fa
Feedback
የጌታ ባሪያ የሲሳይ አበበ ገጽ

የጌታ ባሪያ የሲሳይ አበበ ገጽ

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የቴሌግራም ቻናል ልዩ ልዩ መልእክቶችን እና ትምህርቶችን ማስተላለፊያ ገፅ ነው፡፡

نمایش بیشتر
494
مشترکین
-124 ساعت
-187 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
ራእይ 1:3 3 ዘመኑ ቀርቧል፤ እንግዲህ ይህን የትንቢት ቃል የሚያነብብ ብፁዕ ነው፤ የሚሰሙትና የተጻፈውንም የሚጠብቁ ብፁዓን ናቸው።

ራእይ 1:3 3 ዘመኑ ቀርቧል፤ እንግዲህ ይህን የትንቢት ቃል የሚያነብብ ብፁዕ ነው፤ የሚሰሙትና የተጻፈውንም የሚጠብቁ ብፁዓን ናቸው።

‼️እውነትን እፈልጋለሁ ብሎ እውነት ሲነገር አለመስማትና አለመታዘዝ በሽታ ነው፣ ይገድላል‼️ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ይናገራል። እንደ እግዚአብሔር ሕዝብ፣ እንደ ክርስቲያንና በሕይወት መኖር እንደሚፈልግ እርሱን ከመስማት ውጭ ሌላ አማራጭ የለም። 1ነገስት 22 ያለ ታሪክ ከዚህ የተነሳ ይህ የእስራኤል ንጉስ እግዚአብሔርን መስማት ፈለገ፣ የእግዚአብሔር ቃል ያለውን አገልጋይ አስጠራ። የእግዚአብሔርን እውነትን ብቻ እንዲነግረው አስጠነቀቀው። በጣም ጥሩ ነው። “ንጉሡም፡— ከእውነት በቀር በእግዚአብሔር ስም እንዳትነግረኝ ስንት ጊዜ አምልሃለሁ? አለው።” አገልጋዩም እውነተኛውን ነገረው። ነገር ግን የሰሚው ምላሽ ግራ የገባውና ከእውነት ይልቅ በልቡ ያለውን የስጋውን ምኞት እንዲያፀናለት ፈልጎ አገልጋዩንና መልዕክቱን ተቃወመ። “እርሱም፡— እስራኤል ሁሉ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች በተራሮች ላይ ተበትነው አየሁ፤ እግዚአብሔርም፡— ለእነዚህ ጌታ የላቸውም፥ እያንዳንዱም በሰላም ወደ ቤቱ ይመለስ፡ አለ፡ ብሎ ተናገረ።” የእስራኤልም ንጉሥ ኢዮሣፍጥን፡— ክፉ እንጂ መልካም እንደማይናገርልኝ አላልሁህምን? አለው።” ቁ 17-8 ወገኔ የእግዚአብሔርን ቃልና መልዕክተኛውን የልባችንን ምኞት እንዲደግፋልንና “እርስዎ እንዳሉት” እንዲሉን አንጠብቅ። እግዚአብሔር እውነትን ይናገራል፣ እውነቱም ለዘላለም አይለወጥም። ለእኛ የሚበጀን ቃሉን መስማትና እንደ ቃሉ መታዘዝ ብቻ ነው። ያ ካልሆነ እግዚአብሔርን ለመስማትና ለመታዘዝ ባልወደድን መጠንና ልባችንን ባደነደንን ልክ ለጠላትና ለሐሰተኞች አልፈን እንሰጣለን። ከላይ ባየነው ንጉስና ህዝብ ሕይወት የሆነው እንደዚህ ነው፤ “ሚክያስም አለ፡— እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ እግዚአብሔር በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ። አሁንም፡— እነሆ፥ እግዚአብሔር በእነዚህ በነቢያትህ ሁሉ አፍ ሐሰተኛ መንፈስ አድርጎአል፤ እግዚአብሔርም በላይህ ክፉ ተናግሮብሃል።” ቁ 19-23 የእግዚአብሔር ሕዝብ ሆይ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፣ ስትሰሙ እንደ ወረደ ስሙት እንጂ የልባችሁን ምኞትና የስጋችሁን ሀሳብ እንዲያፀናላችሁ አትስሙ። የእግዚአብሔርን የልቡን ሐሳብና ፈቃድ በሙሉ ልብ ለመቀበል ስሙት! ደግሞም መስማት ብቻ ሳይሆን በሙሉ ስልጣኑና ሀይሉ በእኛ እንዲሰራ እንፍቀድለት፣ እንታዘዘው። ያኔ ማምለጥ፣ ማትረፍ፣ መለወጥ ይሆናል። “እኔ የምነግርህን የእግዚአብሔርን ቃል እባክህ፥ ስማ፤ ይቀናሃል፥ ነፍስህም በሕይወት ትኖራለች።” ኤር 38:20 በሕይወት የመኖራችንና የስኬታችን ቁልፍ ያለው የእግዚአብሔርን ቃል በመስማትና በመታዘዛችን ውስጥ ነው!!! ቃሉን ሰምቶ “እኔ እንደምፈልገው ወይም እንደለመድሁት አይደለም” ብሎ ቃሉን ከሚቃወም ክፉ *የልብ በሽታ* ይፈውሰን። “ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና።” 2ቆሮ 13:8 እግዚአብሔር ሁላችንንም የቃሉን እውነት በመስማትና በመታዘዝ በረከት ይባርከን🙏🙏🙏

