en
Feedback
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/-ኢኦተቤ EOTC-Addis Ababa Diocese Media service

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/-ኢኦተቤ EOTC-Addis Ababa Diocese Media service

Open in Telegram

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል ነው። መንፈሳዊ አገልግሎትና ሰሞነኛ ጉዳዮች ይቀርቡበታል። አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

Show more
5 799
Subscribers
-424 hours
-47 days
+2830 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+13
in 0 channels
August '26
+100
in 1 channels
Get PRO
July '26
+104
in 2 channels
Get PRO
June '26
+55
in 2 channels
Get PRO
May '26
+62
in 0 channels
Get PRO
April '26
+39
in 2 channels
Get PRO
March '26
+76
in 2 channels
Get PRO
February '26
+51
in 1 channels
Get PRO
January '26
+51
in 0 channels
Get PRO
December '25
+140
in 1 channels
Get PRO
November '25
+122
in 2 channels
Get PRO
October '25
+117
in 3 channels
Get PRO
September '25
+94
in 0 channels
Get PRO
August '25
+102
in 1 channels
Get PRO
July '25
+405
in 3 channels
Get PRO
June '25
+133
in 3 channels
Get PRO
May '25
+172
in 1 channels
Get PRO
April '25
+75
in 3 channels
Get PRO
March '25
+92
in 0 channels
Get PRO
February '25
+108
in 1 channels
Get PRO
January '25
+84
in 0 channels
Get PRO
December '24
+77
in 0 channels
Get PRO
November '24
+60
in 0 channels
Get PRO
October '24
+94
in 2 channels
Get PRO
September '24
+127
in 2 channels
Get PRO
August '24
+106
in 0 channels
Get PRO
July '24
+67
in 1 channels
Get PRO
June '24
+60
in 1 channels
Get PRO
May '24
+41
in 0 channels
Get PRO
April '24
+36
in 1 channels
Get PRO
March '24
+41
in 0 channels
Get PRO
February '24
+77
in 2 channels
Get PRO
January '24
+44
in 0 channels
Get PRO
December '23
+64
in 0 channels
Get PRO
November '23
+46
in 0 channels
Get PRO
October '23
+31
in 0 channels
Get PRO
September '23
+30
in 0 channels
Get PRO
August '23
+30
in 0 channels
Get PRO
July '23
+59
in 0 channels
Get PRO
June '23
+57
in 0 channels
Get PRO
May '23
+284
in 0 channels
Get PRO
April '23
+265
in 0 channels
Get PRO
March '23
+258
in 0 channels
Get PRO
February '23
+2 165
in 0 channels
Get PRO
January '23
+678
in 0 channels
Get PRO
December '22
+236
in 0 channels
Get PRO
November '22
+276
in 0 channels
Get PRO
October '22
+293
in 0 channels
Get PRO
September '22
+262
in 0 channels
Get PRO
August '22
+229
in 0 channels
Get PRO
July '22
+209
in 0 channels
Get PRO
June '22
+183
in 0 channels
Get PRO
May '22
+261
in 0 channels
Get PRO
April '22
+298
in 0 channels
Get PRO
March '22
+161
in 0 channels
Get PRO
February '22
+183
in 0 channels
Get PRO
January '22
+1 265
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September+1
06 September+1
05 September+2
04 September+2
03 September+4
02 September+2
01 September+1
Channel Posts
2
+9
No text...
594
3
+9
No text...
531
4
+9
No text...
579
5
"#ወንጌል_በመስበክ አብራችሁን ስለደከማችሁ እናመሰግናለን" ፊል ፩:፫ የኢኦተቤ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ያዘጋጀው የአንድ ከመቶ (1%) ወርኀዊ መዋጮ በአግባቡ ላወጡ አካላት የምስጋና መርሐ ግብር ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በተገኙበት በካፒታል ሆቴል እየተከናወነ ይገኛል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service
549
6
+5
No text...
