የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/-ኢኦተቤ EOTC-Addis Ababa Diocese Media service
رفتن به کانال در Telegram
ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል ነው። መንፈሳዊ አገልግሎትና ሰሞነኛ ጉዳዮች ይቀርቡበታል። አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
نمایش بیشتر5 805
مشترکین
+224 ساعت
+27 روز
+3230 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+9
در 0 کانالها
اوت '26
+100
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئیه '26
+104
در 2 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+55
در 2 کانالها
Get PRO
مه '26
+62
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+39
در 2 کانالها
Get PRO
مارس '26
+76
در 2 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+51
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+51
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+140
در 1 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+122
در 2 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+117
در 3 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+94
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+102
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+405
در 3 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+133
در 3 کانالها
Get PRO
مه '25
+172
در 1 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+75
در 3 کانالها
Get PRO
مارس '25
+92
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+108
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+84
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+77
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+60
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+94
در 2 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+127
در 2 کانالها
Get PRO
اوت '24
+106
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+67
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+60
در 1 کانالها
Get PRO
مه '24
+41
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+36
در 1 کانالها
Get PRO
مارس '24
+41
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+77
در 2 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+44
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+64
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+46
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '23
+31
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+30
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+30
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+59
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+57
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+284
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+265
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+258
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+2 165
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+678
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+236
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '22
+276
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '22
+293
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+262
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '22
+229
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '22
+209
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '22
+183
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+261