ምሳሌ 1:33 (አዲሱ መደበኛ ትርጉም / NASV) 33 የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤ ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል። ይህ ጥቅስ የጥበብን (ወይም የእግዚአብሔርን ምክር) የሚያዳምጥ ሰው በሰላም፣ በደህንነትና ያለ ፍርሃት እንደሚኖር ያስተምራል። ከዚህ በፊት ባሉት ጥቅሶች (ምሳሌ 1:20–32) ጥበብ እያስጠነቀቀች ሞኞችንና የማይሰሙትን ትናገራለች፤ ይህ ግን የሚሰማውን ሰው የሚጠብቀውን መልካም ውጤት ያሳያል። እንግሊዝኛ ትርጉም (NIV): “but whoever listens to me will live in safety and be at ease, without fear of harm.” ሌሎች አማርኛ ትርጉሞችም ተመሳሳይ ትርጉም ይሰጣሉ፦ አዲስ ዓለም ትርጉም፦ “እኔን የሚሰማ ሰው ግን ተረጋግቶ ይኖራል፤ መከራ ይደርስብኛል የሚል ስጋትም አያድርበትም።” ሌሎች፦ “የሚሰማኝ ግን ተረጋግቶ ይቀመጣል፥ ከክፉም ሥጋት ያርፋል።” ይላል

ምሳሌ 1:33 33 የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤   ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል።”

ምሳሌ 1:33 33 የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤ ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል።”

ዘኍልቍ 11:33-34 33 ነገር ግን ሥጋው ገና በጥርስና በጥርሳቸው መካከል ሳለ አላምጠው ሳይውጡት የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በላያቸው ነደደ፤ እግዚአብሔርም ሕዝቡን በታላቅ መቅሠፍት ክፉኛ መታ። 34 ሌላ ምግብ ለማግኘት የጐመጁትን ሰዎች በዚያ ስለ ቀበሯቸው የቦታው ስም “ቂብሮት ሃታአባ” ተባለ

ዘኍልቍ 11:33-34 33 ነገር ግን ሥጋው ገና በጥርስና በጥርሳቸው መካከል ሳለ አላምጠው ሳይውጡት የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በላያቸው ነደደ፤ እግዚአብሔርም ሕዝቡን በታላቅ መቅሠፍት ክፉኛ መታ። 34 ሌላ ምግብ ለማግኘት የጐመጁትን ሰዎች በዚያ ስለ ቀበሯቸው የቦታው ስም “ቂብሮት ሃታአባ” ተባለ