899
7
"መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ" በሚል የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የአብነት ትምህርት ቤት ሕንጻ ግንባታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በተገኙበት ተሰጠ። ▮EOTC TV ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓም▮ ታሪካዊና ጥንታዊው የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም፣ የቤተ ክርስቲያናችንን የትምህርትና የመንፈሳዊ ሀብት መሠረት የሆነውን የአብነት ትምህርት ቤት ዘመናዊ ሕንጻ ለመገንባት የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊና መንፈሳዊ ጥሪ አቅርቧል። ገዳሙ "መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ" በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው መርሐ ግብር፣ የመሠረት ድንጋይ ለማኖር የሚሆንና ግንባታውን ለማስጀመር የሚያስችል የ5,000 ብር ቻሌንጅ ማስጀመሩን አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞችና ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በንግግራቸው በአታ ለማርያም ገዳም ዛሬ ትልቅ ሥራ ለመስራት ጽንስ ላይ ነችና ቅዱስ እግዚአብሔር በሰላም ይገላግላት ዘንድ ልንማጸን እና ልንረዳ ይገባል በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ሊቀ ሊቃውንት ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ዋና አስተዳዳሪ ''ግንባታ'' ለበአታ 20 ሺህ ሰዎች ድጋፍን ተከትሎ በመስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም በበአታ ለማርያም ዕለት የግንባታው የመሠረት ድንጋይ የሚቀመጥ መሆኑን ገልፀዋል ። በመርሐ ግብሩም ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የአብነት ትምህርት ቤት ደረጃውን የጠበቀ ሕንጻ በመገንባት ለተተኪ ትውልድ ሊቃውንት ምቹ የመማርያና የመኖሪያ ቦታ ማዘጋጀት ፤ 20,000 (ሃያ ሺህ) በጎ ፈቃደኛ ምእመናንን እያንዳንዳቸው 5,000 ብር በቻሌንጅ በማሳተፍ ለቦታው የመሠረት ድንጋይ ማኖሪያና ለግንባታ ማስጀመሪያ የሚሆን በቂ ገቢ መሰብሰብን ግብ አድርጎ መነሳቱ ተጥቅሷል። ይህ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ጥሪ የሁላችንንም ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና ቅርሶቿን የምንወድ፣ የሃይማኖታችንና የታሪካችን ጥበቃ የሚያስጨንቀን ምእመናን በሙሉ በዚህ በጎ ሥራ ላይ በቻሌንጁ በመሳተፍ የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል። የመሠረት ድንጋይ ማኖር ሥነ ሥርዓትም መስከረም 03 ቀን 2019 ዓ/ም እንደሆነም ተገልጿል። ይህ ታሪካዊ ገዳም የዳግማዊ አጼ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ እና የንግሥት ዘውዲቱ መካነ መቃብር የሚገኝበትና በርካታ ጥንታዊ ቅርሶችን የያዘ መሆኑ፣ ይታወቃል ። ግንባታው 4 መሠረታዊ ሕንጻዎችን የያዘ መሆኑም፣ የግንባታ ፍቃድ መውሰዱም እና 2.5 ቢሊዮን ብር የሚፈጅ መሆኑን በተጨማሪም ግንባታው ሲጠናቀቅ 1500 የአብነት ተማሪዎችን እንደሚቀበል ተብራርቷል። በዕለቱም ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ፤ አባ ተክለ ሃይማኖት የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ዋና አስተዳዳሪ ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ። እያንዳንዱ የ5,000 ብር አስተዋጽኦ የአብነት ትምህርቱንና የታሪካችንን መሠረት ያጠናክራል። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/
872
8
+9
No text...
878
9
+9
No text...