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+298
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+161
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+183
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+1 265
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 04 سپتامبر | +2 | |||
| 03 سپتامبر | +4 | |||
| 02 سپتامبر | +2 | |||
| 01 سپتامبر | +1 |
پستهای کانال
| 2 | በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አይሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።
ነሐሴ፳፯ ቀን፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥንታዊት፤ ብሔራዊት፤ ዓለም አቀፋዊት፤ሐዋርያዊት እና ሲኖዶሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋ መጠን ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን፤ትውፊቷንና ሥርዓቷን በጠበቀ መልኩ መንፈሳዊ እና ማኀበራዊ አገልግሎቷን ለማጠናከር እና ተደራሽ ለማድረግ ከምታከናውናቸው በርካታ ተግባራት መካከል ዘመኑ የደረሰበት የአይሲቲና የዲጂታል ሽግግር ሥራ ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል::
ከዚሁ አንጻር የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በመላው ዓለም ለማስፋፋት፣ ታሪካዊ ቅርሶችን እና አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ሀብትና ንብረቷን ለመጠበቅ እንዲሁም አስተዳደራዊ ተግባራትን ለማሳለጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራን በበላይነት የሚመራና የሚያስተባብር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ እንዲሁም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ተቃቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል፡፡
በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር አህጉረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ ስምና ፊርማ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በተላከ ደብዳቤ፤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ መቋቋሙን ገልጾ ቀደም ሲል እንደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያሉ አይሲቲን በዋና ክፍል አደራጅተው እየሠሩ የሚገኙ አህጉረ ስብከት በተላከላቸው ዝርዝር የሥራ መመሪያ ቁጥር 3/3018 መሠረት እስከ አጥቢያ ቤተ ከርስቲያን ጽ/ቤት ድረስ ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲደረግ በተሰጠው መመሪያ መነሻነት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትም በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከመቸውም ጊዜ በተሻለ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየሠራ ይገኛል ሲሉ ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዋና ክፍል ኃላፊ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) እንደገለጹት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ሰበሳቢ ቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ እና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ጥበብ ሙሉዓለም አስራት በጋር በመሆን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያለውን የጂታል ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን በእርሳቸው አማካይነት ቀደም ሲል ስለተሠሩ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ሥራዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
በገለጻቸውም አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሥሩ ብዙ ሠራተኞች እና ሀብት የሚያስተዳድር ሀገረ ስብከት እንደመሆኑ ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መጠቀም ዘመኑ የሚጠይቀው ሥራ ሆኖ በመገኘቱ ቀደም ሲል ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ክፍሉን በማደራጀት የሀገረ ስብከቱ ኦፊሻል ድረ-ገጽ www.eotcaa.org እና ሙሉ የሀገረ ስብከቱ ሕንፃ በኔትዎርክ በማገናኘት ፈጣን የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት የቻለ ሲሆን፣ የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መከታተያ ሲስተም www.aadapp.org በማበልጸግ እንዲሁም ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የመዝገብ ቤት እና ንብረት አስተዳዳር ሲስተም ተሰርተው የሀገረ ስብከቱ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል እያስተዳደራቸው እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በማስከተልም በማዕከል ደረጃ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አማካኝነት ስለተዘጋጁትና ተግባራዊ ስለተደረጉት ስትራቴጂ፣ ፖሊሲ እና መመሪያዎች እንዲሁም በለሙት የሰው ሀብት፤ የሰበካ ጉባኤ አስተዳዳር ሲስተም፣ ዌብ ፖርታል እና በመሳሰሉት የቴክኖሎጂ ሥራዎች በተመለከተ ከሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስከያጅ ከክቡር መልአከ ብርሃን ሰለሞን በቀለ ጋር በመገናኘት ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