ዘኍልቍ 11:33-34 33 ነገር ግን ሥጋው ገና በጥርስና በጥርሳቸው መካከል ሳለ አላምጠው ሳይውጡት የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በላያቸው ነደደ፤ እግዚአብሔርም ሕዝቡን በታላቅ መቅሠፍት ክፉኛ መታ። 34 ሌላ ምግብ ለማግኘት የጐመጁትን ሰዎች በዚያ ስለ ቀበሯቸው የቦታው ስም “ቂብሮት ሃታአባ” ተ

ፍሬአማነትን የሚከለክሉ ሶስቱ እንቅፋቶች ማቴ13:4-9; 18-23 ጌታ ኢየሱስ የዘሪውን ምሳሌ ካስተማረ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ለምን በምሳሌ ትናገራለህ ብለው ጠይቀውት ነበር እርሱም “ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም” በማለት መለሰላቸው፡፡ በዚህም ተስፋ መሰረት የተናገረውን ምሳሌ ይተረጉምላቸው ዘንድ ጀመረ፡፡ በክርስቶስ የዳነ ሰው ቃሉን ይረዳና ይገልጥለት፣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶታል፡፡ ስለዚህ እያንዳንዱ አማኝ ቃሉን ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ መማር ያስፈልገዋል፡፡ የኤማዎስ መንገደኞች በክርስቶስ ሞት ተስፋ ቆርጠውና ጠውልገው ወደ ቀዬአቸው ሲመለሱ ጌታ ቀርቦ “ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጐመላቸው” ሉቃ24፡27 በዚህ ጊዜ ዓይናቸው ተከፍቶ ቀድሞ ወደ ተሰጣቸው ተስፋ ተመለሱ፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚያውቁት ከጊዜው ሁኔታ ጋር አመሳክሮ ለመረዳት ከደራሲው ከራሱ፣ ትርጓሜ አስፈልጓቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ነው ለእናንተስ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል የተባለው፡፡ ስለዚህ ጌታ የዘሪውን ምሳሌ ስሙ በማለት ትርጓሜውን ይነግራቸው ጀመር፡- 1. አለማስተዋል "የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ሁሉ፥ ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው" ማቴ13:19 ዘሪው የምስራቹን ቃል የሚያበስር፣ ቃሉን የሚያስተምርን ሰውን የሚወክል ሲሆን ዘሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ይህ ቃል በሰው ጆሮ ከደረሰ በኋላ ከሰዎች የሚገኘው ምላሽና በዚያ ሰው ህይወት የሚገኘው ፍሬ እንደየ ሰው ልብ ምንነት ይለያያል፡፡ በዚህ ምሳሌ ጌታ ያቀረበው የመጀመሪያው ቃሉ ፍሬ እንዳያፈራ እንቅፋት የሚሆነበት ዋንኛ ጉዳይ አለማስተዋል ነው፡፡ ቃሉን በደስታ ይሰማል ግን አያስተውለውም የዚህ ሰው ልብ ልክ ብዙ ሰው እየረገጠው እንደሚሄድና በሰዎች እግር እንደ ተደመደመ መንገድ በመሆኑ የተዘራው ዘር ወደ ውስጥ የመግባት እድል አያገኝም፡፡ ይህ ማለት ይህ ሰው ብዙ አሳቦች ልቡን ስለሚያደነደኑት ቃሉ ወደ ልቡ አይገባም ስለዚህ ወደ መሬት ያልገባ ዘር በወፎች እንደ ሚለቀም ሁሉ እንዲሁ ወደ ልብ ያልገባ ወይም ቃሉ ሲነገር በሚገባ ያልተረዳ ሰው የሰማውን ቃል በሰይጣን ይነጠቃል፡፡ ይህ ሰው ቃሉን ስለተነጠቀ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም፡፡ ሰው ቃሉን ሲሰማ ልቡን ከተለያዩ አሳቦች ሰብስቦ በጥሞና መስማት ያስፈልገዋል፡፡ በተለያየ አሳብ የሚዋከብ ሰው ቃሉን በሚገባ ሊሰማና ሊረዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ነው