776
10
ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በማጠናቀቃቸው የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ደስታቸውን ገለጹ!! ▮ነሐሴ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ▮አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ (ዶ/ር) ከሊበርቲ ዩኒቨርሲቲ በኢዱኬሽናል ሊደርሺፕ ያጠናቀቁትን የዶክትሬት ዲግሪ በማስመረቃቸው ልዩ የደስታና የምስጋና መርሐ ግብር አካሒደዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራንና ሠራተኞች የብፁዕነታቸው የትምህርት ስኬት ለተቋሙና ለቤተ ክርስቲያን የዕውቀትና የአመራር አቅም የሚያጎለብት መሆኑን ገልጸው ደስታቸውን አጋርተዋል። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ፦ ከስድስት ዓመታት በላይ በትጋት በማጥናትና በምርምር ያጠናቀቁት ጥናት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያለውን አገልጋይ መሪነት፣ የሥራ ተሳትፎና መንፈሳዊነት በማጣመር የሚመረምር መሆኑን ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ የብፁዕነታቸውን የሕይወት ታሪክ የሚያስረዳ “ፍኖተ ሕይወት” መጽሔትና “ከአሜሪካ እስከ ጂንካ” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ቀርቧል። የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲን ከምሥረታው ጀምሮ ያለውን የዕድገት ጉዞ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይም ተከፍቷል። ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ (ዶ/ር) በበኩላቸው የትምህርት ስኬት ለማስመዝገብ ግልጽ ዓላማ፣ ጽናትና ራስን መግዛት፣ የጊዜ አጠቃቀምና ዕቅድ፣ ትክክለኛ የጥናት ስልት እንዲሁም የአካባቢና የማኅበራዊ ድጋፍ አስፈላጊ መሆናቸውን ገልጸዋል። ብፁዕነታው በዚህ መርሐ-ግብር ላይ ለተሳተፉ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል። በመርሐ-ግብሩ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስን ጨምሮ በርካታ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነትና የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራን፣ ሠራተኞች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። EOTC TV
673
11
+1
No text...
715
12
+9
No text...
698
13
የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም ለአምስተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን 24 ደቀ መዛሙርት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በተገኙበት አስመረቀ:: ▮ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም▮አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከተለያዩ ወረዳ ቤተ ክህነቶች የተወጣጡ 24 ደቀ መዛሙርትን ለሦስት ወራት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮዎች ዙሪያ አሰልጥኖ አስመረቀ። የሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት ባስተላለፉት መልዕክት የዛሬ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት የቤተክርስቲያንን ቀኖናዋን፤ ዶግማዋን ፤ሳይፋለስ፤ ሳይከለስ፤ ቀጥተኛውን የቤተክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምሩና በሕይወታቸው ወንጌልን መስበክ እንዳለባቸው፤የቤተክርስቲያን ኃላፊነትም ጭምር እንዳለባቸው አሳስበዉ ፣ለአዲሱ የማሰልጠኛዉ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር መርተዋል። በብፁዕነታቸው ሥልጠናውን ለተከታተሉ ደቀመዛሙርት የሽልማት እና የምስክር ወረቀት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ አኅጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ ለተመራቂ ልጆቻቸዉ ባስተላልፉት አባታዊ መልዕክት የዛሬ ተመራቂዎቹ የነገዋ ቤተክርስቲያን ተረካቢዎች መሆናቸዉን ገልጸዉ፣የተሰጣቸዉን አደራ በመጠበቅ የገጠሪቷን ቤተክርስቲያን እንዲያገለግሉ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዉ በብፁዕነታቸዉ ጸሎት የምረቃ መርሐ ግብሩ ፍጻሜውን አግኝቷል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ የሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የሀገረስብከቱ የክፍል ኃላፊዎች ፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፤ የወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ፣ ሊቃውነት ፣የሀገር ባህል ሽማግሌዎች ፣የጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ የተመራቂ ደቀመዛሙርት ቤተሰቦች ተገኝተዋል። © ብህንሳ በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
779
14
+1
No text...
