሏህ ውድ ተማሪዎች ከዚህ በፊት ይጀመራል ያልናችሁ ቋሚ የደርስ ፕሮግራም ከቀናት በኋላ ይጀመራል። ፕሮግራሙ ➊ኛ የአረብኛ ቋንቋ ትምህርት      => ፅሁፍ ለጀማሪዎች      => የነህው ትምህርት      => የሶርፍ ትምህርት ❷ኛ አጫጭር ኪታቦች      => የአቂዳ ኪታቦች      => የመንሃጅ ኪታቦች      => የፊቅህ ኪታቦች ❸ የቁርኣን ትምህርት 👉 በዚህ ፕሮግራም ስር እህቶች በእህቶቻቸው ብቻ የሚማሩ ይሆናል። ይህም የተለያዩ ደረጃዎች ላይ ላሉ ሁሉ የተመቻቸ ነው።      => የቃኢደቱ-ኑራንያህ      => የቁርኣን ነዞር      => የተጅዊድ ህግጋት ✅ በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ እቅዱ ያላችሁ በሚከተለው አድራሻ ፈጥናችሁ ተመዝገቡ!      👇👇👇 @Medresaa_bot 🌐 ስለ ደርሱ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን ለማግኘት እና ሀሳብ ለመስጠት የሚከተለውን ግሩፕ ተቀላቀሉ! 👇👇👇👇👇👇 https://t.me/arabic_grammer_m