ቀደም ሲል የለሙት የሀገረ ስብከቱ መዝገብ ቤት እና ንብረት ሀብት አስተዳደር ሲስተሞች በክፍላተ ከተማ እና በገዳማትና አድባራት በማዕከል ደረጃ አገልግሎቱን ማግኘት ካለመቻላቸውም በላይ አሁን ላይ ቴክኖሎጂው ከደረሰበት አንፃር በእጅጉ ወደ ኋላ የቀሩ ሆነው በመገኘታቸው ሲስተሞቹ እንዲዘምኑ፤ እንዲሻሻሉ፣ ወቅታዊ እንዲሆኑ እና ጥቅም ላይ እንዲውሉ በመልአከ ብርሃን ሰሎምን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅ አማካኝነት ሥራው ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች የሥራ መመሪያ መስጠታቸው እና የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መመከታቲያ ሲስተም www.aadapp.org በተመለከተም በቂ ሥልጠና ተሰጥቶ ከመስከረም 2019 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ሥራው እንዲጀምር የሥራ መመሪያ መተላለፉን የሀገረ ስብከቱ የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የለሙ/የበለጸጉ ሲስተሞችን ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ድረስ ሥራ ለማጀመር ሀገረ ስብከቱ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ እየጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ክፍሎችና የገዳማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎች ከወዲሁ በቂ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣ የሰውና የቴክኖሎጂ ግብአት ዝግጅት እንዲያደርጉ እና ማንኛውም ከቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መዋቅሩን ጠብቆ ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣቸው የአይሲቲ ፖሊሲና መመሪያዎች መሠረት ብቻ መከናወን እንዳለባቸው አውቀው ከዚህ ቀደም የለሙ እና ወደፊትም የታቀዱትን ሲስተሞች፣ ድረ ገጾች እና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ዝርዝር ለዋና ክፍሉ በደብዳቤ እንዲያሳውቁ አሳስበዋል።
ድረ-ገጽ፡ www.eotcaa.org
የባለ ጉዳይ መከታቲያ፡ www.aadapp.org
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service | 903 |
| 3 | بدون متن... | 751 |
| 4 | በጅግጅጋ ከተማ እየተሠራ የነበረው መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ላይ አጋጥሞ የነበረው ችግር በውይይት መፍትሔ አገኘ።
▮ነሐሴ_፳፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም▮ አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ
በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በሐረር ኬላ አካባቢ እየተሠራ የነበረው መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ምክንያት ተከሰቶ የነበረው አለመግባባት በውይይት ሰላማዊ መፍትሔ አጊንቷል፤
ስምምነቱ የተደረሰው ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ክልል ጅግጅጋና የአርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በሶማሌ ክልላዊ መንግስት ጽ/ቤት በመገኘት ከክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ጋር ባካሄዱት ውጤታማ ውይይት ነው።
በውይይቱ የተደረሱ ዋና ዋና ስምምነቶች፦
• ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ታስረው የነበሩ 6 የቤተ ክርስቲያን ልጆች እና የሥራ መሪዎች ከእስር ተፈትተዋል።
• የቦታ ጥያቄውን በተመለከተ ከክልሉ መንግሥት ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት ሕጋዊ አሠራርን ተከትሎ እንዲፈጸም ውሳኔ ላይ ተደርሷል።
ብፁዕነታቸው ከክልሉ መንግሥት ጋር ባለው መልካም ግንኙነት፣ ጥያቄዎችን በቅደም ተከተል በማቅረብና በጋራ በመሥራት ለተደረገው መልካም ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።
በመጨረጨረሻም ችግሩ በሰላም እንዲፈታ አስተዋጽኦ ላደረጉት መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወልደ ኢየሱስ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የእቅድና ልማት ክፍል ኃላፊ፣ ለክልሉ የመንግሥት አካላት እና ለምዕመናን በሙሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ምስጋና አቅርበዋል::
ዘገባው የሱማሌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል | 836 |