1 536
15
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አይሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ። ነሐሴ፳፯ ቀን፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥንታዊት፤ ብሔራዊት፤ ዓለም አቀፋዊት፤ሐዋርያዊት እና ሲኖዶሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋ መጠን ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን፤ትውፊቷንና ሥርዓቷን በጠበቀ መልኩ መንፈሳዊ እና ማኀበራዊ አገልግሎቷን ለማጠናከር እና ተደራሽ ለማድረግ ከምታከናውናቸው በርካታ ተግባራት መካከል ዘመኑ የደረሰበት የአይሲቲና የዲጂታል ሽግግር ሥራ ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል:: ከዚሁ አንጻር የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በመላው ዓለም ለማስፋፋት፣ ታሪካዊ ቅርሶችን እና አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ሀብትና ንብረቷን ለመጠበቅ እንዲሁም አስተዳደራዊ ተግባራትን ለማሳለጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራን በበላይነት የሚመራና የሚያስተባብር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ እንዲሁም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ተቃቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል፡፡ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር አህጉረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ ስምና ፊርማ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በተላከ ደብዳቤ፤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ መቋቋሙን ገልጾ ቀደም ሲል እንደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያሉ አይሲቲን በዋና ክፍል አደራጅተው እየሠሩ የሚገኙ አህጉረ ስብከት በተላከላቸው ዝርዝር የሥራ መመሪያ ቁጥር 3/3018 መሠረት እስከ አጥቢያ ቤተ ከርስቲያን ጽ/ቤት ድረስ ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲደረግ በተሰጠው መመሪያ መነሻነት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትም በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከመቸውም ጊዜ በተሻለ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየሠራ ይገኛል ሲሉ ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዋና ክፍል ኃላፊ ገልጸዋል፡፡ ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) እንደገለጹት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ሰበሳቢ ቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ እና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ጥበብ ሙሉዓለም አስራት በጋር በመሆን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያለውን የጂታል ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን በእርሳቸው አማካይነት ቀደም ሲል ስለተሠሩ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ሥራዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ በገለጻቸውም አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሥሩ ብዙ ሠራተኞች እና ሀብት የሚያስተዳድር ሀገረ ስብከት እንደመሆኑ ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መጠቀም ዘመኑ የሚጠይቀው ሥራ ሆኖ በመገኘቱ ቀደም ሲል ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ክፍሉን በማደራጀት የሀገረ ስብከቱ ኦፊሻል ድረ-ገጽ www.eotcaa.org እና ሙሉ የሀገረ ስብከቱ ሕንፃ በኔትዎርክ በማገናኘት ፈጣን የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት የቻለ ሲሆን፣ የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መከታተያ ሲስተም www.aadapp.org በማበልጸግ እንዲሁም ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የመዝገብ ቤት እና ንብረት አስተዳዳር ሲስተም ተሰርተው የሀገረ ስብከቱ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል እያስተዳደራቸው እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በማስከተልም በማዕከል ደረጃ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አማካኝነት ስለተዘጋጁትና