ሰይጣን ሰዎች ቃሉን በሚሰሙበት ሰዓት ማስተዋል እንዳያገኙ በተለያዩ አሳቦች ልባቸውን የሚሞላው፡፡ ይህንን የተረዳ ሰው ይህንን ችግር ድል መንሳት ይችላል፡፡  2. በፈተና መፈታት "በጭንጫ ላይ የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ ወዲያው በደስታ የሚቀበለው ነው፤ “ነገር ግን ለጊዜው ነው እንጂ በእርሱ ሥር የለውም፥ በቃሉ ምክንያትም መከራ ወይም ስደት በሆነ ጊዜ ወዲያው ይሰናከላል" ማቴ13:20,21 ሁለተኛው ቃሉ ወደ ሰው ህይወት መጥቶ ፍሬ እንዳያፈራ የሚያደርገው ልክ በጭንጫ ወይንም ትንሽ አፈር ብቻ ያለበት ድንጋያማ ቦታ እንደ ተዘራና ተክሉ ሥር ባለመስደዱ ምክንያት ጸሐይ በወጣ ሰዓት እንደሚጠወልግ ተክል እንዲሁ ቃሉን የሰማ ሰው ቃሉን በቀጣይነት የሚማር ካልሆነ በቃሉ ምክንያት ስደት፣ መከራ ሲመጣበት ወዲያውኑ መሰናከል ይጀምራል፡፡ ጌታ ላመኑ አይሁድ ይህንን ችግር ስለሚያውቅ ካመኑ በኋላ እንዲህ አላቸው "በትምህርቴ ብትጸኑ እናንተ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል" ዮሐ8:31-32 በቃሉ አማካኝነት አርነት ማግኘት በቃሉ የምናገኘው አንድ ፍሬ ነው፡፡ ለዚህም አማኝ በቃሉ መጽናት፣ በቃሉ ትምህርት መቀጠል ይኖርበታል፡፡ በዚህ ጊዜ የትኛውም ፈተናና መከራ በህይወቱ ሲመጣ ሊነቀንቀው አይችልም፡፡ ይህ ማለት የእግዚአብሔርን ቃሉ ከብዙ የህይወት አቅጣጫ አኳያ ሊማረው ያስፈልገዋል ምክንያቱም ቃሉ ለየትኛውም የህይወት ትግል መልስና መፍትሄ አለው፡፡ ቃሉን መማር ያቆመ ሰው ለህይወት ፈተናዎች ይረታል፣ ስለዚህ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም፡፡ 3. የዚህ ዓለም አሳብ "“በእሾህ መካከል የተዘራውም ይህ ቃሉን የሚሰማ ነው፥ የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል ቃሉን ያንቃል፥ የማያፈራም ይሆናል" ማቴ13:22 አማኝ ፍሬ የማያፈራበት፣ በህይወት ጸንቶ የማይቆምበት ሌላው ሶስተኛው ችግር ልክ ዘሩ በእሾህ መካከል እንደተተከለ ዘርና ባደገ ጊዜ አረሙ አንቆት ፍሬአማ እንዳይሆን እንደሚያደርገው ሁሉ እንዲሁም የሰው ልብ በዚህ ዓለም አሳብ፣ በባለጠግነት ጉዳይ ሲጠመድ ቃሉ ፍሬ እንዳያፈራ አረም ይሆንበታል፡፡ መቼም ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚችል ስለሌለ ሁለቱንም አብሮ ማስኬድ አይቻለውም፡፡ አንዱ በዚህ ዓለም የኑሮ አሳብ ሌትና ቀን ተጠምዶ ቃሉን የሚፈልግበት ክፍተት ያለው ልብ የለውም ልቡ ቢዚ በመሆኑ ቃሉን ሲሰማ እንቅልፍ እንቅልፍ ይለዋል፡፡ የሚውልበት አሳብ ለመንፈሳዊው ነገር ረሃብ እንዳይኖረው ያደርገዋል፡፡ ሌላው በእጁ ገንዘብ የያዘ ሰው መተማመኑን በገንዘቡና በንብረቱ ላይ ስለሚያደርግ ቃሉን ተጠምቶ አይፈልገውም ወይም ቃሉን የህይወቱ መሪና መተማመኛ ሊያደርገው አይችልም፡፡ 4. ድል ነሺው ልብ "በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል" ማቴ13:23 በመጨረሻም ከላይ የተዘረዘሩትን ችግሮች በሙሉ ድል የነሳ የትኛውም ሰው እርሱ የፍሬ ባለቤት ነው፡፡ የመልካም መሬት ባለቤት ለመሆን አለማስተዋልን፣ ቃሉን በቀጣይነት አለመማርንና የዚህን ዓለም አሳብና በባለጠግነት መታለልን መስወገድ ግድ ይላል፡፡ ፍሬ የሚያፈሩ ራሳቸው በፍሬአቸው ብዛት ይለያያሉ ይህ የሚያሳየው ብዙ መሰጠትን ነው፡፡ ትጋት፣ መሰጠት መቶ ወይም ፍጹም ፍሬአማ ለመሆን ምክንያት ይሆናል፡፡ ምንጭ ወ/ዊ ምንተስኖት