| 5 | بدون متن... | 1 031 |
| 6 | የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ የሚታይ የሚጨበጥ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ።
ነሐሴ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ/ም አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ በተቋሙ የሚታይ የሚጨበጥ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ።
በቅርቡ የተመደቡት መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ አዲሶቹንና ነባር የዋና ክፍል ሐላፊዎች ጋር መደበኛ የአስተዳዳር ጉባኤ ማካሔድ ጀምረዋል።
በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መነሻነት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የተመደቡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ ከአዲሶቹና ከነባሮቹ የዋና ክፍል ሐላፊዎች ጋር በመሆን መደበኛ የአስተዳዳር ጉባኤ ጀምረዋል።
የጉባኤ ላይ ነባሮቹ የሥራ ሐላፊዎች ለአዲሶቹ የዋና ክፍል ሐላፊዎች እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት መልካም አገልግሎት ምኞት የተመኙ ሲሆን በአንድነትና በኅብረት የቤተ ክርስቲያን የጣለችብንን አደራ ለመወጣት የሚቻለንን ሁሉ እናደርጋለንም ብለዋል።
አዲሶቹ የሥራ ሐላፊዎች በበኩላቸው ስለተደረጋላቸው መልካም አቀባበል አመስግነው አገባባችን መልካም እንደሆነ በሥራችን ለመግለጥ የእግዚአብሔርን ቸርነት ተማምነን የበኩላችንን እንወጣለን ብለዋል።
ክቡር መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ በበኩላቸው "ሰማይ ሩቅ አደራ ጥብቅ" እንደሚባለው ከቤተ ክርስቲያን የተሰጠንን ሕያው ተልእኮ ለውጥ በማምጣት ያከበረችንን ቤተ ክርስቲያን፣ የመረጡንን አባቶችን፣ ተስፋ ያደረጉንን የሀገረ ስብከቱንና የአብያተ ክርስቲያናቱን አገልጋዮች እንዲሁም ቡሩካን ምእመናንን ማስደሰት ይገባናል ብለዋል።
👉አስተዳደር ጉባኤውም ክቡር ሥራ አስኪያጁ ባነሱት የሀገረ ስብከቱ የአሠራር ለውጥ ጉዞ ላይ ከተወያየ በኋላ ከዚህ በታችን በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ የጋራ ስምምነት ላይ በመድረስ ውሳኔ አሳልፏል።
👉ከዚህ ቀደም በተለያየ ምክንያት ከመደበኛ የአገልግሎት ሥራቸው የታገዱ ሠራተኞችን ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት ሕግን ተከትሎ መፍትሔ እንዲሰጥ ውሳኔ ተላልፏል።
👉የአብያተ ክርስቲያናት የደመወዝ ጭማሬን አስመልክቶም በሕጉና በአሠራሩ የተቀመጡትን መስፈርቶች ማሟላታቸውን በሚመለከተው አካል በማረጋገጥ በጥቂት ቀናቶች እንዲጸድቅላቸው ከዚሁ ጋር በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት በሕገውጥ መንገድ ለደሞዝ ማጸደቂ በሚል የሚደረጉ ሕገወጥ ድርጊቶች እንዳይኖሩና በዚህ ሕገወጥ ድርጊት ሲያስተባብርና ሲተባበር የተገኘ አካል አስተዳደራዊ ርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል።
👉 የቤተ ክርስቲያናችንን አደራና ሐላፊነት ለመወጣት ይቻል ዘንድ ሁሉም በየተመደበበት የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሐላፊነት ላይ የድርሻውን እንዲወጣ አስተዳዳር ጉባኤ አሳስቧል።
👉በሀገረ ስብከቱን የሚስተዋሉና የተስተዋሉ ችግሮች ምክንያታቸው ብዙ ጉዳያቸው ውስብሰብ በመሆኑ ለሁለንተናዊ መፍትሔ ሁለንተናዊ ትብብርና የእኔ ባይነት በእጅጉ ያስፈልጋልም ብሏል ጉባኤው።
ስለሆነም ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ድጋፍ ሊሆኑ የሚችሉ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን፣ ቃለ ዓዋዲን፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሠራተኛ መተዳደሪ ደንብንና የሀገረ ስብከቱን ደንብ በተጨማሪም በቅዱስ ሲኖዶስና ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጡ መመሪያዎችን ጋር በማገናዘብ መፍትሔ የሚሰጥና ሐላፊነትነ ከተጠያቂነት ጋር የጣመረ የውስጥ አሠራር System ለመዘርጋት ውሳኔ አሳልፏል።
💠ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን 💠
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service | 1 023 |
| 7 | بدون متن... | 1 064 |
| 8 | بدون متن... | 1 026 |
| 9 | بدون متن... | 896 |
| 10 | የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ::
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።
በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክብሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተወካይ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ፤ ብፁዕ አቡነ መልኬጸዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት እና የአቡነ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ፤ ፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች የተለያዩ የቤተክርስቲያን ተወካይ አባቶች ፤ የልዩ ልዩ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች እና ሥራ አስፈጻሚዎች፤ የክልል እና የአዲስ አበባ ተወካዮች፤ የተቋሙ የቦርድ አባላት እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