ተግባራዊ ስለተደረጉት ስትራቴጂ፣ ፖሊሲ እና መመሪያዎች እንዲሁም በለሙት የሰው ሀብት፤ የሰበካ ጉባኤ አስተዳዳር ሲስተም፣ ዌብ ፖርታል እና በመሳሰሉት የቴክኖሎጂ ሥራዎች በተመለከተ ከሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስከያጅ ከክቡር መልአከ ብርሃን ሰለሞን በቀለ ጋር በመገናኘት ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል የለሙት የሀገረ ስብከቱ መዝገብ ቤት እና ንብረት ሀብት አስተዳደር ሲስተሞች በክፍላተ ከተማ እና በገዳማትና አድባራት በማዕከል ደረጃ አገልግሎቱን ማግኘት ካለመቻላቸውም በላይ አሁን ላይ ቴክኖሎጂው ከደረሰበት አንፃር በእጅጉ ወደ ኋላ የቀሩ ሆነው በመገኘታቸው ሲስተሞቹ እንዲዘምኑ፤ እንዲሻሻሉ፣ ወቅታዊ እንዲሆኑ እና ጥቅም ላይ እንዲውሉ በመልአከ ብርሃን ሰሎምን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅ አማካኝነት ሥራው ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች የሥራ መመሪያ መስጠታቸው እና የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መመከታቲያ ሲስተም www.aadapp.org በተመለከተም በቂ ሥልጠና ተሰጥቶ ከመስከረም 2019 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ሥራው እንዲጀምር የሥራ መመሪያ መተላለፉን የሀገረ ስብከቱ የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የለሙ/የበለጸጉ ሲስተሞችን ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ድረስ ሥራ ለማጀመር ሀገረ ስብከቱ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ እየጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ክፍሎችና የገዳማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎች ከወዲሁ በቂ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣ የሰውና የቴክኖሎጂ ግብአት ዝግጅት እንዲያደርጉ እና ማንኛውም ከቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መዋቅሩን ጠብቆ ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣቸው የአይሲቲ ፖሊሲና መመሪያዎች መሠረት ብቻ መከናወን እንዳለባቸው አውቀው ከዚህ ቀደም የለሙ እና ወደፊትም የታቀዱትን ሲስተሞች፣ ድረ ገጾች እና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ዝርዝር ለዋና ክፍሉ በደብዳቤ እንዲያሳውቁ አሳስበዋል። ድረ-ገጽ፡ www.eotcaa.org የባለ ጉዳይ መከታቲያ፡ www.aadapp.org የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service
1 237
16
+5
No text...
894
17
በጅግጅጋ ከተማ እየተሠራ የነበረው መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ላይ አጋጥሞ የነበረው ችግር በውይይት መፍትሔ አገኘ። ▮ነሐሴ_፳፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም▮ አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በሐረር ኬላ አካባቢ እየተሠራ የነበረው መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ምክንያት ተከሰቶ የነበረው አለመግባባት በውይይት ሰላማዊ መፍትሔ አጊንቷል፤ ስምምነቱ የተደረሰው ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ክልል ጅግጅጋና የአርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በሶማሌ ክልላዊ መንግስት ጽ/ቤት በመገኘት ከክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ጋር ባካሄዱት ውጤታማ ውይይት ነው። በውይይቱ የተደረሱ ዋና ዋና ስምምነቶች፦ • ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ታስረው የነበሩ 6 የቤተ ክርስቲያን ልጆች እና የሥራ መሪዎች ከእስር ተፈትተዋል። • የቦታ ጥያቄውን በተመለከተ ከክልሉ መንግሥት ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት ሕጋዊ አሠራርን ተከትሎ እንዲፈጸም ውሳኔ ላይ ተደርሷል። ብፁዕነታቸው ከክልሉ መንግሥት ጋር ባለው መልካም ግንኙነት፣ ጥያቄዎችን በቅደም ተከተል በማቅረብና በጋራ በመሥራት ለተደረገው መልካም ትብብር ምስጋና አቅርበዋል። በመጨረጨረሻም ችግሩ በሰላም እንዲፈታ አስተዋጽኦ ላደረጉት መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወልደ ኢየሱስ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የእቅድና ልማት ክፍል ኃላፊ፣ ለክልሉ የመንግሥት አካላት እና ለምዕመናን በሙሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ምስጋና አቅርበዋል:: ዘገባው የሱማሌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል
1 018
18
+4
No text...