ሐዋ. ሥራ 13:49-52 49 የጌታም ቃል በአካባቢው ባለው አገር ሁሉ ተስፋፋ። 50 አይሁድ ግን በመንፈሳዊ ነገር የተጉትንና የከበሩትን ሴቶች፣ እንዲሁም የከተማውን ታላላቅ ወንዶች ቀስቅሰው በጳውሎስና በበርናባስ ላይ ስደትን አስነሡ፤ ከአገራቸውም አስወጧቸው። 51 ጳውሎስና በርናባስም ተቃውሟቸውን ለመግለጽ የእግራቸውን ትቢያ አራግፈው ወደ ኢቆንዮን ሄዱ። 52 ደቀ መዛሙርቱም በደስታና በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ።

ሐዋ. ሥራ 13:49-52 49 የጌታም ቃል በአካባቢው ባለው አገር ሁሉ ተስፋፋ። 50 አይሁድ ግን በመንፈሳዊ ነገር የተጉትንና የከበሩትን ሴቶች፣ እንዲሁም የከተማውን ታላላቅ ወንዶች ቀስቅሰው በጳውሎስና በበርናባስ ላይ ስደትን አስነሡ፤ ከአገራቸውም አስወጧቸው። 51 ጳውሎስና በርናባስም ተቃውሟቸውን ለመግለጽ የእግራቸውን ትቢያ አራግፈው ወደ ኢቆንዮን ሄዱ። 52 ደቀ መዛሙርቱም በደስታና በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ።

ጥበብን የተሞላ ልብ (12) «ጥበብን የተሞላ ልብ ይኖረን ዘንድ፣ ዕድሜያችንን መቍጠር አስተምረን።» ይህ የመዝሙሩ ልብ ነው። ሕይወት አጭር መሆኑን ማወቅ ጥበብን ያስገኛል። ጊዜን መቍጠር ማለት እያንዳንዱን ቀን በጥበብና በፍርሃተ እግዚአብሔር መኖር

መዝሙር 90:12 12 ጥበብን የተሞላ ልብ ይኖረን ዘንድ፣   ዕድሜያችንን መቍጠር አስተምረን።

መዝሙር 90:12 12 ጥበብን የተሞላ ልብ ይኖረን ዘንድ፣ ዕድሜያችንን መቍጠር አስተምረን።

የሚያድን ስም እንጂ የሚፈውስ ዘይት የለም

መክብብ 10:12 12 ከጠቢብ አፍ የሚወጣ ቃል ባለ ሞገስ ነው፤   ሞኝ ግን በገዛ ከንፈሩ ይጠፋል፤

መክብብ 10:12 12 ከጠቢብ አፍ የሚወጣ ቃል ባለ ሞገስ ነው፤ ሞኝ ግን በገዛ ከንፈሩ ይጠፋል፤