መርሐ ግብሩ በሃይማኖት አባቶች የመክፈቻ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የ15 ዓመታት የጉዞ ታሪክ የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም ቀርቧል።
በተጨማሪም ጉባኤው ባሳለፋቸው 15 ዓመታት ከጎኑ በመቆም በአህጉራዊ ሰላምና ፀጥታ ዙሪያ፣ በሰብአዊ መብቶች እና በሴቶች ዙሪያ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አብረው ሲያከናውኑ የቆዩ እንደ UNICEF (ዩኒሴፍ) እና ሰተርሊንግ ፋውንዴሽን ያሉ በርካታ ዓለም አቀፍ አጋር ተቋማትና ተወካዮች፣ ወደፊት በሚያከናወኑት አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተልዕኮዎች ላይ ገለጻ በማድረግ የ15 ዓመታት ሰላማዊ የአብሮነት ጉዞን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ ጉባኤው በይፋ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ አባል የሃይማኖት ተቋማት ከመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ጎን ለጎን በሀገራዊ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ላይ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ የማቀድ፣ የማስተባበርና የማመቻቸት ሥራዎችን ሲሠራ መቆየቱን ገልጸዋል።
አክለውም ከመንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሰላምና የመከባበር የጋራ እሴቶች እንዲጠበቁ ሃይማኖታዊ አስተምህሮን መሠረት ያደረጉ የግንዛቤና የአብሮነት ሥራዎች በሀገር አቀፍ፣ በክልልና በከተማ አስተዳደሮች ደረጃ ሲከናወኑ መቆየታቸውንና አሁንም እየተሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ መሐመድ ኢድሪስ ባስተላለፉት መልእክት፣ በ15 ዓመታት ውስጥ በየደረጃው የተካሄዱ መድረኮች የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተከታይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የእርስ በእርስ አስተምህሮን እንዲረዱ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም እንዲህ ዓይነቱ ጉባኤ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ፍላጎቶችንን የምናሰፍንበት፣ እምነትን በተግባር የምናጸናበትና የአብሮነትን ታላቅ ቁምነገር የምናሳይበት፣ ባለፉት 15 ዓመታት የሕዝባችንን የሞራልና የስነ-ምግባር እሴቶች ሲቀርጹ የነበሩ የዕድገት ምሳሌዎች መሆናቸውን በመጠቆም፣ በቀጣይም "ለሃይማኖትና ለሀገር የማይሆን ዜጋ እንዳንፈጥር በርትተን ከዘመኑ ጋር በመፍጠን ልንሠራ ይገባል" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በመጨረሻም ለጉባኤው ስኬት የሙያዊና የፋይናንስ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እና በሌሎች የሃይማኖት መሪዎች አማካይነት የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/ | 825 |
| 11 | بدون متن... | 960 |
| 12 | بدون متن... | 853 |
| 13 | بدون متن... | 867 |
| 14 | بدون متن... | 805 |
| 15 | በአቃቂ ክፍለ ተከተማ ቤተ ክህነት "ቅድሚያ ለወንጌል" በሚል ርእስ በሥሩ ለሚገኙት የገዳማትና የአድባራት የሥራ መሪዎች የሥልጠና መርሐ ግብር ተጀመረ።
▮ የአ/አ/ሀጌ ስብከት ሚዲያ
“ቅድሚያ ለወንጌል” በሚል ርዕስ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሥር ለሚገኙ አድባራትና ገዳማት ከነሐሴ 25 እስከ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚቆይ የስልጠና መርሐ ግብር በአቃቂ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን አዳራሽ ተዘጋጅቶ ተጀምሯል።
በመርሐ ግብሩም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሥር ለሚገኙ የቢሮ አስተዳደር ኃላፊዎች፣ ለሰበካ ጉባኤ ም/ሊቃነ መናብርት፣ ለሰንበት ት/ቤቶች አመራሮችና ማኅበራት፣ ለካህናት አባቶች እና ለሰባክያነ ወንጌል ልዩ የስልጠና መርሐ ግብር እየተሰጠ ይገኛል።
የመርሐ ግብሩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ዕዝራ ሲሆኑ፣ በመክፈቻ ንግግራቸውም የስልጠናው ዋና ዓላማ በቤተ ክርስቲያን የተሰጠንን ኃላፊነት በታማኝነት፣ በጥበብ፣ በትጋትና በተጠያቂነት እንድንወጣ አቅማችንን ለማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል።
ስልጠናው ለመማር ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ልምዶችንና ዕውቀቶችን በመለዋወጥ የአገልግሎት አፈጻጸምን ለማሻሻል የተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም “ብረት በብረት ይሳላል፤ ሰውም የወዳጁን ፊት ያስላል” በሚል በምሳሌ 27፥17 የተጠቀሰውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በመጥቀስ፣ አንድ ብረት ከሌላ ብረት ጋር ሲገናኝ እንደሚሳል ሁሉ፣ እኛም የየራሳችን ዕውቀትና ልምድ ቢኖረንም ዕውቀትና ልምድ በጋራ ውይይትና በመማማር ይበልጥ እንደሚጎለብቱ አስገንዝበዋል።