1 506
19
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ የሚታይ የሚጨበጥ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ። ነሐሴ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ/ም አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ በተቋሙ የሚታይ የሚጨበጥ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ። በቅርቡ የተመደቡት መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ አዲሶቹንና ነባር የዋና ክፍል ሐላፊዎች ጋር መደበኛ የአስተዳዳር ጉባኤ ማካሔድ ጀምረዋል። በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መነሻነት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የተመደቡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ ከአዲሶቹና ከነባሮቹ የዋና ክፍል ሐላፊዎች ጋር በመሆን መደበኛ የአስተዳዳር ጉባኤ ጀምረዋል። የጉባኤ ላይ ነባሮቹ የሥራ ሐላፊዎች ለአዲሶቹ የዋና ክፍል ሐላፊዎች እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት መልካም አገልግሎት ምኞት የተመኙ ሲሆን በአንድነትና በኅብረት የቤተ ክርስቲያን የጣለችብንን አደራ ለመወጣት የሚቻለንን ሁሉ እናደርጋለንም ብለዋል። አዲሶቹ የሥራ ሐላፊዎች በበኩላቸው ስለተደረጋላቸው መልካም አቀባበል አመስግነው አገባባችን መልካም እንደሆነ በሥራችን ለመግለጥ የእግዚአብሔርን ቸርነት ተማምነን የበኩላችንን እንወጣለን ብለዋል። ክቡር መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ በበኩላቸው "ሰማይ ሩቅ አደራ ጥብቅ" እንደሚባለው ከቤተ ክርስቲያን የተሰጠንን ሕያው ተልእኮ ለውጥ በማምጣት ያከበረችንን ቤተ ክርስቲያን፣ የመረጡንን አባቶችን፣ ተስፋ ያደረጉንን የሀገረ ስብከቱንና የአብያተ ክርስቲያናቱን አገልጋዮች እንዲሁም ቡሩካን ምእመናንን ማስደሰት ይገባናል ብለዋል። 👉አስተዳደር ጉባኤውም ክቡር ሥራ አስኪያጁ ባነሱት የሀገረ ስብከቱ የአሠራር ለውጥ ጉዞ ላይ ከተወያየ በኋላ ከዚህ በታችን በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ የጋራ ስምምነት ላይ በመድረስ ውሳኔ አሳልፏል። 👉ከዚህ ቀደም በተለያየ ምክንያት ከመደበኛ የአገልግሎት ሥራቸው የታገዱ ሠራተኞችን ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት ሕግን ተከትሎ መፍትሔ እንዲሰጥ ውሳኔ ተላልፏል። 👉የአብያተ ክርስቲያናት የደመወዝ ጭማሬን አስመልክቶም በሕጉና በአሠራሩ የተቀመጡትን መስፈርቶች ማሟላታቸውን በሚመለከተው አካል በማረጋገጥ በጥቂት ቀናቶች እንዲጸድቅላቸው ከዚሁ ጋር በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት በሕገውጥ መንገድ ለደሞዝ ማጸደቂ በሚል የሚደረጉ ሕገወጥ ድርጊቶች እንዳይኖሩና በዚህ ሕገወጥ ድርጊት ሲያስተባብርና ሲተባበር የተገኘ አካል አስተዳደራዊ ርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል። 👉 የቤተ ክርስቲያናችንን አደራና ሐላፊነት ለመወጣት ይቻል ዘንድ ሁሉም በየተመደበበት የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሐላፊነት ላይ የድርሻውን እንዲወጣ አስተዳዳር ጉባኤ አሳስቧል። 👉በሀገረ ስብከቱን የሚስተዋሉና የተስተዋሉ ችግሮች ምክንያታቸው ብዙ ጉዳያቸው ውስብሰብ በመሆኑ ለሁለንተናዊ መፍትሔ ሁለንተናዊ ትብብርና የእኔ ባይነት በእጅጉ ያስፈልጋልም ብሏል ጉባኤው። ስለሆነም ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ድጋፍ ሊሆኑ የሚችሉ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን፣ ቃለ ዓዋዲን፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሠራተኛ መተዳደሪ ደንብንና የሀገረ ስብከቱን ደንብ በተጨማሪም በቅዱስ ሲኖዶስና ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጡ መመሪያዎችን ጋር በማገናዘብ መፍትሔ የሚሰጥና ሐላፊነትነ ከተጠያቂነት ጋር የጣመረ የውስጥ አሠራር System ለመዘርጋት ውሳኔ አሳልፏል። 💠ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን 💠 የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service
1 151
20
+8
No text...
1 351