አክለውም በስልጠናው በዋናነት የሥራ ኃላፊነትንና የአመራር ክህሎትን ማጎልበት፣ የምእመናንን ሁኔታ ያገናዘበ አስተዳደር ማዳበር፣ የቤተ ክርስቲያንን የሥራ ሥርዓትና ቀጣይነት ማጠናከር፣ ለወንጌል ሥራ ቅድሚያ መስጠት፣ የገንዘብና የቁጥጥር ሥራን በግልጽነት ማከናወን፣ እንዲሁም ወጣቶችን፣ ማኅበራትንና የሰንበት ት/ቤቶችን በዕውቀት፣ በመንፈሳዊ ሕይወትና በተግባር ማበልጸግ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
አክለውም በሥልጠናው ወቅት ተሳታፊዎች በጊዜ በመገኘት፣ በንቃት በመሳተፍ፣ ጥያቄዎችን በመጠየቅና ሐሳቦቻቸውን በመጋራት፣ እንዲሁም የሚያገኙትን ዕውቀት ከየሥራ አገልግሎታቸው ጋር በማያያዝ እንዲተገብሩም ጥሪ አቅርበዋል።
በዛሬው ዕለትም “ኦርቶዶክሳዊ የቤተ ክርስቲያን አመራርና አስተዳደር” በሚል ርዕስ በረዳት ፕሮፌሰር መምህር ግርማ ባቱ ለአስተዳዳሪዎችና ለጸሐፊዎች ስልጠና ተሰጥቷል። በተጨማሪም “የቤተ ክርስቲያን የንብረት አያያዝና አመዘጋገብ” በሚል ርዕስ በመምህር ይድነቃቸው ተፈራ ለገንዘብ ያዦች፣ ለቁጥጥር ኃላፊዎችና ለሂሳብ ሹሞች ስልጠናና ውይይት ተካሂዷል።
በቀጣዮቹ ቀናትም የስልጠና መርሐ ግብሩ በተለያዩ የተሳታፊ ክፍሎች መሠረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ማክሰኞ ነሐሴ 26 ቀን የሰበካ ጉባኤ ም/ሊቀመንበር፣ ከየሰንበት ት/ቤቶች ሁለት ተወካዮች፣ እንዲሁም ከሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ክፍል አንድ ተወካይ በመርሐ ግብሩ ይሳተፋሉ።
ረቡዕ ነሐሴ 27 ቀን ብዙ የሰንበት ት/ቤት ልጆች ያሏቸው አምስት ካህናት አባቶችና የደብሩ ሰባኪ ወንጌል በሙሉ በስልጠናው ይሳተፋሉ።
ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን ከላይ ከ1 እስከ 3 የተጠቀሱት ሁለገብ ስልጠናዎች በጋራ እንዲገኙ በማድረግ የስልጠና መርሐ ግብሩ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
በዛሬው መርሐ ግብር ላይ ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ግርማ ባቱ፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የማኅበራዊና ኢኮኖሚ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣ ሊቀ ካህናት ዕዝራ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ መጋቢ ሐዲስ ጊዜው አሸናፊ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሰው ሀብት አስተዳደር ኃላፊ፣ የክፍለ ከተማው የሥራ ኃላፊዎች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ዋና ጸሐፊዎች፣ የሒሳብ ክፍል ኃላፊዎች፣ የቁጥጥር ክፍል ኃላፊዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንደነት ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ማኅበር አባላት እንዲሁም የሰባክያን ሕብረት አባላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ጽናት አስቻቸለው
📷ዲ/ን ቅዱስ ጥበቡ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service | 873 |
| 16 | بدون متن... | 1 156 |
| 17 | #የነሐሴ_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_በዓል በዋሻ ተክለ ሃይማኖት
የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ ዕረፍት አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከብሯል። በጥንቱ ዋሻ ሚካኤል ይባል የነበረው ይህ ቤተ ክርስቲያን በርካታ ዓመታትን ያስቀጠረ ቅዱስ ቦታ ነው።
📷መንክር ሚዲያ-Menker Media
ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፰ ዓ/ም
እንኳን አደረሳችሁ
የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በረከት ረድኤት ይደርብን!
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service | 1 007 |
| 18 | بدون متن... | 939 |
| 19 | #የነሐሴ አቡነ ተክለ ሃይማኖት #በሳሪስ_ዳማ አቡነ ተ/ሃይማኖት
የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሳሪስ ዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ስር በሚገኘው በሳሪስ ዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ የክፍለ ከተማው ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ሊ/ካህናት ዕዝራ ንዋይ፣የክፍለ ከተማው ቤተክህነት የሰው ኃይል አስተዳደር መ/ሐዲስ ጊዜው አሸናፊ፣የደብሩ አስተዳዳሪ መ/ሰላም ደነቀው ጎቤ፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
📷የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት
ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፰ ዓ/ም
እንኳን አደረሳችሁ
የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በረከት ረድኤት ይደርብን!
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service | 769 |
| 20 | بدون متن... | 725 |
